en
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Open in Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 411 subscribers, ranking 5 577 in the Religion & Spirituality category and 2 191 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 411 subscribers.

According to the latest data from 11 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 64 over the last 30 days and by 24 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 24.26%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 9.47% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 737 views. Within the first day, a publication typically gains 1 458 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 23.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 12 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

15 411
Subscribers
+2424 hours
+237 days
+6430 days
Posts Archive
#የትንሣኤ_ልዩ_ዝግጅት፤ #የዐርብ_ጕባኤ_፻፳፯ኛ_ሳምንት #ሚያዝያ_፳፭/፳፻፲፩ዓ.ም. ከ፲፪-፪ ሰዓት፤ #በሰዐቱ_ይገኙ!!!!!!!! እንዳያመልጥዎ!! በእለቱ ልዩ ልዩ መርሐ ግብሮችና ውዳሴ ማርያም በዜማ ይካሄዳል:: ላልሰሙት ያሰሙ፤ <<Like, Share>> በማድረግ ይተባበሩ የቀ.ደ.ሰ መድኀኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት::

አስቸኳይ ማስተካከያ፤ ሚያዝያ 23 ሰሙነ ፋሲካ ላይ ስለዋለ፤ ከትንሣኤ እስከ ዳግም ትንሣኤ ደግሞ የሚውሉ በዓላት ማኅሌታቸው የጌታችን የሰሙነ ፋሲካን እንጂ የቅዱሳንና የቅዱሳት መልክእ ማኅሌት ስለማይቆም፤ ቀን ላይ ለጥፈነው የነበረው ሥርዐተ ማኅሌት በዚህኛው እንዲስተካከልና፤ ላላስተካከሉ እንዲያስተካክሉ ታደርሱ ዘንድ እናሳስባለን፡፡ ... በነገራችን ላይ በጎንደርና በአዲስ አበባ ባሉ ታላላቅ አድባራት (ለምሳሌ እንደ ቀጨኔ ደብረ ሰላም፤ መናገሻ ገነተ ጽጌ፤ ታዕካ ነገሥት በኣታ ለማርያም፤ መካነ ሥላሴ /መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ/ ከትንሣኤ እስከ ዳግም ትንሣኤ ማኅሌት ይቆማሉ፡፡ የጎንደር አድባራት ደግሞ ከዳግም ትንሣኤ በኋላ ያለውን ተጨማሪ አንድ ሳምንትን ‹‹ጠፈረ ጽድቅ›› የሚለውን ማኅሌት በልዩ ሁኔታ ይቆማሉ፡፡ /ለዚህ ሥርዐተ ማኅሌት አስተዋጽዖ ላደረጉት፤ ለሊቀ ጠበብት ይልማ (የደብራችን ሊቀ ጠበብት)ና ለሊቀ ጠበብት ፀጋዬ (የመናገሻ ገነተ ጽጌ ሊቀ ጠበብት) አምላከ ቅዱስ ጊዮርጊስ ይስጥልን፡፡

ዛሬ ሚያዝያ 22/2011ዓ.ም. ወንድማችንና መምህራችን ስለሺ ብርሃኑ (ብርሃነ መስቀል) በሥጋ ከተለየን 6ኛ ዓመቱ ኾነ፤ የአባቶቻችን አምላክ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ነፍሱን ከቅዱሳኑ ጋር ይደምርልን፥ ነፍስ ይማርልን፡፡ #መሐራ_እግዚኦ_ለነፍሰ_እኁነ_ብርሃነ_መስቀል፡፡ ያረፈበት ቀንም ዓለም ከተፈጠረ፥ ዘመን ከተቈጠረ በ7506 ዓመት(በፀሐይ)፤ በ2006 ዓመተ ምሕረት (በፀሐይ)፤ በ58 ዐውደ ቀመር፤ በወንጌላዊ ማርቆስ፤ በ1 ጥንተ ዮን፥ በ6 እንድክትዮን፥ በአልቦ አበቅቴ፤ በሚያዝያ ወር በ22ኛ ቀን (በፀሐይ)፤ በ26 ሠርቀ ሌሊት፤ በ1730 ዓመተ ሰማዕታት ነው፡፡ በዕለቱ ከቀረቡ ግጥሞችና ቅኔዎች የተወሰኑትን እነሆ ብለናችኋል፡፡ (ግጥሞቹና ቅኔዎቹ ከሕይወቱ ታሪክ ጋር /በፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት አገልጋይ ከመኾኑ ጋር፣ 2ት ሕንፃ ቤተ ክርስቲያንን ከማሠራቱ ጋር፣ በዳግማዊት ስሪንቃ ቅድስት አርሴማ ጠበል ቦታ ከማገልገሉ ጋር ….. የተመሳጠሩ ድንቅ የሆኑ ግጥምና ቅኔዎች ናቸው)፡፡ #ስለሺ ወንድሜ በነበረህ ለዛ፣ በሚጥመው ቃልህ በስብከት መዐዛ፣ ቀና በል ተናገር ዝምታ አታብዛ፣ ሁሉም ያልፋልና ድንገት እንደዋዛ፡፡ #ክፉ ሰው ሞት በሰው ላይ ነገረ ሠሪ፣ ለምድር አሽከርካሪ ለሰማይ አብራሪ፣ ደኅና ሰውን መስሎ የቅርብ ዘመድ መካሪ፣ ደርሶ የሚያጣላ ፍጡርን ከፈጣሪ፣ ክፉ ሰው ሞት በሰው ላይ ነገረ ሠሪ፣ ዛሬ ምን በደለው ስለሺ የብዙዎች(የብዙኃን) አስተማሪ፡፡ #በነገረ ሠሪ ኅልፈት ክፉ መሃለኛ፣ ከፊትህ ብትርቅ ድንገት ሕይወት ወረተኛ፣ የነበረው ቀርቶ ብትሆንም ብቸኛ፣ ብቸኛ ነኝ አትበል ስለሺ በሠራኸው ሥራ ነህና ዝነኛ፡፡ #ስለሺ ለብዙዎች ብሎ የጸለየው ጸሎት ተግቶ፣ በማርያም ምልጃ ከእግዚአብሔር ተሰምቶ፣ ሲሻው የነበረ እንዲሰጥ ጽዋ ሞት ተቀድቶ፣ ተቀበለ ዛሬ ከቅዱስ ዑራኤል እጅ ነስቶ፡፡ #ሥጋም በምድር ላይ መከራን ታገሺ ነፍስም በሰማይ ላይ በገነት ንገሺ፣ ክርስቶስ በዳግም ትንሣኤ እስኪነግስ ስለሺ፡፡ #ጕባኤ_ቃና_ቅኔ ……. ቃልየ አጽምዕ እግዚኦ ወለቡ ጽራሕየ ……. በሕማም ወጸዕር ሶበ ወጽአት ለብርሃነ መስቀል ነፍሱ፤ እጼ ወዝኅር አዝማዱ ንብረተ ሥጋሁ ወረሱ፡፡ #ሥላሴ_ቅኔ …….. ይትባረክ እግዚአብሔር አምላከ አበዊነ …….. ብርሃነ መስቀል በአዕይንቲሁ ወኢይርዓይ መልክዐ ብእሲት ዓለም አበሳ ዘብዙሃነ ፈተነ፤ ሥጋ ሰብእ ዓይነ እንቲአሁ በልብሱ ከደነ፤ በቃለ ሐዲስ ወንጌል እምንእሱ እስመ አእመረ ወኮነ፤ ወበዝ ዓለም እስከ ሀለውነ፤ ኢርዕዮተ ዓለም ብእሲት ዘገብሮ እኁነ፣ ለኵልነ ትምህርተ ይኵነነ፡፡ #መወድስ_ቅኔ ……. ፍትሃ ሊተ እግዚኦ ወተበቀል በቀልየ ………. እንበለ ኢምንት ፍጥረተ ኀበ ተኀሰበ በዓይነ አብዕልት ሕዝብ ወበእግረ ንዑስ ወዐቢይ፤ ዘይትከየድ ዘልፈ መቃብረ ሥጋ ነዳይ፤ ሞተ አቤል ወርኅ ጊዜ አንገሦ፤ በዓለም ተፈጥሮተ ሥጋ ዘብዙኅ ጌጋይ፤ ይቀውም ከመ ቆሙ ዲበ ዘገፍዕዎ ቅድመ ገበርተ ዓመጻ ወእከይ፤ ንሕነኒ ይደልወነ ከመ ንጸልይ፤ ጸሎተ ንስሓ መንገሌሁ ለአምላከ ምድር ወሰማይ፤ ሊቀ ካህናት ክርስቶስ እምነ አእላፍ ኅሩይ፤ በኢያእምሮ ዘአበስናሁ ወዘጌገይ ናሁ ከመ ይሥረይ፡፡

፨፨#ጽሑፎቻችን ለሌሎችም እንዲዳረሱ #የቴሌግራም_አድራሻችንን_ለሌሎችም_ያስተዋውቁ፡፡ (የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት) ወይም https://t.me/medihanaelem ፨፨#የፌስቡክ_ገጻችንን_ለምትፈልጉ፡፡ (የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት) ወይም https://www.facebook.com/%E1%8B%A8%E1%89%80%E1%8C%A8%E1%8A%94-%E1%8B%B0%E1%89%A5%E1%88%A8-%E1%88%B0%E1%88%8B%E1%88%9D-%E1%88%98%E1%8B%B5%E1%8A%80%E1%8A%94%E1%8B%93%E1%88%88%E1%88%9D%E1%8A%93-%E1%8B%B0%E1%89%A5%E1%88%A8-%E1%89%B5%E1%8C%89%E1%88%83%E1%8A%95-%E1%89%85%E1%8B%B1%E1%88%B5-%E1%8C%88%E1%89%A5%E1%88%AD%E1%8A%A4%E1%88%8D-%E1%89%A4%E1%89%B0-%E1%8A%AD%E1%88%AD%E1%88%B5%E1%89%B2%E1%8B%AB%E1%8A%95-%E1%8D%8D%E1%8A%96%E1%89%B0-%E1%88%95%E1%8B%AD%E1%8B%88%E1%89%B5-%E1%88%B0%E1%8A%95%E1%89%A0%E1%89%B5-%E1%89%B5%E1%88%9D%E1%88%85%E1%88%AD%E1%89%B5-%E1%89%A4%E1%89%B5-1620932764891482/

#ሚያዝያ_23_በዓለ_ክላሌሁ_ለሊቀ_ሰማዕታት_ቅዱስ_ጊዮርጊስ፡፡ ኦ ፍጡነ ረድኤት … ብለው ኢትዮጵያውያን በእምነት ኾነው ሲጠሩት፤ ከዐይን ጥቅሻና ከዐውሎ ነፋስ ይልቅ ፈጥኖ የደረሰላቸው የሊቀ ሰማዕታት የቅዱስ ጊዮርጊስ ክብረ በዓሉ ነው፡፡ #ኮከበ ክብር፥ *ሊቀ ሰማዕታት፥ *መክብበ ሰማዕታት፥ *የፋርስና የቤሩት ኮከብ፥ *የልዳ ፀሐይ፥ *የኢትዮጵያ ገበዝ፥ *ባለ ፀዓዳ ፈረስ፥ *፸ ነገሥታትን ድል ያደረገ፥ *በሕይወቱ ክርስትናን ያስፋፋ፥ በዕረፍቱ ክርስቶስን የሰበከ፥ ከዕረፍቱ በኋላ ዛሬን ጨምሮ ፈትኖ የሚራዳ፥ *፫ት ጊዜ ሞቶ ፫ት ጊዜ የተነሣ፥ *፯ት አክሊላትን የተቀናጀ፤ *እመቤታችንን በጣም ስለሚወድ ስሙ ከስሟ፥ ዝክሩ ከዝክሯ ጋር፥ ፍልሰቱ ከፍልሰቷ ጋር እንዲኾን ያደረገችለት፤ #.... የሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስን በዓለ ክላሌ (ሚያዝያ 23) ከዋይዜማው ጀምሮ በመላው ሃገራችን የሚቆመውን ሙሉውን ሥርዐተ ማኅሌት አቅርበንላችኋል፡፡ #አማን በአማን፥ አማን በአማን፤ ኮከበ ልዳ፥ ፀሐየ ፋርስ፡፡ #በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ፤ ዘአንበሩ ብየ አክሊለ ሞገስ፤ መዘምረ እኩን ለጊዮርጊስ፡፡ #ኀያል መስተጋድል ኀያል ኮከበ ክብር፤ ኀያል ገባሬ ተአምር፤ ጊዮርጊስ ቅዱስ ለእግዚአብሔር፡፡ #በእንተ ጊዮርጊስ ፍቁርከ(ሰማዕትከ፥ ምዕመንከ)፤ ምህላነ ስማዕ በዕዝንከ፡፡ #ሥርዐተ ማኅሌቱን ሌሎችም እንዲደርሳቸው ከዚህ በታች የሰፈረውን ገጻችንን LIKE LIKE እንዲያደርጉ ያስተዋውቁ፤ INVITE INVITE INVITE ያድርጉ፡፡ (የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት)

ለአባላት በሙሉ፤ #የኪዳነ_ምሕረት_ማኅበራችን ሰሙነ ሕማማት ላይ ውሎ ስለነበረ፤ የሚደረገው ዛሬ ሰኞ ሚያዝያ ፳፩ በመኾኑ፤ በሰዐቱ እንድትገኙ እናሳስባለን።

ሰሙነ ፋሲካ (ከቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ሰሌዳ መጽሔት የተወሰደ) ከትንሣኤ እሑድ ቀጥለው ያሉት ዕለታት ሰሙነ ፋሲካ ወይም ትንሣኤ እየተባሉ የየራሳቸው ምስጢራዊ ስያሜ አላቸው፡፡ ይኸውም፡- ✞ ሰኞ- ማዕዶት ይባላል፡- ማዕዶት ማለት መሻገር፣ ማለፍ ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት በፋሲካችን በክርስቶስ ትንሣኤ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ከሃሳር ወደ ክብር መሻገራችንን እናስባለን፡፡ ጌታችን በሞትና ትንሣኤው ነፍሳትን ከሲኦል አውጥቶ ወደ ገነት አሻግሮ ለማስገባቱ መታሰቢያ ሆና «ፀአተ ሲኦል ማዕዶት» ትባላለች፡፡ ዮሐ. 19-18 ሮሜ. 5-10-17 የዳግም ትንሣኤው ማግሥት ያለችው ግን ገበሬው፤ ወንዶቹ እርሻ ቁፋሮውን፣ ንግዱን፣ ተግባረ እዱን ሁሉ ሴቶቹ ወፍጮውን፣ ፈትሉን፣ ስፌቱን የሚጀምሩባት ዕለት ስለሆነች «እጅ ማሟሻ» ሰኞ ትባላለች፡፡ ✞ ማክሰኞ- ቶማስ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ፤ ጌታዬና አምላኬ ብሎ መመስከሩ ይዘከራል፡፡ ዮሐ. 20፡27-29 የትንሣኤው ዕለት እሑድ ማታ ጌታችን በዝግ ቤት ገብቶ ለሐዋርያት ሲገለጽ ቶማስ ሐዋርያ አልነበረም ኋላ ከሔደበት ሲመጣ ሌሎቹ ሐዋርያት ትንሣኤውን ቢነግሩት እኔ ሳላይ አላምንም በማለቱ በዚህ ጥያቄው መሠረት በሳምንቱ ጌታችን በድጋሚ ስለተገለጸ ለዚህ መገለጹ መታሰቢያ ሆና ዕለቲቱ «በቶማስ» ተሰየመች፡፡ ዮሐ. 20-24-30 ✞ ረቡዕ- አልአዛር ይባላል፡- በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አልአዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን፡፡ ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ፤ የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ፡ በድልም ያረገ ንጉሥ መሆኑን እንመሰክራለን፡፡ ከሞተና ከተቀበረ አራት ቀን በኋላ ከመቃብር ጠርቶ ላሥነሣው፣ አላዓዛር መታሰቢያ የእርሱንም ተነሥቶ በማየት በጌታችን ብዙ ሕዝብ ስለአመነበት ቀኒቱ «አላዓዛር» ተብላ ትታሰባለች፡፡ ዮሐ. 11-38-46 ✞ ሐሙስ- አዳም ሐሙስ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና የተገባለት ኪዳን እንደተፈጸመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን፡፡ የአዳም ተስፋው ተፈጽሞለት ከነልጅ ልጆቹ ወደቀደመ የገነት ክብሩ ለመግባቱ መታሰቢያ ሆና «የአዳም ኀሙስ» ተብላ ይኸው ትከበራለች፡፡ ሉቃ. 24-25-49 ✞ አርብ- ቅድስት ቤተክርስቲያን ይባላል፡- በክርስቶስ ደም ተዋጅታ በተመሠረተችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታላቅ መታሰቢያ በመሆኗ በሰሙነ ፋሲካው ያለችው ዐርብ «ቤተ ክርስቲያን» ተብላ ትጠራለች፡፡ ማቴ. 26-26-29 የሐ. ሥራ. 20-28 በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል፡፡ ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው፤ ክርስቶስ ለሕንፃ አልሞተምና፡፡ ✞ ቅዳሜ- ቅዱሳት አንስት ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል፡፡ በሰሙነ ፋሲካው ያለችው ቀዳሚት ሕዝቡ ከአንዳንዱ በስተቀር ገበያ እንኳን ስለማይገበይባት «የቁራ ገበያ» የገበያ ጥፊያ ስትባል በቤተ ክርስቲያን ግን በዘመነ ሥጋዌው በገንዘባቸውና ጉልበታቸው ለአገለገሉት በስቅለቱ ዋይ ዋይ እያሉ እስከ ቀራንዮ ለተከተሉት፣ የትንሣኤው ዕለት ገና ከሌሊቱ ወደ መቃብሩ ሽቱና አበባ ይዘው በመገሥገሣቸው ትንሣኤው ከሁሉ ቀድሞ ለተገለጸላቸው ቅዱሳት አእንስት መልካም መታሰቢያ ሆና «አእንስት» ተብላ ትጠራለች፡፡ ሉቃ. 23-27-33፣ 24-1-01፣ ማቴ. 25-1-11 ✞ እሑድ- ዳግም ትንሣኤ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡ (የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ሰሌዳ መጽሔት) + + + መልካም በዓል!!! + + +

፠በሕማሙ በከይነ፤ ወበትንሣኤሁ ተፈሣሕነ። (#በሕማሙ_አዘንን፤ #በትንሣኤው_ደግሞ_ተደሰትን) ቅዱስ ያሬድ፨ /እንኳን አደረሳችሁ፤ ከቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት፨/

ሰቅለ ቦቱ መድኀኔዓለም» እያሉ ይሳለማሉ፡፡ ካህኑም «እግዚአብሔር ይፍታ» ይላል፡፡ ግብረ ሕማማት ሲነበብበት ከሰነበተው ጠበልም ይረጫል፡፡ የተረፈውንም ጠበል ሕዝቡ ለበረከት ወደየቤቱ ይወስደዋል፡፡ ከዚያም ልኡካኑ ለቅዳሴ እየተዘጋጁ ሊቃውንት መዘምራኑ ምስማክ መወድሱን ካዜሙ በኋላ በመቋሚያ ይዘምሙታል፡፡ አያይዞም በዓመት ሦስት ጊዜ የሚዘመረውን «ይትፌሣሕ» የተባለውን መዝሙር ቃኝተው ከዘመሙ በኋላ «ወምድርኒ ትገብር ፋሲካ፤ ተኀፂባ በደመ ክርስቶስ = ምድርም በክርስቶስ ደም ታጥባ ፋሲካውን ታደርጋለች፡፡» እያሉ ይጸነጽላሉ፡፡ አያይዘውም የመዝሙሩን ሰላም ይጸፋሉ፡፡ ወዲያው መንፈቀ ሌሊት ሲሆን ቅዳሴ ተቀድሶ ይቆረባል፡፡ ከዚያም ዕጣነ ሞገር = በዕጣን ፈንታ ቅኔው ተቁሞ ሠርሖተ ሕዝብ = የሕዝብ ስንብት ከሆነ በኋላ ለመፈሰክ ሕዝቡ ወደየ ቤቱ ይሔዳል፡፡ ሕዝቡ በየቤቱ፣ ካህናቱም ከቤተ ክርስቲያን በየአካባቢው ባህል በተለይ አክፋዮች መጀመሪያ ቅባት አጥቶ የሰነበተ ሆድ እንዲለሰልስ የተሞቀ የተልባ ጭልቃ ይጠጣና የሹሮ ወጥ በቅቤ፣ በአይብ፣ የበረታም በዶሮ ወጥ፣ ወይም በበግና በከብት ሥጋ ወጥ ይገድፋል፡፡ በእርጎ፣ በአይብ የተደራረበ እንጀራ በግፍልፍል የሚገድፉም አሉ፡፡ በአንዳንድ የሰሜኑ ሀገራችን ደግሞ የተልባ፣ የኑግና የሱፍ ጭልቃ ከማር ጋር ታሽቶ ከተጠጣ በኋላ በእርጎ፣ በአይብ፣ በወተት፣ በቅቤና ድልህ በተቀባ እንጀራ ይገድፋሉ፡፡ ሲነጋም ከጾሙ አጋማሽ ጀምሮ ወንዱ ለእርድ የሚሆነውን ሰንጋውን፣ ሲቀልብ፣ በጉን ፍየሉን ሲሞክት ዶሮውን ሲመርጥ፣ ሲገዛ ሲለውጥ፣ ሰንብቶ ነበርና በግልም በኅብረትም ያ ይታረዳል፡፡ ሴቶችም ቅቤውን ሲያነጥሩ፣ በርበሬውን ሲደልሁ፣ ለእንጀራና ዳቦ የሚሆነውን ዱቄት ሲያዘጋጁ ለጠላ የሚሆነውንም እኸል ሲያሰናዱ አይቡን በልዩ ልዩ ቅመም መጣጣ ሲያደርጉና ባዶ ማለትም ወገሚት የተባለውን በሽንኩርት፣ በጤና አዳም፣ ጣዕሙ እንዳይለወጥ ሲቀምሙ ሰንብተው ዝግጅቱ ተከናውኖ ነበር፡፡ ጧትም ይህ የመግደፊያ ዝግጅት በየቤታቸው ለሌላቸው ድኾች በየመንደሩ እየተዞረ «እንኳን ጾመ ልጓሙን ፈታላችሁ» እየተባለ ከሥጋውም፣ ከአይቡም፣ ከቅቤውም ከመጣጣሙም፣ ከእርጐውም ይታደላል፡፡ ከትንሣኤ እሑድ ጀምሮ እስከ ዳግም ትንሣኤ ድረስ ሕዝበ ክርስቲያኑ «እንኳን ጾመ ልጓሙን ፈታላችሁ» እየተባባለ በመጠራራት ዐብሮ ሲበላ ሲጠጣ ልዩ ልዩ ጨዋታ ሲጨዋወት ለንስሐ አባትና ለሽማግሌዎች ለወዳጅ ዘመድም የአክፋይ ዳቦ፣ ወይም የሥጋ ወጥ ግፍልፍል ሲወስድ ይሰነብታል፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን፡፡ (የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ሰሌዳ መጽሔት)

እንኳን በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡ #ፋሲካ_ፋሲካ_ፋሲካ፤ #ተዝካረ_ትንሣኤሁ_ለክርስቶስ፡፡ #ትንሣኤ_ትርጉም_በዓሉና_አከባበሩ_ (ከቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ሰሌዳ መጽሔት የተወሰደ) «ትንሣኤ» የሚለው ቃል የግእዝ ቋንቋ ነው፡፡ መገኛ ቃሉም «ተንሥአ» = ተነሣ የሚለው ግሥ ይሆናል፡፡ «ትንሣኤ» ማለት ታዲያ = መነሣት፣ አነሣሥ ሐዲስ ሕይወት ማግኘት ማለትን ያመለክታል፡፡ «ትንሣኤ» በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በየመልኩ፣ በየዐይነቱ ሲተረጐም ዐምስት ክፍል አለው፡፡ አንደኛው «ትንሣኤ» ኅሊና ነው፡፡ ይህም ማለት ተዘክሮተ እግዚአብሔር ነው፡፡ ሁለተኛውም «ትንሣኤ» ልቡና ነው፡፡ የዚህም ምስጢሩ ቃለ እግዘብሔርን መስማትና በንስሐ እየታደሱ በሕይወት መኖር ነው፡፡ ሦስተኛው «ትንሣኤ» ለጊዜው የሙታን በሥጋ መነሣት ይሆናል፡፡ ነገር ግን ድጋሚ ሞት ይከተለዋል፡፡ አራተኛው «ትንሣኤ» የክርስቶስ በገዛ የባሕርይ ሥልጣኑ ሞትን ድል አድርጎ መነሣት ነው፡፡ የእርሰ ትምህርታችንም መሠረት ይኸው እንደሆነ ይታወሳል፡፡ አምስተኛውና የመጨረሻው «የትንሣኤ» ደረጃም የባሕርይ አምላክ የጌታችን የመድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን «ትንሣኤ» መሠረት ያደረገ «ትንሣኤ ዘጉባኤ» ነው፡፡ ይህም ከዓለም ኅልፈት በኋላ ሰው ሁሉ እንደየሥራው ለክብርና ለውርደት፣ ለጽድቅና ለኩነኔ በአንድነት የሚነሣው የዘለዓለም ትንሣኤ ይሆናል፡፡ ወደተነሣንበት ዐላማ ስንመለስ የትንሣኤ በዓል በቃሉም ምስጢር በይዘቱም ስለሚመሳሰሉ ጥላው ምሳሌውም፣ ስለሆነ «ፋሲካ» ተብሎ ይጠራል፡፡ «ፋሲካ» ማለት በዕብራይስጥ ቋንቋ «ፌሳሕ» በጽርእ በግሪክኛው «ስኻ» ይባላል፡፡ ይህም ወደ እኛው ግእዝና ዐማርኛ ቋንቋችን ሲመለስ ፍሥሕ ዕድወት = ማዕዶት፣ በዓለ ናእት = የቂጣ በዓል፣ እየተቸኮለ የሚበላ መሥዋዕት፣ መሻገር መሸጋገር ማለት ነው፡፡ ነጮቹ በእንግሊዝኛው «ስኦቨር» ይሉታል የዚህም ታሪካዊ መልእክቱ በዘመነ ኦሪት ይከበር የነበረው በዓለ ፋሲካ እስራኤል ዘሥጋ ከግብጽ የባርነት ቀንበር ወደነፃነት የተላለፉበት፣ ከከባድ ሐዘን ወደ ፍጹም ደሰታ፣ የተሸጋገሩበት በዓል ነበር፡፡ በዚህ ኦሪታዊ ምሳሌ በዓል አሁን አማናዊው በዓል «ትንሣኤ» ተተክቶበታል፡፡ ፋሲካ፣ በዓለ ትንሣኤ በዘመነ ሐዲስ እስራኤል ዘነፍስ የሆኑት ምእመናነ ክርስቶስ ትንሣኤውን የሚያከብሩበት ዕለት ሆኖ በእርሱ ትንሣኤ ከኀጢአት ወደ ጽድቅ፣ ከኀሳር = ከውርደት ወደክብር፣ ከጠላት ሰይጣን አገዛዝ ወደ ዘለዓለማዊ ነፃነት፣ ከአደፈ፣ ከጐሰቆለ አሮጌ ሕይወት ወደ ሐዲስ ሕይወት የተሻገሩበት ታላቅ መንፈሳዊ የነፃነት በዓል ነው፡፡ ክርስቲያኖች የትንሣኤን በዓል በታላቅ ደስታና መንፈሳዊ ስሜት ያከብሩታል፡፡ ስለዚህም ከበዓላት ሁሉ የበለጠ ሆኖ ይታያል፡፡ #የበዓሉ_አከባበር መድኀኒታችን ሞትን በሞቱ ድል መትቶ፣ ስሙና መቃብርን አጥፍቶ በሥልጣኑ የተነሣው መጋቢት 29 ቀን በ34 ዓ.ም እንደሆነ ታሪከ ቤተ ከርስቲያን ያስረዳል፡፡ የትንሣኤ በዓል መከበር የጀመረው በቅዱሳን ሐዋርያትና በሰብዐ አርድእት፣ ኋላም በየጊዜው በተነሡት ተከታዮቹ ምእመናን ነው፡፡ ድምቀቱና የአከባበር ሥርዐቱ ይበዛ ይቀነስ እንደሆን እንጂ መከበሩ ተቋርጦ አያውቅም፡፡ «እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው አደረሰን» ሲወርድ ሲወራረድ ከዚህ በደረሰው ትውፊት መሠረት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ግብረ ሕማማቱን ስታነብ ሰንብታ ለትንሣኤ እሑድ አጥቢያ ማታ በ2 ሰዓት «ለጸሎት ተሰብሰቡ» የደወል ድምፅ-ታሰማለች፡፡ ካህናቱ ተሰብስበው ሥርዐቱን በጸሎት ይጀምራሉ፡፡ ሕዝቡም ይሰበሰባል፡፡ ቤተ ክርስቲያኑንም ይሞላዋል፡፡ ካህናቱ ሁሉ ለጸሎተ ፍትሐትም፣ ለሥርዐቱም መዝሙረ ዳዊት፣ ነቢያት፣ ሰሎሞንና ውዳሴ ማርያም ከደገሙ በኋላ «ተፈሥሒ ማርያም ለአዳም ፋሲካሁ» የሚለውን ግጥማዊ የደስታ መዝሙር ይዘምራሉ፡፡ ቀጥሎም ምንባባቱና ሌላውም ሥርዐት ከተፈጸመ በኋላ ጸሎተ አኰቴት ተደርሶ ዲያቆኑ «ወተንሥአ እግዚአብሔር ከመ ዘንቃህ እምንዋም፣ ወከመ ኀያል ወኅዳገ ወይን፣ ወቀተለ ፀሮ በድኅሬሁ = እግዚአብሔር ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተነሣ፤ የወይን ስካር እንደተወው ኀያል ሰውም፣ ጠላቱን በኋላው ገደለ፡፡» የሚለውን የዳዊት መዝሙር ለመስበክ = ለመዘመር ነጭ ልብሰ ተክህኖ ለብሶ አክሊል ደፍቶ፣ የመጾር መስቀል ይዞ፣ እንደእርሱው ነጭ ልብሰ ተክህኖ በለበሱ ደማቅ የጧፍ መብራት በሚያበሩና ድባብ = ጃንጥላ በያዙ ሁለት ዲያቆናት በግራ በቀኝ ታጅቦ ከመቅደስ ብቅ ብሎ በቅድስት ይቆማል፡፡ መዝ. 77-65 ይህም በጌታችን መቃብር በራስጌና በግርጌ በታዩት መላእክት ምሳሌ ነው፡፡ ዮሐ.20-12 ዲያቆኑ ከላይ የተጠቀሰውን ምስባክ በረጅም ያሬዳዊ ዜማ በሰበከ ጊዜ ካህናቱ ከበሮ እየመቱና በእርጋታ እያጨበጨቡ ተቀብለው ይዘምራሉ፡፡ ሕዝቡም የቻለው በዝማሬው ያለበለዚያም በጭብጨባና በልልታ የደስታ ዝማሬው ተሳታፊ ይሆናል፡፡ ይህ ምስባኩ በዲያቆኑ 2 ጊዜ በመላው ካህናትም 2 ጊዜ ለመጨረሻ ጊዜ ዲያቆኑም መላው ካህናትም አንድ ጊዜ ብለው 5 ጊዜ ይሆናል፡፡ 5500 ዘመን ሲፈጸም በጌታችን ሞትና ትንሣኤ ዓለም ለመዳኑ ምሳሌያዊ ማስረጃ ነው፡፡ ቀጥሎም ካህኑ ትንሣኤውን የሚያበሥር ወንጌል ከማቴዎስ፣ ከማርቆስና ከሉቃስ አውጥቶ ያነባል፡፡ ከዮሐንስ ወንጌል ያለው የትንሣኤው ወንጌል ኋላ ለቅዳሴው ጊዜ ይቆያል፡፡ ዮሐ. 20-1-09 በማስከተል የዲያቆኑን መስቀል ጨብጦ ከሊቃውንቱ መዘምራን ሥራው የሚመለከተው ወይም የተመደበው ባለሙያ መዘምር «ትንሣኤከ ለእለ አመነ» የሚለውን እስመ ለዓለም ከቃኘ በኋላ ለበዓሉ ተስማሚ የሆነው 2 አርያም ተመርቶ በመቋሚያ ይዘመማል፤ በማስከተልም «ዮም ፍሥሐ ኮነ በሰንበተ ክርስቲያን፣ እስመ ተንሥአ ክርስቶስ እሙታን = ክርስቶስ ከሙታን ቀድሞ ተለይቶ ተነሥቷልና በሰንበተ ክርስቲያን ዛሬ ደስታ ሆነ፡፡...» የሚለውን አንገርጋሪ ያመለጥናል = ይመራል፡፡ በግራ በቀኝ እየተነሣ መዘምራኑም ይዘምሙታል ይጸፉታል፤ ያለዝቡታል፤ ወዲያውም «ብርሃነከ ፈኑ፤ ለእለአመነ = ለአመነው ብርሃንህን ላክልን፡፡» የሚለውን እስመ ለዓለም እየወረቡ መብራት እያበሩ ዑደት ያደርጋሉ = ቤተ ክርስቲያኑን በውስጥ ይዞራሉ፡፡ በዚህ ጊዜ «በጨለማ የነበራችሁ ሕዝቦች ኑ የትንሣኤውን ብርሃን እዩ፣ ብርሃኑንም ወስዳችሁ የብርሃኑ ተካፋይ ሁኑ፡፡» እያለች ቅ/ቤተ ክርስቲያን ስታዘጋጅ የሰነበተችውን ጧፍ እያበራች ታድላቸዋለች፡፡ ሕዝቦቹም ካህናቱን ተከትለው በታላቅ ደስታና ድምቀት ዑደት ያደርጋሉ፡፡ መዘምራኑና ካህናቱ ከዑደት ሲመለሱ «ይእቲ ማርያም» የተባለው የኪዳን ሰላም ይጸፋና ኪዳን ተደርሶ ሲያበቃ እንደ ቦታው ደረጃ ፓትርያርኩ ወይም ሊቀ ጳጳሱ ወይም ደግሞ አለቃው፣ ቆሞሱ፣ ካህኑ ዘለግ ባለ ድምፅ በንባብ «ክርስቶስ ተንሥአሙታን = ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሣ፡፡» ሲል ካህናቱና መዘምራኑ በዐቢይ ኀይል ወሥልጣን = በታላቅ ኀይልና ሥልጣን፡፡» ብለው ይቀበላሉ፡፡ አሁንም ካህኑ «አሰሮ ለሰይጣን = ሰይጣንን አሰረው» ባለ ጊዜ መላው ካህናት «አግዐዞ ለአዳም = አዳምን ሐርነት ነጻነት አወጣው» ይላሉ፡፡ ቀጠል አድርጎ ቄሱ «ሰላም፣ ፍቅር፣ አንድነት» ሲላቸው ሁሉም ካህናት «እምይእዜሰ = ከዛሬ ጀምሮ» ብለው ይቀበላሉ፡፡ ቄሱም «ኮነ ፍሥሐ ወሰላም = ሰላምና ደስታ ሆነ» ብሎ ሦስት ጊዜ ዐውጆ ሲያበቃ «ነዋ መስቀለ ሰላም» እያለ መስቀል ሲያሳልም ካህናትና ሕዝቡም «ዘተ

ነዳያንን በማስፈሰክ የ50 የዓመታት አገልግሎት ጕዞ፡፡ በአዲስ አበባና በሃገራችን ላሉ ሌሎች ሰንብት ትምህርት ቤቶች ፋና ወጊ የኾነ አገልግሎት፡፡ ወንድማችንና አባታችን አርቲስት ችሮታው በዚህ አገልግሎት ላይ ግንባር ቀደምት ናቸው፡፡ ነዳንንና አቅመ ደካሞችን በትንሣኤ በዓል ላይ አብሮ መፈሰክ ከዛሬ 50 ዓመታት በፊት በ1961 ዓ.ም. በ1 በግ ተጀምረ፤ ለ3 ዓመታት በ1ድ በግ ቀጥሎ፤ በ1964 ዓ.ም. ወደ 2 በግ እንዲሁም አንዲት እናት ባመጡት 1 መሶብ እንጀራና 1 ብረት ድስተ ወጥ ተስፋፋ፤ ….. ወደ 1 በሬ.. ወደ 2 በሬ… አድጎ ዛሬ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ደግሞ በ3ት በሬዎች እያስተናገድን እንገኛለን፡፡ እንደ መድኀኔ ዓለም ፈቃድ በየዓመቱ እንደሚደረገው ዘንድሮም ነዳያንን በደብራችን ምርፋቅ ቤት (ሰንበቴ ቤት /ደጀ ሰላም/)፣ በጸበል ቦታ ያሉትን፣ በገዳም ውስጥ ያሉትን መነኰሳትና የአብነት ተማሪዎች ሰለምናስፈስክ፤ ለመርዳት የሚያስፈልጉትን በየቤታችሁ እንጀራና የወጥ መሥሪያ ጥሬ ዕቃዎችን ለመሰብሰብ ለሚመጡ አባላቶቻችን እንደተለመደው አዘጋጅታችሁ እንድትጠብቁ፤ እንዲሁም (ገንዘብ፣ ልብስ፥ ሳሙና፥ ንጽሕና መጠበቂያ፣ በሬ፥ በግ፥ ፍየል፣ የተማሪዎች የመማሪያ ቊሳቊሶችን) ሰ/ት/ቤታችን ድረስ በመምጣት አስተዋጽዖ እንድታደርጉ በመድኀኔዓለም ስም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡ ‹‹ለችግረኛና ለምስኪን የሚያስብ ምስጉን ነው፤ እግዚአብሔር በክፉ ቀን ያድነዋል፡፡›› መዝ. 40፥1

#የዐርብ_ፎቶ_ስብስብ_፭፤ ወደ ቀጨኔና ሰሜን ማዘጋጃ በነጻ የታክሲ አገልግሎት 7 ዓመታት በላይን ያስቈጠረ፡፡