en
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Open in Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 381 subscribers, ranking 5 584 in the Religion & Spirituality category and 2 199 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 381 subscribers.

According to the latest data from 03 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 21 over the last 30 days and by -7 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 21.13%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 9.50% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 250 views. Within the first day, a publication typically gains 1 462 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 16.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 04 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

15 381
Subscribers
-724 hours
+117 days
+2130 days
Posts Archive
በድጋሚ ፤ አዎ የብጹዕነታችው ውሳኔ እየተከበረ አይደለም :: ሊንኩን 👇👇👇👇በመጫን ወደ facebook ገጹ ሔደው አስተያየት ይስጡ ::አሁኑኑ! https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool/posts/2884002708584475

ለሰ/ት/ቤቱ አባላት እንዲሁም ለአጥቢያችን ምእመናን በሙሉ #_የብጹዕ_አባታችን_አቡነ_መልከጼዴቅ ውሳኔ አሁንም ሊተገበር አልቻለም:: የአካባቢው ምእመናን እና ሰ/ት/ቤቱ በጋራ ሆነን ወደ ሐገረ ስብከቱ #_ለአፈጻጸም_እንሂድ_የሚል_ጥያቄ_እየበረታ_ነው፡፡ ብጹዕነታቸው የካቲት 29/2013 ዓ.ም የደብሩን አስተዳደር እና የደብሩን ሰንበት ት/ት ቤት እንዲሁም የአጥቢያውን ምእመናን በሐገረ ስብከቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ ካወያዩ በኋላ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ በዚሁ እለት ወደ ደብራችን በመምጣት የመስክ ምልከታ አድርገው እንደነበር የሚታወቅ ነው፡፡ ብጹዕነታቸው ከመስክ ምልከታ በኋላ መጋቢት 10/2013 ዓ.ም በደብዳቤ ቁጥር 3008/13/13 የደብሩ ሰንበት ት/ት ቤት ወደ ቀደመ ቦታው መዋዕለ ህጻናት ግቢ ውስጥ እንዲገባ ውሳኔያቸውን ልከዋል፡፡ ከውሳኔውም በኋላ መጋቢት 20/2013 ዓ.ም በሐገረ ስብከቱ ቢሮ የደብሩን ሰንበት ት/ት ቤትና የደብሩን አስተዳደር ሰራተኞችን በመጥራት ሰላማዊ በሆነ መንገድ ውሳኔው እንዲፈጸምና የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ እንዴት መፈጸም እንዳለበት በቃለ ጉባኤ ተነጋግረን እንድንመጣ መመርያ ተሰጥቶን በብጹዕነታቸው ጸሎት ስብሰባውን አጠናቀን ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ የደብሩ ማኅበረ ካህናት የመረጧቸው 4 ካህናት አባቶች ጋር ሆነን የጋራ ስብሰባ ካደረግን በኋላ በ24/07/2013 ዓ.ም ስብሰባችንን ጨርሰን የጋራ ቃለ ጉባኤ ይዘን ተፈራርመን የጨረስን ቢሆንም አሁንም የደብራችን አስተዳደር ከካህናቱ ጋር የተፈራረምነውን ቃለ ጉባኤ ለብጹዕነታቸው አስማሚ በሆነ መንገድ ሊያደርስ አልቻለም፡፡ ሰ/ት/ቤቱም ቃለ ጉባኤውን ያቀረብን ቢሆንም እስካሁን ድረስ ከስራ አስኪያጁ ቢሮ ወጥቶ ብጹዕነታቸው ጋር መድረስ ግን አልቻለም፡፡ ከብጹዕነታቸው ስር ያሉ #_ሹማምንቶች_ውሳኔው ወደ አፈጻጸም እንዲሄድ የሚያደርጉት ምንም አይነት ጥረት አይታይም፡፡ ለበርካታ ጊዜያት ይህንን የሰ/ት/ቤቱን ጉዳይ እያስተባበሩ የሚገኙ ወንድሞች እና እህቶች ወደ ሀገረ ስብከቱ በተደጋጋሚ ቢያቀኑም ተጨባጭ መልስ የሚሰጣቸው አካል አላገኙም :: በዚህ ምክንያት የደብሩ ሰ/ት/ቤት በቀን 9/08/2013 ዓ.ም በጠራው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ጉዳያችንን #_በህብረት_ሄደን_ማስፈጸም_መቻል_ አለብን የሚል ውሳኔ ወስኗል፡፡ የአካባቢው ምእመናን እና ወጣቶችም በዚህ ሳምንት ውስጥ በህብረት ሆነን ለልጆቻችን የተወሰነውን ውሳኔ ማስፈጸም መቻል አለብን የሚል ጥያቄ በብርቱ #_እያነሱ_ነው፡፡ ሰ/ት/ቤቱ ለሰላም ሲባል፣ ለአንድነት ሲባል ብዙ ብንጥርም ፣ አንጋፋ የሆኑ የአካባቢውን ሽማግሌዎች ብንልክም የደብሩ አስተዳደር ሽማግሌዎቹን መቀበልም አልቻለም፣ ከዚህ ይልቅ 14 የሰንበት ት/ት ቤታችን አባላት ‹‹ ሰላም በማደፍረስ ከሰናል›› ብለው የደብራችን አስተዳዳሪ በተናገሩት መሰረት #ክስ_ከፍተዋል፡፡ ምድራዊ እስር ቤትን የሚፈራ ሰንበት ተማሪ ባይኖርም አሁንም ግን የምንጠይቀው ጥያቄ #_የብጹእነታቸው_መመርያ_ይተግበር የሚል ነው፡፡ ስለሆነም ይህንን ጥያቄ ከመላው የቀጨኔ ምእመናን ጋር ሆነን ለብጹዕነታቸው እናቀርባለን:: #Share በማድረግ ለመላው የአጥቢያችን ምዕመናን እንድናደርስ በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃልን፡፡ #share #_ሰላመ_እግዚአብሔር_አይለየን

#መጋቢት 10/2013 ዓ.ም ቡራኬያቸው ይድረሰንና የካቲት 29/2013 ዓ.ም ብጹእ አቡነ መልከጸዴቅ የአ.አ እና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የደብሩን ሁኔታ በአካል ተገኝተው የመስክ ምልከታ
#መጋቢት 10/2013 ዓ.ም ቡራኬያቸው ይድረሰንና የካቲት 29/2013 ዓ.ም ብጹእ አቡነ መልከጸዴቅ የአ.አ እና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የደብሩን ሁኔታ በአካል ተገኝተው የመስክ ምልከታ ካደረጉ በኀላ የወሰኑት ውሳኔ::

#ታህሳስ 12/2013 ዓ.ም አሁን በአገልግሎት ላይ የሚገኙት የአ.አ ሐገረ ስብከት ስራ አስኪያጅ መምህር አካለወልድ ተሠማ መስከረም 28/2013 ዓ.ም የተወሰነው ውሳኔ የደብሩ አስተዳደር አለመፈጸሙ
#ታህሳስ 12/2013 ዓ.ም አሁን በአገልግሎት ላይ የሚገኙት የአ.አ ሐገረ ስብከት ስራ አስኪያጅ መምህር አካለወልድ ተሠማ መስከረም 28/2013 ዓ.ም የተወሰነው ውሳኔ የደብሩ አስተዳደር አለመፈጸሙን ተረድተው የወሰኑት ውሳኔ::

#መስከረም 28/2013 ዓ.ም በወቅቱ የነበሩት የአ.አ ሐገረ ስብከት ስራ አስኪያጅ መልአከ ሕይወት አባ ኃ/ገብርኤል ነጋሽ ለውሳኔ እንዲረዳቸው ከቅዱስ ፓትርያሪኩ በተሰጠ መመርያ 5 አባላት ያሉትን
#መስከረም 28/2013 ዓ.ም በወቅቱ የነበሩት የአ.አ ሐገረ ስብከት ስራ አስኪያጅ መልአከ ሕይወት አባ ኃ/ገብርኤል ነጋሽ ለውሳኔ እንዲረዳቸው ከቅዱስ ፓትርያሪኩ በተሰጠ መመርያ 5 አባላት ያሉትን አጣሪ ኮሚቴዎች ልከው ከኮሚቴው በቀረበው ሪፖርት መነሻነት የወሰኑት ውሳኔ:

ሰንበት ት/ት ቤታችን ላለፉት 2 ዓመታት በቋሚ የማስተማርያ ቦታ ጥያቄ ምክንያት በርካታ ፈተናዎችን በመድኃኔዓለም ቸርነት እያለፈ እዚህ ደርሷል፡፡ በተለያዩ ጊዜያትም የተለያዩ ውሳኔዎች ተወስነዉለታል እነዚህም፡- #መስከረም 28/2013 ዓ.ም በወቅቱ የነበሩት የአ.አ ሐገረ ስብከት ስራ አስኪያጅ መልአከ ሕይወት አባ ኃ/ገብርኤል ነጋሽ ለውሳኔ እንዲረዳቸው ከቅዱስ ፓትርያሪኩ በተሰጠ መመርያ 5 አባላት ያሉትን አጣሪ ኮሚቴዎች ልከው ከኮሚቴው በቀረበው ሪፖርት መነሻነት የወሰኑት ውሳኔ:: #ታህሳስ 12/2013 ዓ.ም አሁን በአገልግሎት ላይ የሚገኙት የአ.አ ሐገረ ስብከት ስራ አስኪያጅ መምህር አካለወልድ ተሠማ መስከረም 28/2013 ዓ.ም የተወሰነው ውሳኔ የደብሩ አስተዳደር አለመፈጸሙን ተረድተው የወሰኑት ውሳኔ:: #መጋቢት 10/2013 ዓ.ም ቡራኬያቸው ይድረሰንና የካቲት 29/2013 ዓ.ም ብጹእ አቡነ መልከጸዴቅ የአ.አ እና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የደብሩን ሁኔታ በአካል ተገኝተው የመስክ ምልከታ ካደረጉ በኀላ የወሰኑት ውሳኔ::

ሰባተኛው ሳምንት ꔰኒቆዲሞስꔰ ይባላል፤ በዚህ ሳምንትም ይህ ይታሰብበታል፡፡ ‹‹ኒቆዲሞስ››፤ * አይሁዳዊ ሲሆን ከፈሪሳውያን ወገን የነበረ ነው * በኢየሩሳሌም በሀብት ቢሉ በዕውቀት እንዲሁም በሥልጣን የአይሁድ አለቃ ነበር፡፡ * ማታ ማታ ጌታችን ዘንድ እየተገኘ ይማር ነበር፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ እንዲህ አስቀምጦልናል፦ ꔰ ‹‹ከፈሪሳውያን ወገን የአይሁድ አለቃ የሆነ ኒቆዲሞስ የተባለ አንድ ሰው ነበር፤ እርሱም በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ፦ ‹‹መምህር ሆይ እግዚአብሔር ከእሱ ጋር ከሆነ በቀር አንተ የምታደርጋቸውን እነዚህ ተዓምራቶች ሊያደርግ የሚችል የለምና መምህር ሆነህ ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደመጣህ እናውቃለን›› አለው፡፡ ꔰ ጌታችን ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው። ጌታችን ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው። ፨ ኒቆዲሞስም፦ ሰው ከሸመገለ በኋላ እንዴት ሊወለድ ይችላል? ሁለተኛ ወደ እናቱ ማኅፀን ገብቶ ይወለድ ዘንድ ይችላልን? አለው። ꔰ ጌታችን ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም። ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው፥ ከመንፈስም የተወለደ መንፈስ ነው።›› /ዮሐ. ፫፥ ዘ፩-፲፭//ፍ.ሕ.ሰ.ት.ቤት/ ለምን በሌሊት ይመጣ ነበር? ꔰ አይሁድ ‹‹ማንም ከእኛ ወገን የሆነ የክርስቶስ ደቀ መዝሙር ከሆነ ሀብት ንብረቱ ይወሰድ፣ በቤተመቅደስ አይግባ፣ መሥዋዕት አይሥዋ›› ብለው ነበርና አይሁድን ፈርቶ፥ ሀብት ንብረቱን ወዶ እንዳይታወቅበት በሌሊት ይመጣ ነበር፡፡ ꔰ በሌላ በኩል ደግሞ የቀን ልብ ባካና ነው፤ ዓይን ብዙ ያያል፥ ሐሳብ ይበታተናል፡፡ በተሰበሰበ ልብ ለመማር፤ በተጨማሪ ‹‹ሊቅ ነኝ›› እያለ ‹‹እስከ ዛሬ ትምህርት አልጨረሰም›› እንዳይሉት በሌሊት ይመጣ ነበር፡፡ ꔰ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም እንኳን ለመማር የመጣውን እራሱ እየሄደ ያስተምር ነበርና ኒቆዲሞስ ምንም በሌሊት ቢመጣም ማወቅን ፈልጎ ነውና ስለዳግም መወለድ /ስለጥምቀት/ በእግዚአብሔር ልጅ ስለማመንና ስለ ጽድቅ ስራ በዝርዝር አስተምሮታል፡፡ ꔰ ኒቆዲሞስ በመጨረሻው ቀን በዕለተ ዐርብ በስቅለቱ ጊዜ፤ ከመስቀል ላይ ሥጋውን ለማውረድና ገንዞ ለመቅበር ቀድሞ ተገኝቷል፡፡ /ዮሐ. ፲፱፥፴፰/ /ፍ.ሕ.ሰ.ት.ቤት/ ከኒቆዲሞስ ሕይወት የምንማረው፡- ፩. ትሕትና፦ ኒቆዲሞስ በትምህርት፣ በሹመት፣ በባለጸግነት የአይሁድ አለቃ ሲሆን አለቅነቱ ግን ከጌታ እግር ስር ቁጭ ብሎ እርሱ ተገኝቶ ለመማር አልከለከለውም፡፡ /በጽሑፉ መጨረሻ ያለውን ቅኔ ተመልከቱ/ ፪. አለማመካኘት፦ ከመጀመሪያ ሰዎች ከአዳምና ከሔዋን ጀምሮ ሰዎች በምክንያተኝነት በአመፅ መንገድ ይጓዛሉ፡፡ ኒቆዲሞስም ወደ ጌታ በመቅረቡ የጸሐፍት ፈሪሳውያን አድማና ግርግር ታላቅ እንቅፋትና ምክንያት መሆን እንደሚችል ያውቃል፡፡ ነገር ግን ይህ ምክንያት በእግዚአብሔር ፊት እንደማያዋጣ አውቆ የሚያወጣውን አደረገ፡፡ ፫. ጥበብ፦ በክርስትና ጉዞ ውስጥ ጥበብ የመጀመሪያ ቦታ ትይዛለች፡፡ ኒቆዲሞስም ጕዞውን በጥበብ አደረገ፡፡ በሌሊት ያደረገበት ምክንያት፡- ራሱ መምህር ሆኖ ሌላ ትምህርት አስፈለገው ብለው ሌሎች እንዳይሰናከሉበት፣ የመዓልት ልቦና ስለሚሰበሰብ በቂ ዕውቀት ለማግኘት፣ መንፈሳዊ ፍሬ ለማፍራት በመዓልትም በሌሊትም ወደ እግዚአብሔር መቅረብ እንዳለብን ለማጠየቅ፣ ከአዳም ጀምሮ እስከ ክርስቶስ ያሉ ነፍሳት በሲዖል ይገኛሉ ሲል፣ በመዓልትም በሌሊትም ብትፈልጉ ትገኛለች ሲል ነው፡፡ በእውነት ግሩም ጥበብ! ፬. የተነገረውን አምኖ በመቀበሉ፡- ጸሐፍት ፈሪሳውያን ብዙ ምክንያቶች እየደረደሩ የጌታን አምላክነት አምኖ መቀበል ሲያቅታቸው እርሱ ግን ጌትነቱን ለመቀበል ጊዜ አልወሰደበትም፡፡ ፭. ለእውነት መመስከር፡- እነርሱ ሲክዱ ጌታ ላይም ትርፍ ቃል ሲናገሩ፤ በድፍረት መክሰሳቸውን እየነገራቸው የጌታችን አምላክነቱን በግልጽ ይመሰክር ነበር፡፡ ፮. ጽንዓት፡- ብዙዎች በመከራ ጊዜ ላይለዩት ቃል ቢገቡም መጨረሻ ላይ ያኔ በመከራ ሰዓት ከመስቀሉ ሥር ሊገኙ የቻሉ ጥቂቶች ናቸው፡፡ ኒቆዲሞስም በዚች ሰዓት ያንን መከራ ታግሶ በጽነዓት ከዮሴፍ ጋር የጌታን ሥጋ ከመስቀል አውርደው በአዲስ መቃብር ቀብረውታል፡፡ ꔰ ወስብሐት ለእግዚአብሔርꔰ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/ #share Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem Finotehiwotsundayschool.com

ሚያዝያ 6 ጌታችን በትንሣኤው ሳምንት ለሐዋርያው ቶማስ ተገለጸለት:: #share በእጆቹና በእግሮቹና ውስጥ የችንካሮቹን ምልክትም አሳየው የቶማስንም እጅ ይዞ በመለኮታዊ ጎኑ ውስጥ አኖረውና በጦር የ
ሚያዝያ 6 ጌታችን በትንሣኤው ሳምንት ለሐዋርያው ቶማስ ተገለጸለት:: #share በእጆቹና በእግሮቹና ውስጥ የችንካሮቹን ምልክትም አሳየው የቶማስንም እጅ ይዞ በመለኮታዊ ጎኑ ውስጥ አኖረውና በጦር የተወጋበትን ቦታ አሳየው ቶማስም ጌታዬና ፈጣሪዬ ሆይ መነሣትህን አመንኩ አለ ፡፡ ጌታችንም የሚመሰገንስ ሳያየኝ የሚአምንብኝ ነው ብሎ መለሰለት፡፡ ቶማስ እጁን ወደ ጎኑ ባስገባ ጊዜ እጁ በመለኮት እሣት ተቃጠለ በአመነ ጊዜ ደግሞ እጁ ከመቃጠል ዳነች ፡፡ ‹‹ ትርጓሜ ወንጌል ›› ሚያዝያ 6 ይህች ዕለት የአዳም እና የሔዋና መታሰቢያ ናት! ሚያዝያ 6 ልደቱ ለኖኀ ወቅዱስ ዳዊት /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/ #share Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem Finotehiwotsundayschool.com