en
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Open in Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 406 subscribers, ranking 5 570 in the Religion & Spirituality category and 2 189 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 406 subscribers.

According to the latest data from 12 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 76 over the last 30 days and by 7 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.12%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 9.38% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 871 views. Within the first day, a publication typically gains 1 446 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 23.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 13 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

15 406
Subscribers
+724 hours
+347 days
+7630 days
Posts Archive
የሰው ጭንቅላቱ ትግሬ፥ አንገቱ ዐማራ፥ ወገቡ ኦሮሞ፥ ክንዶቹ ጉራጌ፥ እግሩ ደቡብ፥ ዐይኑ ቤንሻንጉል ፥ ታፋው ሺናሻ፥ ደረቱ ሱማሌ፥ ታፋው ቅማንት፥ ትከሻው አፋር፥ ክርኖቹ አገው፥ …….. ቢሆኑ፤ ሁሉም አካላት ካልተባበሩና ካልተናበቡ ሰው ሊሆንና ሊባል እንደማይችል ሁሉ፤ በኢትዮጵያ የምንገኝ ከ80 በላይ ቋንቋ የምንናገር ካልተደማመጥንና ካልተናበብን ኢትዮጵያ አንሆንም፥ አንባልምም፡፡ የዘረኝነት ጭቅቅትና ቆሻሻ የሚለቀውና የሚወገደው በጾምና በጸሎት ነው፡፡ /በ06/07/2011ዓ.ም. ከተካሄደ የከዐርብ ጕባኤ የተወሰደ/ #1123ኛ_ሳምንት_የዐርብ_ጕባኤ_በተለመደው_ሰዐት_ዛሬ_ መጋቢት_13_ይቀጥላል፡፡ ** የሰው በርካታ አካላት አሉት (212 አጥንቶች፤ 600አካቢ የሥጋ ክፍሎች /Mussels/ ፤ እጅግ በጣም ብዙ ነርቮች፤ ሌሎችም ብዙ የብዙ ብዙ የሰውነት አካላት ያሉት ነው፤ ከዕለታት አንድ ቀን ሁሉም እኔ እበልጥ ፥ እኔ እበልጥ /ነፋስ ማስተንፈሻን ከነመፈጠሯም ረስተዋት/ ሲፎካከሩ እርሷ ግን ዝም ብላ ቆየች፤ ጭቅጭቁና ንትርኩ እያገረሸና እየበሳበት ሄደ እንጂ መፍትሔ አለመምጣቱን ያየችው የነፋስ መውጫ ቀዳዳም ትዕግትስቷን ስለተፈታተኑት ነፋስ እንዳይወጣ ከለከለች፤ በዚህ ጊዜ ሁሉንም ጭንቅ ያዘው፤ እንኳን ሊጨቃጨቅ ለራሱ ሕልውናም የሚያሰጋው ሆነና ጭቅጭቁን ትቶ ማሪን አስተንፍሺን፥ ተጨንቀን ልንሞት ነው፤ እንስማማለን፤ ተስማምተንም እንደማመጣለን አሉ፤ …. እርሷም ከልባቸው እስኪመለሱ ትምህርት ሰጥታ ይቅር አለቻቸው፤ በኢትዮጵያ ውስጥ የምንገኝ ከ80 በላይ ቋንቋ ተናጋሪዎችም ከእነዚህ የሰውነት ክፍሎቻችን ትምህርት ወስደን መደማመጥና መናበብ ከምንጊዜውም በላይ ያስፈልገናል፡፡

የኢትዮጵያን ምሥጢራት ከጥራዝ እስከ ጥራዝ ያጠኑት፤ ከልጅነት /ከ7 ዓመታቸው/ እስከ እውቀት በታላቁ ገዳማችን ገዳመ ዋሊ (ዋልድባ) ያደጉት ፥ የተማሩትና የመነኮሱት፥ በዋልድባ ያሉ በርካታ ምሥጢራትን የቀሰሙት፤ .... ኀዋላ ምስካዬ ኅዙናን ገዳምን ለበርካታ ዓመታት ያስተዳደሩት፤ ወደ ውጭ በመውጣት የPHD ትምህርት የተማሩት፤ በጠቅላይ ቤተ ክህነት የቅርስ ጥበቃ መምሪያ ኃላፊ የነበሩት፤ ፫ት መጻሕፍትን የከተቡት ምሁሩና ሊቁ ፥ ተመራማሪውና ተጠያቂ የኾኑት አባት አባ ተሥፋ ሥላሴ ሞገስ አርፈዋል፤ ቀብራቸውም ዛሬ መጋቢት ፲፪ ፳፻፲፩ ዓ.ም. በደብረ ዘይት ሂዲ ካህኑ መልከ ጼዴቅ ከ፱ - ፲ ሰዐት ይፈጸማል፨ ወተቀወልዎ መላእክት በስብሐት ወበማኅሌት፤ ወአብዕዎ ኢየሩሳሌም ሰማያዊተ (ሂዲ ካህን መልከ ጼዴቅ)፤ አብዕዎ ተሥፋ ሥላሴ፨

አንብብዋ ለዛቲ ጦማር እምጥንታ፥ እስከ ተፍጻሜታ፤ በትዕግስት (ይህችን ጽሑፍ በትዕግስት ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ አንብቧት)፤ ብዙ ጥቅም ታገኙበታላችሁና፡፡ #ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን)፤#ክፍል#፲፩_ #ሰይጣን_በውኃ_ምንጮች_ለምን_እንደሚያድር፤ #ነገሥታት_መኳንንትንና_መሣፍንትን_በምን_እንደሚፈትናቸው፡፡ #ጳጳሳትንና_መነኰሳትን_በምን_እንደሚፈትናቸው፡፡ አባ ጳውሊ፤ በውሃ ምንጮች እንደምታድሩ ሰዎች የሚናገሩት እውነት ነውን? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ አዎ እውነት ነው አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ የምታድሩት በምን ምክንያት ነው አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ የፈጣሪያቸውን ሕጉንና ትእዛዙን ቢያፈርሱና ስሙንም ባይጠሩ፥ የእኛን ፈቃድ ቢፈጽሙ፥ በስማችን ጠርተው ቢያመልኩን ነው እንጂ፤ በመልካም ምግባር ሆነው በፍጹም ሃይማኖት የእግዚአብሔርን ስም ቢጠሩ ኃይል የለንም፡፡ #እኛ_ብዙ_ዓይነት_በሽታን_አእምሮ_ማጣትን_እብደትን_እናመጣለን፡፡ #ሰውን_ባሳመምነው_ጊዜ_ሄዶ_በእኛ_ስም_ሲጠመቅ_ከበሽታው_ይድናል፡፡ #በዚህም_ስመ_ክርስትናው_ትጠፋለች፡፡ #ሰዎች_የታመመው_ሲድን_ባዩና_በሰሙ_ጊዜ_እኛን_ያመልካሉ፡፡ #ባላወቋት_መንገድ_አሳስተን_እናጠፋቸዋለን፡፡ #መንፈሳውያንን_መንፈሳዊ_በማስመሰል_እናጠምዳቸዋለን፡፡ #መንፈሳዊ_በሚመስል_ነገር_የተጠመዱ_ከእኛ_አያመልጡም_አለው፡፡ /ማቴ.፯፥፲፭፤ ፳፬፥፲፩/ አባ ጳውሊ፤ አስቀድመህ ለነገሥታት፥ ለመኳንንት፥ ለስልጣናት፥ ለታላላቆቹ ለመሳፍንት፥ ለሊቃውንት አልቅስ ያልከኝ ስለምንድን ነው አለው፡፡ ሰይጣን፤ ሹመታቸው ታላቅ እንደመሆኑ ኃጢአታቸውም ብዙ ነውና፡፡ በሹመት ራስን ከፍ ማድረግን፥ ውዳሴ ከንቱን፥ ትምክሕትን፥ ትዕቢትን እናመጣባቸዋለንና፡፡ መሻርን መድከምን ሞትን እንዳያስቡ እናደርጋቸዋለንና፡፡ ቀናውን ፍርድ ትተው በመማለጃና በአድልዎ እንዲፈርዱ፤ የማስተዋል አእምሯቸውን እናጠፋዋለንና፡፡ እውነተኛውን ፍርድንና ቀናውን መንገድ ይተዋሉ ፤ ስለዚህ ዘወትር ድሆችን፥ ደካሞችን ያስለቅሳሉ፡፡ ከእግዚአብሔር ትእዛዝና ፈቃድ እናርቃቸዋለን ፤ ስሙን እንዳይጠሩ እናደርጋቸዋለን ፤ ትምክሕትን፥ ትዕቢትን፥ ገንዘብ መውደድን በልባቸው እናሳድርባቸዋለን፡፡ በዚህ ምክንያት ጦርነት አሥነስተው እርስ በርሳቸው ይጋደላሉ ፤ የእነርሱ መከራ ለታላቁም ለታናሹም ለሀገሩ ሁሉ ይተርፋል፡፡ በኃጢአታቸውም ይጠፋሉ አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ አንተ የተረገምክ፤ በሊቃነ ጳጳሳት ፥ በጳጳሳት ፥ በኤጲስ ቆጶሳትስ ላይ ምን ምክንያት አግኝተህ ትዋጋቸዋለህ አለው፡፡ ሰይጣን፤ ከሁሉ አብልጠው ብርን ፥ ወርቅን ፥ ገንዘብን እንዲወዱ አደርጋቸዋለሁ፡፡ #ለማይገባው ሥልጣነ ክህነትንም በገንዘብ እንዲሰጡ ፤ ለነዳያን ለድሆች እንዳያዝኑ አደርጋቸዋለሁ፡፡ ለሌላው የሚያስተምሩትን የሕጋቸውን ጎዳና እንዳያስተውሉ አደርጋቸዋለሁ፡፡ ዘወትር ኃላፊውን የምድር ተድላ ደስታ እንዲያስቡ አደርጋቸዋለሁ፡፡ ጠብን ፥ ጥላቻን በልቡናቸው አሳድራለሁ ፤ አንዱ ጓደኛውን በቅናት እንዲከሰው አደርጋለሁ፡፡ #ለጸሎትም በቆሙ ጊዜ ጠባቸውን እንዲያስቡ አደርጋቸዋለሁ፡፡ ቂማቸውን እንዳይረሷዋትም አንዱ ባልንጀራውን እንዲረግም አደርጋቸዋለሁ፡፡ #ኃላፊውን ገንዘብ ለመሰብሰብ እንዲተጉ አደርጋቸዋለሁ፡፡ በዚህ ምክንያት እኔ የማሳያቸውን የልብስ ዓይነት የልብስ ይለብሳሉ፡፡ ዳግመኛም በገዳም የሚኖሩትን መነኮሳት አብልጬ እጣላቸዋለሁ፤ የኅሊና ጦር አመጣባቸዋለሁ፡፡ #ከእንቅልፍ_በነቁ_ሰዓት_ወይም_ለጸሎት_ሲነሡ_የውዳሴ ከንቱና የቅንዓት የትምክሕት ሐሳቦችን አመጣባቸዋለሁ፡፡ ድካማቸውን ከንቱ አደርጋለሁ፡፡ በጾማቸውና በተጋድሏቸው እንዳይጠቀሙ አደርጋቸዋለሁ፡፡ #በበአታቸው_በአንድ_ቦታ_እንዳይጸኑ_አደርጋቸዋለሁ፡፡ በሥራ ላይ ያሉትንም ሥራቸውን እንዲያመልኩና እኔ እበልጣለሁ እንዲሉ አደርጋቸዋለሁ፡፡ በዚህ ሥራቸው ትቢትን ፥ ትምክሕትን ፥ ውዳሴ ከንቱ አመጣባቸዋለሁ፡፡ #የዚህ_ዓለም_ተድላና_ደስታ_እንዲወዱ በማድረግ እዋጋቸዋለሁ፡፡ #የውሸት_ሕልም_በማሳየት አሳስታቸዋለሁ፡፡ #የመምህሮቻቸውን_ትእዛዝ_እንዳይቀበሉ አደርጋቸዋለሁ፡፡ ከልባቸው ትሕትናንና ታዛዥነትን የምትጠቅም#የአበውን_ምክር_መስማትን_አጠፋባቸዋለሁ፡፡ እንደ መቃብር በውጫዊ እይታቸው ያማሩ በውስጣቸው ግን ኃጢአትን ርኵሰትን የተሞሉ አደርጋቸዋለሁ፡፡ አንድ ስንኳ ሳላስቀር ከእግዚአብሔር ቸርነት ፈጽሜ እስከ ማርቃቸው ድረስ ባለኝ ዐቅሜ ሁሉ እዋጋቸዋለሁ፡፡ እነሆ የጠየቅኸኝን ክፉ የሆነች የማሳት ምስጢሬንና የክፋት ሥራዬን ሁሉ ምንም ሳልደብቅህ ያለ ፈቃዴ ነገርሁህ አለው፡፡ #ቅዱሳን ሰይጣንን እንደሚያዙት፤ ቀሲስ አባ ጳውሊ የሰይጣንን ምሥጢር ስላውጣጣው እንዳይተናኰሉት ስለመጠየቁና የነገሩት እውነት መሆኑን፤ የነገሩትም ወደፊት እንደሚፈጸምና በጽሑፍ እንዲቀመጥ ማድረጉን…….. ክፍል ፲፪.… ይቀጥላል ነገ ዐርብ ይጠብቁን/ /#ዋልድባ_ዋሊ_ገጽ/

ከማኅሌት እስከ ሠርክ ጕባኤ፤ መስቀለ ኢየሱስ፤ መጋቢት 10 በደብራችን ይህንን ይመስላል፤ ከአዲስ አበባ ውጭና ከኢትዮጵያ ውጭ ላላችሁና በመንፈስ በዓሉን ላስታወሳችሁ፤ በአካል ላልተገኛችሁ እንዲሆን ነው፡፡

#ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን)፤#ክፍል#፲_ #ሰይጣን ያልበደሉትን ሰዎች ለምን እንደሚፈትናቸው፤ በኋላኛው ዘመን ደጋግ ነገሥታትና መኳንንት፤ ንጹሐን ካህናት ፥ ሊቃውንትና መምህራን ፤ ጳጳሳትና ቆሞሳት እንደሚታጡ፤ መነኰሳትም የሰይጣን ወዳጅ እንደሚሆኑና ይህን ለማራቅ መጸለይ እንደሚገባ፡፡ አባ ጳውሊ፤ አንተን ያልበደሉህን ሰዎች እንዲህ የምታደርገው ለምንድን ነው አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ሃይማኖታቸው የቀና፥ ሥነ ምግባራቸው ያማረ ስለሆነ እንቀናባቸዋለን፡፡ ስለዚህ አሕዛብ ክፉ ሥራቸውን አይተው ሃይማኖታቸውን እንዲነቅፏት ለማድረግ ነው አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ ከሕይወትና ከመልካም ሥራ የተለየህ ክፉ ባላጋራ፤ ኀጢአት በእነርሱ ላይ ከወዴት ትመጣለች? የዓመፅ መገኛ፥ የኃጢአት መኖሪያ፥ የጽድቅ ጠላት አንተ ነህ እንጂ አለው፡፡ /ዮሐ.፰፥፵፫/ ዲያብሎስ፤ የዓመፅና የክፋት ሁሉ መገኛ ብሆንም፤ የኀጢአት ፈጻሚዋ እኔ ብቻ አይደለሁም፡፡ #የማቀርብላቸውን_የክፋት_ሥራ_ካልተቀበሉኝ_እነርሱን_በኃይል_ማስገደድ_አይቻለኝም፡፡ ነገር ግን በብዙ ዘዴና ተንኮል ሥራዬን እንዲቀበሉ አቀርብላቸዋለሁ፡፡ #ለመልካም_ሥራ_መንፈሳዊና_አስተዋይ_ካልሆኑ የክፋት ሥራዬን ሳይመረምሩ ይቀበሉኛል፡፡ እነርሱን ለማሳት አመች ጊዜና ወቅት ሳገኝ ከመልካም ሥራ ሁሉ አርቃቸዋለሁ፡፡ በክፉ ሥራ ፈጽሜ እገዛቸዋለሁ፡፡ ለእያንዳንዳቸው በመካከላቸው ዘወትር ጠብ፥ ክርክር ይሆናል፡፡ የነፍሳቸውንና የሥጋቸውን ረብ ጥቅም አጠፋለሁ፡፡ ቃሌን ትእዛዜን አንቀበልም ብለው ቢያሸንፉኝ #በትንሽ_ኃጢአት_እቀርባቸዋለሁ፡፡ በልቡናቸው ሐሜትን፥ ነቀፋን አሳድርባቸዋለሁ፡፡ በመሥዋዕቱ ፊት በቤተ መቅደስ የማይገባ ሥራ እንዲሠሩና እንዲናገሩ አደርጋቸዋለሁ፡፡ በክፉ ሥራቸው ፈጽሞ ደስ ይለኛል፡፡ ዳግመኛ #ሕዝቡ_ቀሳውስቱንና_ካህናቱን_ሊቃውንቱንም_እንዲነቅፉ_አደርጋለሁ፡፡ ሁላቸውንም ከጽድቅ ሥራ ሰንፈው ለኃጢአት ሥራ እንዲተጉ አደርጋቸዋለሁ፡፡ ንስሐ እንዳይገቡ በውስጣቸው ፍርሐትን ፥ ትምክሕትን ፥ ስንፍናን አሳድርባቸዋለሁ፡፡ በዚህ ምክንያት የወንድሞቻቸውን ኀጢአት እንጂ የራሳቸውን ኀጢአት አይናዘዙም፡፡ በዚህ ምክንያት ለበደላቸው ስርየት የለውም፡፡ ከኀጢአት እንዳይርቁ በእነርሱ ላይ የማላመጣው ምክንያት የለም፡፡ ምክሬን ከሰሙኝ ፈጽሜ የክርስቶስን ጸጋ አሳጣቸዋለሁ አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ ይህንን ሰምቶ ፈጽሞ አለቀሰ፡፡ ሰይጣንም፤ አባ ጳውሊ ሲያለቅስ ባየ ጊዜ ደስ አለው፤ ይስቅበትም ጀመር፡፡ እንደ አንተ ካህናት ናቸውና ስለ እነርሱ ታለቅሳለህን አለው፡፡ በእውነቱ ማልቀስ ከወደድክ ስለ ደጋግ ነገሥታትና ስልጣናት ፥ ስለ መኳንንትና ስለ ሊቃውንት ፥ ስለ መሳፍንትና ስለ ገዢዎች መታጣት ፊትህን ጸፍተህ አልቅስ፡፡ ዳግመኛም ስለ ንጹሐን ሊቃነ ጳጳሳትና ስለ ኤጲስ ቆጶሳት ፥ ስለ ቆሞሳትና ስለ ሁሉም ደጋግ ንጹሐን ካህናት መታጣት አልቅስ፡፡ አብዝተህም ስለ ቤተክርስቲያንና ስለ ገዳማት አልቅስ፡፡ ይልቁንም በገዳማት ስለሚኖሩ ስለወንድሞችህ መነኰሳትና ስለ እኅቶችህ መነኰሳይያት ፈጽመህ አልቅስ፡፡ #በኋላ_ዘመን_ዘመዶቼና_ወዳጆቼ_አደርጋቸዋለሁና_አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ በምን ሥራ እንዲህ ታደርጋቸዋለህ? አለው፡፡ ሰይጣንም፤ እነርሱ ራሳቸው በፈቃዳቸው ጎዳናዬን ሁሉ ይከተላሉና ፤ ፈቃዴንም ይፈጽማሉና ፤ የማሳስባቸውን ይሠራሉና ፤ ቃሌን አይተላለፉምና ፤ መዐዛዬንም ይወዳሉና ነው አለው፡፡ ቅዱስ አባ ጳውሊ፤ ይህንን የሰይጣን ነገር በሰማ ጊዜ ታላቅ ሐዘን አዘነ፡፡ ያን ጊዜ ሰይጣንን እንዲህ አለው፡፡ አንተ የተረገምህ ክፉ ርኩስ እነሆ! ሌላ የክፋትህን ምክንያት እጠይቅሃለሁና እንዳትሸሽገኝ እምልሐለሁ አለው፡፡ ሰይጣን፤ ታላቅና ኃያል በሆነ ፤ ብርሃንን በፈጠረ በእርሱ ማልኩ፡፡ ከአንተ ምስጢሬን ልሸሽግ ብወድም አልቻልኩም፡፡ ምንም ፈጽሞ ልዋሽህ ስልጣን የለኝምና የምትጠይቀኝ ምንድን ነው? አለው፡፡ #ሰይጣን በውኃ ምንጮች ለምን እንደሚያድርና ነገሥታት፥ መኳንንትንና መሣፍንትን በምን እንደሚፈትናቸው… ክፍል ፲፩.… ይቀጥላል ረቡዕ ይጠብቁን/ /#ዋልድባ_ዋሊ_ገጽ/

እንደ መድኀኔ ዓለም ፈቃድ፤ በመጋቢት 10 በመስቀለ ኢየሱስ ክብረ በዓል ላይ ከንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ጀምሮ በአዲስ አበባ በብቸኝነት ክብረ በዓሉ በሚከበረው በታላቁ ደብር በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም እንገናኝ፡፡ (በነገራችን ላይ በዚህ ደብር እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ አገልጋይ ካህናቱ የመድኀኔ ዓለምና የመስቀል አገልጋይ ካህናት ተብለው በ2ት የተመደቡና የመስቀል አገልጋይ ካህናትን ደመወዝ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የሚከፍለው ቤተ መንገሥት ነበር፡፡) በከሰዓት በዋይዜማው፤ በሠርክ፤ በሠርክ ጕባኤ ማታ በማኅሌቱ፤ ሌሊት በሰዐታቱ፤ ንጋት ላይ በኪዳኑ፤ ረፋድ ላይ በዑደተ ታቦተ ሕጉ፤ በ6 ሰዐት በቅዳሴው፡፡ በመስቀለ ኢየሱስ ክብረ በዓል ላይ እንገናኝ፡፡ ‹‹በቀራንዮ መካን ዘደፈኑ አይሁድ፤ መስቀል ዕፀ ሕይወት፥ ዕፀ መድኀኒት፡፡›› በቀራንዮ መካን አይሁድ የቀበሩት የሕይወት የመድኒት መስቀል ነው፡፡

ምኵራብ፤ ሦስተኛው ሳምንት ሦስተኛ ሳምንት ምኵራብ ይባላል፡፡ ጌታ በምኵራብ ማስተማሩን የሚዘከርበት ሳምንት ሲሆን ‹‹ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ›› የሚልና ይህን የመሰለ ጌታ በምኩራብ ማስተማሩን የሚያዘክር ምስጋና የሚቀርብበት ሳምንት ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን ዘመን በኢሩሳሌም የአይሁድ ቤተመቅደስ ነበራቸው፡፡ ናቡከደነጾር ኢየሩሳሌምን በወረረ ጊዜ ግን ቤተመቅደሱን አፈረሰ፤ ሕዝቡንም ወደ ባቢሎን አፈለሰ፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ አይሁድ በሚኖሩባቸው ስፍራዎች ሁሉ ለጸሎት ቤት ይሰሩ ነበር፤ በዚህም ምክንያት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በኢየሩሳሌም እየተዘዋወረ በሚያስተምርበት ጊዜ ብዙ ምኵራቦች ነበሩ፡፡ ሐዋርያት በሚያስተምሩበት ወቅት ከአንዳንድ ቦታዎች በቀር በምኵራቦች ገብተው ወንጌልን አስተምረዋል፡፡ በብሉይ ዘመን ቢያንስ ዐስር የጎለመሱ ወንዶች (የቤተሰብ ኃላፊዎች) በቦታው ከተገኙ እነዚህን ምኵራቦችን ለመስራት ይፈቀድላቸው ነበር፡፡ ነገር ግን ዋናው ቤተ መቅደሱ ያለው በኢየሩሳሌም ብቻ ነበር፡፡ በምኵራብ ውስጥም የኦሪት የሕግ መጻሕፍትና በቅዱሳን ነቢያት የተጻፉ ጽሑፎች በብራና ጥቅልል ይገኛሉ፡፡ ምዕመኑ እንዲሰማቸው እንደ መድረክ ባለ ቦታ ላይ ካህናትና መምህራን ቆመው መጻሕፍትን ያነባሉ፤ ቃለ እግዚአብሔርንም ያስተምሩ ነበር፡፡ በኦሪቱ ምኵራብን የሚመሩት አለቆች ጥፋተኛ ሰው ሲገኝ፤ በመግረፍ ወይም ከምኵራብ በማስወጣት ሊቀጡ ስልጣን ነበራቸው፡፡ አገልጋይ ወይም የሚራዱ ወጣቶችም ልጆችን በማስተማር ጥቅሎችን በማቅረብ በተጨማሪ የአለቆችን ትዕዛዝ በመፈጸም ያገለግላሉ፡፡ በየሰንበቱ ሕዝብ ሁሉ በምኵራብ ተሰብስበው አምልኮታቸውን ይፈጸሙ ነበር፤ በአምልኮታቸው ውስጥም ጸሎት፤ ከሕግና ከነቢያት ንባብ፤ ስብከትና ቡራኬ ነበር፡፡ በዚህ በምኩራብ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሰንበት ተገኝቶ ሕዝቡን አስተምሯል፤ ሕሙማንን ፋውሷል፡፡ የኢሳይያስን መጽሐፍ ምዕራፍ ፷፩ን አንብቧል፡፡ በዚህ በዐቢይ ጾም ሦስተኛ ሳምንት(ምኵራብ) የሚታሰበውም ይህ ነው፡፡ ፨ ‹‹ወደ አደገበትም ወደ ናዝሬት መጣ፤ እንደ ልማዱም በሰንበት ቀን ምኵራብ ገባ ሊያነብም ተነሳ፡፡›› ሉቃ. 4፥16 ፨ ‹‹ወደ ገዛ አገሩም መጥቶ እስኪገረሙ ድረስ በሚገባቸው ያስተምራቸው ነበር፡፡›› ማቴ. 13፥52 ፨ ‹‹ሰንበትም በሆነ ጊዜ በምኵራብ ያስተምር ጀመር፡፡››ማር 6፥1 ፨ በዕለቱ ቅዳሴ ላይ የሚነበቡ ምንባባትም፤ ጌታችን ቤተ መቅደሱን የንግድ ማዕከል ያደረጉትን ዓይቶና አዝኖ ነጋዴዎቹን ከነመንጋቸው በጅራፍ እንዳስወጣቸውና ‹‹ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት በሦስተኛው ቀን እኔ እሠራዋለሁ፡፡›› ብሎ ስለመ ሞቱና ስለ ትንሣኤው ማስተማሩን የሚገልጽ ነው፡፡ ፨፨፨ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፨፨፨ በዕለቱ ሌሊት የሚባለውን መዝሙር፤ ጠዋት በቅዳሴ የሚነበቡትን ምንባባት፥ የሚሰበከውን ምስባክ (መዝሙረ ዳዊት)፥ የሚነበበውን ወንጌል፥ የየትኛው ቅዳሴ እንደሚቀደስ አቅርበንላችኀዋል፨

አንኳን ለመስቀለ ኢየሱስ መጋቢት 10 በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፥ አደረሰን፡፡ (ይህንን ያውቃሉ????? በአዲስ አበባ በብቸኝነት ከቀድሞ ጀምሮ የመስቀለ ኢየሱስ በዓል በታላቁ ደብር በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ቤተ ክርስቲያን ክብረ በዓሉ እንደሚከበር፡፡ በዚሁ ደብር በቀደሙት ዘመናት አገልጋዮች የመድኀኔ ዓለምና የመስቀል አገልጋዮች ተብለው በሁለት ምድብ የሚያገለግሉ አገልጋዮች የነበሩ መኾኑን ፤ ** የመስቀል አገልጋይ ካህናት እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ደመወዛቸው ከቤተ መንግሥት እንደሚከፈላቸው፤ ….) በቀራንዮ መካን ዘደፈኑ አይሁድ፤ መስቀል ዕፀ ሕይወት፥ ዕፀ መድኀኒት፡፡ (የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም የቤቱ የመስቀል ወረብ) በሃገራችን ኢትዮጵያ መስቀልን በሚመለከት ከሚከበሩ በዓላት ውስጥ የደመራ መስቀል በዓል /መስከረም 16ና 17/ እንዲሁም መጋቢት 10 የመስቀለ ኢየሱስ በዓል ተያያዥነት ያላቸውና ዋነኞቹ ናቸው፡፡ የጌታችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ከጌታችን ሞትና ትንሣኤ በኋላ በቀራንዮ አደባባይ ጥቂት ጊዜ ከቆየ በኋላ ጌታችንን የገነዙት ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ከቀራንዮ ወደ ጎልጎታ (ጌታችን ተቀብሮባት ወደነበረው መካነ መቃብር) ወስደው አኑረውታል፡፡ አበው ሐዋርያት ወደየሀገረ ስብከታቸው ሲሄዱ የኢየሩሳሌሙ ጳጳስ ሐዋርያው ያዕቆብ በኃላፊነት እንዲጠብቀው አድርገዋል፤ ከየአህጉረ ስብከታቸው ሲመለሱም በእግረ መስቀሉ ሥር እየተሰበሰቡ ይጸልዩ ነበር፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ጠዋትና ማታ በመስቀሉ ሥር ትጸልይ ነበር፡፡ ብዙ ሰዎች ታሪኩንና ቦታውን በክርስቶስ ደም የተቀደሰውን ክቡር መስቀሉን ለማየት ያመኑትም በረከት ለማግኘት ከየአቅጣጫው ይመጡ ነበር፡፡ በመስቀሉ ተዓምራት ብዙዎች ከተለያዩ ደዌ /በሽታ/ ተፈውሰዋል፡፡ ይህም በጣም ብዙ ሰዎች ክርስቶስን ወደ ማመን ስቧቸዋል፡፡ ይህን ድንቅ ሥራ የተመለከቱ የክርስቶስ ሰቃዮች /ሰቃልያነ ክርስቶስ/ በሁኔታው ባለመደሰታቸው ሕይወት የሆነውን የጌታ መስቀሉን ከጎልጎታ አንስተው ቀብረውት ለ300 ዓመታት ያህል የከተማው ጉድፍና ጥራጊ እየጣሉበት የተቀበረበት ቦታ ኮረብታ እስኪሆን ድረስ ቆይቷል ‹‹በቀራንዮ መካን ዘደፈኑ አይሁድ፤ መስቀልከ ዕፀ ሕይወት፥ ዕፀ መድኀኒት›› እንዲል፡፡ ሆኖም በ4ኛው መ/ክ/ዘመን ለክርስቲያኖች ነፃነት የሚያስብና የሚያስከብር ንጉሥ በሮም ተነሣ፡፡ የንጉሡም ስም ቈስጠንጢኖስ ይባል ነበር፡፡ ይህ ንጉሥ ክርስቲያኖችን ይበልጥ እንዲወድ ያደረገው በጠላቱ በማክሴንዲዩስ (መክስምያኖስ) ላይ በዘመተበት ጊዜ ገና በጉዞ ላይ እያለ ‹‹በዝንተ ትእምርተ መስቀል ትመውዕ ፀርከ (በዚህ የመስቀል ምልክት ጠላትህን ድል ታደርጋለህ)›› የሚል በመስቀለኛ ቅርፅ የተጻፈ ጽሑፍ በጠፈር ሰማይ አይቶ በመስቀል ምልክት ድል በማድረጉ ነው፡፡ የንጉሥ ቈስጠንጢኖስ እናት ንግሥት እሌኒ የመስቀሉ ፍቅር ያደረባት፥ ታሪኩ በውስጧ የሰረጸባት ቅድስት እናት ነበረች ቈስጠንጢኖስም በዘመነ መንግሥቱ በትዕምርተ መስቀል ብዙ የድል ሥራ ስለሠራ ለመስቀሉ ታላቅ አክብሮትና አድናቆት ነበረው፡፡ ንግሥት እሌኒም መስቀሉን ለማግኘት ሰው ብትጠይቅ የሚያውቅ አላገኘችም፡፡ በመጨረሻ ግን የመስቀሉ መውጣት የእግዚአብሔር ፈቃድ በመሆኑ ኪራኮስ የሚባል አረጋዊና መቃርስ የሚባል ኤጲስ ቆጶስ አገኘች፡፡ ከእነዚህም አረጋዊው ኪራኮስ ዕድሜው የሸመገለና በእስራኤል ባህልና ደንብ ያደገ ነበር፡፡ እሌኒም እሱን ጠይቃ መስቀሉን ለማግኘት እንዲተባበራት ጠየቀችው ሆኖም ሊተባበራት ፈቃደኛ አልሆነም፡፡ ረሃብና ጽም ስታበዛበት ግን የረሃብና የጽሙን መጽናት ተመልክቶ ከእነዚህ ከሦስት ተራሮች አንዱ እንደሆነ ነገራት፤ ከሦስቱ ተራራ የትኛው እንደሆነ ለማወቅ በእግዚአብሔር ፈቃድ ሱባኤ እንድትይዝ ነገራት፤ ሱባኤም ያዘች፡፡ ከዚህም በኋላ እግዚአብሔር መልአኩን ልኮ እንዲህ አላት ‹‹አንቺም ሰውም በከንቱ አትድከሙ እንጨት አሰብስበሽ፥ ደመራ አስደምረሽ፥ በእሣት አያይዘሽ፥ በፍሕሙ ላይ ዕጣን አፍስሽ፤ የዕጣኑ ጢስ ወደ ላይ ወጥቶ ወደ ታች ሲመለስ አቅጣጫውን ተመልክተሽ ጢሱ ያረፈበትን ቦታ አስቆፍሪው›› አላት፡፡ እርሷም መልአኩ እንዳላት እንጨት አሰብስባ ደመራ አስደመረች ዕጣንም አፈሰሰችበት ጭሱም ሰማይ ደርሶ ወደ ምድር ሲመለስ ቦታውን አመለከታት ይህም የሆነው መስከረም 16 ቀን ነው፡፡ እኛ ደመራ ብለን የምናከብረው ይህን አብነት በማድረግ ነው፡፡ መስከረም 17 ቀን ማለትም የደመራ በዓል ማግስት የምናከብረው የመስቀል በዓል ደግሞ ንግሥት እሌኒ ደመራ አስደምራ እጣን አጢሳ (አስጢሳ) የመስቀሉን ቦታ ካወቀች በኋላ ቁፋሮውን ያስጀመረችበት ዕለት ስለሆነ ነው፡፡ ከቁፋሮውም በኋላ የጌታችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ዳግመኛ በእግዚአብሔር ፈቃድ፤ በእሌኒ ተነሳሽነት፤ በረዳቶቿ አጋዥነት ቁፋሮ በተጀምረ ከ5 ወር ከ23 ቀን በኋላ መስቀሉ መጋቢት 10 ተገኝቷል፤ ከ10 ዓመት በኋላም ቤተ መቅደሱ ታንጾ ቅዳሴ ቤቱ ተከብሯል፡፡ መስቀሉም እንደቀድሞ ድውያንን ሲያድን፣ ለምጻምን ሲያነጻ፣ ሽባዎችን ሲያቀና፣ ሙታንን ሲያስነሳ፣ የማያምኑትን ወደ ማመን ሲመልስ ነበር፡፡ ዛሬም የክርስቶስ መስቀል በዓለም እያበራ ሕሙማንን እየፈወሰ ይገኛል፡፡ ይህ የጌታ ዕፀ መስቀልም በዓፄ ዳዊት ዘመን ወደ ሃገራችን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ በለያዩ ቅዱሳት መካናት (እንጦጦ ማርያም፣ ጋራ መድኃኔዓለም፣…..) ሲያርፍ ቆይቶ በስተመጨረሻው ‹‹አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል›› ተብሎ ለዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ በተነገረው መሠረት በደብረ ከርቤ ግሸን ማርያም በክብር አርፏል፡፡ እኛንም በመስቀሉ ፈዋሽነት ይማረን የመስቀሉን ፍቅር በልባችን ይሳልብን አሜን፡፡ * "መስቀል መልዕልተ ኩሉ ነገር: ያድኅነነ እምጸር" /ሊቁ ቅዱስ ያሬድ/ * ‹‹ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ።›› /ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ዻውሎስ ገላ.6፥14፣ 1ኛቆሮ.1፥18/ ***** እንደተለመደው ሥርዐተ ማኅሌቱንም አቅርበንላችኋል፡፡ እንደ መድኀኔ ዓለም ፈቃድ በዋይዜማ፣ በሰርክ ጕባኤ፣ በሰዐታቱ በኪዳኑ፣ በዑደተ ታቦተ ሕጉና በቅዳሴው እንገናኝ፡፡ (ከቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ታሪክ የፍኖተ ሕይወት ሰንበት ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት ላይ የተወሰደ) ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡

በድጋሚ የምሥራች፡፡ አለህም እንዳልል እንዲህ ይደረጋል!!፤ የለህም እንዳልል ጠበሉ ይፈልቃል፡፡ በድጋሚ የምሥራች የምሥራች፤ በደብራችን ከዚህ ቀደም 4ት ጠበሎች መፍለቃቸውን ዘግበን ነበር አሁን ደግሞ 5ኛ ጠበል ባለፈው ኀሙስ የካቲት 21 ፈልቋል፡፡ በተጨማሪ ደግሞ ዓይናቸው የበራላቸው ቊጥር ባለፈው ስንዘግብ 3ት ነበሩ አሁን ደግሞ በተጨማሪ 2ት ሰዎች ዓያናቸው በርቷል /አንዱ ወነድማችን ከጎጃም የመጣ ነው፡፡/ አንድ ሰው ከዐልጋ ላይ መነሳት የማይችል ተፈውሷል፡፡ የወገኑ ዓይን ሲበራለት የማይደሰት ማን አለ!!!????፡፡ ቸርነቱን ያላራቀብን ምሕረቱን ያበዛልን በፍቅሩ የጎበኘን የአባቶቻችን አምላክ መድኀኔ ዓለም ይመስገን፡፡ (ፎቶዎቹ፤ በደስታ ብዛት የካቲት 16 በብዚ ሺህዎች ለመጡ ምዕመናን በንፍሮ ውኃና በንፍሮ፤ በዳቦ በእንጀራና በጠላ ሲዘከር፤ ማኅበረ ጎዶልያስ ዝማሬ ሲያቀርቡ) ሲሆን የወደቁት ደግሞ በደቡብ (በጌዲኦ) በግጭት ምክንያት የወደቁ ወንድሞቻችንን ነው፡፡ የጠበሉን ቦታ በተደጋጋሚ ለጠየቃችሁን፤ ከቀጨኔ መድኀኔ ዓም ቤተ ክርስቲያን በሁለገብ (በበሃ ሰፈር) በኩል ወደ 19ኝ (ሽሮ ሜዳ) መሻገሪያ ድልድዩ ጋር፡፡

እንዳያመልጥዎ ከመጋቢት 9-11 ልዩ ጕባኤ፤ የመስቀለ ኢየሱስ (መጋቢት 10) በአዲስ አበባ በብቸኝነት በሚከበርበት በታላቁ ደብራችን፡፡ ሥርዐተ ማኅሌቱን አስቀድመን ልከንላችኋል፤ እንደ አምላክ ፈቃድ ሁላችንም ከዋይዜማው ጀምሮ በማኅሌቱ፣ በሰርክ ጕባኤ፣ በሰዐታት፣ በኪዳን፣ በዑደተ ታቦተ ሕግና በቅዳሴ እንገናኝ፡፡ /በዕለቱ ማኅሌት ላይ በደብሩ ብቻ የሚባሉትንም ልዩ ልዩ ወረብ በአካል ተገኝተው በማዳመጥ ነፍስዎን ይመግቡ፤ ይመስጡ)