en
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Open in Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 391 subscribers, ranking 5 586 in the Religion & Spirituality category and 2 200 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 391 subscribers.

According to the latest data from 01 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 22 over the last 30 days and by -7 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 21.30%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 10.19% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 278 views. Within the first day, a publication typically gains 1 569 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 17.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 02 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

15 391
Subscribers
-724 hours
+227 days
+2230 days
Posts Archive
በዓለ አቡነ ሀብተማርያም 26 እንኳን አደረሳቸሁ #የአቡነ ሀብተማርያም ወረብ በደብረ መድኀኒት አቡነ ሀብተማርያም ሊቃውንት ፤ ከሠተ አፉሁ፡፡ #ከሠተ አፉሁ ወልሳኑ ነበበለ አእቶ ወባረኮ ለእግዚአብሔር መልዐ መንፈስ ቅዱስ ላዕለ ሀብተማርያም #ይህንን ሊንክ በመጫን ይመልከቱ https://youtu.be/GIzYreXgSOY

የታሰሩት 3 የሰንበት ት/ቤት አባላት በዋስ ተፈተዋል!! ላለፉት 2 አመታት የሰንበት ትምሕርት ቤቱ መማሪያ ቦታ ለሆንው የአዳራሽ ተለዋጭ ቦታ ሳይሰጠው ሊፈርስ አይገባም ፤ ከሕንጻ ልማት ይልቅ ለሰው ቅድሚያ ሊሰጠው ይገባል በማለት ሲከራከሩ ከነበሩት አባላት መካከል የደብሩ አስተዳዳሪ የሆኑት መልአከ ሰላም ስዩም ወልደ ገብርኤል አስራ አራቱን መክሰሳቸው ይታወቃል፡፡ የቀጨኔ ፓሊስ መምሪያ የምርመራ መዝገቡን አደራጅቶ የከሳሽ እና የምስክር ቃል ከተቀበለ በኃላ ከ14ቱ ተከሳሾች የ5ቱን ቃል ተቀብሏል፡፡ 5ቱም በዋስ የተለቀቁ ሲሆን በቅርቡ ለአቃቤ ሕግ ቀርቦ ጉዳዩ ውሳኔ ይሰጥበታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ቢሆንም አሁንም ክሱ ሙሉ ለሙሉ የተዘጋ ስላልሆነ በሰ/ት/ቤቱ ማኀበራዊ ሚዲያ እና በውስጥ ገጽ ለሰ.ት.ቤቱ ጠበቃ ሆነን በመቆም በረከት እናግኝ ብላችሁ የጠየቃችሁን የህግ ሰዎች እና የመታሰራችንን ዜና ሰምታቹህ በማኀበራዊ ሚዲዎቻቹኅ ጉዳያችንን አሰስቧቹህ ላጋራቹሁት ለ .አ.አ ሰንበት ት/ቤቶች እንዲሁም ለቤ.ክ አገልጋዮች ከልብ እያመሰገንን በቀጣይ ሰ/ት/ቤቱ ፍትህ እስኪያገኝ ድረስ ትግሉ የሚቀጥል ስለሆነ አሁንም አንድነታችንና አብሮነታቸን እንዳይለየን እንጠይቃለን፡፡ በቀጣይም ፤ መጻፍያ ብዕሩን ለክስ ሳይሆን የጠፉ ልጆቹን ፅፎ ለሚሰበስብ ፤ አንደበቱን ለፖሊስ ሳይሆን ለቃለ እግዚአብሔር ፣ ልጆቹን ፍርድ ቤት ሳይሆን ለማኀሌት የሚያቆም እንደ ቅዱስ ጴጥሮስ ያለ ትክክለኛ የመንጋ ጠባቂ እስኪመጣልን ድረስ ጉዳያችንን አጠናክረን ለአ.አ ሐገረ ስብከት ሆነ ለሚመለከታችው የቤተ ክህነት አካላት የምናሳውቅ ይሆናል፡፡ በአገልግሎታቸን ሁሉ መድኀኔዓለም ይቅደም ፡፡

1. እጮኛ አለዎት ወይም ለመያዝ አስበዋል? የእጮኝነት ሕይወትዎ ለትዳር እንዲበቃ በክርስቲያናዊ መንገድ እንዴት መጓዝ እንዳለብዎት ያውቃሉ? ከእጮኝነት ጀምሮ ክርስቲያናዊ ሕይወትን እንዴት መለማመድ
1. እጮኛ አለዎት ወይም ለመያዝ አስበዋል? የእጮኝነት ሕይወትዎ ለትዳር እንዲበቃ በክርስቲያናዊ መንገድ እንዴት መጓዝ እንዳለብዎት ያውቃሉ? ከእጮኝነት ጀምሮ ክርስቲያናዊ ሕይወትን እንዴት መለማመድ ይቻላል? ይምጡ ለእነዚህና መሰል ጥያቄዎቾ በዐውደ ጥናቱ በቂ ምላሽ ያገኛሉ። 2. የትዳር ሕይወትዎ እንዴት ነው ኦርቶዶክሳዊ መዐዛ አለው? በቤታችሁ ያለችው ትንሽዋ ቤተ ክርስቲያን ተዘግታለች ወይስ አገልግሎት እየሰጠች ነው? ትዳርዎ ጠንካራ መሠረት እንዲኖረው ምን እያደረጉ ነው? ትዳርዎ አደጋ እንዳንዣበበበት ይሰማዎታል? የእርስዎ እና የትዳር አጋርዎ መንፈሳዊ ሕይወት እኩል አለመራመዱ አሳስብዎታል?ይምጡ ለእነዚህና መሰል ጥያቄዎቾ በዐውደ ጥናቱ በቂ ምላሽ ያገኛሉ። 3. የወለዱዋቸው ልጆች ምክርዎን ይሰማሉ? ወይስ በራሳቸው መንገድ ነው የሚጓዙት? ልጆችዎን በኦርቶዶክሳዊ መንገድ እንዴት መቅረጽ እንዳለብዎ ያውቃሉ? ልጆችዎ ላይ እንዴት በጎ ተጽእኖ ማሳደር እንደሚችሉስ? ይምጡ ለእነዚህና መሰል ጥያቄዎቾ በዐውደ ጥናቱ በቂ ምላሽ ያገኛሉ። 4. ልጆችዎ ከመስመር የመውጣት አዝማሚያ ሲያሳዩ እንዴት እንደሚመልሷቸው ምን ያስባሉ? ክር፣ ከልጆችዎ ጋር አወንታዊ ንግግር እንዴት ማድረግ እንዳለብዎ ያውቃሉይት? ይምጡ ለእነዚህና መሰል ጥያቄዎቾ በዐውደ ጥናቱ በቂ ምላሽ ያገኛሉ። 5. ከዐውደ ጥናቱ ርዕሰ ጉዳይ ጋር የተገናኙ ጥያቄዎችዎን ይላኩልን፣ በዕለቱ ምላሽ ይሰጥባቸዋል።

ሁለት ቀን ብቻ ቀረዉ፤ የ55ኛ አመት ሀለተኛ መርሃ ግብር፤ 0ውደ ጥናት :: 1. እጮኛ አለዎት ወይም ለመያዝ አስበዋል? የእጮኝነት ሕይወትዎ ለትዳር እንዲበቃ በክርስቲያናዊ መንገድ እንዴት መጓዝ እ
ሁለት ቀን ብቻ ቀረዉ፤ የ55ኛ አመት ሀለተኛ መርሃ ግብር፤ 0ውደ ጥናት :: 1. እጮኛ አለዎት ወይም ለመያዝ አስበዋል? የእጮኝነት ሕይወትዎ ለትዳር እንዲበቃ በክርስቲያናዊ መንገድ እንዴት መጓዝ እንዳለብዎት ያውቃሉ? ከእጮኝነት ጀምሮ ክርስቲያናዊ ሕይወትን እንዴት መለማመድ ይቻላል? ይምጡ ለእነዚህና መሰል ጥያቄዎቾ በዐውደ ጥናቱ በቂ ምላሽ ያገኛሉ።

1. እጮኛ አለዎት ወይም ለመያዝ አስበዋል? የእጮኝነት ሕይወትዎ ለትዳር እንዲበቃ በክርስቲያናዊ መንገድ እንዴት መጓዝ እንዳለብዎት ያውቃሉ? ከእጮኝነት ጀምሮ ክርስቲያናዊ ሕይወትን እንዴት መለማመድ ይቻላል? ይምጡ ለእነዚህና መሰል ጥያቄዎቾ በዐውደ ጥናቱ በቂ ምላሽ ያገኛሉ። 2. የትዳር ሕይወትዎ እንዴት ነው ኦርቶዶክሳዊ መዐዛ አለው? በቤታችሁ ያለችው ትንሽዋ ቤተ ክርስቲያን ተዘግታለች ወይስ አገልግሎት እየሰጠች ነው? ትዳርዎ ጠንካራ መሠረት እንዲኖረው ምን እያደረጉ ነው? ትዳርዎ አደጋ እንዳንዣበበበት ይሰማዎታል? የእርስዎ እና የትዳር አጋርዎ መንፈሳዊ ሕይወት እኩል አለመራመዱ አሳስብዎታል?ይምጡ ለእነዚህና መሰል ጥያቄዎቾ በዐውደ ጥናቱ በቂ ምላሽ ያገኛሉ። 3. የወለዱዋቸው ልጆች ምክርዎን ይሰማሉ? ወይስ በራሳቸው መንገድ ነው የሚጓዙት? ልጆችዎን በኦርቶዶክሳዊ መንገድ እንዴት መቅረጽ እንዳለብዎ ያውቃሉ? ልጆችዎ ላይ እንዴት በጎ ተጽእኖ ማሳደር እንደሚችሉስ? ይምጡ ለእነዚህና መሰል ጥያቄዎቾ በዐውደ ጥናቱ በቂ ምላሽ ያገኛሉ። 4. ልጆችዎ ከመስመር የመውጣት አዝማሚያ ሲያሳዩ እንዴት እንደሚመልሷቸው ምን ያስባሉ? ክር፣ ከልጆችዎ ጋር አወንታዊ ንግግር እንዴት ማድረግ እንዳለብዎ ያውቃሉይት? ይምጡ ለእነዚህና መሰል ጥያቄዎቾ በዐውደ ጥናቱ በቂ ምላሽ ያገኛሉ። 5. ከዐውደ ጥናቱ ርዕሰ ጉዳይ ጋር የተገናኙ ጥያቄዎችዎን ይላኩልን፣ በዕለቱ ምላሽ ይሰጥባቸዋል።

#_ለአጥቢያችን_ምዕመናን_በሙሉ ለቤተክርስቲያን ሕጻናትና ወጣቶች የታገሉ፣ የደከሙና ሁሉነገራቸውን የሰጡ የሰ/ት/ቤታችን_አባላት ታሰሩ!!! ሁሉም እንደሚያውቀው በደብራችን አስተዳደር እና የሰንበት ት/ት/ቤታችን መካከል ከቋሚ የሰ/ት/ቤት የመማርያ ቦታ ጥያቄ ጋር በተያያዘ ከ 2 ዓመታት በላይ ከፍተኛ አለመግባባት ተከስቶ መቆየቱ የሚታወቅ ነው፡፡ በዚህ ሂደት ህጋዊ በሆነ መልኩ ሲሞግቱ ፣ ሁሉነገራቸውን ሰጥተው ለቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ህጻናትና ወጣቶች እድገት ሲታገሉ የነበሩ የሰ/ት/ቤቱ አባላት ላይ የደብሩ አስተዳደር በአጠቃላይ በተለይም ደግሞ የደብሩ አስተዳዳሪ በብዙ ድካም ሰ/ት/ቤቱ ባገኘው ተደጋጋሚ ውሳኔ ቂም ቋጥረው በቀል ይዘው ቆይተው በ 14 የሰ/ት/ቤቱ ወጣቶች ላይ ክስ መስርተዋል፡፡ ይሁንና የሀገረ ስብከታችን ሊቀ ጳጳስ በ20/07/2013 ዓ.ም ደብሩ ክሱን እንዲያቋጥ ለደብሩ አስተዳዳሪ አመራር የሰጡና የደብሩ አስተዳዳሪም በቀን 22/09/2013 ዓ.ም የሰበካ ጉባኤ ሪፖርት ለምዕመናን በቀረበበት ወቅት በአውደ ምህረት ላይ ለእናንተ ለምእመናን ክስ አንስቻለሁ፣ አቋርጫለሁ በማለት የሰጡትን ቃል በተግባር አጥፈው ክሱን ውስጥ ለውስጥ በመቀጠል በአሁኑ ሰዓት ከ14ቱ ክስ የተመሰረተባቸው አባላት መካከል በ 5ቱ ላይ የቅድሚያ የተከሳሽ ቃል ተወስዶ 3ቱ በቀጨኔ ፖሊስ ጣቢያ ታስረዋል፡፡

#እንኳን_ደስ_አለህ! የሁል ጊዜም አገልጋያችን የሆንከው #መ_ር #ኢዮብ_በቀለ ፤ የበኵር ልጅክ የሆነችውን #ዕፀ_ዘዌ_ክርስቶስ የተሰኘችውን መጽሐፍህን ለአንባብያን በማቅረብክ እንኳን ደስ አለህ እያ
#እንኳን_ደስ_አለህ! የሁል ጊዜም አገልጋያችን የሆንከው #መ_ር #ኢዮብ_በቀለ ፤ የበኵር ልጅክ የሆነችውን #ዕፀ_ዘዌ_ክርስቶስ የተሰኘችውን መጽሐፍህን ለአንባብያን በማቅረብክ እንኳን ደስ አለህ እያልን እጅግ የላቀውን ደስታችንን ልንነግርክ እንወዳለን ፡፡ #በነገረ_ድኀነት ላይ ያተኮረችው ይህች መጽሐፍህ ለብዙኀን ዕውቀትን እንደምታሰገኝ፤ ግሩም ከሆነው መጽሐፍክ ውስን ገጾች በማንበብ ብቻ መናገር ይቻላል፡፡ ደከምኝ ሰለቸኝ ሳትል በምታገለግለው አገልግሎት አምላከ ቅዱስ ጊዮርጊስ ፀጋውን አብዝቶ እንዲሰጥክ ጸሎታችን ነው ፡፡ ቀጣይ ስራዎችህንም በእግዚአብሔር ፈቃድ እንጠብቃለን ፡፡ ወላዲተ አምላክ ቅድስት ድንግል ማርያም አገልግሎትክን ትባርክ፡፡ ꔰ ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ꔰ Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem www.Finotehiwotsundayschool.com

ዓርብ ጉባዔ ዘሰኔ 18 #ትምሕርት በሊቀ ኅ ሩያን ቀሲስ ጥላሁን የ ደብረ ምጥማቅ ሰዐሊተ ምህረት ቅድስት ማርያም ካቴድራል ስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊ #ዝማሬ በሙሐዘ ስብሀት ዲያቆን ልዑል ሰገድ ጌ
+6
ዓርብ ጉባዔ ዘሰኔ 18 #ትምሕርት በሊቀ ኅ ሩያን ቀሲስ ጥላሁን የ ደብረ ምጥማቅ ሰዐሊተ ምህረት ቅድስት ማርያም ካቴድራል ስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊ #ዝማሬ በሙሐዘ ስብሀት ዲያቆን ልዑል ሰገድ ጌታቸው እና በዘማሪ ሚኪያስ ፀጋዬ በስብሐት አልፏል ለሳሞንቱ ያድርሰን ፤ አሜን፡፡ ትምህርቱን በዩቲዩብ ገጻችን የምንለጥፍ ይሆናል ፡፡ ጉባዔዉ ሳምንት ዓርብ ይቀጥላል።

#ሰኔ_21 #ሰኔ_ጐልጐታ ወሕንፀተ ቤተክርስቲያን እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ለቅድስተ ቅዱሳን ለድንግል ማርያም ሰኔ ጐልጐታና ሕንፀተ ቤተ ክርስቲያን (ለመጀመሪያ ጊዜ ቤተ ክርስቲያን ለታነጸበት) ክብረ በዓል በሰላምና በጤና አደረሰን አደረሳችሁ፡፡ ꔰ ꔰሰኔ ጎልጎታ፤ ‹‹ሰኔ ጐልጐታ፤ ችግር የምትፈታ፤ ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያም በዚህ ቀን (ሰኔ 21) ልጇን ወዳጇን ጐልጐታ በሚባል ቦታ ላይ እንበዋ እንደ ጅረት እስኪፈስ ድረስ ለኃጥአን ምሕረትን ለምናዋለች:: ጌታችንም ‹‹ስምሽን የጠራውን፤ በቃል ኪዳንሽ ያመነውን ሁሉ እምርልሻለሁ፡፡›› ብሎ ቃል ኪዳን ሰጥቷታል፡፡ ꔰꔰ ሕንፀተ ቤተ ክርስቲያን፤ ሰኔ 21 ከእመቤታችን #33ቱ በዓላት አንዱ ሲኾን፤ ሕንጸተ ቤተክርስቲያን ይባላል፡፡ በሐዲስ ኪዳን የመጀመሪያዋ ቤተክርስቲያን በአምላክ እናት ስም የታነጸችው በዚሁ እለት በሰኔ 20 ቀን ነው፡፡ አናጺውም ደግሞ እራሱ ባለቤቱ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን፤ ቦታው በፊልጵስዩስ ነው፤ ቤተክርስቲያኗ የተሰየመችው ደግሞ በእመቤታችን ስም ነው፤ ጥንተ ነገሩስ (ታሪኩ) እንደምን ነው ቢሉ፤ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና አምላካችን መደኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀመዛሙርቱን ‹‹ሑሩ ወመሐሩ ኵሎ አሕዛበ፤ አሕዛብን ሁሉ ሒዱና አስተምሩ፡፡›› /ማቴ. 28፥19/ ባላቸው ቃል መሠረት ሐዋርያት በወንጌል ያርሷት ዘንድ በዕጣ ተካፍለዋታል:: የሰው ልጅ ድኅነቱ የሚፈጸመው ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ሲቀበል ነውና (ዮሐ. 6፥ 56) አበው ሐዋርያት ቊርባንን በተመረጡ ሰዎች ቤት እያዘጋጁ ቀድሰው ያቆርቡ ነበር:: በመጀመሪያ በጽርሐ ጽዮን፣ ቀጥሎም በተለያዩ ሰዎች ቤት እንዲህ ይከናወን ነበር፡፡ ለጸሎት ሥራ ደግሞ አንዳንዴ ምኵራበ አይሁድን ይጠቀሙ ነበር:: እየቆየ ሲሔድ ግን ከአሕዛብ ያመኑ ሰዎች ቊጥር እጅጉን በመብዛቱ /በተለይ ቅዱስ ዻውሎስ ያሳመናቸው ለጸሎት እያሉ ወደ ጣዖት ቤት መግባት አመጡ::/ በዚህ ምክንያት መምህራን ሕዝቡን ‹‹ካመናችሁ በኋላ እንዴት ወደ ጣዖት ቤት ትገባላችሁ?›› ቢሏቸው ‹‹እኛ ምን እናድርግ! የምንጸልይበት ቤት የለን›› ሲሉ መለሱላቸው:: ነገሩ ሲያያዝ ከደጋጉ ሐዋርያት ዻውሎስና በርናባስ ደረሰ:: ወዲያውኑ አንዳንድ ወንድሞች ቤት ‹‹ለምን አናንጽም?›› ብለው ነበር:: ቅዱስ ዻውሎስ ግን ‹‹ሊቀ ሐዋርያቱ ሳይፈቅድ አይሆንም›› አለ:: (ለዚህ ነው ዛሬም ሊቀ ዻዻስ ካልፈቀደ ቤተክርስቲያን የማይታነጸው፡፡) ከዚያ ቅዱሳን ዻውሎስና በርናባስ ሐዋርያቱ ወዳሉበት ሔደው ነገሩን ለቅዱስ ዼጥሮስ አስረዱ:: ሊቀ ሐዋርያቱ ቅዱስ #ዼጥሮስም ‹‹የጌታችን ፈቃዱ መኾኑን እናውቅ ዘንድ ተያይዘን ሱባዔ እንግባ›› ብሎ አዋጅ ነገረ:: በዓለም ያሉ ክርስቲያኖች ሁሉ በአንድ ልብ ሱባዔ ገቡ:: በሱባዔያቸው መጨረሻም ክብር ይግባውና ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በኪሩቤል ጀርባ ላይ ሆኖ እልፍ አእላፍ መላአክትን አስከትሎ በግርማ ወደ እነርሱ ወረደ፤ እመቤታችን በቀኙ ነበረች፡፡ ኹሉንም ሐዋርያት በሩቅም በቅርብም ያሉትን ደቀ መዛሙርቱን በደመና ጠቅሶ ፊልጵስዩስ በሚባል ሃገር ሰበሰባቸው፡፡ ከዚያም በስተምሥራቅ ከከተማ ወጣ ወዳለ ሥፍራ ወሰዳቸው፡፡ በዚያም ተራርቀው የነበሩ 3 ደንጊያዎች ነበሩ፡፡ 3ቱንም ድንጋዮችን በተአምራት አቀራርቦ አንሥቶ ጎተታቸው፡፡ ድንጋዮቹም እንደሰም ተለጠጡ፣ እንደ ግድግዳም ሆኑ፡፡ ቁመቱን ወርዱን መጥኖ ለሐዋርያቱ ሰጣቸው፡፡ እነርሱም እሳት እንዳየው ሰም በእጃቸው እየለመለሙ (እየሳቡ) ቁመቱን 24፥ ወርዱን 12 ክንድ አድርገው ዕጽብት፥ ግርምት የምትኾን 3 ክፍል ያላትን የመጀመሪያዋን ቤተክርስቲያን በ52 ዓ/ም ሰኔ 20 ቀን አነጹ፡፡ዳግመኛም የብርሃን ምሰሶ ወረደ፤ ጌታችንም በሰማያዊቷ ኢየሩሳሌም አምሳያ አድርጎ አነጻት፤ ሁለንተናዋም ተጠናቀቀ፡፡ ከዚህም በኋላ ጌታችን ለሐዋርያቱ ‹‹እንግዲህ እናንተም እንዲህ አድርጋችሁ ሥሩ፡፡›› ብሏቸው ዐረገ፡፡ ꔰꔰበማግስቱ ሰኔ 21 ዕለት ደግሞ ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አእላፍ መላእክትን፣ ሰማያውያን ቅዱሳንን እና እናቱን ቅድስት ድንግል ማርያምን ይዞ ወረደ:: ሐዋርያቱ አብዛኞቹ እዛው ሲጸልዩ አድረው ነበርና ጌታችን ከቅዳሴው በፊት 2 ነገሮችን አሳየ፤ አስቀድሞ ቤተክርስቲያኗን በድንግል እናቱ ስም አክብሮ ሥርዐተ ቤተክርስቲያንን አሳየ:: ቀጥሎ ደግሞ ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስን ከመካከል አቁሞ ‹‹አርሳይሮስ›› ሲል ሾመው:: ይኼውም የዓለም ሁሉ ሊቀ ዻዻሳት (ፓትርያርክ) ማለት ነው:: በዚህ ጊዜ ቅዱሳን መላእክት ‹‹አክዮስ›› እያሉ 3 ጊዜ አሰምተው ጮሁ:: አክዮስ ማለት በግዕዙ ‹‹ይደልዎ›› በአማርኛው ደግሞ ‹‹ይገባዋል፤ ያስምርለት›› እንደ ማለት ነው:: ጌታችን ይህን ከከወነ በኋላ ይቀድስ ዘንድ ጀመረ:: አማናዊት ማኅደሩን ድንግል ማርያምን መንበር አድርጎ፣ ቅዱስ ጴጥሮስ እንደ ተራዳኢ ካህን ቆሞ፣ ቅዱስ እስጢፋኖስ ሠራኢ ዲያቆን ኾኖ፣ ሐዋርያት ድንግልን ከበው፣ መላእክተ ብርሃን በክብራቸው ቆመው ጌታችን ቀድሶ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ለወዳጆቹ አቀበለ:: በዚያች ዕለት በፍጡር አንደበት ተከናውኖ ሊነገር የማይችል ደስታ ተደረገ:: ከቅዳሴ በኋላ ጌታችን ሐዋርያትን አዘዛቸው:: ‹‹ከዚህ ቀን ጀምሮ በመላው ዓለም በእናቴ በማርያም ስም አብያተ ክርስቲያናትን አንጹ፤ #ይህችን _እለት_የሚያከብራትን_አከብረዋለሁ::›› ብሏቸው ከድንግል እናቱና ከመላእክቱ ጋር ዐረገ:: ✤✤ ሥርዐተ ማኅሌቱ እንደየደብራችሁ ይትበሃል ትጠሙበበት ዘንድ የሁለቱንም (የላይ ቤት የግምጃ ቤትና የታች ቤት የበአታን) አብነት አስቀምጠንላችኋል፤:: ꔰ ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ꔰ Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem www.Finotehiwotsundayschool.com ✼ የድንግል እመቤታችን ልመናዋ ክብሯ፣ ጣዕመ ፍቅሯና በረከቷ በሁላችን ላይ ይደርብን::