Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览
频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 391 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 586,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 200 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 391 名订阅者。
根据 01 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 22,过去 24 小时变化为 -7,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 21.30%。内容发布后 24 小时内通常能获得 10.19% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 278 次浏览,首日通常累积 1 569 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 17。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 02 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
15 391
订阅者
-724 小时
+227 天
+2230 天
帖子存档
በዓለ አቡነ ሀብተማርያም 26
እንኳን አደረሳቸሁ
#የአቡነ ሀብተማርያም ወረብ በደብረ መድኀኒት አቡነ ሀብተማርያም ሊቃውንት ፤ ከሠተ አፉሁ፡፡
#ከሠተ አፉሁ ወልሳኑ ነበበለ አእቶ ወባረኮ ለእግዚአብሔር
መልዐ መንፈስ ቅዱስ ላዕለ ሀብተማርያም
#ይህንን ሊንክ በመጫን ይመልከቱ
https://youtu.be/GIzYreXgSOY
የታሰሩት 3 የሰንበት ት/ቤት አባላት በዋስ ተፈተዋል!!
ላለፉት 2 አመታት የሰንበት ትምሕርት ቤቱ መማሪያ ቦታ ለሆንው የአዳራሽ ተለዋጭ ቦታ ሳይሰጠው ሊፈርስ አይገባም ፤ ከሕንጻ ልማት ይልቅ ለሰው ቅድሚያ ሊሰጠው ይገባል በማለት ሲከራከሩ ከነበሩት አባላት መካከል የደብሩ አስተዳዳሪ የሆኑት መልአከ ሰላም ስዩም ወልደ ገብርኤል አስራ አራቱን መክሰሳቸው ይታወቃል፡፡
የቀጨኔ ፓሊስ መምሪያ የምርመራ መዝገቡን አደራጅቶ የከሳሽ እና የምስክር ቃል ከተቀበለ በኃላ ከ14ቱ ተከሳሾች የ5ቱን ቃል ተቀብሏል፡፡ 5ቱም በዋስ የተለቀቁ ሲሆን በቅርቡ ለአቃቤ ሕግ ቀርቦ ጉዳዩ ውሳኔ ይሰጥበታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ቢሆንም አሁንም ክሱ ሙሉ ለሙሉ የተዘጋ ስላልሆነ በሰ/ት/ቤቱ ማኀበራዊ ሚዲያ እና በውስጥ ገጽ ለሰ.ት.ቤቱ ጠበቃ ሆነን በመቆም በረከት እናግኝ ብላችሁ የጠየቃችሁን የህግ ሰዎች እና የመታሰራችንን ዜና ሰምታቹህ በማኀበራዊ ሚዲዎቻቹኅ ጉዳያችንን አሰስቧቹህ ላጋራቹሁት ለ .አ.አ ሰንበት ት/ቤቶች እንዲሁም ለቤ.ክ አገልጋዮች ከልብ እያመሰገንን በቀጣይ ሰ/ት/ቤቱ ፍትህ እስኪያገኝ ድረስ ትግሉ የሚቀጥል ስለሆነ አሁንም አንድነታችንና አብሮነታቸን እንዳይለየን እንጠይቃለን፡፡
በቀጣይም ፤ መጻፍያ ብዕሩን ለክስ ሳይሆን የጠፉ ልጆቹን ፅፎ ለሚሰበስብ ፤ አንደበቱን ለፖሊስ ሳይሆን ለቃለ እግዚአብሔር ፣ ልጆቹን ፍርድ ቤት ሳይሆን ለማኀሌት የሚያቆም እንደ ቅዱስ ጴጥሮስ ያለ ትክክለኛ የመንጋ ጠባቂ እስኪመጣልን ድረስ ጉዳያችንን አጠናክረን ለአ.አ ሐገረ ስብከት ሆነ ለሚመለከታችው የቤተ ክህነት አካላት የምናሳውቅ ይሆናል፡፡
በአገልግሎታቸን ሁሉ መድኀኔዓለም ይቅደም ፡፡
1. እጮኛ አለዎት ወይም ለመያዝ አስበዋል? የእጮኝነት ሕይወትዎ ለትዳር እንዲበቃ በክርስቲያናዊ መንገድ እንዴት መጓዝ እንዳለብዎት ያውቃሉ? ከእጮኝነት ጀምሮ ክርስቲያናዊ ሕይወትን እንዴት መለማመድ ይቻላል? ይምጡ ለእነዚህና መሰል ጥያቄዎቾ በዐውደ ጥናቱ በቂ ምላሽ ያገኛሉ።
2. የትዳር ሕይወትዎ እንዴት ነው ኦርቶዶክሳዊ መዐዛ አለው? በቤታችሁ ያለችው ትንሽዋ ቤተ ክርስቲያን ተዘግታለች ወይስ አገልግሎት እየሰጠች ነው? ትዳርዎ ጠንካራ መሠረት እንዲኖረው ምን እያደረጉ ነው? ትዳርዎ አደጋ እንዳንዣበበበት ይሰማዎታል? የእርስዎ እና የትዳር አጋርዎ መንፈሳዊ ሕይወት እኩል አለመራመዱ አሳስብዎታል?ይምጡ ለእነዚህና መሰል ጥያቄዎቾ በዐውደ ጥናቱ በቂ ምላሽ ያገኛሉ።
3. የወለዱዋቸው ልጆች ምክርዎን ይሰማሉ? ወይስ በራሳቸው መንገድ ነው የሚጓዙት? ልጆችዎን በኦርቶዶክሳዊ መንገድ እንዴት መቅረጽ እንዳለብዎ ያውቃሉ? ልጆችዎ ላይ እንዴት በጎ ተጽእኖ ማሳደር እንደሚችሉስ? ይምጡ ለእነዚህና መሰል ጥያቄዎቾ በዐውደ ጥናቱ በቂ ምላሽ ያገኛሉ።
4. ልጆችዎ ከመስመር የመውጣት አዝማሚያ ሲያሳዩ እንዴት እንደሚመልሷቸው ምን ያስባሉ? ክር፣ ከልጆችዎ ጋር አወንታዊ ንግግር እንዴት ማድረግ እንዳለብዎ ያውቃሉይት? ይምጡ ለእነዚህና መሰል ጥያቄዎቾ በዐውደ ጥናቱ በቂ ምላሽ ያገኛሉ።
5. ከዐውደ ጥናቱ ርዕሰ ጉዳይ ጋር የተገናኙ ጥያቄዎችዎን ይላኩልን፣ በዕለቱ ምላሽ ይሰጥባቸዋል።
ሁለት ቀን ብቻ ቀረዉ፤
የ55ኛ አመት ሀለተኛ መርሃ ግብር፤
0ውደ ጥናት ::
1. እጮኛ አለዎት ወይም ለመያዝ አስበዋል? የእጮኝነት ሕይወትዎ ለትዳር እንዲበቃ በክርስቲያናዊ መንገድ እንዴት መጓዝ እንዳለብዎት ያውቃሉ? ከእጮኝነት ጀምሮ ክርስቲያናዊ ሕይወትን እንዴት መለማመድ ይቻላል? ይምጡ ለእነዚህና መሰል ጥያቄዎቾ በዐውደ ጥናቱ በቂ ምላሽ ያገኛሉ።
ሁለት ቀን ብቻ ቀረዉ፤
የ55ኛ አመት ሀለተኛ መርሃ ግብር፤
0ውደ ጥናት ::
1. እጮኛ አለዎት ወይም ለመያዝ አስበዋል? የእጮኝነት ሕይወትዎ ለትዳር እንዲበቃ በክርስቲያናዊ መንገድ እንዴት መጓዝ እንዳለብዎት ያውቃሉ? ከእጮኝነት ጀምሮ ክርስቲያናዊ ሕይወትን እንዴት መለማመድ ይቻላል? ይምጡ ለእነዚህና መሰል ጥያቄዎቾ በዐውደ ጥናቱ በቂ ምላሽ ያገኛሉ።
2. የትዳር ሕይወትዎ እንዴት ነው ኦርቶዶክሳዊ መዐዛ አለው? በቤታችሁ ያለችው ትንሽዋ ቤተ ክርስቲያን ተዘግታለች ወይስ አገልግሎት እየሰጠች ነው? ትዳርዎ ጠንካራ መሠረት እንዲኖረው ምን እያደረጉ ነው? ትዳርዎ አደጋ እንዳንዣበበበት ይሰማዎታል? የእርስዎ እና የትዳር አጋርዎ መንፈሳዊ ሕይወት እኩል አለመራመዱ አሳስብዎታል?ይምጡ ለእነዚህና መሰል ጥያቄዎቾ በዐውደ ጥናቱ በቂ ምላሽ ያገኛሉ።
3. የወለዱዋቸው ልጆች ምክርዎን ይሰማሉ? ወይስ በራሳቸው መንገድ ነው የሚጓዙት? ልጆችዎን በኦርቶዶክሳዊ መንገድ እንዴት መቅረጽ እንዳለብዎ ያውቃሉ? ልጆችዎ ላይ እንዴት በጎ ተጽእኖ ማሳደር እንደሚችሉስ? ይምጡ ለእነዚህና መሰል ጥያቄዎቾ በዐውደ ጥናቱ በቂ ምላሽ ያገኛሉ።
4. ልጆችዎ ከመስመር የመውጣት አዝማሚያ ሲያሳዩ እንዴት እንደሚመልሷቸው ምን ያስባሉ? ክር፣ ከልጆችዎ ጋር አወንታዊ ንግግር እንዴት ማድረግ እንዳለብዎ ያውቃሉይት? ይምጡ ለእነዚህና መሰል ጥያቄዎቾ በዐውደ ጥናቱ በቂ ምላሽ ያገኛሉ።
5. ከዐውደ ጥናቱ ርዕሰ ጉዳይ ጋር የተገናኙ ጥያቄዎችዎን ይላኩልን፣ በዕለቱ ምላሽ ይሰጥባቸዋል።
አስቸኳይ የጠቅላላ ጉባኤ ጥሪ
ዛሬ እሮብ 12፡00 ሰዓት
#_ለአጥቢያችን_ምዕመናን_በሙሉ
ለቤተክርስቲያን ሕጻናትና ወጣቶች የታገሉ፣ የደከሙና ሁሉነገራቸውን የሰጡ የሰ/ት/ቤታችን_አባላት ታሰሩ!!!
ሁሉም እንደሚያውቀው በደብራችን አስተዳደር እና የሰንበት ት/ት/ቤታችን መካከል ከቋሚ የሰ/ት/ቤት የመማርያ ቦታ ጥያቄ ጋር በተያያዘ ከ 2 ዓመታት በላይ ከፍተኛ አለመግባባት ተከስቶ መቆየቱ የሚታወቅ ነው፡፡
በዚህ ሂደት ህጋዊ በሆነ መልኩ ሲሞግቱ ፣ ሁሉነገራቸውን ሰጥተው ለቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ህጻናትና ወጣቶች እድገት ሲታገሉ የነበሩ የሰ/ት/ቤቱ አባላት ላይ የደብሩ አስተዳደር በአጠቃላይ በተለይም ደግሞ የደብሩ አስተዳዳሪ በብዙ ድካም ሰ/ት/ቤቱ ባገኘው ተደጋጋሚ ውሳኔ ቂም ቋጥረው በቀል ይዘው ቆይተው በ 14 የሰ/ት/ቤቱ ወጣቶች ላይ ክስ መስርተዋል፡፡
ይሁንና የሀገረ ስብከታችን ሊቀ ጳጳስ በ20/07/2013 ዓ.ም ደብሩ ክሱን እንዲያቋጥ ለደብሩ አስተዳዳሪ አመራር የሰጡና የደብሩ አስተዳዳሪም በቀን 22/09/2013 ዓ.ም የሰበካ ጉባኤ ሪፖርት ለምዕመናን በቀረበበት ወቅት በአውደ ምህረት ላይ ለእናንተ ለምእመናን ክስ አንስቻለሁ፣ አቋርጫለሁ በማለት የሰጡትን ቃል በተግባር አጥፈው ክሱን ውስጥ ለውስጥ በመቀጠል በአሁኑ ሰዓት ከ14ቱ ክስ የተመሰረተባቸው አባላት መካከል በ 5ቱ ላይ የቅድሚያ የተከሳሽ ቃል ተወስዶ 3ቱ በቀጨኔ ፖሊስ ጣቢያ ታስረዋል፡፡
#እንኳን_ደስ_አለህ!
የሁል ጊዜም አገልጋያችን የሆንከው #መ_ር #ኢዮብ_በቀለ ፤ የበኵር ልጅክ የሆነችውን #ዕፀ_ዘዌ_ክርስቶስ የተሰኘችውን መጽሐፍህን ለአንባብያን በማቅረብክ እንኳን ደስ አለህ እያልን እጅግ የላቀውን ደስታችንን ልንነግርክ እንወዳለን ፡፡
#በነገረ_ድኀነት ላይ ያተኮረችው ይህች መጽሐፍህ ለብዙኀን ዕውቀትን እንደምታሰገኝ፤ ግሩም ከሆነው መጽሐፍክ ውስን ገጾች በማንበብ ብቻ መናገር ይቻላል፡፡
ደከምኝ ሰለቸኝ ሳትል በምታገለግለው አገልግሎት አምላከ ቅዱስ ጊዮርጊስ ፀጋውን አብዝቶ እንዲሰጥክ ጸሎታችን ነው ፡፡ ቀጣይ ስራዎችህንም በእግዚአብሔር ፈቃድ እንጠብቃለን ፡፡
ወላዲተ አምላክ ቅድስት ድንግል ማርያም አገልግሎትክን ትባርክ፡፡
ꔰ ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ꔰ
Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
Telegram https://t.me/medihanaelem
www.Finotehiwotsundayschool.com
ዓርብ ጉባዔ ዘሰኔ 18
#ትምሕርት በሊቀ ኅ ሩያን ቀሲስ ጥላሁን የ ደብረ ምጥማቅ ሰዐሊተ ምህረት ቅድስት ማርያም ካቴድራል ስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊ
#ዝማሬ በሙሐዘ ስብሀት ዲያቆን ልዑል ሰገድ ጌታቸው እና በዘማሪ ሚኪያስ ፀጋዬ
በስብሐት አልፏል
ለሳሞንቱ ያድርሰን ፤ አሜን፡፡ ትምህርቱን በዩቲዩብ ገጻችን የምንለጥፍ ይሆናል ፡፡
ጉባዔዉ ሳምንት ዓርብ ይቀጥላል።
#ሰኔ_21 #ሰኔ_ጐልጐታ ወሕንፀተ ቤተክርስቲያን
እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ለቅድስተ ቅዱሳን ለድንግል ማርያም ሰኔ ጐልጐታና ሕንፀተ ቤተ ክርስቲያን (ለመጀመሪያ ጊዜ ቤተ ክርስቲያን ለታነጸበት) ክብረ በዓል በሰላምና በጤና አደረሰን አደረሳችሁ፡፡
ꔰ ꔰሰኔ ጎልጎታ፤
‹‹ሰኔ ጐልጐታ፤ ችግር የምትፈታ፤
ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያም በዚህ ቀን (ሰኔ 21) ልጇን ወዳጇን ጐልጐታ በሚባል ቦታ ላይ እንበዋ እንደ ጅረት እስኪፈስ ድረስ ለኃጥአን ምሕረትን ለምናዋለች:: ጌታችንም ‹‹ስምሽን የጠራውን፤
በቃል ኪዳንሽ ያመነውን ሁሉ እምርልሻለሁ፡፡›› ብሎ ቃል ኪዳን ሰጥቷታል፡፡
ꔰꔰ ሕንፀተ ቤተ ክርስቲያን፤
ሰኔ 21 ከእመቤታችን #33ቱ በዓላት አንዱ ሲኾን፤ ሕንጸተ ቤተክርስቲያን ይባላል፡፡ በሐዲስ ኪዳን የመጀመሪያዋ ቤተክርስቲያን በአምላክ እናት ስም የታነጸችው በዚሁ እለት በሰኔ 20 ቀን ነው፡፡
አናጺውም ደግሞ እራሱ ባለቤቱ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን፤ ቦታው በፊልጵስዩስ ነው፤ ቤተክርስቲያኗ የተሰየመችው ደግሞ በእመቤታችን ስም ነው፤ ጥንተ ነገሩስ (ታሪኩ) እንደምን ነው ቢሉ፤ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና አምላካችን መደኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀመዛሙርቱን ‹‹ሑሩ ወመሐሩ ኵሎ አሕዛበ፤ አሕዛብን ሁሉ ሒዱና አስተምሩ፡፡›› /ማቴ. 28፥19/ ባላቸው ቃል መሠረት ሐዋርያት በወንጌል ያርሷት ዘንድ በዕጣ ተካፍለዋታል::
የሰው ልጅ ድኅነቱ የሚፈጸመው ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ሲቀበል ነውና (ዮሐ. 6፥ 56) አበው ሐዋርያት ቊርባንን በተመረጡ ሰዎች ቤት እያዘጋጁ ቀድሰው ያቆርቡ ነበር:: በመጀመሪያ በጽርሐ ጽዮን፣ ቀጥሎም በተለያዩ ሰዎች ቤት እንዲህ ይከናወን ነበር፡፡ ለጸሎት ሥራ ደግሞ አንዳንዴ ምኵራበ አይሁድን ይጠቀሙ ነበር:: እየቆየ ሲሔድ ግን ከአሕዛብ ያመኑ ሰዎች ቊጥር እጅጉን በመብዛቱ /በተለይ ቅዱስ ዻውሎስ ያሳመናቸው ለጸሎት እያሉ ወደ ጣዖት ቤት መግባት አመጡ::/ በዚህ ምክንያት መምህራን ሕዝቡን ‹‹ካመናችሁ በኋላ እንዴት ወደ ጣዖት ቤት ትገባላችሁ?›› ቢሏቸው ‹‹እኛ ምን እናድርግ! የምንጸልይበት ቤት የለን›› ሲሉ መለሱላቸው:: ነገሩ ሲያያዝ ከደጋጉ ሐዋርያት ዻውሎስና በርናባስ ደረሰ:: ወዲያውኑ አንዳንድ ወንድሞች ቤት ‹‹ለምን አናንጽም?›› ብለው ነበር:: ቅዱስ ዻውሎስ ግን ‹‹ሊቀ ሐዋርያቱ ሳይፈቅድ አይሆንም›› አለ::
(ለዚህ ነው ዛሬም ሊቀ ዻዻስ ካልፈቀደ ቤተክርስቲያን የማይታነጸው፡፡) ከዚያ ቅዱሳን ዻውሎስና በርናባስ ሐዋርያቱ ወዳሉበት ሔደው ነገሩን ለቅዱስ ዼጥሮስ አስረዱ:: ሊቀ ሐዋርያቱ ቅዱስ #ዼጥሮስም ‹‹የጌታችን ፈቃዱ መኾኑን እናውቅ ዘንድ ተያይዘን ሱባዔ እንግባ›› ብሎ አዋጅ ነገረ::
በዓለም ያሉ ክርስቲያኖች ሁሉ በአንድ ልብ ሱባዔ ገቡ:: በሱባዔያቸው መጨረሻም ክብር ይግባውና ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በኪሩቤል ጀርባ ላይ ሆኖ እልፍ አእላፍ መላአክትን አስከትሎ በግርማ ወደ እነርሱ ወረደ፤ እመቤታችን በቀኙ ነበረች፡፡ ኹሉንም ሐዋርያት በሩቅም በቅርብም ያሉትን ደቀ መዛሙርቱን በደመና ጠቅሶ ፊልጵስዩስ በሚባል ሃገር ሰበሰባቸው፡፡ ከዚያም በስተምሥራቅ ከከተማ ወጣ ወዳለ ሥፍራ ወሰዳቸው፡፡ በዚያም ተራርቀው የነበሩ 3 ደንጊያዎች ነበሩ፡፡ 3ቱንም ድንጋዮችን በተአምራት አቀራርቦ አንሥቶ ጎተታቸው፡፡ ድንጋዮቹም እንደሰም ተለጠጡ፣ እንደ ግድግዳም ሆኑ፡፡ ቁመቱን ወርዱን መጥኖ ለሐዋርያቱ ሰጣቸው፡፡
እነርሱም እሳት እንዳየው ሰም በእጃቸው እየለመለሙ (እየሳቡ) ቁመቱን 24፥ ወርዱን 12 ክንድ አድርገው ዕጽብት፥ ግርምት የምትኾን 3 ክፍል ያላትን የመጀመሪያዋን ቤተክርስቲያን በ52 ዓ/ም ሰኔ 20 ቀን አነጹ፡፡ዳግመኛም የብርሃን ምሰሶ ወረደ፤ ጌታችንም በሰማያዊቷ ኢየሩሳሌም አምሳያ አድርጎ አነጻት፤ ሁለንተናዋም ተጠናቀቀ፡፡ ከዚህም በኋላ ጌታችን ለሐዋርያቱ ‹‹እንግዲህ እናንተም እንዲህ አድርጋችሁ ሥሩ፡፡›› ብሏቸው ዐረገ፡፡
ꔰꔰበማግስቱ ሰኔ 21 ዕለት ደግሞ ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አእላፍ መላእክትን፣ ሰማያውያን ቅዱሳንን እና እናቱን ቅድስት ድንግል ማርያምን ይዞ ወረደ:: ሐዋርያቱ አብዛኞቹ
እዛው ሲጸልዩ አድረው ነበርና ጌታችን ከቅዳሴው በፊት 2 ነገሮችን አሳየ፤ አስቀድሞ ቤተክርስቲያኗን በድንግል እናቱ ስም አክብሮ ሥርዐተ ቤተክርስቲያንን አሳየ:: ቀጥሎ ደግሞ ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስን ከመካከል አቁሞ
‹‹አርሳይሮስ›› ሲል ሾመው:: ይኼውም የዓለም ሁሉ ሊቀ ዻዻሳት (ፓትርያርክ) ማለት ነው:: በዚህ ጊዜ ቅዱሳን መላእክት ‹‹አክዮስ›› እያሉ 3 ጊዜ አሰምተው ጮሁ:: አክዮስ ማለት በግዕዙ ‹‹ይደልዎ›› በአማርኛው ደግሞ ‹‹ይገባዋል፤ ያስምርለት›› እንደ ማለት ነው::
ጌታችን ይህን ከከወነ በኋላ ይቀድስ ዘንድ ጀመረ:: አማናዊት ማኅደሩን ድንግል ማርያምን መንበር አድርጎ፣ ቅዱስ ጴጥሮስ እንደ ተራዳኢ ካህን ቆሞ፣ ቅዱስ እስጢፋኖስ ሠራኢ ዲያቆን ኾኖ፣ ሐዋርያት ድንግልን ከበው፣ መላእክተ ብርሃን በክብራቸው ቆመው ጌታችን ቀድሶ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ለወዳጆቹ አቀበለ::
በዚያች ዕለት በፍጡር አንደበት ተከናውኖ ሊነገር የማይችል ደስታ ተደረገ:: ከቅዳሴ በኋላ ጌታችን ሐዋርያትን አዘዛቸው:: ‹‹ከዚህ ቀን ጀምሮ በመላው ዓለም በእናቴ በማርያም ስም አብያተ ክርስቲያናትን አንጹ፤ #ይህችን _እለት_የሚያከብራትን_አከብረዋለሁ::›› ብሏቸው ከድንግል እናቱና ከመላእክቱ ጋር ዐረገ::
✤✤ ሥርዐተ ማኅሌቱ እንደየደብራችሁ ይትበሃል ትጠሙበበት ዘንድ የሁለቱንም (የላይ ቤት የግምጃ ቤትና የታች ቤት የበአታን) አብነት አስቀምጠንላችኋል፤::
ꔰ ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ꔰ
Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
Telegram https://t.me/medihanaelem
www.Finotehiwotsundayschool.com
✼ የድንግል እመቤታችን ልመናዋ ክብሯ፣ ጣዕመ ፍቅሯና በረከቷ በሁላችን ላይ ይደርብን::
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
