en
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Open in Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 394 subscribers, ranking 5 590 in the Religion & Spirituality category and 2 197 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 394 subscribers.

According to the latest data from 30 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 21 over the last 30 days and by 1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 21.61%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 10.23% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 327 views. Within the first day, a publication typically gains 1 576 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 17.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 01 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

15 394
Subscribers
+124 hours
+307 days
+2130 days
Posts Archive
#ጥር_7_በዓለ_ሥላሴ_የሰናዖርን_ግንብ_ያፈራረሱበትና_ቋንቋ_የደባለቁበት_ዕለት፡፡ #የሰናዖርን_ግንብ እና #በቅድስት_ሥላሴ_የተሰየሙ_አድባራትና_ገዳማት ፤ከታች ያንብቡ ዘግይተን ስለጻፍንላቹሁ ይቅርታ ጠየቀን ✤✤✤✤✤ “#ንዑ_ንረድ_ወንዝርዎ_ ከመ_ኢይሳምዑ_ነገሮሙ_አሐዱ_ምስለ_ካልኡ፤›› “ኑ ፥እንውረድ ፤ አንዱ የአንዱን ነገር እንዳይሰማ ቋንቋቸውን እንደባልቅባችው”ዘፍ 11፥7 #በባቢሎን የነበሩት በሰናዖር ሰፊ ሜዳ አግኝተው ‹ሳንሞት ስም ማስጠሪያ ግንብ እንገንባ› አገር እናቅና እስከ ሰማይ የመሚደርስ ግንብ እንስራ ተባባሉ ፤ማይ አይኀ በወረደ ጊዜ እንዳያጠፋን የምንጠጋበት ግንብ እንስራ ብለው ሥራ ጀመሩ ፤ አንድም ሞትን የሚያመጡብን ሥላሴ ናቸውና እርሱን ገለን ሞትንም እናጠፋለን ሲሉ፡፡ ✤ይህንን ግንብ #43 ዓመት ሰርተውታል ቁመቱም #5433 ከ2 ስንዝር ነው፤ በፀሐይም እያበሰሉ ይበሉ ጀምረው ነበር ፡፡ ✤ከዚያም ሆነው ጦር እየሰበቁ ይወረውሩ ጀመር ሰይጣን ከደመና በምትሀት ደም እየቀባ ይልክላቸዋል እነርሱም ደሙን እያዩ ‹‹ አሁን አብን ወጋነው አሁን ወልድን ወጋነው ….›› ይሉ ጀመር እግዚአብሔርም የሰናዖርን ግንብ ይጥልባችው ዝንድ ‹‹ንዑ ንረድ ወንዝርዎ ✤ ከመ ኢይሳምዑ ነገሮሙ አሐዱ ምስለ ካልኡ፤›› አሉ የአንዱን ቋንቋ አንዱ እንዳይሰማው ወርደን ቋንቋቸውን እንለያየው ፡፡ ሥላሴ ፍጥረት ሁሉ ቢጎዳ አይወዱምና #72_ቋንቋ አመጡባቸው፤ አንዱ እሣት አምጣ ሲለው አንዱ ውሃ ያመጣል አንዱ ጭቃ ሲል ደግም እንጨት ያመጣለታል፡፡ ✤ከዚያም ትተው ወረዱ ነገር ግን ግንቡን እንደ ጣዖት አርገው ማምልክ ሲጀምሩ ሥላሴ ጽኑ ነፋስ አስነስተው በትነውታል፡፡ #ምሥጢረ_ሥላሴን ሲያስረዳ ( “እግዚአብሔርም አለ” አንድነታቸውን ሲያጠይቅ ድግሞም ኑ እንውረድ አለ ፤ ሶስትነታቸውን ሲያጠይቅ፤) (ዘፍ 11) #ባቢሎን ማለት ዝርው (ዝሩት) ሲሆነ ቋንቋ እና በቦታ ስለተለያዩበት ስያሜውን አግኝቷል (እግዚአብሔር ቋንቋን በትኗልና፣ አህዛብንም በዓለም ሁሉ በትኗልና፡፡ ‹‹…ሥላሴ ሕጸበኒ ወአንጽሐኒ እምአበሳየ በሐሊበ ምሕረትከ ›› ሰይፈ ሥላሴ ዘዓርብ ✤✤✤✤✤ #share እና #Like ማድረግ እንዳይረሱ #በአዲስ_አበባ_የቅድስት_ሥላሴ_በዓል_የሚከበርባቸው_ #፲፭ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. #መካነ_ሥላሴ ( #መንበረ_ፀባዖት_ቅድስት_ሥላሴ_ቤ.ክ.)፤ (አዲስ አበባ ላይ በ1883 ዓ.ም. የተመሠረተ፤ ነገር ግን ታቦቱ ቀድሞ የነበረና ከ600 ዓመታት በላይ ታሪክ ያለው) አድራሻው፤ አራዳ ክፍለ ከተማ፥ 4 ኪሎ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → 4 ኪሎ፤ ፪. #መንበረ_ስብሐት_ቅድስት_ሥላሴ አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ ሽሮ ሜዳ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(ከአራዳ ጊዮርጊስ)(ከመርካቶ)(ከቦሌ)(ከካዛንቺስ)(ከስታዲየም) → ሽሮ ሜዳ፡፡ ፫. #ደብረ_ሲና_ቅዱስ_እግዚአብሔር_አብ፤ (በድርብነት ይከበራል) አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ በአዲሱ ገበያ በቀጨኔና በእንጦጦ መሃል ላይ የሚገኝ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(ከመርካቶ) → አዲሱ ገበያ(ቀጨኔ) → ቅዱስ እግዚአብሔር አብ፡፡ ፬. #መሪ_ምሥራቀ_ፀሐይ_ቅድስት_ሥላሴ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አያት መሪ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → መገናኛ → መሪ/አያት/፡፡ ፭. #ካራ_አሎ_ቅድስት_ሥላሴ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ካራ አሎ ፥ አባዶ አጠገብ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → መገናኛ → ካራ አሎ፡፡ ፮. #ጠሮ_ደብረ_ብርሃን_ቅድስት_ሥላሴ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ከተማ፥ ጠሮ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ አራዳ/መርካቶ/ → ኮልፌ፡፡ ፯. #ጀሞ_ፈለገ_ኮሬብ_ቅድስት_ሥላሴና_ቅድስት_ማርያም አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ጀሞ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ አራዳ ሸዋ ዳቦ ቤት /ሜክሲኮ/ → ጀሞ፡፡ ፰. #ደብረ_ቀራንዮ_መድኀኔ ዓለም፤ (በድርብነት ይከበራል) አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ቀራንዮ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ጦር ኃሎች → ቀራንዮ፡፡ ፱. #አየር_ጤና_አንቀጸ_ብርሃን_ቅድስት_ኪዳነ_ምሕረት፤ (በድርብነት ይከበራል) አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ አየር ጤና፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ጦር ኃሎች → አየር ጤና፡፡ ወይም፤ ከፒያሳ ሸዋ ዳቦ ቤት → አለም ባንክ/ኤር ጤና/፡፡ ፲. #ሰፈረ_ገነት_ቅድስት_ሥላሴ አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ወረዳ 4፤ ታክሲ፤ ከሜክሲኮ → ላፍቶ፡፡ ፲፩. #ፈለገ_ብርሃን_ቅድስት_ሥላሴ አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፤ ታክሲ፤ ከሜክሲኮ → ላፍቶ፡፡ ፲፪. #ቂሊንጦ_ቅድስት_ሥላሴ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ወረዳ 9 ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → /በጎሮ/ ቂሊንጦ ወይም ከፒያሳ → ቃሊቲ → ቂሊንጦ፡፡ ፲፫. #ኤረር_ጽርሐ_አርያም_ቅድስት_ሥላሴ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ወረዳ 9፥ ጎሮ ሰፈር፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ጎሮ፡፡ ፲፬. #መሪ_ቅድስት_ሥላሴ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ መሪ አያት፥ ወረዳ 13፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → መሪ/አያት/፡፡ ፲፭. #ቦሌ_ኆኅተ_ብርሃን_ቅድስት_ማርያም፤ (በድርብነት ይከበራል) አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ገርጂ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ገርጂ፡፡ #በሃገራችን_በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የቅድስት_ሥላሴ_በዓል_የሚከበርባቸው_ #፲ #ገጥንታውያን_ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. #ማኅበረ_ሥላሴ_ገዳም፤ (ከ2014 ዓመታት በላይ ያስቈጠረ፤ የብዙ ቅዱሳን /የአባ ዐምደ ሥላሴ፣ የአባ ክፍለ ማርያም፣ የ7ቱ ዘሥላሴ፣ የአባ አርከ ሥሉስ ቅዱስ፣ …….. ) መፍለቂያ፡፡ አድራሻ፤ ምዕራብ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ቋራ (መተማ)፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር/አዘዞ/ → ሸዲ/መተማ/ → በእግር፡፡ ፪. #ዱጉም_ሥላሴ_ገዳም፤ አድራሻ፤ ትግራይ፥ ገርዓልታ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ → በመቀለ (በጎንደር) → ገርዓልታ፡፡ ፫. #ደብረ_ወገግ_አሰቦት_ቅድስት_ሥላሴና_አቡነ_ሳሙኤል፤ (በ13ኛው ክ/ዘመን በታላቁ ጻድቅ በአቡነ ሳሙኤል ዘደብረ ወገግ የተስፋፋ፥ ቅዱስ ዑርኤል የጌታን ደም በጽዋው የመጨረሻውን እንጥፍጣፊ ያፈሰሰበት፥ በርካታ ቅዱሳን የተሰወሩበት፥ አሁንም የሚሠወሩበት፥ የምሥጢር ቦታ) አድራሻ፤ ሐረርጌ፥ አሰበ ተፈሪ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ናዝሬት/አዳማ/→ አሰበ ተፈሪ → አሰቦት፡፡ ፬. #ሰሜን_ሸዋ_ደብረ_ብርሃን_ሥላሴ_፤ (በ14ኛው ክፍለ ዘመን በዓፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን የተመሠረተ፡፡) አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ደብረ ብርሃን ከተማ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ብርሃን ከተማ፡፡ ፭. #መካነ_ሥላሴ_ደቡብ_ወሎ_ወረኢሉ፤ (በ1500ዓ.ም. በዐፄ ናዖድ የተመሠረተና በልጁ በዐፄ ልብነ ድንግል ሥራው የተጠናቀቀ፤ ባለ 16 መንበር፥ በዕንቊና በወርቅ የታነጸ የነበረ፤ /ኋላ በግራኝ የፈረሰ/፤ ነገር ግን ጽላቱ በዐፄ ምኒልክ ወደ አዲስ አበባ መጥቶ ቀድሞ 4 ኪሎ መካነ ሥላሴ አሁን መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ በመባል የሚጠራው)፤ ጊዜ ገቢር ለእግዚአብሔር ነውና በቀድሞው ቅርጹ በባለ 16 መንበር ተደርጎ 2009 ዓ.ም. አካባቢ የመሠረት ድንጋይ ተጥሎ በመገንባት ላይ ይገኛል፤ (ለሕንፀታ ቤቱ ሁላችንንም ያብቃን)፡፡ አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት፥ ወረኢሉ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ → ወረኢሉ፡፡ ፮. #ፀዓዳ_አምባ_ቅድስት_ሥላሴና_አቡነ_ሰይፈ_ሚካኤል_ገዳም፤ (በ1669 ዓ.ም. የተገደመ፤ መሄጃ መንገዱ እጅግ አስደናቂና በ2ቱም በኩል ገደል የኾነ) አድራሻ፤ ኤርትራ፥ ዞባ አንሰባ፥ ከረን፤

"‹‹የእግዚአብሔርን የቃል ኪዳን ታቦትን ሌዋውያን ካህናት ተሸክመውት ባያችሁ ጊዜ ከሰፈራችሁ ተነሥታችሁ ተከተሉት፡፡›› ኢያሱ ፫፥፫ የ2014 ዓ.ም የ #በዓለ_ጥምቀት ማስታወሻዎች ፎቶ ስብስብ 1"

‹‹የእግዚአብሔርን የቃል ኪዳን ታቦትን ሌዋውያን ካህናት ተሸክመውት ባያችሁ ጊዜ ከሰፈራችሁ ተነሥታችሁ ተከተሉት፡፡›› ኢያሱ ፫፥፫ የ2013 ዓ.ም የ #በዓለ_ጥምቀት ማስታወሻዎች ፎቶ ስብስብ 1

ጥር 6 በዓለ ግዝረት፥ ዕረገተ ኤልያስ ዕረፍተ ኖኅ፥ ልደተ ቅድስት አርሴማ፥ ዕረፍተ ዐቢይ ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ፥ አቡነ ኖኅኖኅ አባ ሙሴ ገዳማዊ፥ አባ ወርክያኖስ፥ ወአባ ሙሴ፡፡ #ግዝረተ_እግዚእነ_ኢየሱስ_ክርስቶስ ፠ ጌታችን በተወለደ በ8ኛ ቀኑ ዕጉለ ማዕነቅ ይዞ ወደ ቤተ ግዝረት በመግባት የኦሪትን ሕግ የፈጸመበት ዕለት ነው፡፡ ፠ ‹‹ጌታ ክርስቶስ በሥጋ ግዝረትን ተቀበለ፣ ለአባቶች የተሰጠውን ቃልኪዳን ይፈጽም ዘንድ›› /ሮሜ.፲፭፥፰/፡፡ ፠ በቅዱስ ወንጌል እንደ ተጻፈ በስምንተኛው ቀን እንደ ኦሪቱ ሥርዓት ግዝረት ይፈጸምለት ዘንድ ሕፃኑ ጌታችንን ወደ ቤተ መቅደስ ወሰዱት፡፡ መጥምቁ ዮሐንስ ሲገረዝ የሊቀ ካህን ልጅ ነው ብለው ሊገርዙት ወደ እርሱ መጡ፡፡ ጌታችን ግን ወደ ምድር የመጣው፡፡ ለትሕትና ነው እንጂ ለልዕልና አይደለምና ወሰዱት አለ /ትርጓሜ ወንጌለ ሉቃስ/፡፡ ፠ የእመቤታችን ድንግልናዋ ሳይለወጥ ከድንግል ማኅፀን እንደመውጣቱ የጌታችን ግዝረቱም የማይመረመር ሆነ፡፡ እንዲሁ በተዘጋ ቤት መግባቱና መውጣቱ እንደማይመረመር እነዲሁ እንደፈቀደ ከረቀቀ ጥበቡ ችሎታውን በመገረዝ ከሥጋው ምንም ምን ሳይቆረጥ ገለጠ፡፡ #ቅዱስ_ኤልያስ_በእሳት_ሰረገላ_ወደ_ብሔረ_ብፁዓን_ያረገበት_ዕለት_ነው፡፡ **በቅዱስ መጽሐፍ ውስጥ ካሉት ቅዱሳን ነቢያት ዝናም በማቆም ብቸኛ ነቢይ ነው፡፡ ✤ የሰማርያው ነቢይ ቴስቢያዊው ኤልያስ ከቅዱሳን አበው ነቢያት አንዱ ሲኾን አባቱ ኢያሴዩ እናቱ ደግሞ ቶናህ(ቶና) ሲባሉ ሲወለድ መላእክት በእሳት ሰፋድል (መጠቅለያ መጐናጸፊያ) ጠቅልለውት ነው፡፡ የስሙ ትርጉምም ‹‹እግዚአብሔር አምላክ ነው›› ማለት ነው፡፡ ** ኤልያስ ብዙ ነገር ስለሚያስተምር የቀና እምነቱን ውጤት ጥቂት መመልከት እኔ ማነኝ? ለሚሉት እጅ ይዞ ይመራል፡፡ ✤ 1. ለሦስት ዓመት ከመንፈቅ ሰማይ ዝናም ለዘር፥ ጠል ለመከር ከመስጠት እንዲከለከል ምድርም የተከሉባትን ✤ 2. አመጸኞች አክአብንና ኤልዛቤልን ምንነታቸውን ካሳወቀ በኋላ የዘጋውን ለመክፈት ወደ ፈጣሪው በመጸለይ ዝናም አዝንሟል፡፡ ✤ 3. በተፈጥሮ የማይመስላቸው በቋንቋም የማይግባባቸው እንኳን ለሰው ሥጋ ሊያመጡ ከሰው ሥጋ የሚነጥቁ አሞራዎች እንጀራና ሥጋ ለምግብ እንዲያመላልሱለት አደረገ 1ኛ ነገሥ. 17፥6-7፡፡ እነዚህ አሞራዎች ለሦስት ዓመት ከመንፈቅ በጋ ከክረምት የለምንም እረፍት ኤልያስን ሲያገለግሉ ኖረዋል፡፡ እምነት ካለ ተአምር መሥራት አይገድም ይህንም ከኤልያስ ይማሯል፡፡ ✤ 4. ለአንዲት መበለት ዱቄትና ዘይት አበረከተ፤ ኤልያስ ቁራሽ እየለመነ ያደረገውን ተአምር ልብ ይሏል፡፡ 1ኛ ነገሥ. 17፥16-24፡፡ ✤ 5. ዱቄትና ዘይት ያበረከተላት የሰራፕታዋ ሴት ልጇ /ኋላ ዮናስ ነቢይ የሆነው/ ቢሞት ከሞት አስነሳው 1ኛ ነገሥ. 17፥20-23 ✤ 6. ለብዙ ጊዜ በቤተ መንግሥት ተሰግስገው አክአብና ኤልዛቤልን በሐሰት ሲደልሉ፥ ግብዝ ሕብረተሰቡን ሲያታልሉ፥ ለፍቶ ያገኘው ገንዘቡን ሲሸልጉ፥ በኀጢአት ሊያስወጉ የነበሩ ነቢያተ ሐሰትና ካህናተ ጣዖትን በሕብረተሰቡ ፊት እስከ መምህራቸው ሰይጣን በቅሌት አከናንቦ ሲያስቅባቸው ውሏል፤ ሐሰቶች የነበሩትን 850 የሚጠጉ የጣዖት ካህናትንም ወደ ቂሶን ወንዝ አውርዶ ፈጅቷቸዋል፡፡ 1ኛ ነገሥ. 18 20 -29 ✤ 7. ወደ ፈጣሪው በጸሎት በማመልከት ያቀረበው ንጹሕ መሥዋዕቱን ከሰማይ እሳት ወርዶ በሰው ፊት በላለት (ተቀበለለት) 1ኛ ነገሥ. 18፥30-40፡፡ በዚህም ማንነቱን በሰይጣንና በሰይጣን አቀንቃኞች ፊት አስመስክሯል፡፡ ✤ 8. እሳት ከሰማይ በማዝነም ሊጣሉት የመጡትን መምለኪያነ ጣኦት፥ ምሉአነ ኀጢአት፤ የሰይጣን ሠራዊት በሰው ደም የሰከሩ፥ በዲያብሎስ የሚመሩ ጠላቶቹን አጋይቷል 2ኛ ነገሥ 1 9-13 ✤ 9. ምግብና መጠጥ መልአክ ከሰማይ አመጣለት ያንን ተመግቦ ለአርባ ቀን ያለምንም ምግብና መጠጥ እስከ እግዚአብሔር ተራራ እስከ ኮሬብ ድረስ 40 ቀንና 40 ሌሊት ተጉዟል 1ኛ ነገሥ. 19፥5-7፡፡ ✤ 10. በመጎናጸፊያው የዮርዳኖስን ባሕር ከፍሎ ከነ ደቀመዝሙሩ በደረቅ ተሻግሯል 2ኛ ነገሥ. 2፥11፡፡ ለደቀመዝሙሩም ሀብተ መንገፈስ ቅዱስን አድሎታል፡፡ ✤ 11. በትህትናው ‹‹ይበቃኛል፤ አሁንም አቤቱ እኔ ከአባቶቼ አልበልጥምና ነፍሴን ውሰድ›› ብሎ እንዲሞት ለመነ፡፡ እግዚአብሔር ግን ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በ918 ዓመተ ዓለም ሳይሞት በሕይወቱ መራራውን ሞት ዕያየው በብርሃን ሠረገላ ወደሰማይ አሳርጎታል፡፡ 2ኛ ነገሥ. 2፥6-9 ✤ 12. እንደ አስፈላጊነቱ ከፈጣሪው ጋር ለብዙ ጊዜ ተነጋግሯል፡፡ ✤✤#ከአንድ እስከ አስራ አንድ ያደረጋቸውን ተአምራት የፈጸመለት ታማኝ ፈጣሪው ሰው በሆነበት ወራት በተራራ ከጓደኞቹ ጋር ብርሃነ መለኮቱን ገለጠለት ማቴ 17፥3፡፡ #ዳግመኛም ዛሬ የአባቶችን ኖኅ መታሰቢው ነው፡፡ ኖኅ ግን በእግዚአብሔር ፊት ሞገስን አገኘ …ኖኅም በትውልዱ ጻድቅ፥ ፍጹምም ሰው ነበር፡፡ ኖኅ አካሔዱን ከእግዚአብሔር ጋር አደረገ፡፡ /ዘፍ. 6፥7/ #ዳግመኛም በዚህች ዕለት በበረሃ ስልሳ ዘመናት የኖረ የቅዱሳንን ልቡና ከማየቱ የተነሣ ያደነቀ፤ ፊቱም ተለውጦ እንደእሳት ፍሕም ሆነ አባ ሙሴ በዓለ ዕረፍቱ ነው፡፡ #በአዲስ_አበባ_የጌታችን_በዓለ_ግዝረት_የሚከበርባቸው_ #፪ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. ገነተ ኢየሱስና ገነተ ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻው፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ፈረንሳይ፤ ታክሲ፤ ከአራዳ ጊዮርጊስ ሞቢሉ ጋር (4 ኪሎ) (6 ኪሎ) → ፈረንሳይ/ኢየሱስ/፤ ፪. ገዳመ ኢየሱስ ቤ/ክ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፤ #በሃገራችን_በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የጌታችን_በዓለ_ግዝረት_የሚከበርባቸው_ #፬ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. ምዕራፈ ቅዱሳን በልበሊት ኢየሱስ ገዳም፤ አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ እንሳሮ ወረዳ፥ ጀማ በረሃ፤ ፪. ለብቃ ኢየሱስ፤ (ተአምረኛ የኾነ ፍልውሃ ጠበል የሚፈልቅበት፤ በቆዳ በሽታ በአካል፥ ደዌ የፈራረሰን ሰውነት ሳይቀር የሚጠግን)፡፡ ከገናናነቱ ተነሣ የሚከተለው ግጥሞች ተገጥሞለታል፡፡ ፨ የለብቃው ኢየሱስ፥ የለብቃው፤ የፈረሰ ገላ ትጠቅማለህ አሉ፡፡ እየተባለ የሚዘመርለት፡፡ አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ መርሐ ቤቴ፥ ሚዳና ወረሞ ወረዳ፤ ወይም፤ ከደቡብ ወሎ (ደሴ ወይም ወግዲ) → መርሃ ቤቴ /አለም ከተማ/ → ለብቃ ኢየሱስ፡፡ ፫. በለስ ዋሻ ኢየሱስ ገዳም፤ (ጥንታዊና የቅዱሳን መናኸሪያ፤ በተጕለት ከሚገኙ ከ5ቱ የቅዱሳን መናኸሪያ ገዳም አንዱ፡፡) አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ተጉለትና ቡልጋ፥ አይዞሽ አሞራ፤ ወይም ከአዲስ አበባ ላምበረት አውቶቡስ ተራ → ደብረ ብርሃን → በኩክ የለሽ መንገድ → ዘንባባ ኢየሱስ → በለስ ዋሻ ፬. አማኑኤል ኢየሱስ ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ ምሥራቅ ጎጃም ሃገረ ስብከት፥ ደንበጫ፥ አማኑኤል ከተማ፤ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/ #share .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #ጾም #አጽዋማት #fasting's #ክብረ_በዓላት #Feast_of_the_lord #በዓለ_እግዚእነ

ጥር 6 በዓለ ግዝረት፥ ዕረገተ ኤልያስ ዕረፍተ ኖኅ፥ ልደተ ቅድስት አርሴማ፥ ዕረፍተ ዐቢይ ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ፥ አቡነ ኖኅኖኅ አባ ሙሴ ገዳማዊ፥ አባ ወርክያኖስ፥ ወአባ ሙሴ፡፡ #ግዝረተ_እግዚእነ_ኢየሱስ_ክርስቶስ ፠ ጌታችን በተወለደ በ8ኛ ቀኑ ዕጉለ ማዕነቅ ይዞ ወደ ቤተ ግዝረት በመግባት የኦሪትን ሕግ የፈጸመበት ዕለት ነው፡፡ ፠ ‹‹ጌታ ክርስቶስ በሥጋ ግዝረትን ተቀበለ፣ ለአባቶች የተሰጠውን ቃልኪዳን ይፈጽም ዘንድ›› /ሮሜ.፲፭፥፰/፡፡ ፠ በቅዱስ ወንጌል እንደ ተጻፈ በስምንተኛው ቀን እንደ ኦሪቱ ሥርዓት ግዝረት ይፈጸምለት ዘንድ ሕፃኑ ጌታችንን ወደ ቤተ መቅደስ ወሰዱት፡፡ መጥምቁ ዮሐንስ ሲገረዝ የሊቀ ካህን ልጅ ነው ብለው ሊገርዙት ወደ እርሱ መጡ፡፡ ጌታችን ግን ወደ ምድር የመጣው፡፡ ለትሕትና ነው እንጂ ለልዕልና አይደለምና ወሰዱት አለ /ትርጓሜ ወንጌለ ሉቃስ/፡፡ ፠ የእመቤታችን ድንግልናዋ ሳይለወጥ ከድንግል ማኅፀን እንደመውጣቱ የጌታችን ግዝረቱም የማይመረመር ሆነ፡፡ እንዲሁ በተዘጋ ቤት መግባቱና መውጣቱ እንደማይመረመር እነዲሁ እንደፈቀደ ከረቀቀ ጥበቡ ችሎታውን በመገረዝ ከሥጋው ምንም ምን ሳይቆረጥ ገለጠ፡፡ #ቅዱስ_ኤልያስ_በእሳት_ሰረገላ_ወደ_ብሔረ_ብፁዓን_ያረገበት_ዕለት_ነው፡፡ **በቅዱስ መጽሐፍ ውስጥ ካሉት ቅዱሳን ነቢያት ዝናም በማቆም ብቸኛ ነቢይ ነው፡፡ ✤ የሰማርያው ነቢይ ቴስቢያዊው ኤልያስ ከቅዱሳን አበው ነቢያት አንዱ ሲኾን አባቱ ኢያሴዩ እናቱ ደግሞ ቶናህ(ቶና) ሲባሉ ሲወለድ መላእክት በእሳት ሰፋድል (መጠቅለያ መጐናጸፊያ) ጠቅልለውት ነው፡፡ የስሙ ትርጉምም ‹‹እግዚአብሔር አምላክ ነው›› ማለት ነው፡፡ ** ኤልያስ ብዙ ነገር ስለሚያስተምር የቀና እምነቱን ውጤት ጥቂት መመልከት እኔ ማነኝ? ለሚሉት እጅ ይዞ ይመራል፡፡ ✤ 1. ለሦስት ዓመት ከመንፈቅ ሰማይ ዝናም ለዘር፥ ጠል ለመከር ከመስጠት እንዲከለከል ምድርም የተከሉባትን ✤ 2. አመጸኞች አክአብንና ኤልዛቤልን ምንነታቸውን ካሳወቀ በኋላ የዘጋውን ለመክፈት ወደ ፈጣሪው በመጸለይ ዝናም አዝንሟል፡፡ ✤ 3. በተፈጥሮ የማይመስላቸው በቋንቋም የማይግባባቸው እንኳን ለሰው ሥጋ ሊያመጡ ከሰው ሥጋ የሚነጥቁ አሞራዎች እንጀራና ሥጋ ለምግብ እንዲያመላልሱለት አደረገ 1ኛ ነገሥ. 17፥6-7፡፡ እነዚህ አሞራዎች ለሦስት ዓመት ከመንፈቅ በጋ ከክረምት የለምንም እረፍት ኤልያስን ሲያገለግሉ ኖረዋል፡፡ እምነት ካለ ተአምር መሥራት አይገድም ይህንም ከኤልያስ ይማሯል፡፡ ✤ 4. ለአንዲት መበለት ዱቄትና ዘይት አበረከተ፤ ኤልያስ ቁራሽ እየለመነ ያደረገውን ተአምር ልብ ይሏል፡፡ 1ኛ ነገሥ. 17፥16-24፡፡ ✤ 5. ዱቄትና ዘይት ያበረከተላት የሰራፕታዋ ሴት ልጇ /ኋላ ዮናስ ነቢይ የሆነው/ ቢሞት ከሞት አስነሳው 1ኛ ነገሥ. 17፥20-23 ✤ 6. ለብዙ ጊዜ በቤተ መንግሥት ተሰግስገው አክአብና ኤልዛቤልን በሐሰት ሲደልሉ፥ ግብዝ ሕብረተሰቡን ሲያታልሉ፥ ለፍቶ ያገኘው ገንዘቡን ሲሸልጉ፥ በኀጢአት ሊያስወጉ የነበሩ ነቢያተ ሐሰትና ካህናተ ጣዖትን በሕብረተሰቡ ፊት እስከ መምህራቸው ሰይጣን በቅሌት አከናንቦ ሲያስቅባቸው ውሏል፤ ሐሰቶች የነበሩትን 850 የሚጠጉ የጣዖት ካህናትንም ወደ ቂሶን ወንዝ አውርዶ ፈጅቷቸዋል፡፡ 1ኛ ነገሥ. 18 20 -29 ✤ 7. ወደ ፈጣሪው በጸሎት በማመልከት ያቀረበው ንጹሕ መሥዋዕቱን ከሰማይ እሳት ወርዶ በሰው ፊት በላለት (ተቀበለለት) 1ኛ ነገሥ. 18፥30-40፡፡ በዚህም ማንነቱን በሰይጣንና በሰይጣን አቀንቃኞች ፊት አስመስክሯል፡፡ ✤ 8. እሳት ከሰማይ በማዝነም ሊጣሉት የመጡትን መምለኪያነ ጣኦት፥ ምሉአነ ኀጢአት፤ የሰይጣን ሠራዊት በሰው ደም የሰከሩ፥ በዲያብሎስ የሚመሩ ጠላቶቹን አጋይቷል 2ኛ ነገሥ 1 9-13 ✤ 9. ምግብና መጠጥ መልአክ ከሰማይ አመጣለት ያንን ተመግቦ ለአርባ ቀን ያለምንም ምግብና መጠጥ እስከ እግዚአብሔር ተራራ እስከ ኮሬብ ድረስ 40 ቀንና 40 ሌሊት ተጉዟል 1ኛ ነገሥ. 19፥5-7፡፡ ✤ 10. በመጎናጸፊያው የዮርዳኖስን ባሕር ከፍሎ ከነ ደቀመዝሙሩ በደረቅ ተሻግሯል 2ኛ ነገሥ. 2፥11፡፡ ለደቀመዝሙሩም ሀብተ መንገፈስ ቅዱስን አድሎታል፡፡ ✤ 11. በትህትናው ‹‹ይበቃኛል፤ አሁንም አቤቱ እኔ ከአባቶቼ አልበልጥምና ነፍሴን ውሰድ›› ብሎ እንዲሞት ለመነ፡፡ እግዚአብሔር ግን ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በ918 ዓመተ ዓለም ሳይሞት በሕይወቱ መራራውን ሞት ዕያየው በብርሃን ሠረገላ ወደሰማይ አሳርጎታል፡፡ 2ኛ ነገሥ. 2፥6-9 ✤ 12. እንደ አስፈላጊነቱ ከፈጣሪው ጋር ለብዙ ጊዜ ተነጋግሯል፡፡ ✤✤#ከአንድ እስከ አስራ አንድ ያደረጋቸውን ተአምራት የፈጸመለት ታማኝ ፈጣሪው ሰው በሆነበት ወራት በተራራ ከጓደኞቹ ጋር ብርሃነ መለኮቱን ገለጠለት ማቴ 17፥3፡፡ #ደመና_ደመና ….. #በሠረገላ_፤ ኤልያስ ኤልያስ ….. በሠረገላ፤ በእሳት ሠረገላ ….. በሠረገላ፤… ሰወረው ደመና ….. በሠረገላ፤ ኤልያስ ያረገው… በሠረገላ፤ በእሳት ሠረገላ…. በሠረገላ፤ በጾም በጸሎት ነው …. በሠረገላ፤ አይደለም በሌላ …. በሠረገላ፡፡ #ዳግመኛም ዛሬ የአባቶችን ኖኅ መታሰቢው ነው፡፡ ኖኅ ግን በእግዚአብሔር ፊት ሞገስን አገኘ …ኖኅም በትውልዱ ጻድቅ፥ ፍጹምም ሰው ነበር፡፡ ኖኅ አካሔዱን ከእግዚአብሔር ጋር አደረገ፡፡ /ዘፍ. 6፥7/ #ዳግመኛም በዚህች ዕለት በበረሃ ስልሳ ዘመናት የኖረ የቅዱሳንን ልቡና ከማየቱ የተነሣ ያደነቀ፤ ፊቱም ተለውጦ እንደእሳት ፍሕም ሆነ አባ ሙሴ በዓለ ዕረፍቱ ነው፡፡ ክብረ በዓሉ የሚከበርባቸው ቦታዎች፤ #ለብቃ_ኢየሱስ/ሰሜን ሸዋ/፣ #በለስ_ዋሻ_ኢየሱስa /ተጉለትና ቡልጋ/፥ #በአ.አ. #ገነተ_ኢየሱስና_ገነተ_ማርያም ቤ/ክ፤ (ፈረንሳይ) #በአ.አ #ገዳመ_ኢየሱስ (ኮልፌ 18) #በአ.አ #እንጦጦ_ደብረ_ኀይል_ቅዱስ_ራጕኤልና_ኤልያስ (የኤልያስ ዕርገቱ) #በጎጃም_ደብረ_ኤልያስ ይከበራል፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #ጾም #አጽዋማት #fasting's #ክብረ_በዓላት #Feast_of_the_lord #በዓለ_እግዚእነ

መስቀል አደባባይን በተመለከተ ቅዱስ ሲኖዶስ ተወያየ። (ኢኦተቤ ቴቪ ጥር ፬ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም ሰሞኑን በመስቀል አደባባይ የተደረገውን የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች መንፈሳዊና የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀ ግብር ላይ የተነሱ የመብትና የይዞታ ጉዳዮች ዙሪያ እንዲሁም ክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስተላለፉት የተባለውን መልዕክት ተከትሎ ቅዱስ ሲኖዶስ ጥር ፫ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም ዓ.ም ረፋድ ዘጠኝ ሰዓት ላይ ጉባኤ አካሒዷል። በጉባኤውም ከፍ ሲል የተገለጸውን ርዕስ መሰረት በማድረግ ሰፊ ውይይት ካደረገ በኋላ ክብርት ከንቲባዋ አርብ ጥር ፮ ቀን ፳ ፻ ወ ፲ ፬ ዓ.ም ጠዋት አራት ሰዓት በቅዱስ ሲኖዶስ መሰብሰቢያ አዳራሽ በሚካሔደው በጉባኤ ጉባዔ ላይ እንዲገኙና ማብራሪያ እንዲሰጡ ቀጠሮ አሰንዲያዝ አና ጉዳዩ በተረጋጋ መንገድ ውሳኔ እንዲያገኝ መመሪያ ሰጥቷል። ይህ ሲኖዶሳዊ ውሳኔ የቤተክርስቲያኒቱ የመጨረሻ የሥልጣን ባለቤት የሆነው ቅዱስ ሲኖዶስ የሰጠው ውሳኔ በመሆኑ ለውሳኔው ተግባራዊነት ሁሉም ወገን የድሻውን ማበርከት የሚጠበቅበት መሆኑን በመገንዘብ ይህን ጉዳይ በተመለከተ ቅዱስ ሲኖዶስ አርብ ጥር ፮ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም በሚካሔደው ጉባዔ እልባት እስከሚሰጠው ይታመናል። ስለሆነም ቅዱስ ሲኖዶስ በጉዳዩ ዙሪያ ውሳኔ እስከሚሰጥ ድረስ ማንኛውም የቤተክርስቲያኒቱ እምነት ተከታይ ህግና ሥርዓትን ጠብቆ ቅዱስ ሲኖዶሱ የሚሰጠውን ውሳኔ ማክ በር እንደሚገባው ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን መልዕክቷን ታስተላልፋለች ሲል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ በፌስ ቡክ ገጹ አስታውቋል።

ታላቅ የምክክር ጉባኤ ጥር አንድ ፤ በዚህችም ዕለት የቅዱስ እስጢፍኖስ ታቦት ሕግ ወጥቶ በዓሉ ከብሮ ፤ ፀሐይ ሳትገባ የኦርቶዶክስ ቤ/ክንን ርስት ለመወርስ በተካሄደ እንቅስቃሴ ፤ አስለቃጭሽ (መርዛ
ታላቅ የምክክር ጉባኤ ጥር አንድ ፤ በዚህችም ዕለት የቅዱስ እስጢፍኖስ ታቦት ሕግ ወጥቶ በዓሉ ከብሮ ፤ ፀሐይ ሳትገባ የኦርቶዶክስ ቤ/ክንን ርስት ለመወርስ በተካሄደ እንቅስቃሴ ፤ አስለቃጭሽ (መርዛማ ) ጭስ በእስጢፍኖስ ቤ.ክ ቤተ መቅደስ ውስጥ ኦርቶዶክሳውያን ላይ ተወረወረ ፡፡ ይህንን ያደረጉትን ፈጽሞ አይማራቸው ! <<ታቦት ይዛ ወጥታ የጠላትን አስለቃሽ ጭስ ወደ ጉም የምትቀይር ቤ.ክ ይኽ አይገባትም ›› ------------------------------------- ታላቅ የምክክር ጉባኤ ስለ ቤተክርስቲያንንም ዝም አንልም ፡ ርስታችንንም አንሰጥም ! ጥር 4 ከቀኑ 10 ጀምሮ በቦሌ ደብረሳሌም መድኀኔዓለም እንድንገናኝ ይሁን !

በኋላ ግን የቤተክህነቱ ባለሥልጣናት ታቦቱን ከአስገባን ዘንድ ንግሥትን ጠርተን ማሳየት ግዴታችን ነው፤ ከአዩት ደግሞ በቤቱ አነስተኛነት መቆጣታቸው አይቀርምና ከዚህ ከፍ ያለ ቤት ብንፈልግ ይሻለናል በማለት በፀበሉ ቦታ ላይ በዘመኑ የተሻለ ነው ተብሎ የሚገመተውን የነጋድራስ ሠርፀ ወልድ ፎቅ ቤትን በማስለቀቅ ጥቅምት 4 ቀን 1914 ዓ.ም. ግርማዊት ንግሥተ ነግሥታት ዘውዲቱ በተገኙበት ለ፪ኛ ጊዜ ታቦተ ቅዱስ ዮሐንስ ከመጀመሪያ የሳር ክዳን ጎጆ ቤት ወደ ሁለተኛው ፎቅ ቤት እንዲገባ ተደረገ፡፡ የመጀመሪያው ሕንፃ ክብ ቤ/ን (ዛሬ የእመቤታችን ቤ/ን ያለበት) የመሠረት ድንጋይ በፊታውራሪ አባ ይሬ ቦታ ላይ በ1924 ተጣለ፤ ከ2ት ዓመታት በኋላም በ1926 ሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ አልቆ ንግሥት ባሉበት ተመርቋል፤ ንግሥቲቱም ሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ አንሶ በመሠራቱ ቅር ተሰኝተዋል፤ በእግዚአብሔር ፈቃድ ታላቅ ቤ/ንን እሠራለታለሁ እስከዚያው ድረስ ከመቃኞው ወደ አዲሱ ክቡ ቤ/ን ይግባ ብለው ገብቷል፡፡ ንግሥቲቱም ያሰቡትን ቤ.ን ሳይሠሩ በ1922 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ ዐርፈዋል፡፡ #የአዲሱ_ሕንፃ_ቤተ_ክርስቲያን_መሠራት፡፡ የዐፄ ኀይለ ሥላሴ ልጅ የሐረሩ መስፍን ልዑል መኮንን የተወለደው በዮሐንስ እለት ሲሆን የክርስትና ስሙም አርአያ ዮሐንስ ነው፡፡ አርአያ ዮሐንስም ቅዱስ ዮሐንስን በስሙ የተሰየመበት በመኾኑ ከብላታ ተሰማ ደባልቄ ጋራ በመሆን አባቱ አፄ ኀይለ ሥላሴን የደብረ ነጐድጓድ ቅ/ዮሐንስ ቤ/ንን በአዲስ መልክ አሻሽለው እንዲሠሩለት ይጠይቃቸዋል፡፡ ነገር ግን አባቱ እኛ እንሠራዋለን የሚል መልስ ሰጡት፤ ለጉዳዩ ብዙም ትኩረት ሳይሰጡት፥ ሕንፃውም ሳያሠራ ቆየ፡፡ ብዙም ሳይቆይ መስፍኑ ልጃቸው በቅዱስ ዮሐንስ እለት በግንቦት 4/1949ዓ.ም. አረፈ፡፡ ንጉሡም የልጃቸውን ምኞት ባለመፈጸማቸው ተጸጽተው፤ ልጃቸው ባረፈ በ12ኛው ቀን ወደ ደብረ ነጐድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ/ን በመምጣት የቤተ ክርስቲያኑን ጥንተ ታሪኩን ጠይቀውና ተረድተው፥ ቤተ ክርስቲያኑን ተሳለመውና አፀዱንና ቅጥሩን ተመልክተው የልጃቸውን ራዕይ ለማሳካት በዘመናዊ አሠራር አዲስ ቤ/ን እንደሚያንፁ ቃል ገቡ፡፡ በቃላቸው መሠረትም አፄ ኀይለ ሥላሴ ራሳቸው ተገኝተው በ1960 የመጀመሪያ መቃኞ ቤተ ክርስቲያን ባለበት ቦታ ላይ የመሠረት ደንጊያ ተጣለ፡፡ የሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ አርቴክት ኢጣሊያዊ ነው፡፡ በዐፄ ኀይለ ሥላሴ የገንዘብ ሥጦታም ከ3 ዓመታት በኋላ በ1963 ሕንፃው አልቆ ተመረቀ፤ የሕንፃ ሥራው የተጓተተበት ምክንያትም በ1960 በጄኔራል መንግሠቱ ንዋይና በወንድሙ ግርማሜ ንዋይ መሪነት በተካሄደው መፈንቅለ መንግሥት የሕንፃው ሥራ እየተቋረጠ እንደገና ሲጀምር ጊዜ በመውሰዱ ነው፡፡ ታቦተ ዮሐንስ ከመጀመሪያው ክብ ቤተ ክርስቲያን ወጥቶ በልዩና ባመረ ኹኔታ፥ በመስቀልኛ ቅርጽ፥ በዘመናዊ አሠራር (በአዲስ አበባ በአሠራሩ አምሳያ በሌለው) ወደተሠራው ሕንፃ ቤ/ን ገባ፡፡ በመጀመሪያ በተሠራው የክብ ቤተ ክርስቲያን ውስጥም ከታቦተ ዮሐንስ ጋር ታቦተ ማርያም አብራ በድርብነት ትኖር ነበርና፤ #በ1963 ታቦተ ዮሐንስ አዲስ ወደታነጸው ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ሲገባ ታቦተ ማርያም ደግሞ በዚሁ በቀድሞው ክብ ቤ/ን ቆየች፤ ስያሜዋም መካነ ጎልጎታ ማርያም ኾነ፤ በዚህም ምክንያት የደብሩ ሙሉ መጠሪያ ስያሜ ደብረ ነጐድጓድ ዮሐንስ ብቻ በመባል ፈንታ #ደብረ_ነጐድጓድ_ዮሐንስ_ወመካነ_ጎልጎታ_ማርያም_ቤተ_ክርስቲያን ሆነ፤ #የቤተ_ክርስቲያኑ_አስተዳደር_ ከ1922 እስከ 1960 ድረስም የተዳደረው በገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ን ሥር ሲኾን የሚያስተዳድሩት አለቃውም ኾነ ገበዙ የገነተ ጽጌ አለቃና ገበዝ ነበሩ፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ በተመሠረተበት ወቅት የሚያገለግሉት በ2ት ምድብ የተመደቡ ሰሞንኛ 10 አገልጋይ ካህናት ብቻ ነበሩ፡፡ ርስት ጉልት ስላልተጎለተለት አገልጋዮቹ የሚተዳደሩትም በደመወዝ ነበር፡፡ ደመወዛቸውም የቀሳውስት በወር 10ብር፥ የዲያቆናት በወር 5 ብር ሲኾን ገንዘቡ የሚከፈለውም ከቤተ ክህነት ለቤተ ክርስቲያኑ ከተበጀተ ገንዘብ ነበር፡፡ #ጠበል_ቤት_ በጠበል ቤቱ ግቢ ውስጥ 9ኝ ጠበሎች ይገኛሉ፡፡ እነዚህም፤ 1ኛ) የሥላሴ ጠበል፤ 2ኛ) የእግዚአብሔር አብ ጠበል፤ 3ኛ) የመድኀኔ ዓለም ጠበል፤ 4ኛ) የእመቤታችን የማርያም ጠበል፤ 5ኛ) የኪዳነ ምሕረት ጠበል፤ 6ኛ) የቅዱስ ሚካኤል ጠበል፤ 7ኛ) የቅዱስ ገብርኤል ጠበል፤ 8ኛ) የቅዱስ ጊዮርጊስ ጠበል፤ 9ኛ) የአቡነ ተክለሃይማኖት ጠበል ናቸው፡፡ #በደብሩ_የሚከበሩ_ክብረ_በዓላት፤ ✧ ጥር 4፤ የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ በዓለ ሥዋሬው፤ ✧ መስከረም 21፣ ኅዳር 21፣ ጥር 21፣ ግንቦት 21፤ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም በዓል፤ ኅዳር 12፣ ሰኔ 12፤ የቅዱስ ሚካኤል በዓል፡፡ ✧ #ታቦተ_ሕጉ_ወጥቶ_ባይከበርም_የሊቁ_የቅዱስ_ዮሐንስ_አፈ_ወርቅ_ታቦትም_ይገኛል፡፡ አምላካችን ደብሩን ይጠብቅልን፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/ ምንጭ፡- ከ አድባራታን ገዳማት ገጽ/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #churches_and_monastries #ገዳማትና_አድባራት #ክብረ_በዓላት #Feasts

#የአዲስ_አበባ_ደብረ_ነጐድጓድ_ቅዱስ_ዮሐንስና_መካነ_ጐልጎታ_ማርያም_ቤተ_ክርስቲያንና_አብሮ_የተመሠረተው_ሰንበቴ_ቤት_የ100 #ዓመታት_ታሪክ፡፡ ✧ ጠባቂዬ የዮሐንስ ወንጌላዊ ታቦት በደቡብ ጎንደር ስላለ እርሱ ሳይመጣ እኔ አልነግሥም፡፡ /ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ/ ✧ ንግሥት ዘውዲቱ የነገሠችው በምትወደውና ታቦተ ሕጉ አብሯት በማይለየው በቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ እለት የካቲት 4 ቀን 1909ዓ.ም. ነው፡፡ ✧ ደብረ ነጐድጓድ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያንም አሁን ባለበት ቦታ ላይ የተመሠረተው ጥቅምት 4ና ጥቅምት 25 ቀን 1914 ዓ.ም. ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ አሁን ባለበት ቦታ የተከሉት ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ምኒልክ /1909-1922ዓ.ም./ ሲሆኑ የተመሠረተበትም፤ በእለተ ዐርብ ጥቅምት 25 ቀን በ1914 ዓ.ም. ነው፡፡ ጽላቱ የመጣው ዐፄ ዮሐንስ 4ኛ /1864-1881ዓ.ም./ ወደ ኢየሩሳሌም በላኳቸው አንድ መነኵሴ አማካይነት ሲሆን፤ መነኵሴው ቅዱስ ዮሐንስን እጅግ ይወዱ ስለነበርና በተለይም የዮሐንስ ወንጌል 1፡14 ቃል ሥጋ ኾነ የሚለው ቃል ምሥጢርን ያደንቁ ነበርና በኢየሩሳሌም ለ፮ ዓመታት ቆይተው ወደ ሃገራቸው ሲመለሱ የቅዱስ ዮሐንስ ስም የተቀረጸበትን ታቦተ ዮሐንስ ወንጌላዊን ይዘው መጥተዋል፡፡ ታቦተ ሕጉ በንጉሡ ዐፄ ዮሐንስ ቤተ መንግሥት /መቀሌ/ ግቢ ከቆየ በኋላ ንጉሡ ለልጃቸው ለአርአያ ሥላሴ /ኋላ ራስ/ ሰጥተውታል፡፡ አርአያ ሥላሴም ጥቅምት 13/1875ዓ.ም. ከንጉሥ ምኒልክ /ኋላ አጼ/ ልጅ ወ/ሮ ዘውዲቱ /ኋላ ንግሥተ ነገሥታት/ ጋር ተጋብተዋል፤ ለባለቤታቸው ወ/ሮ ዘወዲቱ ታቦተ ዮሐንስን ‹‹ብትጠብቂው ይጠብቅሻል›› ብለው አደራ ሰጥተዋቸዋል፡፡ ራስ አርአያ ሥላሴ ዮሐንስም በየካቲት 1880ዓ.ም. ሲያርፉ፤ ዐፄ ምኒልክ ልጃቸው ዘውዲቱን ከመቀሌ ወደ አዲስ አበባ እንዲያመጡ ሊጋባ ገብርኤልንና ደጃች አባተን ላኩ፤ ነገር ግን በጕዞው ላይ ኃይለኛ ዝናብ በመዝነቡ ምክንያት ወንዞች ስለሞሉና ወደ አዲስ አበባ መመለስ ባለመቻሉ ወ/ሮ ዘውዲቱ ለአንድ ዓመት በደብረ ታቦር ተቀመጡ፥ ታቦተ ዮሐንስም በማኅደረ ማርያም ተቀመጠ፡፡ ኋላ ወ/ሮ ዘውዲቱ ደጃዝማች ጉግሣ ወሌን /ኋላ ራስ/ በቊርባን አግብተው ወደ በጌምድር ደብረ ታቦር በሄዱ ጊዜ ታቦተ ዮሐንስን አስመጥተው በደብረ ታቦር ቤተ መንግሥት ግቢ ውስጥ አነስተኛ ቤተ ክርስቲያን አሠርተው ለ12 ዓመታት ሲኖሩ ታቦተ ዮሐንስም በዚሁ ቤተ መንግሥት ግቢ አብሯቸው ኖረ፡፡ ባላቸው ራስ ጉግሣ ወሌ በ1902 ዓ.ም. ታሠሩ እስከ 1906ዓ.ም ወደ አፍቀራ ኮረብታ በግዞት ተወሰዱ፡፡ ወ/ሮ ዘውዲቱም ራስ ጉግሣ ወሌ የቊርባን ባላቸው ስለኾኑ ማንንም ሳያገቡ በአዲስ አበባ ቤተ መንግሥት ቆዩ፡፡ ቀጥሎም ወ/ሮ ዘውዲቱ ወደ ፋሌ በርስታቸው ቦታቸው ላይ ከባላቸው ከራስ ጉግሣ ወሌ ጋር ኖሩ፡፡ በመስከረም 19/1909ዓ.ም. ልጅ ኢያሱ ከሥልጣን ሲሻሩ፤ ወይዘሮ ዘውዲቱ አልጋውን እንዲይዙ አጃቢዎች ተልከው መስከረም 22 ቀን 1909ዓ.ም. አዲስ አበባ ገቡ፤ የዘውድ በዓላቸው በኅዳር 12 ቀን 1909 ዓ.ም. እንዲኾን ሲጠየቁ፤ ጠባቂዬ ታቦተ ዮሐንስ በደብረ ታቦር ስላለ እርሱ ካልመጣ አልነግሥም ስላሉ የዘውድ በዓሉ ተላልፎ፤ ታቦተ ዮሐንስ በጥር 29 ቀን 1909 ዓ.ም. ወደ አዲስ አበባ መጥቶ በዐፄ ምኒልክ ጸሎት ቤት (ሥዕል ቤት) ተቀመጠ፡፡ የንግሥት ዘውዲቱ የዘውድ በዓልም በምትወደውና ታቦተ ሕጉ አብሯት በማይለየው በቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ እለት የካቲት 4 ቀን 1909ዓ.ም. በገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ን ግርማዊት ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ምኒልክ ተብለው በዓሉ ተደረገ፤ በእለቱም ታቦተ ዮሐንስ ከስዕል ቤት ኪዳነ ምሕረት ወደ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ሂዶ ተቀድሶበት ዋለ፤ በዐውደ ምሕረቱም ንግሥቲቱ ከታቦተ ሕጉ ጋር አብረው ዑደት አድርገው የዘውድ በዓሉ ተደረገ፡፡ (በሌላ ታሪክ ዐፄ ዮሐንስ ለወሎው ገዢ ራስ ሚካኤል ታቦተ ዮሐንስን ሰጥተዋቸው ኋላ ላይ በተደረገው የሰገሌ ጦርነት ታቦተ ዮሐንስ ወደ አ.አ. መጥቷል የሚሉም አሉ፡፡) #ንግሥተ_ነገሥታት_ዘውዲቱ_ምኒልክ_ለከተማችን_ብቸኛ_የኾነውን_የቅዱስ#ዮሐንስ_ወንጌላዊ #ቤ/ን #እንድትሠራ_ያደረጓት #፫ት #ምክንያቶች፤ 1ኛ) ከመጀመሪያ ባሏ ከአርአያ ሥላሴ ዮሐንስ የተሰጣት በመኾኑና በችግሯም ኾነ በደስታ ኹሉ አብሯት የነበረ ታቦት በመኾኑ፤ 2ኛ) የመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ን መካነ መቃብር በመሙላቱ ከቤተ ክህነት ጋር በመመካከር ሌላ የቀብር ቦታ እንደሚያስፈልግ በመታመኑ 2033lm2 ያህል ቦታ እንዲኖረው ተደርጎተከልሏል፡፡ 3ኛ) በዓለም አቀፍ ደረጃ የተከሰተውና በከተማችን Nov. 1918 ብዙ ሰዎችን የጨረሰው የኢንፍሉዌንዛ (የኅዳር በሽታ) በፈዋሴ ሕመም የሚታወቀው ሐዋርያና ወንጌላዊው ዮሐንስ ከከተማችንና ከሃገራችን ይህንን የወረርሽኝ በሽታ ነቅሎ እንዲያጠፋው ነው፡፡ ከዘውድ በዓሉ 1909 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ 1914 ዓ.ም. (ለ5ት ዓመታት) በገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቆየ (እስከ 1915 በሥዕል ቤትቆየ የሚሉም አሉ)፡፡ የንግሥት ዘውዲቱ መንፈሳዊ ምኞታቸው ለቅዱስ ዮሐንስ ታቦት ትልቅ ቤ/ን ማሠራት ሲሆን፤ ለጊዜው አሁን ቤተ ክርስቲያኑ ያለበትን ቦታ ጠቁመው መቃኞ እንዲሰራለት በሰጡት ትዕዛዝ መሠረት፤ #በእለተ_ዐርብ_ጥቅምት #25 ቀን #በ1914 ዓ.ም. አሁን የደብረ ነጐድጓድ ዮሐንስ ሕንፃ ቤ/ን የተሠራበት ቦታ ላይ ታቦቱ ከመምጣቱ በፊት መስቀል ዞሮ ቦታው ተከለለ፡፡ የቦታው ባለቤቶች የንጉሣውያን ቤተሰብ የኾኑት ፊታውራሪ አባ ይሬ፣ ደጃዝማች ይገዙ በሀብቴና ነጋድራስ ሠርፀ ወልድ ናቸው፡፡ ይዞታቸውም፤ * መጀመሪያ የታቦተ ዮሐንስ መቃኞ ቤት የነበረበት (አሁን አዲሱ የዮሐንስ ቤ/ን የተሠራበት)ና የመቃብሩ ሥፍራ የደጃዝማች ይገዙ በሀብቴ፤ * ቀድሞ የዮሐንስ ቤ/ን (አሁን የእመቤታችን ቤተ ክርስቲያን) ያለበት ሥፍራ ደግሞ በተለይ የፊታውራሪ አባ ይሬ ቦታ ነው፤ * የጠበሉ ቦታ የነጋድራስ ሠርፀ ወልድ ቦታ ነው፡፡ ከዚያም በቀሳውስት፣ በዲያቆናት በመዘምራን ስበሐተ እግዚአብሔር እየቀረበ፤ ልብሰ ተክህኖ የለበሱ ዲያቆናት በመካከል ሁነው፤ በጥንቱ አራዳ ዘበኞች በሚባሉ ወታደሮች ታጅቦ፥ እምቢልታና መለከት እየተነፋ ከገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ አሁን ቤተ ክርስቲያኑ ወዳለበት ቦታ መጥቶ አንድ የሣር ክዳን ቤተ ንጉሥ የኾነ የደጃዝማች ይገዙ በሀብቴ ቤት ተባርኮ ታቦቱ በመቃኞነት (በመቃረቢያነት) ቆየ፡፡ በእለቱም ታቦተ ሕጉን አጅበው ከመጡት ታዋቂ ሰዎች መካከል ነጋድራስ ወንድማገኘሁ፣ አቶ ይታጠቁ፣ አቶ ዱባለ፣ አቶ ደምሴ በልልኝ፣ አቶ ድልነሣሁ፣ አቶ ተክለማርያም ደምሴና ሌሎችም ነበሩ፡፡ እነዚህ ታዋቂ ሰዎችም ብዙ ርስት ያላቸው ስለበሩ ለቅዱስ ዮሐንስ ባላቸው ጽኑ ፍቀር የተነሣ ታቦቱ በገባበት እለት እህል ውኃ አቅርበው ከዛሬ ጀምሮ እዚህ ቤተ ክርስቲያን ቅጽር ግቢ ውስጥ #ማኅበረ_ሰንበቴ አቋቁመናልና ይዘከርልን በማለት ሰንበቴ ቤቱ ከቤተ ክርስቲያኑ ጋር አብሮ ተመሠረተ፡፡ እስካሁንም ድረስ በየሳምንቱ እየተዘከረ ይገኛል፡፡

/በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #ክብረ_በዓላት #feasts