Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览
频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 401 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 564,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 183 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 401 名订阅者。
根据 29 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 18,过去 24 小时变化为 2,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 21.46%。内容发布后 24 小时内通常能获得 10.24% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 305 次浏览,首日通常累积 1 576 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 17。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 30 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
15 401
订阅者
+224 小时
+327 天
+1830 天
帖子存档
"‹‹የእግዚአብሔርን የቃል ኪዳን ታቦትን ሌዋውያን ካህናት ተሸክመውት ባያችሁ ጊዜ ከሰፈራችሁ ተነሥታችሁ ተከተሉት፡፡›› ኢያሱ ፫፥፫
የ2014 ዓ.ም የ #በዓለ_ጥምቀት ማስታወሻዎች
ፎቶ ስብስብ 1"
‹‹የእግዚአብሔርን የቃል ኪዳን ታቦትን ሌዋውያን ካህናት ተሸክመውት ባያችሁ ጊዜ ከሰፈራችሁ ተነሥታችሁ ተከተሉት፡፡›› ኢያሱ ፫፥፫
የ2013 ዓ.ም የ #በዓለ_ጥምቀት ማስታወሻዎች
ፎቶ ስብስብ 1
ጥር 6 በዓለ ግዝረት፥ ዕረገተ ኤልያስ ዕረፍተ ኖኅ፥ ልደተ ቅድስት አርሴማ፥ ዕረፍተ ዐቢይ ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ፥ አቡነ ኖኅኖኅ አባ ሙሴ ገዳማዊ፥ አባ ወርክያኖስ፥ ወአባ ሙሴ፡፡
#ግዝረተ_እግዚእነ_ኢየሱስ_ክርስቶስ
፠ ጌታችን በተወለደ በ8ኛ ቀኑ ዕጉለ ማዕነቅ ይዞ ወደ ቤተ ግዝረት በመግባት የኦሪትን ሕግ የፈጸመበት ዕለት ነው፡፡
፠ ‹‹ጌታ ክርስቶስ በሥጋ ግዝረትን ተቀበለ፣ ለአባቶች የተሰጠውን ቃልኪዳን ይፈጽም ዘንድ›› /ሮሜ.፲፭፥፰/፡፡
፠ በቅዱስ ወንጌል እንደ ተጻፈ በስምንተኛው ቀን እንደ ኦሪቱ ሥርዓት ግዝረት ይፈጸምለት ዘንድ ሕፃኑ ጌታችንን ወደ ቤተ መቅደስ ወሰዱት፡፡ መጥምቁ ዮሐንስ ሲገረዝ የሊቀ ካህን ልጅ ነው ብለው ሊገርዙት ወደ እርሱ መጡ፡፡ ጌታችን ግን ወደ ምድር የመጣው፡፡ ለትሕትና ነው እንጂ ለልዕልና አይደለምና ወሰዱት አለ /ትርጓሜ ወንጌለ ሉቃስ/፡፡
፠ የእመቤታችን ድንግልናዋ ሳይለወጥ ከድንግል ማኅፀን እንደመውጣቱ የጌታችን ግዝረቱም የማይመረመር ሆነ፡፡
እንዲሁ በተዘጋ ቤት መግባቱና መውጣቱ እንደማይመረመር እነዲሁ እንደፈቀደ ከረቀቀ ጥበቡ ችሎታውን በመገረዝ ከሥጋው ምንም ምን ሳይቆረጥ ገለጠ፡፡
#ቅዱስ_ኤልያስ_በእሳት_ሰረገላ_ወደ_ብሔረ_ብፁዓን_ያረገበት_ዕለት_ነው፡፡
**በቅዱስ መጽሐፍ ውስጥ ካሉት ቅዱሳን ነቢያት ዝናም በማቆም ብቸኛ ነቢይ ነው፡፡
✤ የሰማርያው ነቢይ ቴስቢያዊው ኤልያስ ከቅዱሳን አበው ነቢያት አንዱ ሲኾን አባቱ ኢያሴዩ እናቱ ደግሞ ቶናህ(ቶና) ሲባሉ ሲወለድ መላእክት በእሳት ሰፋድል (መጠቅለያ መጐናጸፊያ) ጠቅልለውት ነው፡፡ የስሙ ትርጉምም ‹‹እግዚአብሔር አምላክ ነው›› ማለት ነው፡፡
** ኤልያስ ብዙ ነገር ስለሚያስተምር የቀና እምነቱን ውጤት ጥቂት መመልከት እኔ ማነኝ? ለሚሉት እጅ ይዞ ይመራል፡፡
✤ 1. ለሦስት ዓመት ከመንፈቅ ሰማይ ዝናም ለዘር፥ ጠል ለመከር ከመስጠት እንዲከለከል ምድርም የተከሉባትን
✤ 2. አመጸኞች አክአብንና ኤልዛቤልን ምንነታቸውን ካሳወቀ በኋላ የዘጋውን ለመክፈት ወደ ፈጣሪው በመጸለይ ዝናም አዝንሟል፡፡
✤ 3. በተፈጥሮ የማይመስላቸው በቋንቋም የማይግባባቸው እንኳን ለሰው ሥጋ ሊያመጡ ከሰው ሥጋ የሚነጥቁ አሞራዎች እንጀራና ሥጋ ለምግብ እንዲያመላልሱለት አደረገ 1ኛ ነገሥ. 17፥6-7፡፡ እነዚህ አሞራዎች ለሦስት ዓመት ከመንፈቅ በጋ ከክረምት የለምንም እረፍት ኤልያስን ሲያገለግሉ ኖረዋል፡፡ እምነት ካለ ተአምር መሥራት አይገድም ይህንም ከኤልያስ ይማሯል፡፡
✤ 4. ለአንዲት መበለት ዱቄትና ዘይት አበረከተ፤ ኤልያስ ቁራሽ እየለመነ ያደረገውን ተአምር ልብ ይሏል፡፡ 1ኛ ነገሥ. 17፥16-24፡፡
✤ 5. ዱቄትና ዘይት ያበረከተላት የሰራፕታዋ ሴት ልጇ /ኋላ ዮናስ ነቢይ የሆነው/ ቢሞት ከሞት አስነሳው 1ኛ ነገሥ. 17፥20-23
✤ 6. ለብዙ ጊዜ በቤተ መንግሥት ተሰግስገው አክአብና ኤልዛቤልን በሐሰት ሲደልሉ፥ ግብዝ ሕብረተሰቡን ሲያታልሉ፥ ለፍቶ ያገኘው ገንዘቡን ሲሸልጉ፥ በኀጢአት ሊያስወጉ የነበሩ ነቢያተ ሐሰትና ካህናተ ጣዖትን በሕብረተሰቡ ፊት እስከ መምህራቸው ሰይጣን በቅሌት አከናንቦ ሲያስቅባቸው ውሏል፤ ሐሰቶች የነበሩትን 850 የሚጠጉ የጣዖት ካህናትንም ወደ ቂሶን ወንዝ አውርዶ ፈጅቷቸዋል፡፡ 1ኛ ነገሥ. 18 20 -29
✤ 7. ወደ ፈጣሪው በጸሎት በማመልከት ያቀረበው ንጹሕ መሥዋዕቱን ከሰማይ እሳት ወርዶ በሰው ፊት በላለት (ተቀበለለት) 1ኛ ነገሥ. 18፥30-40፡፡ በዚህም ማንነቱን በሰይጣንና በሰይጣን አቀንቃኞች ፊት አስመስክሯል፡፡
✤ 8. እሳት ከሰማይ በማዝነም ሊጣሉት የመጡትን መምለኪያነ ጣኦት፥ ምሉአነ ኀጢአት፤ የሰይጣን ሠራዊት በሰው ደም የሰከሩ፥ በዲያብሎስ የሚመሩ ጠላቶቹን አጋይቷል 2ኛ ነገሥ 1 9-13
✤ 9. ምግብና መጠጥ መልአክ ከሰማይ አመጣለት ያንን ተመግቦ ለአርባ ቀን ያለምንም ምግብና መጠጥ እስከ እግዚአብሔር ተራራ እስከ ኮሬብ ድረስ 40 ቀንና 40 ሌሊት ተጉዟል 1ኛ ነገሥ. 19፥5-7፡፡
✤ 10. በመጎናጸፊያው የዮርዳኖስን ባሕር ከፍሎ ከነ ደቀመዝሙሩ በደረቅ ተሻግሯል 2ኛ ነገሥ. 2፥11፡፡ ለደቀመዝሙሩም ሀብተ መንገፈስ ቅዱስን አድሎታል፡፡
✤ 11. በትህትናው ‹‹ይበቃኛል፤ አሁንም አቤቱ እኔ ከአባቶቼ አልበልጥምና ነፍሴን ውሰድ›› ብሎ እንዲሞት ለመነ፡፡ እግዚአብሔር ግን ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በ918 ዓመተ ዓለም ሳይሞት በሕይወቱ መራራውን ሞት ዕያየው በብርሃን ሠረገላ ወደሰማይ አሳርጎታል፡፡ 2ኛ ነገሥ. 2፥6-9
✤ 12. እንደ አስፈላጊነቱ ከፈጣሪው ጋር ለብዙ ጊዜ ተነጋግሯል፡፡
✤✤#ከአንድ እስከ አስራ አንድ ያደረጋቸውን ተአምራት የፈጸመለት ታማኝ ፈጣሪው ሰው በሆነበት ወራት በተራራ ከጓደኞቹ ጋር ብርሃነ መለኮቱን ገለጠለት ማቴ 17፥3፡፡
#ዳግመኛም ዛሬ የአባቶችን ኖኅ መታሰቢው ነው፡፡ ኖኅ ግን በእግዚአብሔር ፊት ሞገስን አገኘ …ኖኅም በትውልዱ ጻድቅ፥ ፍጹምም ሰው ነበር፡፡ ኖኅ አካሔዱን ከእግዚአብሔር ጋር አደረገ፡፡ /ዘፍ. 6፥7/
#ዳግመኛም በዚህች ዕለት በበረሃ ስልሳ ዘመናት የኖረ የቅዱሳንን ልቡና ከማየቱ የተነሣ ያደነቀ፤ ፊቱም ተለውጦ እንደእሳት ፍሕም ሆነ አባ ሙሴ በዓለ ዕረፍቱ ነው፡፡
#በአዲስ_አበባ_የጌታችን_በዓለ_ግዝረት_የሚከበርባቸው_ #፪ #ገዳማትና_አድባራት፡፡
፩. ገነተ ኢየሱስና ገነተ ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻው፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ፈረንሳይ፤
ታክሲ፤ ከአራዳ ጊዮርጊስ ሞቢሉ ጋር (4 ኪሎ) (6 ኪሎ) → ፈረንሳይ/ኢየሱስ/፤
፪. ገዳመ ኢየሱስ ቤ/ክ
አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፤
#በሃገራችን_በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የጌታችን_በዓለ_ግዝረት_የሚከበርባቸው_ #፬ #ገዳማትና_አድባራት፡፡
፩. ምዕራፈ ቅዱሳን በልበሊት ኢየሱስ ገዳም፤
አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ እንሳሮ ወረዳ፥ ጀማ በረሃ፤
፪. ለብቃ ኢየሱስ፤ (ተአምረኛ የኾነ ፍልውሃ ጠበል የሚፈልቅበት፤ በቆዳ በሽታ በአካል፥ ደዌ የፈራረሰን ሰውነት ሳይቀር የሚጠግን)፡፡ ከገናናነቱ ተነሣ የሚከተለው ግጥሞች ተገጥሞለታል፡፡
፨ የለብቃው ኢየሱስ፥ የለብቃው፤
የፈረሰ ገላ ትጠቅማለህ አሉ፡፡ እየተባለ የሚዘመርለት፡፡
አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ መርሐ ቤቴ፥ ሚዳና ወረሞ ወረዳ፤
ወይም፤ ከደቡብ ወሎ (ደሴ ወይም ወግዲ) → መርሃ ቤቴ /አለም ከተማ/ → ለብቃ ኢየሱስ፡፡
፫. በለስ ዋሻ ኢየሱስ ገዳም፤ (ጥንታዊና የቅዱሳን መናኸሪያ፤ በተጕለት ከሚገኙ ከ5ቱ የቅዱሳን መናኸሪያ ገዳም አንዱ፡፡)
አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ተጉለትና ቡልጋ፥ አይዞሽ አሞራ፤
ወይም ከአዲስ አበባ ላምበረት አውቶቡስ ተራ → ደብረ ብርሃን → በኩክ የለሽ መንገድ → ዘንባባ ኢየሱስ → በለስ ዋሻ
፬. አማኑኤል ኢየሱስ ቤ.ክ.፤
አድራሻ፤ ምሥራቅ ጎጃም ሃገረ ስብከት፥ ደንበጫ፥ አማኑኤል ከተማ፤
/በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/
#share
.YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
.Telegram...
https://t.me/medihanaelem
http://tiktok.com/@finotehiwot
www.finotehiwotsundayschool.com
#ጾም #አጽዋማት #fasting's
#ክብረ_በዓላት #Feast_of_the_lord
#በዓለ_እግዚእነ
ጥር 6 በዓለ ግዝረት፥ ዕረገተ ኤልያስ ዕረፍተ ኖኅ፥ ልደተ ቅድስት አርሴማ፥ ዕረፍተ ዐቢይ ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ፥ አቡነ ኖኅኖኅ አባ ሙሴ ገዳማዊ፥ አባ ወርክያኖስ፥ ወአባ ሙሴ፡፡
#ግዝረተ_እግዚእነ_ኢየሱስ_ክርስቶስ
፠ ጌታችን በተወለደ በ8ኛ ቀኑ ዕጉለ ማዕነቅ ይዞ ወደ ቤተ ግዝረት በመግባት የኦሪትን ሕግ የፈጸመበት ዕለት ነው፡፡
፠ ‹‹ጌታ ክርስቶስ በሥጋ ግዝረትን ተቀበለ፣ ለአባቶች የተሰጠውን ቃልኪዳን ይፈጽም ዘንድ›› /ሮሜ.፲፭፥፰/፡፡
፠ በቅዱስ ወንጌል እንደ ተጻፈ በስምንተኛው ቀን እንደ ኦሪቱ ሥርዓት ግዝረት ይፈጸምለት ዘንድ ሕፃኑ ጌታችንን ወደ ቤተ መቅደስ ወሰዱት፡፡ መጥምቁ ዮሐንስ ሲገረዝ የሊቀ ካህን ልጅ ነው ብለው ሊገርዙት ወደ እርሱ መጡ፡፡ ጌታችን ግን ወደ ምድር የመጣው፡፡ ለትሕትና ነው እንጂ ለልዕልና አይደለምና ወሰዱት አለ /ትርጓሜ ወንጌለ ሉቃስ/፡፡
፠ የእመቤታችን ድንግልናዋ ሳይለወጥ ከድንግል ማኅፀን እንደመውጣቱ የጌታችን ግዝረቱም የማይመረመር ሆነ፡፡
እንዲሁ በተዘጋ ቤት መግባቱና መውጣቱ እንደማይመረመር እነዲሁ እንደፈቀደ ከረቀቀ ጥበቡ ችሎታውን በመገረዝ ከሥጋው ምንም ምን ሳይቆረጥ ገለጠ፡፡
#ቅዱስ_ኤልያስ_በእሳት_ሰረገላ_ወደ_ብሔረ_ብፁዓን_ያረገበት_ዕለት_ነው፡፡
**በቅዱስ መጽሐፍ ውስጥ ካሉት ቅዱሳን ነቢያት ዝናም በማቆም ብቸኛ ነቢይ ነው፡፡
✤ የሰማርያው ነቢይ ቴስቢያዊው ኤልያስ ከቅዱሳን አበው ነቢያት አንዱ ሲኾን አባቱ ኢያሴዩ እናቱ ደግሞ ቶናህ(ቶና) ሲባሉ ሲወለድ መላእክት በእሳት ሰፋድል (መጠቅለያ መጐናጸፊያ) ጠቅልለውት ነው፡፡ የስሙ ትርጉምም ‹‹እግዚአብሔር አምላክ ነው›› ማለት ነው፡፡
** ኤልያስ ብዙ ነገር ስለሚያስተምር የቀና እምነቱን ውጤት ጥቂት መመልከት እኔ ማነኝ? ለሚሉት እጅ ይዞ ይመራል፡፡
✤ 1. ለሦስት ዓመት ከመንፈቅ ሰማይ ዝናም ለዘር፥ ጠል ለመከር ከመስጠት እንዲከለከል ምድርም የተከሉባትን
✤ 2. አመጸኞች አክአብንና ኤልዛቤልን ምንነታቸውን ካሳወቀ በኋላ የዘጋውን ለመክፈት ወደ ፈጣሪው በመጸለይ ዝናም አዝንሟል፡፡
✤ 3. በተፈጥሮ የማይመስላቸው በቋንቋም የማይግባባቸው እንኳን ለሰው ሥጋ ሊያመጡ ከሰው ሥጋ የሚነጥቁ አሞራዎች እንጀራና ሥጋ ለምግብ እንዲያመላልሱለት አደረገ 1ኛ ነገሥ. 17፥6-7፡፡ እነዚህ አሞራዎች ለሦስት ዓመት ከመንፈቅ በጋ ከክረምት የለምንም እረፍት ኤልያስን ሲያገለግሉ ኖረዋል፡፡ እምነት ካለ ተአምር መሥራት አይገድም ይህንም ከኤልያስ ይማሯል፡፡
✤ 4. ለአንዲት መበለት ዱቄትና ዘይት አበረከተ፤ ኤልያስ ቁራሽ እየለመነ ያደረገውን ተአምር ልብ ይሏል፡፡ 1ኛ ነገሥ. 17፥16-24፡፡
✤ 5. ዱቄትና ዘይት ያበረከተላት የሰራፕታዋ ሴት ልጇ /ኋላ ዮናስ ነቢይ የሆነው/ ቢሞት ከሞት አስነሳው 1ኛ ነገሥ. 17፥20-23
✤ 6. ለብዙ ጊዜ በቤተ መንግሥት ተሰግስገው አክአብና ኤልዛቤልን በሐሰት ሲደልሉ፥ ግብዝ ሕብረተሰቡን ሲያታልሉ፥ ለፍቶ ያገኘው ገንዘቡን ሲሸልጉ፥ በኀጢአት ሊያስወጉ የነበሩ ነቢያተ ሐሰትና ካህናተ ጣዖትን በሕብረተሰቡ ፊት እስከ መምህራቸው ሰይጣን በቅሌት አከናንቦ ሲያስቅባቸው ውሏል፤ ሐሰቶች የነበሩትን 850 የሚጠጉ የጣዖት ካህናትንም ወደ ቂሶን ወንዝ አውርዶ ፈጅቷቸዋል፡፡ 1ኛ ነገሥ. 18 20 -29
✤ 7. ወደ ፈጣሪው በጸሎት በማመልከት ያቀረበው ንጹሕ መሥዋዕቱን ከሰማይ እሳት ወርዶ በሰው ፊት በላለት (ተቀበለለት) 1ኛ ነገሥ. 18፥30-40፡፡ በዚህም ማንነቱን በሰይጣንና በሰይጣን አቀንቃኞች ፊት አስመስክሯል፡፡
✤ 8. እሳት ከሰማይ በማዝነም ሊጣሉት የመጡትን መምለኪያነ ጣኦት፥ ምሉአነ ኀጢአት፤ የሰይጣን ሠራዊት በሰው ደም የሰከሩ፥ በዲያብሎስ የሚመሩ ጠላቶቹን አጋይቷል 2ኛ ነገሥ 1 9-13
✤ 9. ምግብና መጠጥ መልአክ ከሰማይ አመጣለት ያንን ተመግቦ ለአርባ ቀን ያለምንም ምግብና መጠጥ እስከ እግዚአብሔር ተራራ እስከ ኮሬብ ድረስ 40 ቀንና 40 ሌሊት ተጉዟል 1ኛ ነገሥ. 19፥5-7፡፡
✤ 10. በመጎናጸፊያው የዮርዳኖስን ባሕር ከፍሎ ከነ ደቀመዝሙሩ በደረቅ ተሻግሯል 2ኛ ነገሥ. 2፥11፡፡ ለደቀመዝሙሩም ሀብተ መንገፈስ ቅዱስን አድሎታል፡፡
✤ 11. በትህትናው ‹‹ይበቃኛል፤ አሁንም አቤቱ እኔ ከአባቶቼ አልበልጥምና ነፍሴን ውሰድ›› ብሎ እንዲሞት ለመነ፡፡ እግዚአብሔር ግን ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በ918 ዓመተ ዓለም ሳይሞት በሕይወቱ መራራውን ሞት ዕያየው በብርሃን ሠረገላ ወደሰማይ አሳርጎታል፡፡ 2ኛ ነገሥ. 2፥6-9
✤ 12. እንደ አስፈላጊነቱ ከፈጣሪው ጋር ለብዙ ጊዜ ተነጋግሯል፡፡
✤✤#ከአንድ እስከ አስራ አንድ ያደረጋቸውን ተአምራት የፈጸመለት ታማኝ ፈጣሪው ሰው በሆነበት ወራት በተራራ ከጓደኞቹ ጋር ብርሃነ መለኮቱን ገለጠለት ማቴ 17፥3፡፡
#ደመና_ደመና ….. #በሠረገላ_፤
ኤልያስ ኤልያስ ….. በሠረገላ፤
በእሳት ሠረገላ ….. በሠረገላ፤…
ሰወረው ደመና ….. በሠረገላ፤
ኤልያስ ያረገው… በሠረገላ፤
በእሳት ሠረገላ…. በሠረገላ፤
በጾም በጸሎት ነው …. በሠረገላ፤
አይደለም በሌላ …. በሠረገላ፡፡
#ዳግመኛም ዛሬ የአባቶችን ኖኅ መታሰቢው ነው፡፡ ኖኅ ግን በእግዚአብሔር ፊት ሞገስን አገኘ …ኖኅም በትውልዱ ጻድቅ፥ ፍጹምም ሰው ነበር፡፡ ኖኅ አካሔዱን ከእግዚአብሔር ጋር አደረገ፡፡ /ዘፍ. 6፥7/
#ዳግመኛም በዚህች ዕለት በበረሃ ስልሳ ዘመናት የኖረ የቅዱሳንን ልቡና ከማየቱ የተነሣ ያደነቀ፤ ፊቱም ተለውጦ እንደእሳት ፍሕም ሆነ አባ ሙሴ በዓለ ዕረፍቱ ነው፡፡
ክብረ በዓሉ የሚከበርባቸው ቦታዎች፤
#ለብቃ_ኢየሱስ/ሰሜን ሸዋ/፣
#በለስ_ዋሻ_ኢየሱስa /ተጉለትና ቡልጋ/፥
#በአ.አ. #ገነተ_ኢየሱስና_ገነተ_ማርያም ቤ/ክ፤ (ፈረንሳይ)
#በአ.አ #ገዳመ_ኢየሱስ (ኮልፌ 18)
#በአ.አ #እንጦጦ_ደብረ_ኀይል_ቅዱስ_ራጕኤልና_ኤልያስ (የኤልያስ ዕርገቱ)
#በጎጃም_ደብረ_ኤልያስ ይከበራል፡፡
/በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/
#share
.Facebook...
https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
.YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
.Telegram...
https://t.me/medihanaelem
http://tiktok.com/@finotehiwot
www.finotehiwotsundayschool.com
#ጾም #አጽዋማት #fasting's
#ክብረ_በዓላት #Feast_of_the_lord
#በዓለ_እግዚእነ
መስቀል አደባባይን በተመለከተ ቅዱስ ሲኖዶስ ተወያየ።
(ኢኦተቤ ቴቪ ጥር ፬ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም
ሰሞኑን በመስቀል አደባባይ የተደረገውን የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች መንፈሳዊና የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀ ግብር ላይ የተነሱ የመብትና የይዞታ ጉዳዮች ዙሪያ እንዲሁም ክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስተላለፉት የተባለውን መልዕክት ተከትሎ ቅዱስ ሲኖዶስ ጥር ፫ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም ዓ.ም ረፋድ ዘጠኝ ሰዓት ላይ ጉባኤ አካሒዷል።
በጉባኤውም ከፍ ሲል የተገለጸውን ርዕስ መሰረት በማድረግ ሰፊ ውይይት ካደረገ በኋላ ክብርት ከንቲባዋ አርብ ጥር ፮ ቀን ፳ ፻ ወ ፲ ፬ ዓ.ም ጠዋት አራት ሰዓት በቅዱስ ሲኖዶስ መሰብሰቢያ አዳራሽ በሚካሔደው በጉባኤ ጉባዔ ላይ እንዲገኙና ማብራሪያ እንዲሰጡ ቀጠሮ አሰንዲያዝ አና ጉዳዩ በተረጋጋ መንገድ ውሳኔ እንዲያገኝ መመሪያ ሰጥቷል።
ይህ ሲኖዶሳዊ ውሳኔ የቤተክርስቲያኒቱ የመጨረሻ የሥልጣን ባለቤት የሆነው ቅዱስ ሲኖዶስ የሰጠው ውሳኔ በመሆኑ ለውሳኔው ተግባራዊነት ሁሉም ወገን የድሻውን ማበርከት የሚጠበቅበት መሆኑን በመገንዘብ ይህን ጉዳይ በተመለከተ ቅዱስ ሲኖዶስ አርብ ጥር ፮ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም በሚካሔደው ጉባዔ እልባት እስከሚሰጠው ይታመናል።
ስለሆነም ቅዱስ ሲኖዶስ በጉዳዩ ዙሪያ ውሳኔ እስከሚሰጥ ድረስ ማንኛውም የቤተክርስቲያኒቱ እምነት ተከታይ ህግና ሥርዓትን ጠብቆ ቅዱስ ሲኖዶሱ የሚሰጠውን ውሳኔ ማክ በር እንደሚገባው ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን መልዕክቷን ታስተላልፋለች ሲል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ በፌስ ቡክ ገጹ አስታውቋል።
ታላቅ የምክክር ጉባኤ
ጥር አንድ ፤
በዚህችም ዕለት የቅዱስ እስጢፍኖስ ታቦት ሕግ ወጥቶ በዓሉ ከብሮ ፤ ፀሐይ ሳትገባ የኦርቶዶክስ ቤ/ክንን ርስት ለመወርስ በተካሄደ እንቅስቃሴ ፤ አስለቃጭሽ (መርዛማ ) ጭስ በእስጢፍኖስ ቤ.ክ ቤተ መቅደስ ውስጥ ኦርቶዶክሳውያን ላይ ተወረወረ ፡፡
ይህንን ያደረጉትን ፈጽሞ አይማራቸው !
<<ታቦት ይዛ ወጥታ የጠላትን አስለቃሽ ጭስ ወደ ጉም የምትቀይር ቤ.ክ ይኽ አይገባትም ››
-------------------------------------
ታላቅ የምክክር ጉባኤ
ስለ ቤተክርስቲያንንም ዝም አንልም ፡ ርስታችንንም አንሰጥም !
ጥር 4 ከቀኑ 10 ጀምሮ በቦሌ ደብረሳሌም መድኀኔዓለም እንድንገናኝ ይሁን !
በኋላ ግን የቤተክህነቱ ባለሥልጣናት ታቦቱን ከአስገባን ዘንድ ንግሥትን ጠርተን ማሳየት ግዴታችን ነው፤ ከአዩት ደግሞ በቤቱ አነስተኛነት መቆጣታቸው አይቀርምና ከዚህ ከፍ ያለ ቤት ብንፈልግ ይሻለናል በማለት በፀበሉ ቦታ ላይ በዘመኑ የተሻለ ነው ተብሎ የሚገመተውን የነጋድራስ ሠርፀ ወልድ ፎቅ ቤትን በማስለቀቅ ጥቅምት 4 ቀን 1914 ዓ.ም. ግርማዊት ንግሥተ ነግሥታት ዘውዲቱ በተገኙበት ለ፪ኛ ጊዜ ታቦተ ቅዱስ ዮሐንስ ከመጀመሪያ የሳር ክዳን ጎጆ ቤት ወደ ሁለተኛው ፎቅ ቤት እንዲገባ ተደረገ፡፡
የመጀመሪያው ሕንፃ ክብ ቤ/ን (ዛሬ የእመቤታችን ቤ/ን ያለበት) የመሠረት ድንጋይ በፊታውራሪ አባ ይሬ ቦታ ላይ በ1924 ተጣለ፤ ከ2ት ዓመታት በኋላም በ1926 ሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ አልቆ ንግሥት ባሉበት ተመርቋል፤ ንግሥቲቱም ሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ አንሶ በመሠራቱ ቅር ተሰኝተዋል፤ በእግዚአብሔር ፈቃድ ታላቅ ቤ/ንን እሠራለታለሁ እስከዚያው ድረስ ከመቃኞው ወደ አዲሱ ክቡ ቤ/ን ይግባ ብለው ገብቷል፡፡ ንግሥቲቱም ያሰቡትን ቤ.ን ሳይሠሩ በ1922 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ ዐርፈዋል፡፡
#የአዲሱ_ሕንፃ_ቤተ_ክርስቲያን_መሠራት፡፡
የዐፄ ኀይለ ሥላሴ ልጅ የሐረሩ መስፍን ልዑል መኮንን የተወለደው በዮሐንስ እለት ሲሆን የክርስትና ስሙም አርአያ ዮሐንስ ነው፡፡ አርአያ ዮሐንስም ቅዱስ ዮሐንስን በስሙ የተሰየመበት በመኾኑ ከብላታ ተሰማ ደባልቄ ጋራ በመሆን አባቱ አፄ ኀይለ ሥላሴን የደብረ ነጐድጓድ ቅ/ዮሐንስ ቤ/ንን በአዲስ መልክ አሻሽለው እንዲሠሩለት ይጠይቃቸዋል፡፡ ነገር ግን አባቱ እኛ እንሠራዋለን የሚል መልስ ሰጡት፤ ለጉዳዩ ብዙም ትኩረት ሳይሰጡት፥ ሕንፃውም ሳያሠራ ቆየ፡፡
ብዙም ሳይቆይ መስፍኑ ልጃቸው በቅዱስ ዮሐንስ እለት በግንቦት 4/1949ዓ.ም. አረፈ፡፡ ንጉሡም የልጃቸውን ምኞት ባለመፈጸማቸው ተጸጽተው፤ ልጃቸው ባረፈ በ12ኛው ቀን ወደ ደብረ ነጐድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ/ን በመምጣት የቤተ ክርስቲያኑን ጥንተ ታሪኩን ጠይቀውና ተረድተው፥ ቤተ ክርስቲያኑን ተሳለመውና አፀዱንና ቅጥሩን ተመልክተው የልጃቸውን ራዕይ ለማሳካት በዘመናዊ አሠራር አዲስ ቤ/ን እንደሚያንፁ ቃል ገቡ፡፡
በቃላቸው መሠረትም አፄ ኀይለ ሥላሴ ራሳቸው ተገኝተው በ1960 የመጀመሪያ መቃኞ ቤተ ክርስቲያን ባለበት ቦታ ላይ የመሠረት ደንጊያ ተጣለ፡፡ የሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ አርቴክት ኢጣሊያዊ ነው፡፡ በዐፄ ኀይለ ሥላሴ የገንዘብ ሥጦታም ከ3 ዓመታት በኋላ በ1963 ሕንፃው አልቆ ተመረቀ፤ የሕንፃ ሥራው የተጓተተበት ምክንያትም በ1960 በጄኔራል መንግሠቱ ንዋይና በወንድሙ ግርማሜ ንዋይ መሪነት በተካሄደው መፈንቅለ መንግሥት የሕንፃው ሥራ እየተቋረጠ እንደገና ሲጀምር ጊዜ በመውሰዱ ነው፡፡
ታቦተ ዮሐንስ ከመጀመሪያው ክብ ቤተ ክርስቲያን ወጥቶ በልዩና ባመረ ኹኔታ፥ በመስቀልኛ ቅርጽ፥ በዘመናዊ አሠራር (በአዲስ አበባ በአሠራሩ አምሳያ በሌለው) ወደተሠራው ሕንፃ ቤ/ን ገባ፡፡ በመጀመሪያ በተሠራው የክብ ቤተ ክርስቲያን ውስጥም ከታቦተ ዮሐንስ ጋር ታቦተ ማርያም አብራ በድርብነት ትኖር ነበርና፤ #በ1963 ታቦተ ዮሐንስ አዲስ ወደታነጸው ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ሲገባ ታቦተ ማርያም ደግሞ በዚሁ በቀድሞው ክብ ቤ/ን ቆየች፤ ስያሜዋም መካነ ጎልጎታ ማርያም ኾነ፤ በዚህም ምክንያት የደብሩ ሙሉ መጠሪያ ስያሜ ደብረ ነጐድጓድ ዮሐንስ ብቻ በመባል ፈንታ #ደብረ_ነጐድጓድ_ዮሐንስ_ወመካነ_ጎልጎታ_ማርያም_ቤተ_ክርስቲያን ሆነ፤
#የቤተ_ክርስቲያኑ_አስተዳደር_
ከ1922 እስከ 1960 ድረስም የተዳደረው በገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ን ሥር ሲኾን የሚያስተዳድሩት አለቃውም ኾነ ገበዙ የገነተ ጽጌ አለቃና ገበዝ ነበሩ፡፡
ቤተ ክርስቲያኑ በተመሠረተበት ወቅት የሚያገለግሉት በ2ት ምድብ የተመደቡ ሰሞንኛ 10 አገልጋይ ካህናት ብቻ ነበሩ፡፡ ርስት ጉልት ስላልተጎለተለት አገልጋዮቹ የሚተዳደሩትም በደመወዝ ነበር፡፡ ደመወዛቸውም የቀሳውስት በወር 10ብር፥ የዲያቆናት በወር 5 ብር ሲኾን ገንዘቡ የሚከፈለውም ከቤተ ክህነት ለቤተ ክርስቲያኑ ከተበጀተ ገንዘብ ነበር፡፡
#ጠበል_ቤት_
በጠበል ቤቱ ግቢ ውስጥ 9ኝ ጠበሎች ይገኛሉ፡፡ እነዚህም፤
1ኛ) የሥላሴ ጠበል፤
2ኛ) የእግዚአብሔር አብ ጠበል፤
3ኛ) የመድኀኔ ዓለም ጠበል፤
4ኛ) የእመቤታችን የማርያም ጠበል፤
5ኛ) የኪዳነ ምሕረት ጠበል፤
6ኛ) የቅዱስ ሚካኤል ጠበል፤
7ኛ) የቅዱስ ገብርኤል ጠበል፤
8ኛ) የቅዱስ ጊዮርጊስ ጠበል፤
9ኛ) የአቡነ ተክለሃይማኖት ጠበል ናቸው፡፡
#በደብሩ_የሚከበሩ_ክብረ_በዓላት፤
✧ ጥር 4፤ የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ በዓለ ሥዋሬው፤
✧ መስከረም 21፣ ኅዳር 21፣ ጥር 21፣ ግንቦት 21፤ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም በዓል፤
ኅዳር 12፣ ሰኔ 12፤ የቅዱስ ሚካኤል በዓል፡፡
✧ #ታቦተ_ሕጉ_ወጥቶ_ባይከበርም_የሊቁ_የቅዱስ_ዮሐንስ_አፈ_ወርቅ_ታቦትም_ይገኛል፡፡
አምላካችን ደብሩን ይጠብቅልን፡፡
/በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/ ምንጭ፡- ከ አድባራታን ገዳማት ገጽ/
#share
.Facebook...
https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
.YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
.Telegram...
https://t.me/medihanaelem
http://tiktok.com/@finotehiwot
www.finotehiwotsundayschool.com
#churches_and_monastries #ገዳማትና_አድባራት
#ክብረ_በዓላት #Feasts
#የአዲስ_አበባ_ደብረ_ነጐድጓድ_ቅዱስ_ዮሐንስና_መካነ_ጐልጎታ_ማርያም_ቤተ_ክርስቲያንና_አብሮ_የተመሠረተው_ሰንበቴ_ቤት_የ100 #ዓመታት_ታሪክ፡፡
✧ ጠባቂዬ የዮሐንስ ወንጌላዊ ታቦት በደቡብ ጎንደር ስላለ እርሱ ሳይመጣ እኔ አልነግሥም፡፡ /ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ/
✧ ንግሥት ዘውዲቱ የነገሠችው በምትወደውና ታቦተ ሕጉ አብሯት በማይለየው በቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ እለት የካቲት 4 ቀን 1909ዓ.ም. ነው፡፡
✧ ደብረ ነጐድጓድ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያንም አሁን ባለበት ቦታ ላይ የተመሠረተው ጥቅምት 4ና ጥቅምት 25 ቀን 1914 ዓ.ም. ነው፡፡
ቤተ ክርስቲያኑ አሁን ባለበት ቦታ የተከሉት ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ምኒልክ /1909-1922ዓ.ም./ ሲሆኑ የተመሠረተበትም፤ በእለተ ዐርብ ጥቅምት 25 ቀን በ1914 ዓ.ም. ነው፡፡
ጽላቱ የመጣው ዐፄ ዮሐንስ 4ኛ /1864-1881ዓ.ም./ ወደ ኢየሩሳሌም በላኳቸው አንድ መነኵሴ አማካይነት ሲሆን፤ መነኵሴው ቅዱስ ዮሐንስን እጅግ ይወዱ ስለነበርና በተለይም የዮሐንስ ወንጌል 1፡14 ቃል ሥጋ ኾነ የሚለው ቃል ምሥጢርን ያደንቁ ነበርና በኢየሩሳሌም ለ፮ ዓመታት ቆይተው ወደ ሃገራቸው ሲመለሱ የቅዱስ ዮሐንስ ስም የተቀረጸበትን ታቦተ ዮሐንስ ወንጌላዊን ይዘው መጥተዋል፡፡
ታቦተ ሕጉ በንጉሡ ዐፄ ዮሐንስ ቤተ መንግሥት /መቀሌ/ ግቢ ከቆየ በኋላ ንጉሡ ለልጃቸው ለአርአያ ሥላሴ /ኋላ ራስ/ ሰጥተውታል፡፡ አርአያ ሥላሴም ጥቅምት 13/1875ዓ.ም. ከንጉሥ ምኒልክ /ኋላ አጼ/ ልጅ ወ/ሮ ዘውዲቱ /ኋላ ንግሥተ ነገሥታት/ ጋር ተጋብተዋል፤ ለባለቤታቸው ወ/ሮ ዘወዲቱ ታቦተ ዮሐንስን ‹‹ብትጠብቂው ይጠብቅሻል›› ብለው አደራ ሰጥተዋቸዋል፡፡ ራስ አርአያ ሥላሴ ዮሐንስም በየካቲት 1880ዓ.ም. ሲያርፉ፤ ዐፄ ምኒልክ ልጃቸው ዘውዲቱን ከመቀሌ ወደ አዲስ አበባ እንዲያመጡ ሊጋባ ገብርኤልንና ደጃች አባተን ላኩ፤ ነገር ግን በጕዞው ላይ ኃይለኛ ዝናብ በመዝነቡ ምክንያት ወንዞች ስለሞሉና ወደ አዲስ አበባ መመለስ ባለመቻሉ ወ/ሮ ዘውዲቱ ለአንድ ዓመት በደብረ ታቦር ተቀመጡ፥ ታቦተ ዮሐንስም በማኅደረ ማርያም ተቀመጠ፡፡
ኋላ ወ/ሮ ዘውዲቱ ደጃዝማች ጉግሣ ወሌን /ኋላ ራስ/ በቊርባን አግብተው ወደ በጌምድር ደብረ ታቦር በሄዱ ጊዜ ታቦተ ዮሐንስን አስመጥተው በደብረ ታቦር ቤተ መንግሥት ግቢ ውስጥ አነስተኛ ቤተ ክርስቲያን አሠርተው ለ12 ዓመታት ሲኖሩ ታቦተ ዮሐንስም በዚሁ ቤተ መንግሥት ግቢ አብሯቸው ኖረ፡፡ ባላቸው ራስ ጉግሣ ወሌ በ1902 ዓ.ም. ታሠሩ እስከ 1906ዓ.ም ወደ አፍቀራ ኮረብታ በግዞት ተወሰዱ፡፡ ወ/ሮ ዘውዲቱም ራስ ጉግሣ ወሌ የቊርባን ባላቸው ስለኾኑ ማንንም ሳያገቡ በአዲስ አበባ ቤተ መንግሥት ቆዩ፡፡ ቀጥሎም ወ/ሮ ዘውዲቱ ወደ ፋሌ በርስታቸው ቦታቸው ላይ ከባላቸው ከራስ ጉግሣ ወሌ ጋር ኖሩ፡፡
በመስከረም 19/1909ዓ.ም. ልጅ ኢያሱ ከሥልጣን ሲሻሩ፤ ወይዘሮ ዘውዲቱ አልጋውን እንዲይዙ አጃቢዎች ተልከው መስከረም 22 ቀን 1909ዓ.ም. አዲስ አበባ ገቡ፤ የዘውድ በዓላቸው በኅዳር 12 ቀን 1909 ዓ.ም. እንዲኾን ሲጠየቁ፤ ጠባቂዬ ታቦተ ዮሐንስ በደብረ ታቦር ስላለ እርሱ ካልመጣ አልነግሥም ስላሉ የዘውድ በዓሉ ተላልፎ፤ ታቦተ ዮሐንስ በጥር 29 ቀን 1909 ዓ.ም. ወደ አዲስ አበባ መጥቶ በዐፄ ምኒልክ ጸሎት ቤት (ሥዕል ቤት) ተቀመጠ፡፡
የንግሥት ዘውዲቱ የዘውድ በዓልም በምትወደውና ታቦተ ሕጉ አብሯት በማይለየው በቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ እለት የካቲት 4 ቀን 1909ዓ.ም. በገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ን ግርማዊት ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ምኒልክ ተብለው በዓሉ ተደረገ፤ በእለቱም ታቦተ ዮሐንስ ከስዕል ቤት ኪዳነ ምሕረት ወደ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ሂዶ ተቀድሶበት ዋለ፤ በዐውደ ምሕረቱም ንግሥቲቱ ከታቦተ ሕጉ ጋር አብረው ዑደት አድርገው የዘውድ በዓሉ ተደረገ፡፡ (በሌላ ታሪክ ዐፄ ዮሐንስ ለወሎው ገዢ ራስ ሚካኤል ታቦተ ዮሐንስን ሰጥተዋቸው ኋላ ላይ በተደረገው የሰገሌ ጦርነት ታቦተ ዮሐንስ ወደ አ.አ. መጥቷል የሚሉም አሉ፡፡)
#ንግሥተ_ነገሥታት_ዘውዲቱ_ምኒልክ_ለከተማችን_ብቸኛ_የኾነውን_የቅዱስ#ዮሐንስ_ወንጌላዊ #ቤ/ን #እንድትሠራ_ያደረጓት #፫ት #ምክንያቶች፤
1ኛ) ከመጀመሪያ ባሏ ከአርአያ ሥላሴ ዮሐንስ የተሰጣት በመኾኑና በችግሯም ኾነ በደስታ ኹሉ አብሯት የነበረ ታቦት በመኾኑ፤
2ኛ) የመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ን መካነ መቃብር በመሙላቱ ከቤተ ክህነት ጋር በመመካከር ሌላ የቀብር ቦታ እንደሚያስፈልግ በመታመኑ 2033lm2 ያህል ቦታ እንዲኖረው ተደርጎተከልሏል፡፡
3ኛ) በዓለም አቀፍ ደረጃ የተከሰተውና በከተማችን Nov. 1918 ብዙ ሰዎችን የጨረሰው የኢንፍሉዌንዛ (የኅዳር በሽታ) በፈዋሴ ሕመም የሚታወቀው ሐዋርያና ወንጌላዊው ዮሐንስ ከከተማችንና ከሃገራችን ይህንን የወረርሽኝ በሽታ ነቅሎ እንዲያጠፋው ነው፡፡
ከዘውድ በዓሉ 1909 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ 1914 ዓ.ም. (ለ5ት ዓመታት) በገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቆየ (እስከ 1915 በሥዕል ቤትቆየ የሚሉም አሉ)፡፡ የንግሥት ዘውዲቱ መንፈሳዊ ምኞታቸው ለቅዱስ ዮሐንስ ታቦት ትልቅ ቤ/ን ማሠራት ሲሆን፤ ለጊዜው አሁን ቤተ ክርስቲያኑ ያለበትን ቦታ ጠቁመው መቃኞ እንዲሰራለት በሰጡት ትዕዛዝ መሠረት፤ #በእለተ_ዐርብ_ጥቅምት #25 ቀን #በ1914 ዓ.ም. አሁን የደብረ ነጐድጓድ ዮሐንስ ሕንፃ ቤ/ን የተሠራበት ቦታ ላይ ታቦቱ ከመምጣቱ በፊት መስቀል ዞሮ ቦታው ተከለለ፡፡
የቦታው ባለቤቶች የንጉሣውያን ቤተሰብ የኾኑት ፊታውራሪ አባ ይሬ፣ ደጃዝማች ይገዙ በሀብቴና ነጋድራስ ሠርፀ ወልድ ናቸው፡፡ ይዞታቸውም፤
* መጀመሪያ የታቦተ ዮሐንስ መቃኞ ቤት የነበረበት (አሁን አዲሱ የዮሐንስ ቤ/ን የተሠራበት)ና የመቃብሩ ሥፍራ የደጃዝማች ይገዙ በሀብቴ፤
* ቀድሞ የዮሐንስ ቤ/ን (አሁን የእመቤታችን ቤተ ክርስቲያን) ያለበት ሥፍራ ደግሞ በተለይ የፊታውራሪ አባ ይሬ ቦታ ነው፤
* የጠበሉ ቦታ የነጋድራስ ሠርፀ ወልድ ቦታ ነው፡፡
ከዚያም በቀሳውስት፣ በዲያቆናት በመዘምራን ስበሐተ እግዚአብሔር እየቀረበ፤ ልብሰ ተክህኖ የለበሱ ዲያቆናት በመካከል ሁነው፤ በጥንቱ አራዳ ዘበኞች በሚባሉ ወታደሮች ታጅቦ፥ እምቢልታና መለከት እየተነፋ ከገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ አሁን ቤተ ክርስቲያኑ ወዳለበት ቦታ መጥቶ አንድ የሣር ክዳን ቤተ ንጉሥ የኾነ የደጃዝማች ይገዙ በሀብቴ ቤት ተባርኮ ታቦቱ በመቃኞነት (በመቃረቢያነት) ቆየ፡፡
በእለቱም ታቦተ ሕጉን አጅበው ከመጡት ታዋቂ ሰዎች መካከል ነጋድራስ ወንድማገኘሁ፣ አቶ ይታጠቁ፣ አቶ ዱባለ፣ አቶ ደምሴ በልልኝ፣ አቶ ድልነሣሁ፣ አቶ ተክለማርያም ደምሴና ሌሎችም ነበሩ፡፡ እነዚህ ታዋቂ ሰዎችም ብዙ ርስት ያላቸው ስለበሩ ለቅዱስ ዮሐንስ ባላቸው ጽኑ ፍቀር የተነሣ ታቦቱ በገባበት እለት እህል ውኃ አቅርበው ከዛሬ ጀምሮ እዚህ ቤተ ክርስቲያን ቅጽር ግቢ ውስጥ #ማኅበረ_ሰንበቴ አቋቁመናልና ይዘከርልን በማለት ሰንበቴ ቤቱ ከቤተ ክርስቲያኑ ጋር አብሮ ተመሠረተ፡፡ እስካሁንም ድረስ በየሳምንቱ እየተዘከረ ይገኛል፡፡
/በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/
#share
.Facebook...
https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
.YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
.Telegram...
https://t.me/medihanaelem
http://tiktok.com/@finotehiwot
www.finotehiwotsundayschool.com
#ክብረ_በዓላት #feasts
#አባ_ሊባኖስ_ዘመጣዕ
#በአ.አ. #እንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት ቀድሞ በቅዳሴና በውዳሴ ታቦተ ሕጋቸው ሲከበር የቆየው የአቡነ ሊባኖስ ዘመጣዕ ታቦተ ሕጋቸው #ሰኞ_ጥር 3/2013 ዓ.ም.
ለሁለተኛ ጊዜ_ታቦተ_ሕጋቸው_ወጥቶ_ይከብራል፡፡ (ሁላችሁም እንድትገኙ ገዳሟ ጥሪዋን አስተላልፋላች)፡፡
#ጥር_3 #አባ_ሊባኖስ_ዘመጣዕ_ዕረፍታቸው_ነው_፡፡
፠ #የደብረ_ሊባኖስ_ገዳምን_የመሠረቱና_በስማቸው_የተሠየመላቸው፤
፠ ቅዱስ ላሊበላ ከ11ዱ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት አንዱን በስማቸው ያነፀላቸው፡፡
፠ #ከደረቅ_ዐለት_ላይ_ውኃ_እያፈለቁ_ድውያንን_የሚፈውሱ_ተአምረኛ_አባት
፠ በኤርትራ አካለ ጉዛይ ገዳመ መጣዕ፣ በአኵሱም ከተማ አጠገብ፣ በላስታ ላሊበላ፣ ደብረ ወርቅ አቡነ ሊባኖስ ገዳም፣ እንዲሁም ከ2012 ዓ.ም. ጀምሮ በአ.አ. እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ገዳም ክብረ በዓል የሚከበርላቸው፡፡
(ሌሎቹን የምታውቋቸውን ከነፎቷቸው ላኩልን)
፠ አባታቸው አብርሃም እናታቸው ንግሥት ሊድሯቸው ሲሉ መመነን በመፈለጋቸው መልአክ በሌሊት መጥቶ ወደ ታላቁ አባት አባ ጳኩሚስ ዘንድ አደረሳቸው፡፡
፠ አባ ጳኩሚስም ሥርዐተ ገዳምን፥ አስኬማ መላእክትን፥ ቅናተ ዮሐንስን አስተማሯቸው፤ አመነኮሷቸውና ከ8ቱ ቅዱሳን ጋር እንዲገናኙ አደረጓቸው፡፡
፠ ቀድሞ የመራቸው መልአክ ከአባ ጳኩሚስ ‹‹ወደ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ ሂድና ተጋድሎህን በዚያ ፈጽም ዝናህ በስፋት ይነገራል፣ ለብዙዎችም አባት ትሆናቸዋለህ›› አላቸው፡፡ ቀጥሎም ራሱ መልአኩ ወደ ኢትዮጵያ አመጣቸውና በአኵሱም ተቀመጡ፡፡
፠ በዚያም ብዙ ከተጋደሉ በኋላ ወደ ሸዋ መጡና ወንጌልን ዞረው አስተምረው ብዙ ድውያንን ፈውሰው (ቀድሞ የዋልድባን ገዳም ባስፋፉ አባቶች የተመሠረተችውን #የእንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት_ገዳምን እስፋፍተው፡፡) ተመልሰው ወደ አኵሱም ሄዱ፡፡
፠ በአኵሱምም 7 የተለያዩ ጸበሎችን ከድንጋይ ላይ በተአምራት አፍልቀው ድውያንን ፈውሰው ፥ ዕውራንን አበሩ፡፡ በዓታቸውንም ከአኵሱም ጽዮን ፊት ለፊት አድርገው ሲኖሩ ከዕለታት በአንደኛው ቀን አባታችን በተአምራት ከጭንጫ ካፈለቁት ጸበል ‹‹ተራ ውሃ ነው›› ብላ አንዲት ሴት ልጇን አዝላ ልትቀዳ መጣች፡፡ ወዲውም ከቦታው ስትደርስ አድጧት ወደቀችና ልጇም አምልጥጧት ልቡን ድንጋይ መቶት ሞተ፡፡ ሴትዮዋም ስትጮህ አባ ሊባኖስ ፈጥነው ወጡና በልጁ ላይ ጸልየው በመስቀል ምልክት አማትበው ከሞት አስነሥተውታል፡፡ ሕፃኑ ልጅ ከሞት እንደተነሣ ‹‹አምላከ አባ ሊባኖስ›› ብሎ አመሰገነ፡፡ (ስዕላቸው የሚገልጸው ይህንን ተአምር ነው፡፡)
፠ ይህንንም ደግ ሥራቸውንና ተአምራታቸውን ያዩ አንዳንድ እኩይ ካህናት በቅናት ተመልተው ‹‹ምትሃት ነው የሚያሳየው›› ብለው በጻድቁ ላይ ሕዝቡን አሳደሙባቸው፡፡ አባታችንም ካህናቱን ለመምከር ቢሞክሩም አላስቀምጥ አሏቸው፡፡ ይልቁንም ጦር ጦራቸውን ይዘው አሳደዷቸው፡፡
፠ አባታችንም በዚህ እጅግ አዝነው ከአኵሱም ተነሥተው ደርቃ ወደምትባል ቦታ ሄዱ፡፡ በዚያም በጾም በጸሎት እየተጋደሉ ሲኖሩ፤ በእነዚያ በጠሏቸውና በክፋት በተነሡባቸው ካህናት አገር ግን ለ3 ዓመት ምንም ዝናብ ሳይዘንብ ቀረ፡፡ አባታችን በተሰደዱባት በደርቃ አገር ግን ብዙ ዝናብ ይዘንብ ነበር፡፡ አባታችን በዚያችም አገር እንደልማዳቸው ከዐለት ላይ ውኃ አፍልቀው በውኃው ብዙ ድውያንን ፈውሰውበታል፡፡ በዚያም ትልቅ በዓት መሥርተው በተጋድሎ ሲኖሩ በክፉ የተነሡባቸው እኩይ የሆኑ ካህናት መጥተው ‹‹አባታችን በከንቱ አምተንሃል በድለንሃልና ይቅር በለን፣ በድርቅ ማለቃችን ነውና ዝናብም እንዲዘንብልን ጸልይን›› ብለው ከእግራቸው ሥር ወደቁ፡፡ አባታችንም ይቅር ብለው ከፈጣሪ አማለዷቸው፡፡ ዝናቡም ወዲያው ዘነበላቸውና በአገሪቱ ጥጋብ ሆነ፡፡
፠ ከዚህም በኋላ አባታችን አስቀድመው ወዳዩአት ወደ ሸዋ ምድር ግራርያ (የአሁኗ ደብረ ሊባኖስ) መጡና በዓታቸውን በአሰቦት ጫካ አደረጉ፡፡ ነገር ግን መልአኩ ተገልጦላቸው ‹‹ሊባኖስ ሆይ! ከዚህ ቦታ የአንተ መኖሪያ አይደለም፣ በዚህ ቦታ ላይ እግዚአብሔርንና ሰውን የሚያገናኝ የሚያስታርቅ ታላቅ ጻድቅ (አቡነ ተክለ ሃይማኖት) ይወጣበታልና ይህ ቦታ የእርሱ ርስት ነው፣ የብዙ መነኮሳትም መንደር ይሆናል ነገር ግን የቦታው ስም በአንተ ስም ይጠራልሃል›› አላቸው፡፡ በኋላ አባታችን ተክለ ሃይማኖት ተወልደው በዓታቸውን በዚያ ቦታ ላይ ሲያጸኑ ቦታው ግን ‹‹ደብረ ሊባኖስ›› ተብሎ በመጀመሪያው አባት ስም ተሰየመ፡፡
፠ መልአኩም በሌሊት እየመራ ወደ አኵሱም ወሰዳቸው፡፡ ከዚያም ‹‹ታሪክ ወደምትሠራበት ዕጣ ክፍልህ ወደሆነው ቦታ አደርስሃለሁ›› አላቸውና ወደ ኤርትራ አካለ ጉዛይ አውራጃ ልዩ ስሙ መጣዕ ወደተባለው ቦታ ወሰዳቸው፡፡ በዚያም አባታችን ድውያንን እየፈወሱ፣ ለምፃሞችን እያዳኑ፣ ሙታንን እያስነሡ ብዙ ተአምራትን እያደረጉ ወንጌልን እየሰበኩ ‹‹ሊባኖስ ዘመጣዕ›› የሚባለውን ትልቁን ገዳማቸውን መሠረቱ፡፡ በወቅቱ የነበረው አፄ ገብረ መስቀልም የመጀመሪያውን ቤተ ክርስቲያን አሠራላቸው፡፡
፠ ቅዱስ ላሊበላ 23 ዓመት ሙሉ ካነጻቸው እጅግ ድንቅ 11 ቤተ መቅደሶች ውስጥ አንደኛውን በአባ ሊባኖስ ስም ሰይሞላቸዋል፡፡ አፄ ገብረ መስቀል ያሠራላቸው ሌላኛው ገዳማቸው ትግራይ ተንቤን ውስጥ ይገኛል፡፡ እጅግ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን በማድረግ የሚታወቁት አባታችን እንደ ተስዓቱ ቅዱሳን ከሮም በመምጣት በሀገራችን ላይ ብርሃንን አብርተዋል፡፡
፠+፠ በመጨረሻም ጥቅምት 2 ቀን ተፀንሰው ፤
፠+፠ ሐምሌ 3 ቀን ተወለደው፤
፠+፠ በ140 ዓመታቸው ጥር 3 ቀን በክብር ዐርፈዋል፡፡
፠+፠ ቅዳሴ ቤታቸው ደግሞ ሐምሌ 3 ነው፡፡ ይኸውም ለመጀመሪያ ጊዜ በዐፄ ገብረ መስቀል ጊዜ በስማቸው ቤተ ክርስቲያን ተሠርቶ የተመረቀበት ዕለት ነው፡፡
***** እኛም ለክብረ በዓሉ የሚሆነውን ከዋይዜማው ጀምሮ ሙሉውን ሥርዐተ ማኅሌት እነሆ ብለናል፡፡
(ምንጭ፤ ሊቀ ብርሃናት መርቆሬዎስ አረጋ፣ 5ኛ መጽሐፍ የቅዱሳን ታሪክ)
#እንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት_ገዳም
#ለ1512 #ዓመታት_ባለውለታዋን_ዘንግታ_የቆየችው_እንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት_ገዳም_ጥር_3/2012 ዓ.ም. #ባለውለታዋን_አባ_ሊባኖስ_ዘመጣዕን_ፎቶ_ላይ_በምታዩት_ሁኔታ_ዘክራለች_፡፡ አሁን ደግሞ ለሁለተኛ ጌዜ በድምቀት ተዘክራለች
፠ እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት በ485 ዓ.ም. የሸዋ አባቶች የዐብዩ መድኀኔዓለምንና የበረከት ኪዳነ ምሕረት ታቦትን ይዘው ለ3 ወራት የተሰባሰቡባት ስትሆን፤ ታቦተ ኪዳነ ምሕረትን እንጦጦ ላይ አስቀምጠውና ገዳሟን መሥርተው፤ ታቦተ መድኀኔ ዓለምን ይዘው ወደ ዋልድባ በመሄድ ቀድሞ ጌታችን የገደመውን ገዳም ለ2ኛ ጊዜ አስፋፍተውታል፡፡
፠ ከ16 ዓመታትት በኋላ በ500 ዓ.ም. ደግሞ አቡነ ሊባኖስ ዘመጣዕ ከአኵሱም ወደ ሸዋ ሲመጡ ሐመረ ኖኅን በገዳምነት ገድመው ጠበሏን አፍልቀው ሕሙማንን ፈውሰው ተመልሰዋል፡፡
፠ በ197 ዓ.ም. አንድ ምዕመን ለአቡነ ተክለሃይማኖት አስፈቅደው፤ ገድላቸውን ከአኵሱም አጽፈው በማምጣት ማኅሌቱ እንዲቆም፣ ገድላቸው እንዲነበብ፤ 50 ብር እየከፈሉ የጻድቁን ዝክር እንዲገለገል አስደርገዋል፡፡
፠ የአባቶቻችን አምላክ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ይመስገን፨
#ሰኞ_ጥር 3/2013 ዓ.ም. በገዳሙ እንገናኝ::
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
