en
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Open in Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 391 subscribers, ranking 5 586 in the Religion & Spirituality category and 2 200 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 391 subscribers.

According to the latest data from 01 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 22 over the last 30 days and by -7 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 21.30%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 10.19% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 278 views. Within the first day, a publication typically gains 1 569 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 17.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 02 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

15 391
Subscribers
-724 hours
+227 days
+2230 days
Posts Archive
ዛሬም ከቅዳሴ በኋላ የሰንበት ት/ት ቤታችን አባላት እየታደኑ ነው፡፡ ***************************************** የቅዳሴው ስርዓት በሰላም ግቡ ተብሎ ምዕመኑ ከተሸኘ በኋላ የሰንበት ት/ት ቤታችንም አባላት ወደ ቤት ሊሄዱ ሲሉ የሲቪል ልብስ የለበሱ የፖሊስ አካላት መኪና ይዘው በመምጣት አባሎቻችንን ሊወስዱ ሲሉ በጊዜው የነበረው ምእመን ልጆቻችን እንዳይያዙ በማለት አስጥሏቸዋል፡፡ በአሁን ሰዓት ሁሉም የሰ/ት/ቤቱ አባላት ከግቢ ሳይወጡ በአንድ ላይ ይገኛሉ፡፡ ከታሰርን ሁላችንም እንታሰር እያሉ ናቸው፡፡ የራሳችንን ችግር በቤታችን እንፈታዋለን ብንልም የሚሆን አልሆነም፡፡ ስለሆነም ሰ/ት/ቤቱ በዚህ ሁኔታ እየታደነ እና አገልግሎቱ እየተስተጎለ መቀጠል ስለሌለበት የአ.አ ሰንበት ት/ት ቤቶች እና የአጥቢያው ማኅበራት እንዲሁም የአጥቢያችን ምእመናን በዚሁ ጉዳይ የስብሰባ ጥሪ በቅርቡ የምንጠራችሁ ይሆናል፡፡ የአ.አ ሐገረ ስብከትም ላይ ያላችሁ አመራሮች ለህሊናችሁ ስትሉ እየሆነብን ያለውን ተመልክታችሁ እልባት ስጡ::

#አሳዛኝ ዜና #ዛሬም የደብራችን አስተዳደር የሰ/ት/ቤት አባሎቻችንን እያሳሰረ ይገኛል፡፡ በዛሬው እለት ምክንያቱ በውል ባልታወቀ ሁኔታ አባሎቻችንን መታወቂያ በመጠየቅ እየታሰሩብን ይገኛሉ ፡፡ የደብራችን ማኅበረ ካህናት እኛን የሰ/ት/ቤት ልጆቻችሁ ለበርካታ ዓመታት በፍቅር እና በአንድነት ኮሽታ ሳይሰማብን ስናገለግል ኖረን ዛሬ በእስር ቤት ስንታሰር እያያችሁ እንዳላያችሁ ፣ እየሰማችሁ እንዳልሰማችሁ የምትሆኑት እስከ መቼ ድረስ ነው ፡፡ ልጆቻችን ከመታሰራቸው በላይ የእናንተ ዝምታ ልባችንን ያደማል፡፡ የአ.አ ሀገረ ስብከከትም ጉዳዩን በተደጋጋሚ ብናሳውቅም ‹‹ሰው ካልሞተ በቀር አንነቃም›› ያሉ ይመስላል ፡፡ ምን እስኪመጣ ነው እየተጠበቀ ያለው? #ደብረ ሰላም መቼ ይሆን ወደ ሰላሟ የምትመለሰው የሰ/ት/ቤታችን አባላትስ ለምን በየጊዜው ይታሰሩብናል፡፡ ትውልድ ማፍሪያ የሚሆን ተለዋጭ ቦታ ሳይሰጥ አዳራሻችን አይፍረስብን ስላሉ?? ሀገረ ስብከት ተመላልሰው ለ 5 ጊዜያት ውሳኔ ስላስወሰኑ?? ተማሪዎች አይበተኑ ስላሉ?? ዛሬ ላይ ህጻናትን ለማስተማር የሚወጡ መምህራን ቤተሰቦቻቸውን ‹‹ከታሰርኩ አታስቡ›› እያሉ ነው እየወጡ ያሉት መቼ ይሆን የደብረ ሰላም ስቃይዋ የሚያበቃው #የታሰሩት አባላት ፤ ለቀን ህጻናትና ወጣት ክፍል ተማሪዎች ትምህርት አስተምረው ሲውጡ ነው ፡፡ ይህ ወንጌልን ለማመስ እና ለማጥፋት ሆን ተብሎ የተሴረ ተግባር እንደሆነ እንረዳለን ፡፡ሰንበት ትምህርት ቤቱ ባገኛት ቦታ ዋና ዓላማው የሆነውን ቃለ እግዚአብሔርን ማስተማር እንዲያቆም ማድረግ ከሁሉ ነገር የከፋ ነው ፡፡ ሰ/ት.ቤቱም ትልቅ ትኩረት እንሚስጠው ልናሳውቅ እንወዳለን፡፡ #ሰንበት ት/ት ቤታችን ዛሬም እንደትላንቱ አገልግሎቱን አጠናክሮ ይቀጥላል፣ ህጻናትም አይበተኑም ፣ አባቶቻችን ‹‹ ክርስቲያን እንደ ሚስማር ሲመታ ይጠነክራል›› እንዳሉ እኛም ጠንክረን አገልግሎታችንን ለአጥቢያችን ፣ ከአጥቢያችን አልፈን ለከተማችን ፣ ከከተማችን አልፈን ለሀገራችን ፣ ከሀገራችን አልፈን ለአለማችን እናዳርሳለን መጽሐፉም የሚለው ይህንኑ ነውና፡፡ በአገልግሎታችን ሁሉ #መድኀኔዓለም ይቅደምልን!!! የታሰሩትን ያስፈታልን ።

#እንኳን ደስ አላቹህ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የጎፋ መካነ ሕያዋን ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል ሰንበት ት/ቤት የሰማዕቱ የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ አንዱ ራዕይ ሊፈፀም ጅማሬ እውን ሆነ ። በዛ
+1
#እንኳን ደስ አላቹህ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የጎፋ መካነ ሕያዋን ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል ሰንበት ት/ቤት የሰማዕቱ የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ አንዱ ራዕይ ሊፈፀም ጅማሬ እውን ሆነ ። በዛሬው ዕለት ብፁዕ አቡነ መልብ ጼዴቅ የአዲስ አበባ እና የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ፣ መልአከ ሕይወት አባ ወልደ ኢየሱስ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የካህናት መምሪያ ሃላፊ ፣ ሊቀ ማዕምራን አካለወልድ ተሰማ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ በተገኙበት የሕንፃ ግንባታ ጅማሬው ተከናውኗል ። በጎፋ መካነ ሕያዋን ቅ/ገብርኤል ካቴድራል የሕንፃ ግንባታ ቦታ ይቀየር አይቀየር በሚል ምክንያት በካህናትና በሰንበት ት/ቤት አባላት መካከል ተከስቶ የነበረ አለመግባባት በግንቦት 26/2013 ዓ/ም ችግሩን ለመፍታት የስብሰባ መርሐ ግብር የተደረገ ሲሆን በስብሰባው የካቴድራሉ የበላይ ጠባቂ ብፁዕ አቡነ ቴዎፍሎስ በሰሜን አሜሪካ የካሊፎርንያ አካባቢ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት አለመግባባቱ ተፈቶ ነገሩ ዕልባት ማግኘቱ ይታወቃል። ምንጭ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት

ꔰ ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ꔰ Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSun
+6
ꔰ ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ꔰ Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem www.Finotehiwotsundayschool.com

...#እረፍታቸው ✼#ሐዋርያው_ቅዱስ_ጴጥሮስ ከእዚያም እግዚአብሔር በሞቱ እንደሚያከብረው ነግሮት ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡ በመጨረሻም ቅዱስ ጴጥሮስ በሮም አደባባይ በጨካኙ በኔሮን ቄሳር ዘመነ መንግሥት ቁልቁል (እንደ አምላኬ አልሰቀልም ብሎ) በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ሐምሌ 5 ቀን በ67 ዓ.ም. በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡ ✼#ሐዋርያው_ቅዱስ ጳውሎስ ለ 2 ዓመት ከ6 ወር በጨለማ ቤት ታሥሮ ከቆየ በኋላ በ74 ዓመት ዕድሜው በሮም ከተማ በኦስትያ መንገድ በኔሮን ቄሳር ዘመነ መንግሥት አንገቱን በሠይፍ ተሠይፎ ሐምሌ 5 ቀን በ67 ዓ.ም. በሰማዕትነት አረፈ፡፡ አምላካችን እግዚአብሔር ከቅዱስ ጴጥሮስና ከቅዱስ ጳውሎስ ረድኤት በረከታቸው ይክፈለን፤ አሜን፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ቤተ ክርስቲያኖቹ፤ #ብርሃናተ_ዓለም_ጴጥሮስ-ወጳውሎስ፤ ከፒያሳ ወደ አስኮ በሚወስደው መስመር መንገድ ላይ የሚገኝ፡፡ #ሰዋስወ_ብርሃን_ቅዱስ-ጳውሎስ_ገዳም፤ ከ3ቱ መንፈሳውያኝ ኮሌጆች አንዱና ዋነኛው የሚገኝበት፡፡ ከመርካቶ አውቶቡስ ተራ 18ት ማዞሪያ ብላችሁ ስትሄዱ የሚገኝ፡፡ ጴጥሮስና ጳውሎስ ጽኑዕ ነው ፍቅራቸው፤ በተጠሩ ጊዜ ሞትም አልለያቸው፤ ፍቅራቸውን አውቆ አንድ ቀን ጠራቸው፡፡ /በሊቁ መልአከ ብርሃን ቤተ ማርያም ግዛው/ የሐምሌ 5 ማኅሌት ቁመት እንደ ቀጨኔ ደብረ ሰላም ባሉ ታላላቅ አድባራት ይቆማል፡፡ ꔰ ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ꔰ Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem www.Finotehiwotsundayschool.com

እንኳን ፤ለብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ በዓለ ዕረፍት እንዲሁም ለሐዋርያት (የሰኔ) ጾም ፍቺ አደረሳችሁ፡፡ ✤✤ #ብርሃናተ_ዓለም_ጴጥሮስ_ወጳውሎስ_ወሥርዐተ_ማኅሌት_ዘሐምሌ_፭፡፡ ✼#ሐዋርያው_ቅዱስ_ጴጥሮስ፤ በገሊላ ባሕር ዳርቻ በምትገኘው በቤተሳይዳ ተወለደ፡፡ የአባቱ ስም ዮና የእናቱ ስም ሃውኒን ይባላል፡፡ ከ 5 ዓመቱ ጀምሮ ያደገው በቅፍርናሆም ከተማ ነው የመጀመሪያው ስሙ ስምዖን ሲሆን ይህንንም እናቱ በነገዷ ስም እንዳወጣችለት ይነገራል፡፡ ✼#ሐዋርያው_ቅዱስ_ጳውሎስ፤ ነገዱ ከዕብራውያን ከብንያም ነገድ ነው አባቱ ዮስአል ሲሆን የተወለደውም በጠርሴስ ከተማ ነው፡፡ ጠርሴስ በንግድ የታወቀች የኬልቅያ ዋና ከተማ ናት፡፡ ሮማውያን በሥራቸው ለሚተዳደሩት ሕዝቦች ሮማዊ ዜግነት ይሰጡ ስለነበር የቅዱስ ጳውሎስ አባት በዜግነት ሮማዊ ነበር፡፡ ይህም ለቅዱስ ጳውሎስ ተላልፎለታል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ በ15 ዓመት ዕድሜው ወደ ትውልድ ሐገሩ በመመለስ በኢየሩሳሌም ከነበረው የታወቀ የገማልያል ትምህርት ቤት ገባ፡፡ በዚያም የአይሁድን ሕግና ሥርዐት እየተማረ እስከ 3ዐ ዓመቱ ቆየ፡፡ በ3ዐ ዓመቱ የአይሁድን ሸንጐ አባል ሆኖ ተቈጠረ፡ ...#ለአገልግሎት_አጠራራቸው ✤✼ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በጐልማሳነቱ ከወንድሙ ከእንድርያስ ጋር በገሊላ ባሕር ዓሣ ማሥገር ጀመረ፡፡ ለደቀመዛሙርትነት ሲመረጥ እድሜው 55 ዓመት ሲሆን ወደጌታችን ያመጣውም ወንድሙ እንድርያስ ነው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ለሐዋርያነት ሲጠራ መተዳደሪያው የነበረውን መረቡን ታንኳውን እንዲህም አባቱን ትቶ ጌታውን የተከተለ ሐዋርያ ነው፡፡ በቂሳርያ ከተማ መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ማን ትሉኛላችሁ ብሎ በጠየቀ ጊዜ አንተ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ነህ ብሎ ለአይሁድ ሊቃውንት የተሰወረ ምሥጢረ ተዋሕዶ ገልጦ በመመስከሩ ጌታችን አንተ ጴጥሮስ ነህ ብሎታል ይህን በጽርዕ ቋንቋ «ዐለት» ማለት ነው በአረማይክ ደግሞ ኬፋ ይባላል፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ጌታን ይወድ ነበር፡፡ ፍቅሩ ግን ቅንዓት የተቀላቀለ በመሆኑ ጌታችን ለደቀመዛሙርቱ የሞቱን ነገር ቀድሞ ሲነግራቸው አይሁንብህ በማለት ተከራክሯል፡፡ ማቴ 16፥23 በኋላም ሁሉም በአንተ ቢሰናከሉ እኔ ከቶ አልሰናከልም ብሎ በራሱ ቅንዓት ተማምኖ ተናግሮ ነበር፡፡ ጌታችን ዶሮ ሳይጮህ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ ያለው እንኳን ከአንተ ጋር መሞት እንኳ የሚያስፈልገኝ ቢሆን ከቶ አልክድህም በማለት የተናገረ ሐዋርያ ነው፡፡ ማቴ 26፥34 ነገር ግን 3 ጊዜ ጌታችንን አላውቀውም ብሎ ካደ፤ ዶሮ በጮኸና አምላኩን መበደሉን እንዳወቀ ከግቢው ወጥቶ አለቀሰ ንስሐ ገባ፡፡ ጴጥሮስ በዕድሜው ታላቅነት በሐዋርያት ዘንድ እንደ አባት ይታይ ስለነuር ጌታ በተለየው ጊዘ? ሐዋርያቱን ሊመግብ ወደሚያውቀው ሙያ ዓሣ ወደማስገሩ ተሠማራ ጌታም አስቀድሞ የመረጠው እርሱ ነውና ቢከዳው እንኳን በንስሐ በመመለሱ ንስሐውን መቀበሉን ዛሬም እንደሚወደው ይገልጽለƒም ዘንድ በጥብርያዶስ ባሕር ተገለጠለት፡፡ ሦስት ጊዜ ክዶት ነበርና ቀኖና ሰጠው፡፡ አሁን ቅዱስ ጴጥሮስ በራስ መተማመኑ እንዳላዋጣው አውቆ ትወደኛለህ ተብሎ ሲጠየቅ አንተ ታውቃለህ ነበረ መልሱ የራሱ እውቀት የት እንዳደረሰው ያውቃልና ጌታችንም ኀዳጌ በቀል /በቀልን የሚተው/ ነውና ዛሬም እንደሚወደው በንሰሐ ተመልሷልና ዛሬም ለእርሱ የሰጠውን ክብር እንደማያጐልበት ሲነግረው ግልገሎቼን አሠማራ ጠቦቶቼን ጠብቅ በጐቼን አሠማራ በማለት አደራውን አስረከበው፡፡ ዮሐ 21፥15-17 ✼#ሐዋርያው_ቅዱስ_ጳውሎስ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚያስተምርበት ዘመን ቅዱስ ጳውሎስ በኢየሩሳሌም ስለነበረ በአይሁድ ሸንጐ አባልነት ለ2 ዓመታት በሠራበት ወቅት እምነቱ ቀናተኛ ፈሪሳዊ በመኾኑ ክርስቲያኖችን በማናቸውም አጋጣማ> ይቃወም ነበር፡፡ ቅዱስ እስጢፋኖስ በድንጋይ ተወግሮ በሰማዕትነት ሲያርፍም የወጋሪዎችን ልብe ይጠብቅ የነበረው እርሱ ነው፡፡ በ32 ዓመት ዕድሜው ከኢየሩሳሌም 223 ኪ.ሜ ርቀት በስተሰሜን በኩል በምትገኘው የደማስቆ ከተማ ብዙ ክርስቲያኖች መኖራቸውን ሲሰማ ወደ ሊቀ ካህናቱ ቀርቦ ክርስቲያኖችን ለማጥፋት የሚያስችKውን የፈቃድ ደብዳቤ ጠይቆ ካገኘ በኋላ ጭፍሮችን አስከትሎ ወደ ደማስቆ አመራ፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ ወደ ከተማዋ ለመድረስ ጥቂት ሲቀረው ነበር ከሰማይ የወረደው ብርሃን አካባቢውን ያለበሰውና ሳዖል፥ ሳዖል ስለምን ታሳድደኛለህ? የሚለውን ድምፅ የሰማው፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስም ጌታ ሆይ ማን ነህ? ብሎ ጠየቀ የምታሳድደኝ እኔ የናዝሬቱ ኢየሱስ ነኝ የመውጊያውን ብረት ብትቃወም ለአንተ ይብስብሃል ሲል መድኀኒታችን ተናገረው፡፡ ያንን በወደቀበት ሆኖ እየተንቀጠቀጠ ጌታ ሆይ ምን አደርግ ዘንድ ትወዳለህ ሲል ጠየቀው ከዚህ በኋላ ተነሥቶ ወደ ደማስቆ እንዲገባ ተነገረው፡፡ የሐዋ 9፥1 የሐዋርያው ዓይኖች ለማየት አልቻሉም፡፡ እየተመራ ወደ ደማስቆ ገባ ለ3 ቀናት ያህልም እህል ሳይቀምስ ቆየ በዚያች ዕለት እግዚአብሔር አምላክ በደማስቆ ለሚገኘው እና ሐናንያ ለተባለው አባት በራዕይ ተገለጠለት፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም ያለበትን አድራሻ ነገረውና እንዲያጠምቀው አዘዘው፡፡ ሐናንያ አስቀድሞ የቅዱስ ጳውሎስን ማንነት ያውቃል፡፡ አብዛኞቹ በደማስቆ የሚገኙት ክርስቲያኖች ከኢየሩሳሌም በስደት ጊዜ የመጡ ናቸው፡፡ ያን ስደት ያስነሳው ደግሞ በቅዱስ እስጢፋኖስ ላይ የደረሰው መከራ ነው፡፡ በዚህ በቅዱስ እስጢፋኖስ ሰማዕትነት ደግሞ ዋናው ተዋናይ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ነበርና ነው፡፡ ሐናንያ ቅዱስ ጳውሎስን ካጠመቀውና ካስተማረውም በኋላ ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ዓረብ ሐገር መሄዱን ^c< }“ÓbM:: ÑL 1፥17 ለሦስት ዓመታት በዓረቢያ በረሃ ከቆየ በኋላ ወደ ደማስቆ ከተማ ተመለሰ፡፡ በዚያም በነበሩ አይሁድ መካከል በፊት ያሳድደው የነበረውን ኢየሱስ ክርስቶስን መስበክ ጀመረ፡፡ ከዚያ በፊት በፈሪሳዊነቱና ለአይሁድ ሕግ በነበረው ቅንዓት የሚታወቀው ጳውሎስ ዛሬ ወንጌል ሲሰብክ በማየታቸው አይሁድ ተነሡበት፡፡ በዚያም የተነሣ የደማስቆ ክርስቲያኖች በቅርጫት አውርደው ወደ ኢየሩሳሌም ላኩት፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ኢየሩሳሌም ሲደርስ አይሁድ ጳውሎስን እንደሚያውቁት እና እንደለመዱት ሆኖ ስላላገኙት ሊገድሉት ተነሱ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ክርስቲያኖች የቅዱስ ጳውሎስን መመለስ ሊያምኑ አልቻሉም፡፡ በመጨረሻ ግን በርናባስ ወደ ሐዋርያት ዘንድ ወስዶ የጳውሎስን መመለስ በመተረክ እንዲያምኑት አደረጋቸው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በኢየሩሳሌም በድፍረት በማስተማሩ አይሁድ ስለተቃወሙት ከተማዋን ትቶ በቂሳርያ በኩል ወደ ትውልድ ሐገሩ ጠርሴስ ተመለሰ፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በጠርሴስ ከተማ ለ9 ዓመታት ቆይቷል፡፡ ከኢየሩሳሌም ውጭ የአሕዛብ ከተማ በነበረችው በአንጾኪያ የክርስትና ሃይማኖት ተስፋፋ፡፡ ከዚህም በኋላ ሐዋርያው ሦስት ታላላቅ ሐዋርያዊ ጉዞዎችን አድርጓል፡፡ በመጀመሪያው ጉዞው ወደ 2,ዐዐዐ ኪ.ሜ የሚደርስ መንገድ በእግር ተጉዟል፤ ይህም የተከናወነው በ46 ዓ.ም. ነው፡፡ በሁለተኛው ሐዋርያዊ ጉዞው ከ18 በላይ ከተሞችን ሸፍኗል፤ ጉዞውም በ5ዐ ዓ.ም. የተደረገ ነው፡፡ በሦስተኛው ሐዋርያዊ ጉዞው ከ2ዐ በላይ ከተሞችን ሸፍኗል፤ ጉዞውም በ54 ዓ.ም. የተደረገ ነው፡፡ ብዙም ጊዜ በቁም እሥር በብዙም መከራ ሥቃይ እንግልት ያሳለፈ ታላቅ ሐዋርያ ነው፡፡ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

የ55ኛ ዓመት የምስረታ በዓል 3 ኛ መርኀ ግብር በቅርቡ የምናሳውቅ ይሆናል:: ሁለተኛው መርኀ ግብር በከፊል ይህን ይመስል ነበር፡፡ ከፎቶማኀደር ፤ ዐውደ ጥናት ( ርዕስ ክርስቲያናዊ ጋብቻ ፣ ኦርቶ
የ55ኛ ዓመት የምስረታ በዓል 3 ኛ መርኀ ግብር በቅርቡ የምናሳውቅ ይሆናል:: ሁለተኛው መርኀ ግብር በከፊል ይህን ይመስል ነበር፡፡ ከፎቶማኀደር ፤ ዐውደ ጥናት ( ርዕስ ክርስቲያናዊ ጋብቻ ፣ ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ እና የልጆች አስተዳደግ ) ቅዳሜ ሰኔ 26 ፣ 2013 ዓ.ም ::

#የሁልጊዜም አገልጋያችን የሆነው ወንድማችን መ/ር ኢዮብ በቀለ ሰኔ 27/2013 ዓ.ም "ዕፀ ዘዌ" የተሰኘው መጽሐፉን በገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ ሰ/ት/ቤት አዳራሽ አስመርቋል:: #በብጹእ አቡነ ፊልጶስ የተፈረመበትን መጽሐፉንና የምስጋና ምስክር ወረቀትም አበርክቶልናል ፡፡ አገልጋያችን ን እና ወንድማችንን እጅግ አድርገን እያመሰገንህ ቀሪው የአገልግሎት ዘመንህ መልካም እንዲሆንልህ ሰ/ት/ቤታችን እየተመኘ ምእመናን መጽሐፉን በመግዛት ለሕይወታችሁ ስንቅ እንድትይዙ እንላልን:: ወላዲተ አምላክ አገልግሎትክን ትባርክ ꔰ ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ꔰ

ዛሬ 9፡30 ማንም እንዳይቀር የ55ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ሁለተኛ መርሃ ግብር #ዐውደ_ጥናት 1. እጮኛ አለዎት ወይም ለመያዝ አስበዋል? የእጮኝነት ሕይወትዎ ለትዳር እንዲበቃ በክርስቲያናዊ መንገድ
ዛሬ 9፡30 ማንም እንዳይቀር የ55ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ሁለተኛ መርሃ ግብር #ዐውደ_ጥናት 1. እጮኛ አለዎት ወይም ለመያዝ አስበዋል? የእጮኝነት ሕይወትዎ ለትዳር እንዲበቃ በክርስቲያናዊ መንገድ እንዴት መጓዝ እንዳለብዎት ያውቃሉ? ከእጮኝነት ጀምሮ ክርስቲያናዊ ሕይወትን እንዴት መለማመድ ይቻላል? ይምጡ ለእነዚህና መሰል ጥያቄዎቾ በዐውደ ጥናቱ በቂ ምላሽ ያገኛሉ። 2. የትዳር ሕይወትዎ እንዴት ነው ኦርቶዶክሳዊ መዐዛ አለው? በቤታችሁ ያለችው ትንሽዋ ቤተ ክርስቲያን ተዘግታለች ወይስ አገልግሎት እየሰጠች ነው? ትዳርዎ ጠንካራ መሠረት እንዲኖረው ምን እያደረጉ ነው? ትዳርዎ አደጋ እንዳንዣበበበት ይሰማዎታል? የእርስዎ እና የትዳር አጋርዎ መንፈሳዊ ሕይወት እኩል አለመራመዱ አሳስብዎታል?ይምጡ ለእነዚህና መሰል ጥያቄዎቾ በዐውደ ጥናቱ በቂ ምላሽ ያገኛሉ። 3. የወለዱዋቸው ልጆች ምክርዎን ይሰማሉ? ወይስ በራሳቸው መንገድ ነው የሚጓዙት? ልጆችዎን በኦርቶዶክሳዊ መንገድ እንዴት መቅረጽ እንዳለብዎ ያውቃሉ? ልጆችዎ ላይ እንዴት በጎ ተጽእኖ ማሳደር እንደሚችሉስ? ይምጡ ለእነዚህና መሰል ጥያቄዎቾ በዐውደ ጥናቱ በቂ ምላሽ ያገኛሉ። 4. ልጆችዎ ከመስመር የመውጣት አዝማሚያ ሲያሳዩ እንዴት እንደሚመልሷቸው ምን ያስባሉ? ክር፣ ከልጆችዎ ጋር አወንታዊ ንግግር እንዴት ማድረግ እንዳለብዎ ያውቃሉይት? ይምጡ ለእነዚህና መሰል ጥያቄዎቾ በዐውደ ጥናቱ በቂ ምላሽ ያገኛሉ። 5. ከዐውደ ጥናቱ ርዕሰ ጉዳይ ጋር የተገናኙ ጥያቄዎችዎን ይላኩልን፣ በዕለቱ ምላሽ ይሰጥባቸዋል።