en
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Open in Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 395 subscribers, ranking 5 567 in the Religion & Spirituality category and 2 182 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 395 subscribers.

According to the latest data from 27 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 5 over the last 30 days and by 20 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 21.05%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 10.41% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 240 views. Within the first day, a publication typically gains 1 602 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 17.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 28 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

15 395
Subscribers
+2024 hours
+257 days
+530 days
Posts Archive
ሰኔ 21 ሰኔ ጐልጐታ ወሕንፀተ ቤተክርስቲያን እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ለቅድስተ ቅዱሳን ለድንግል ማርያም ሰኔ ጐልጐታና ሕንፀተ ቤተ ክርስቲያን (ለመጀመሪያ ጊዜ ቤተ ክርስቲያን ለታነጸበት) ክብረ በዓል በሰላምና በጤና አደረሰን አደረሳችሁ፡፡ ✤✤ ሰኔ ጎልጎታ፤ ‹‹ሰኔ ጐልጐታ፤ ችግር የምትፈታታ፡፡›› ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያም በዚህች ቀን (ሰኔ 21) ልጇን ወዳጇን ጐልጐታ በሚባል ቦታ ላይ እንባዋ እንደ ጅረት እስኪፈስ ድረስ ለኃጥአን ምሕረትን ለምናዋለች:: ጌታችንም ‹‹ስምሽን የጠራውን፤ በቃል ኪዳንሽ ያመነውን ሁሉ እምርልሻለሁ፡፡›› ብሎ ቃል ኪዳን ሰጥቷታል፡፡ ሰኔ ጐልጐታን ተመልከት ✤✤ ሕንፀተ ቤተ ክርስቲያን፤ ሰኔ 21 ከእመቤታችን #33ቱ በዓላት አንዱ ሲኾን፤ ሕንጸተ ቤተክርስቲያን ይባላል፡፡ በሐዲስ ኪዳን የመጀመሪያዋ ቤተክርስቲያን በአምላክ እናት ስም የታነጸችው በዚሁ እለት በሰኔ 20 ቀን ነው፡፡ አናጺውም ደግሞ እራሱ ባለቤቱ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን፤ ቦታው በፊልጵስዩስ ነው፤ ቤተክርስቲያኗ የተሰየመችው ደግሞ በእመቤታችን ስም ነው፤ ጥንተ ነገሩስ (ታሪኩ) እንደምን ነው ቢሉ፤ ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና አምላካችን መደኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርቱን ‹‹ሑሩ ወመሐሩ ኵሎ አሕዛበ፤ አሕዛብን ሁሉ ሒዱና አስተምሩ፡፡›› /ማቴ. 28፥19/ ባላቸው ቃል መሠረት ሐዋርያት በወንጌል ያርሷት ዘንድ በዕጣ ተካፍለዋታል:: የሰው ልጅ ድኅነቱ የሚፈጸመው ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ሲቀበል ነውና (ዮሐ. 6፥ 56) አበው ሐዋርያት ቊርባንን በተመረጡ ሰዎች ቤት እያዘጋጁ ቀድሰው ያቆርቡ ነበር:: በመጀመሪያ በጽርሐ ጽዮን፣ቀጥሎም በተለያዩ ሰዎች ቤት እንዲህ ይከናወን ነበር፡፡ ለጸሎት ሥራ ደግሞ አንዳንዴ ምኵራበ አይሁድን ይጠቀሙ ነበር:: እየቆየ ሲሔድ ግን ከአሕዛብ ያመኑ ሰዎች ቊጥር እጅጉን በመብዛቱ /በተለይ ቅዱስ ዻውሎስ ያሳመናቸው ለጸሎት እያሉ ወደ ጣዖት ቤት መግባት አመጡ::/ በዚህ ምክንያት መምህራን ሕዝቡን ‹‹ካመናችሁ በኋላ እንዴት ወደ ጣዖት ቤት ትገባላችሁ?›› ቢሏቸው ‹‹እኛ ምን እናድርግ! የምንጸልይበት ቤት የለን››ሲሉ መለሱላቸው:: ነገሩ ሲያያዝ ከደጋጉ ሐዋርያት ዻውሎስና በርናባስ ደረሰ:: ወዲያውኑ አንዳንድ ወንድሞች ቤት ‹‹ለምን አናንጽም?›› ብለው ነበር:: ቅዱስ ዻውሎስ ግን ‹‹ሊቀ ሐዋርያቱ ሳይፈቅድ አይሆንም›› አለ:: (ለዚህ ነው ዛሬም ሊቀ ዻዻስ ካልፈቀደ ቤተክርስቲያን የማይታነጸው፡፡) ከዚያ ቅዱሳን ዻውሎስና በርናባስ ሐዋርያቱ ወዳሉበት ሔደው ነገሩን ለቅዱስ ዼጥሮስ አስረዱ:: ሊቀ ሐዋርያቱ ቅዱስ #ዼጥሮስም ‹‹የጌታችን ፈቃዱመኾኑን እናውቅ ዘንድ ተያይዘን ሱባዔ እንግባ›› ብሎ አዋጅ ነገረ:: በዓለም ያሉ ክርስቲያኖች ሁሉ በአንድ ልብ ሱባዔ ገቡ:: በሱባዔያቸው መጨረሻም ክብር ይግባውና ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በኪሩቤል ጀርባ ላይ ሆኖ እልፍ አእላፍ መላአክትን አስከትሎ በግርማ ወደ እነርሱ ወረደ፤እመቤታችን በቀኙ ነበረች፡፡ ኹሉንም ሐዋርያት በሩቅም በቅርብም ያሉትን ደቀ መዛሙርቱን በደመና ጠቅሶ ፊልጵስዩስ በሚባል ሃገር ሰበሰባቸው፡፡ ከዚያም በስተምሥራቅ ከከተማ ወጣ ወዳለ ሥፍራ ወሰዳቸው፡፡ በዚያም ተራርቀው የነበሩ 3 ደንጊያዎች ነበሩ፡፡ 3ቱንም ድንጋዮችን በተአምራት አቀራርቦ አንሥቶ ጎተታቸው፡፡ ድንጋዮቹም እንደሰም ተለጠጡ፣ እንደ ግድግዳም ሆኑ፡፡ ቁመቱን ወርዱን መጥኖ ለሐዋርያቱ ሰጣቸው፡፡ እነርሱም እሳት እንዳየው ሰም በእጃቸው እየለመለሙ (እየሳቡ) ቁመቱን 24፥ ወርዱን 12 ክንድ አድርገው ዕጽብት፥ ግርምት የምትኾን 3 ክፍል ያላትን የመጀመሪያዋን ቤተክርስቲያን በ52 ዓ/ም ሰኔ 20 ቀን አነጹ፡፡ ዳግመኛም የብርሃን ምሰሶ ወረደ፤ ጌታችንም በሰማያዊቷ ኢየሩሳሌም አምሳያ አድርጎ አነጻት፤ ሁለንተናዋም ተጠናቀቀ፡፡ ከዚህም በኋላ ጌታችን ለሐዋርያቱ ‹‹እንግዲህ እናንተም እንዲህ አድርጋችሁ ሥሩ፡፡›› ብሏቸው ዐረገ፡፡ ✜ በማግስቱ ሰኔ 21 ዕለት ደግሞ ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አእላፍ መላእክትን፣ ሰማያውያን ቅዱሳንን እና እናቱን ቅድስት ድንግል ማርያምን ይዞ ወረደ:: ሐዋርያቱ አብዛኞቹ እዛው ሲጸልዩ አድረው ነበርና ጌታችን ከቅዳሴው በፊት 2 ነገሮችን አሳየ፤ አስቀድሞ ቤተክርስቲያኗን በድንግል እናቱ ስም አክብሮ ሥርዐተ ቤተክርስቲያንን አሳየ:: ቀጥሎ ደግሞ ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስን ከመካከል አቁሞ ‹‹አርሳይሮስ›› ሲል ሾመው:: ይኼውም የዓለም ሁሉ ሊቀ ዻዻሳት (ፓትርያርክ) ማለት ነው:: በዚህ ጊዜ ቅዱሳን መላእክት ‹ ‹‹አክስዮስ››(አክዮስ)እያሉ 3 ጊዜ አሰምተው ጮሁ:: አክዮስ ማለት በግዕዙ ‹‹ይደልዎ›› በአማርኛው ደግሞ ‹‹ይገባዋል፤ ያስምርለት›› እንደ ማለት ነው:: ጌታችን ይህን ከከወነ በኋላ ይቀድስ ዘንድ ጀመረ:: አማናዊት ማኅደሩን ድንግል ማርያምን መንበር አድርጎ፣ ቅዱስ ጴጥሮስ እንደ ተራዳኢ ካህን ቆሞ፣ ቅዱስ እስጢፋኖስ ሠራኢ ዲያቆን ኾኖ፣ ሐዋርያት ድንግልን ከበው፣ መላእክተ ብርሃን በክብራቸው ቆመው ጌታችን ቀድሶ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ለወዳጆቹ አቀበለ:: በዚያች ዕለት በፍጡር አንደበት ተከናውኖ ሊነገር የማይችል ደስታ ተደረገ:: ከቅዳሴ በኋላ ጌታችን ሐዋርያትን አዘዛቸው:: ‹‹ከዚህ ቀን ጀምሮ በመላው ዓለም በእናቴ በማርያም ስም አብያተ ክርስቲያናትን አንጹ፤ ይህችን እለት የሚያከብራትን አከብረዋለሁ::›› ብሏቸው ከድንግል እናቱና ከመላእክቱ ጋር ዐረገ:: ✤✤ ሥርዐተ ማኅሌቱ እንደየደብራችሁ ይትበሃል ትጠሙበበት ዘንድ አስቀምጠንላችኋል፤ ✼ የድንግል እመቤታችን ልመናዋ ክብሯ፣ ጣዕመ ፍቅሯና በረከቷ በሁላችን ላይ ይደርብን:: አሜን! /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ፤ ትምሕርት ዋና ክፍል ፥ ንዑስ ክፍል /ሕትመት እና ሚዲያ/ የተዘጋጀ :: ꔰ #share Contact: https://t.me/finotehiwot1927 .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot .YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w www.finotehiwotsundayschool.com ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ት.ቤት . Telegram (https://t.me/finotehiwot1927)

ሰኔ ፲፯፤ በዓለ አባ ገሪማ (ይስሐቅ) ዘመደራ፡፡አባ ገሪማ የተሠወሩበት( ሰኔ ፲፯) #በዓለም ላይ በእድሜ ረጅም ዓመታት (ከ1500ዓመታት በላይ) ያስቈጠረውን የብራና ወንጌል ጽፈው ያቆዩልን፤ #ዓድዋ የሚለውን ስያሜ ያወጡ፤ #አሁንም ድረስ ከደረቅ ዓለት ላይ ጠበል እንዲፈልቅ ቃል ኪዳን የተሰጣቸው፤ ሂዳችሁ እዩ!! #በአንድ ቀን ዘርተው ለ9 ሰዓት ቅዳሴ መሥዋዕት ያደረሱ፤ በዚህና በሌሎች ምግባሮቻቸው ወንድሞቻቸው የሚኾኑ ቅዱሳን ሳይቀር ገሪማ ገረምከን ብለው የመሰከሩላቸው፤ *#የኢትዮጵያ ታሪክን የያዘ ታላቁን መደራ ገዳም የመሠረቱ፤ የታላላቅ የአድዋ ጀግኖቻችን መሪያቸው ራስ አሉላ አባ ነጋን ጨምሮ አጽማቸው ያረፉበት ነው፡፡ (ክብረ በዓላቸው በዓድዋ በሚገኘው ገዳማቸው፣ በጎንደር ተክለሃይማኖት፣ በአዲስ አበባ ካራአሌ መድኀኔዓለም ወአቡነ ገሪማ ገዳም) #አባ_ገሪማ_(ይስሐቅ)#ዘመደራ በአልአሜዳ ዘመነ መንግሥት በ፬፻፹ ዓ.ም ወደ አገራችን ወደ ኢትዮጵያ በሃይማኖት ምክንያት ከሶርያና ከታናሽ እስያ ተሰደው ከመጡት ተስዓቱ (ዘጠኙ) ቅዱሳን መነኮሳት (አባ አሌፍ፣ አባ አረጋዊ፣ አባ አፍጼ፣ አባ ሊቃኖስ፣ አባ ገሪማ፣ አባ ጉባ፣ አባ ይምአታ፣ አባ ጰንጠሌዎን እና አባ ጽሕማ) መካከል በትምህርታቸው የላቁ፣ ቅዱስ ያሬድ በድጓው (በመዝሙር)፣ በዝማሬና በመዋሥዕት ድርሰቱ ውስጥ ‹‹ገሪማ ገረምከኒ አስኬማከኒ አልባቲ ሙስና፤ አባ ገሪማ አስገረምኸኝ፡፡ ለምንኵስናህም እንከን የለባትም›› በማለት የደረሰላቸውና አድዋ የሚለውን ስያሜ የሰየሙ፣ በዓለማችን ላይ እስካሁን ከተገኙት የብራና ወንጌሎች መካከል በእድሜው ረዥሙንና ባለሠንጠረዡን /ከ1400ዓመታት በላይ/ የጻፉ፣ እስከ አሁንም ድረስ የሚያስደንቅ ከደረቅ ዓለት ላይ እንደ እንባ የሚወጣው ፈዋሽ ጠበል ያፈለቁ አባ ገሪማ ዘመደራ ናቸው፡፡ እነዚህ ዘጠኙ ቅዱሳን በመላው ኢትዮጵያ ተዘዋውረው ወንጌልን ሰብከዋል፤ በወቅቱ ብሔራዊ ቋንቋ የነበረዉን ግእዝን በሚገባ አጥንተው ቅዱሳት መጻሕፍትን ከሱርስትና ከጽርዕ ቋንቋዎች ወደ ግእዝ ተርጕመዋል፡፡እንደዚሁም ገዳማትንና አብያተ ክርስቲያናት አሳንጸዋል፡፡ ቤተ ክርስቲያናችንም ከፈጸሟቸው መንፈሳውያን ተልእኮዎች፣ ካደረጓቸው ተአምራትና መልካም ሥራዎች አኳያ ቅዱሳን በሚል መዓርግ ትጠራቸዋለች፤ በስማቸውም ጽላት ቀርፃ በዓላቸውን ታከብርላቸዋለች፡፡ የአባ #ገሪማ አባት መስፍንያኖስ የሮም አገር ንጉሥ ነበረ፤ ሚስቱም ሰፍንግያ ትባላለች፡፡ መካን ስለነበረች በቅድስት #ድንግል_ማርያም ስም በመማጸን ልጅ እንዲሰጣት እግዚአብሔርን ስትለምን ከኖረች በኋላ ወንድ ልጅ ወለደች፤ስሙንም ይስሐቅ አለችው፡፡ የያን ጊዜው ይስሐቅ የኋላው አባ ገሪማ በመንፈሳዊ ሥርዓት ካደገ በኋላም የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ተምሮ በዲቁና ማገልገል ጀመረ፡፡ ይስሐቅ ወላጅ አባቱ ሲሞትም በአባቱ ዙፋን ተተክቶ ለሰባትዓመታት ሮምን በንጉሥነት ሲያስተዳድር ከቆየ በኋላ በዋሻ ይኖሩ የነበሩት አባ ጰንጠሌዎን ዘጾማዕት ‹‹ይስሐቅ ሆይ፣ ሙታኖቻቸውን ይቀብሩ ዘንድ ሙታንን ተዋቸውና የማያልፈዉን የክርስቶስን መንግሥት ትሻ ዘንድ ወደ እኔ ና›› ብለው መልእክት ላኩበት፡፡ መልእክቱ እንደ ደረሰውም መንግሥቱን ትቶ በሌሊት ወደ አባ ጰንጠሌዎን ሲሔድ ቅዱስ ገብርኤል ተገልጾ በብርሃናውያን ክንፎቹ ተሸክሞ ዐሥር ወር የሚወስደዉን መንገድ በሦስት ሰዓታት አስጉዞ ከአባ ጰንጠሌዎን በዓት አደረሰው፡፡አባ ይስሐቅ (አባ ገሪማ) በአባ ጰንጠሌዎን እጅ ከመነኰሱ በኋላ በጾም፣ በጸሎትና በስግደት ተጠምደው ቆዳቸው ከዐፅማቸው እስኪጣበቅ ድረስ ተጋድሎ ሲፈጸሙ ቆዩ፡፡ ከዚያ በኋላ ወደ መደራ ሔደው በእግዚአብሔር ኃይል ድንቆችንና ተአምራትን እየያደረጉ፣ በሽተኞችን እየፈወሱ፣ አጋንንትን እያስወጡ ብዙ ዓመታት ኖሩ፡፡ ካደረጓቸው ተአምራት መካከልም በጠዋት ሥንዴ ዘርተው፣ በሠርክ ሰብስበው መሥዋዕት ካሳረጉ በኋላ በማግሥቱ ከግራር ዛፍ ላይ በሬዎችን አውጥተው ሥንዴዉን አበራይተው ሰባ ሰባት የእንቅብ መሥፈሪያ መሰብሰባቸው አንደኛው ሲኾን፤ በዓለት ላይ የተከሏት ወይን ወዲያው በቅላ፣ አብባ ፍሬ እንድታፈራ ማድረጋቸውና በወይኑም መሥዋዕት ማሳረጋቸው ደግሞ ሌላኛው ተአምር ነው፡፡ #አባ ገሪማ መጽሐፍ እየጻፉ ሳሉ #ፀሐይ ሊጠልቅ በተቃረበ ጊዜ ጸሎት አድርሰው ጽሕፈታቸዉን እስኪፈጽሙ ድረስ እንደ ኢያሱ #ፀሐይን_በቦታው እንዲቆም ማድረጋቸውም በመጽሐፈ ስንክሳር ተመዝግቧል፡፡ ከእጃቸው የወደቀው ብርዕ ወዲያው በቅሎ፣ አቈጥቍጦ እንደ አደገ፤ ምራቃቸዉን ትፍ ያሉበት ሥፍራም እስከ ዛሬ ድረስ ሕሙማንን እንደሚፈውስ መጸሐፈ ስንክሳር ይናገራል፡፡ በአንዲት ዕለትም መቅኑናቸውን ተቀብለው ከመነኮሳት ጋር ሲሔዱ መንገድ ላይ ቤተ ክርስቲያን አግኝተው ሲጸልዩ ካህናቱ ቅዳሴ እንዲያሟሉላቸው ጠየቋቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ሌሎቹ ምግብ በልተው ነበርና ‹‹አንችልም›› ሲሉ አባ ይስሐቅ ምግብ አልተመገቡም ነበርና መቅኑናቸዉን አስቀምጠው ቅዳሴውን አሟሉ፡፡ ባልንጀሮቻቸው ግን በልተው የቀደሱ መስሏቸው ወደ አባ ጰንጠሌዎን መጥተው ‹‹ቀሲስ ይስሐቅ ከበላ በኋላ ቀደሰ›› ብለው ከሰሷቸው፡፡ አባ ጰንጠሌዎንም አባ ይስሐቅ ሲመለሱ ‹‹የምጠይቅህ ምሥጢር ስላለኝ ሰዎችን ከአጠገብህ ገለል አድርጋቸው›› ሲሏቸው አባ ይስሐቅም ‹‹ሰዎች ብቻ ሳይኾኑ ዕንጨቶችና ድንጋዮችም ገለል ይበሉ›› ብለው መለሱላቸው፡፡ ወዲያዉኑም ዕንጨቶችና ድንጋዮች አንድ ምዕራፍ ያህል ከቦታቸው ሸሹ፡፡ በዚህ ጊዜ አባ ጰንጠሌዎን ‹‹ኦ ወልድየ ይስሐቅ ገረምከኒ፤ ልጄ ይስሐቅ ሆይ! ገረምኸኝ›› እያሉ አደነቋቸው፡፡ አባ ገሪማን ሳያዉቁ የከሰሷቸው መነኮሳትም ይቅርታ ጠይቀዋቸዋል፡፡ አባ ገሪማ ተብለው መጠራት የጀመሩትም ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ነው፡፡ ይህንን መሠረት በማድረግ ‹‹#ገሪማ_ገረምከኒ_አስኬማከኒ_አልባቲ_ሙስና፤ አባ ገሪማ አስገረምኸኝ፡፡ ለምንኵስናህም እንከን የለባትም›› በማለት #ቅዱስ_ያሬድ በመዝሙሩ አመስግኗቸዋል፡፡ ከዚያም በትግራይ ክፍለ ሀገር ልዩ ስሙ መደራ ከሚባል ቦታ ገብተው በዓት ሠርተው ለ፳፫ ዓመታት በትኅርምት ኖረው መልካም ተጋድሏቸውንና የቀና አካሔዳቸዉን በፈጸሙ ጊዜ ክብር ይግባውና ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰኔ ፲፯ ቀን ተገልጦ ስማቸውን የሚጠሩትን፣ መታሰቢያቸዉን የሚያደርጉትን፣ ገድላቸዉን የሚጽፉ፣ የሚያነቡና የሚተረጕሙትን፣ ቤተ ክርስቲያን የሚያንጹትንና የሚያገለግሉትን ስማቸውን በሕይወት መጽሐፍ እንደሚጽፍላቸው ቃል ኪዳን ሰጥቷቸዋል፡፡ አባ ገሪማም ይህንን ታላቅ ሀብት የሰጣቸዉን እግዚአብሔርን አመስግነው ከተደሰቱ በኋላ በብርሃን ሠረገላ ተነጥቀው #ብሔረ_ሕያዋን ገብተዋል፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን በተለይ በገዳማቸው በመደራ አባ ገሪማ የተሠወሩበት ሰኔ ፲፯ ቀን በየዓመቱ በድምቀት ይከበራል፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይኹን፡፡ እኛንም በጻድቁ ጸሎት ይማረን፤ በረከታቸዉም ከእኛ ጋር ትኑር፤ ለዘለዓለሙ አሜን፡፡ ሰአል ለነ አባ ገሪማ፤ ꔰ ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ꔰ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ፤ ትምሕርት ዋና ክፍል ፥ ንዑስ ክፍል /ሕትመት እና ሚዲያ/ የተዘጋጀ :: ꔰ

በአርብ ጉባኤ | ፀሎት ፣ ዝማሬ ፣ ትምሕርት(ለተከታታይ 3 ሳምንታት በተጠቀሰው ርእስ)
በአርብ ጉባኤ | ፀሎት ፣ ዝማሬ ፣ ትምሕርት(ለተከታታይ 3 ሳምንታት በተጠቀሰው ርእስ)

መርዓዊ ደብረ ኀይል ቅዱስ ሚካኤል ባሕር ዳር ድባንቄ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል አዘዞ አይራ ቅዱስ ሚካኤል 40. ዛራ ቅዱስ ሚካኤል (ባሕር ዳር አጠገብ ሐሙሲት) ጉመር ደብረ ኅሩያን ቅዱስ ሚካኤል ካምባ ቅዱስ ሚካኤል ሳንቃ ወይራ ቅዱስ ሚካኤል ዳስ ዓምባ ቅዱስ ሚካኤል 45. ላሐ ቅዱስ ሚካኤል 46. ጊራራ ቅዱስ ሚካኤል 47. መለኮዛ ቅዱስ ሚካኤል 48. ዋይሎ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል

አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ኮተቤ፥ ካራ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ኮተቤ (ካራ) ፴፰. ረቢ መካነ ጎልጎታ መድኃኔ ዓለም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ካራ ቆሬ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ አራዳ → አለም ባንክ → ካራቆሬ (ረጲ)፡፡ ፴፱. ፉሪ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ጋራ ኦዳ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ጋራ ኦዳ፡፡ ፵. ሐመረ ወርቅ ማርያምና አርሴማ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ወርቁ ሰፈር፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ቃሊቲ → ወርቁ ሰፈር፡፡ ፵፩. ቶታል ደብረ ገነት ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ሰፈረ ገነት፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መርካቶ) → ሰፈረ ገነት፡፡ ፵፪. ቦሌ ቡልቡላ ምስካበ ቅዱሳን አባ ሳሙኤል ዘዋልድባና ቅዱስ አማኑኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ቡልቡላ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ሳሪስ አቦ → ቡልቡላ መድኀኔ ዓለም (ኮንዶሚኒየም)→ ወደ ላይ በአስፓልቱ የ5 ደቂቃ የእግር መንግድ፡፡ ወይም፤ ከቦሌ መድኃኔ ዓለም → ቡልቡላ (በአዲሱ መንገድ) ፵፫. አቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔ ዓለም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ አቃቂ፥ ጋራው መድኃኔዓለም፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ቃሊቲ → አቃቂ፡፡ ፵፬. ሣሎ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ሣሎ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ቃሊቲ → ሣሎ፡፡ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከበርባቸው_ጥንታውያን #፲፱ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. #እየላ_ቅዱስ_ሚካኤል፤ (#የ3 #ሺህ_ዓመታት_ባለታሪክ፤ ከታቦተ ጽዮን ጋራ በ980 ከክ.ል.በ. ታቦቱ የመጣ፤ መሥዋዕተ ኦሪት ይቀርብበት የነበረ፤ አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን መጥቶ የባረከው) ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ላሊበላ → ግዳን (እየላ)፡፡ ፪. ሰሜን ትግራይ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል፤ (መሥዋዕተ ኦሪት ይቀርብበት የነበረ) አድራሻው፤ ሰሜን ትግራይ ሀገረ ስብከት፥ ሰሜን ትግራይ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎሃ ጽዮን ወይም ደብረ ማርቆስ በሚለው መኪና ዐባይ በረሃ ላይ መውረድ፤ ፫. ጎሐ ጽዮን ቅዱስ ሚካኤል፤ (በ4ኛው ክፍለ ዘመን በአብርሃ ወአጽብሃ ዘመን የተሠራ) አድራሻው፤ ሰሜን ሸዋ ሰላሌ ፍቼ ሀገረ ስብከት፥ ጎሐ ጽዮን፥ ዐባይ በረሃ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎሃ ጽዮን ወይም ደብረ ማርቆስ በሚለው መኪና ዐባይ በረሃ ላይ መውረድ፤ ፬. ሸኖ ጎልባ ደብረ ሣሕል ቅዱስ ሚካኤል ደብር፤ (በአብርሃ ወአጽብሃ ዘመን የተመሠረተ) አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ሰኖ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ሸኖ፡፡ ፭. መላሃይዘንጊ ቅዱስ ሚካኤል፤ (በ8ኛው ክፍለ ዘመን የታነጸ) አድራሻው፤ ሰሜን ሸዋ ሰላሌ ፍቼ ሀገረ ስብከት፥ ጎሐ ጽዮን፥ ዐባይ በረሃ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎሃ ጽዮን ወይም ደብረ ማርቆስ በሚለው መኪና ዐባይ በረሃ ላይ መውረድ፤ ፮. ላስታ ላሊበላ ቤተ ሚካኤል፤ (በ11ኛው ክፍለ ዘመን በቅዱስ ላሊበላ የታነፀ፥ ከ11ዱ የላስታ ላሊበላ ፍልፍል ሕንጻዎች አንዱ) አድራሻው፤ ላስታ ሀገረ ስብከት፥ ላሊበላ ከተማ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ላሊበላ፡፡ ፯. ገርዓልታ ዋሻ ቅዱስ ሚካኤል፤ አድራሻው፤ ትግራይ ሀገረ ስብከት፥ ገርዓልታ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → መቀለ → ገርዓልታ፡፡ ፰. ሚካኤል ዓምባ፤ (በ11ኛው ክፍለ ዘመን የታነጸ) አድራሻው፤ ትግራይ ሀገረ ስብከት፥ ውቅሮ፥ (በመቀለና በአዲግራት መሃል)፥ አጽቢ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ውቅሮ → አጽቢ፤ ፱. ባሕር ዳር ሽምብጥ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ (በ13ኛው ክፍለ ዘመን የተመሠረተ) አድራሻ፤ ምዕራብ ጎጃም ባሕር ዳር ሀገረ ስብከት፥ ባሕር ዳር ከተማ፥ ቀበሌ 13 ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ባሕር ዳር ከተማ → ሆስፒታል በሚል ታክሲ (ዲፖ ጋር)፡፡ ፲. እስቴ አበርጉት ቅዱስ ሚካኤል ፤ (በአፄ ዓምደ ጽዮን ዘመነ መንግስት በልጃቸው በአቡነ ፊልሞና የተሠራ ታሪካዊ ጠበል ያለበት) አድራሻ፤ ደቡብ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ እስቴ ወረዳ፥ ደስኳ አጋማች ቀበሌ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → እስቴ፡፡ ፲፩. በሮ ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል፤ በ16ኛው መ/ክ/ዘመን መጨረሻ የተመሠረተ አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት፥ ሳይንት ወረዳ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ → አማራ ሳይንት፡፡ ወይም፤ ከጎጃም በመርጠሉ ማርያም → አማራ ሳይንት ፲፪. ጎንደር ፊት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ በአፄ ፋሲለደስ ዘመነ መንግሥት ተመሠረተ፤ አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር፡፡ ፲፫. ጎንደር አጣጣሚ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር፡፡ ፲፬. ተንታ ደብረ ብርሃን ቅዱስ ሚካኤል፤ (ንጉሥ ሚካኤል በሚያስደንቅ ሁኔታ ያሠሩት) አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት፥ አምባሰል፥ ተንታ ወረዳ፥ ጠዓት ቀበሌ፥ እሜገኝ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ጻድቃኔ፡፡ ፲፭. አጃና ቅዱስ ሚካኤል፤ (በቀስተ ደመና ጠበል አጥማቂው) አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ተጉለት፥ አጃና፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ጻድቃኔ → አጃና፡፡ ፲፮. ቦንብ አርግፍ ቅዱስ ሚካኤል (ሰሜን ወሎ ሀ/ስብከት፤ የጁ ወልዲያ) ፲፯. ቦረዳ ቅዱስ ሚካኤል ፲፰. ዋሻ ቅዱስ ሚካኤል (ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፣ ኢቲሳ) ፲፱. አንኮበር ቅዱስ ሚካኤል (ሰሜን ሸዋ ሀ/ስብከት) ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከበርባቸው_ #፵፰ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ 1.. ግሸን ደብረ ከርቤ ቅዱስ ሚካኤል ጎሚስታው ሚካኤል (ትግራይ) እንዳ ቅዱስ ሚካኤል (ትግራይ) መቀለ ቅዱስ ሚካኤል 5. ጾረና ቅዱስ ሚካኤል (ኤርትራ) ዓለም ገና ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ደብረ ዘይት /ቢሾፍቱ/ ደብረ አሚን ቅዱስ ሚካኤል ዱከም ቅዱስ ሚካኤል ናዝሬት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል 10. ድሬዳዋ ቅዱስ ሚካኤል ጭሮ አሰበ ተፈሪ ቅዱስ ሚካኤል (ድሬዳዋ፥ አሰበ ተፈሪ) ሻሸመኔ ቅዱስ ሚካኤል አርባ ምንጭ ላከ ኢየሱስና ሚካኤል ዲላ ቅዱስ ሚካኤል 15. አሰላ ደብረ ሰላም ቅድስ ሚካኤል ጂጂጋ ቅዱስ ሚካኤል ሚዛን ቴፒ ደብረ ኀይል ቅዱስ ሚካኤል ቦንጋ ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ኢሉባቦር ሌንቃ ቅዱስ ሚካኤል 20. እነሞርና ኤነር ወረዳ ቅዱስ ሚካኤል (ጉራጌ ሀ/ስብከት) አሰቦት ደብረ ወገግ ቅዱስ ሚካኤል (ምሥ. ሀረርጌ ሀ/ስብከት) ሽንቁሩ ቅዱስ ሚካኤል ኩክ የለሽ ዛሪያ ቅዱስ ሚካኤል ጅሩ ሞቶሎኒ ቅዱስ ሚካኤል (ጅሩ አርሴማ ውስጥ) 25. መንዝ ይገም ቅዱስ ሚካኤል መሐል ሜዳ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል የሲጠር ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል (መንዝ ቀያ ገብርኤል ወረዳ) ወንጪት ቅዱስ ሚካኤል (በነብር የሚጠበቅ) ሸዋሮቢት ጫሬ ቅዱስ ሚካኤል 30. ወልዲያ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ኮምቦልቻ ቅዱስ ሚካኤል ደሴ ጢጣ ደብረ ሲና ቅዱስ ሚካኤል ራያ ቆቦ ቅዱስ ሚካኤል ደብረ ማርቆስ ዋሻው ቅዱስ ሚካኤል 35. ደብረ ማርቆስ አጠገብ ብዕርና ቅዱስ ሚካኤል ደምበጫ ቅዱስ ሚካኤል

#በአዲስ_አበባ_የሚከብርባቸው_ #፵፬ #ገዳማትና_አድባራት፡፡፡(አቅጣጫ ምንጭ ፤ ዋሊ ገጽ) ፩. የካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (በኦሪት ዘመን መሥዋዕተ ኦሪት ይሰዋበት የነበረ፥ ዋሻ ቤተ ክርስቲያኑ በ4ኛው ክ/ዘመን በአብሃ ወአጽብሃ ዘመን የተመሠረተ) አድራሻው፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ሾላ መገናኛ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(4 ኪሎ) → ሾላ መገናኛ፤ ፪. አንቀጸ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (ራስ ካሳ ሚካኤል) (ጭቁኑ)፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ራስ ካሳ ታክሲ፤ ከ4ኪሎ(ከ6 ኪሎ) → ፈረንሳይ፡፡ ፫. ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (አዲሱ ሚካኤል) አድራሻ፤ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ፥ አውቶቡስ ተራ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(4ኪሎ) → አውቶቡስ ተራ፡፡ ፬. አፍሪካ ኅብረት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (ወህኒ ቤት) (ከርቸሌ) አድራሻ፤ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ፥ ቡልጋርያ (ከርቸሌ) (አፍሪካ ኅብረት)፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ቄራ፡፡ ፭. ኮተቤ (ሲኤምሲ) ደብረ ጽባሕ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ /ሳጠራው/ (ቀድሞ ኮተቤ አሁን ሲኤምሲ) አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ካራ አሎ ፥ አባዶ አጠገብ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ሲኤምሲ፡፡ ፮. መካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ መካኒሳ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → መካኒሳ፡፡ ፯. ላፍቶ ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ላፍቶ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ላፍቶ፡፡ ፰. ቤተል ደብረ ኢዮር ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ቤተል፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ጦር ኃሎች → አየር ጤና፡፡ ወይም፤ ከፒያሳ ሸዋ ዳቦ ቤት → አለም ባንክ/ኤር ጤና/፡፡ ፱. ኤረር በር መካነ ሰላም ቅዱስ ሚካኤልና ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ጎሮ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ (ፒያሳ) → ጎሮ፡፡ ፲. መንበረ ክብር ቅዱስ ሚካኤል ወአቡነ ተክለ ሃይማኖትና ቅድስት አርሴማ ገዳም፤ አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ ቀጨኔ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(ከመርካቶ)(ከአዲሱ ገበያ) → ቀጨኔ፡፡ ፲፩. አያት ጨፌ ኢያሪኮ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ (በ1980ዓ.ም ጽላቱ ከነ ድርሳናቱ ተቀብሮ የተገኘበት) አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ወረዳ 9፥ ጎሮ ሰፈር፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ጎሮ፡፡ ፲፪. ካራ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ሚካኤል፥ 24ቱ ካህናተ ሰማይና ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አባዶ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → አባዶ ፲፫. ቦሌ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ቦሌ ሚካኤል፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ቦሌ ሚካኤል፡፡ ፲፬. የካ አባዶ ገ/አ/ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አባዶ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → አባዶ ፲፭. ምሥራቀ ፀሐይ ዳንሴ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ወረዳ 10 ከጉራራ ከፍ ብሎ፤ ታክሲ፤ ከጊዮርጊስ (4 ኪሎ) (6 ኪሎ) → ፈረንሳይ → ጉራራ፡፡ ፲፮. ወረገኑ ቅዱስ ሚካኤልና አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ሩዋንዳ አጠገብ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ (ቦሌ) → ወረገኑ፡፡ ፲፯. ቃሊቲ ሰፈረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ሰፈረ ገነት፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ቃሊቲ → ሰፈረ ገነት፡፡ ፲፰. ንቡ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ሃራብሳ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ቱሉ ዲምቱ → ንቡ ሚካኤል፡፡ ፲፱. ጀሞ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ጀሞ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (ሜክሲኮ) → ጀሞ፡፡ #እንዲሁም_በአንድነት_በተሠሩ_በሚከተሉት_አብያተ_ክርስቲያናት_ይከበራል፤ ፳. ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ልደታ ክፍለ ከተማ፥ ጎላ (ኢምግሬሽን ጀርባ)፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል (ኢምግሬሽን)፡፡ ፳፩. ደብረ ናዝሬት ቅዱስ ዮሴፍና ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ዮሴፍ፥ ደጃዝማች መርዕድ መንገድ፥ ቀለበት መንገድ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ከላጋር (ከፒያሣ) (ከ4 ኪሎ) (ከቦሌ)(ከመገናኛ) → ቃሊቲ መናኸሪያ /በቀለበት መንገድ/ ወይም፤ ከሳሪስ አቦ → ቦሌ /በቀለበት መንገድ/ ፳፪. ጀሞ ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስና ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ጀሞ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (ሜክሲኮ) → ጀሞ፡፡ ፳፫. ቃሊቲ ደብረ ቊስቋም ማርያምና ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ሰፈረ ገነት፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ቃሊቲ → ሰፈረ ገነት፡፡ ፳፬. ኮተቤ ማኅደረ ቅዱሳን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስና ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ሎቄ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ሎቄ፡፡ ፳፭. ፉሪ መካነ ቅዱሳን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ እና ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ለቡ፥ ፉሪ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ለቡ፡፡ ፳፮. ቂሊንጦ መካነ ፍስሐ ቅዱስ ሚካኤልና በዓታ ለማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ቂሊንጦ አደባባይ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ቱሉዲምቱ፡፡ ወይም፤ ከፒያሳ → ቃሊቲ → ቂሊንጦ፡፡ ፳፯. ቱሉ ዲምቱ ደብረ ሰላም ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ አቃቂ ኬላ አጠገብ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ቱሉዲምቱ፡፡ ወይም፤ ከፒያሳ → ቃሊቲ → ቱሉዲምቱ፡፡ #እንዲሁም_በድርብነት_በሚከተሉት_አብያተ_ክርስቲያናት_ይከበራል፤ ፳፰. መንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ 6 ኪሎ ዐደባባይ፤ ታክሲ፤ ከጊዮርጊስ → 6 ኪሎ (ማርቆስ)፡፡ ፳፱. ደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ገርጂ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ቦሌ በሚል ታክሲ → መስቀል ዐደባባይ፡፡ ፴. ማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያምና ደብረ መድኃኒት መድኃኔ ዓለም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ልደታ ክፍለ ከተማ፥ ልደታ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ጦር ኃይሎች በሚለው ታክሲ → ልደታ፡፡ ፴፩. ደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስና መካነ ጎልጎታ ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አረዳ ክፍለ ከተማ፥ ሰባራ ባቡር፥ ራስ ደስታ ዳምጠው ሆስፒታል አጠገብ (አርበኞች መንገድ)፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ አራዳ → በዊንጌት አስኮ /ሩፋኤል ፊንሐስ/ ታክሲ → ዮሐንስ፡፡ ፴፪. ኮልፌ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ዊንጌት፥ ጠሮ፥ አራት መንታ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ አራዳ → ዊንጌት፡፡ ፴፫. ሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ገዳም፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ልኳንዳ፥ ፈጥኖ ደራሽ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → መርካቶ → ኮልፌ አጣና ተራ → ልኳንዳ → (በስተግራ ባለው አስፓልት በእግር 5 ደቂቃ ፈጥኖ ደራሽ ማሰልጠኛ)፡፡ ፴፬. ቃሌ ተራራ ደብረ መድኀኒት አቡነ ሀብተ ማርያም ወቅድስት ልደታ ወቅድስት አርሴማ ገዳም፤ አድራሻው፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ አስኮ፥ ካኦ ጄጄ ዱቄት ፋብሪካ፥ ቃሌ ተራራ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መርካቶ) → አስኮ፤ ፴፭. ማኅደረ መለኮት ወይብላ ቅድስት ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ የሺ ደበሌ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → መርካቶ → የሺ ደበሌ፡፡ ፴፮. ቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ገርጂ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ገርጂ፡፡ ፴፯. ኮተቤ ደብረ ልዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቅድስት ኪዳነ ምሕረትና አቡነ ሀብተ ማርያም ቤ/ክ፤

ከላይ እንዳየነው በመጀመሪያ ባል ሳታገባ ማገልገሏን ትታ ሌላ ባል አግብታ ልጅ ወልዳ እንድትኖር በብዙ ማባበል ጠየቃት፡፡ ባሏ መንግሥተ ሰማያትን ስለወረሰ ምንም ምጽዋት እንደማይሻ አስመስሎ ነገራት፡፡ ቅድስት አፎምያ ግን ዳግመኛ ትዳር ላለመመሥረት ቃል ኪዳን እንደገባች ርግብንና ዖፈ መንጢጥን አብነት አድርጋ እነርሱ እንኳ በሕይወት ዘመናቸው ከአንድ ባል ውጪ ሌላ ባል እንደማያውቁ በመጥቀስ አሳቡን እንደማትቀበለው ገለጸችለት፡፡ ሰይጣንም አስመሳይ መሆኑ አላዋጣ ሲለው ማንነቱን ቀይሮ ሊያንቃት ቢሞክር የእግዚአብሔርንና የቅዱስ ሚካኤልን ስም ጠርታ አባረረችው፡፡ እርሱም ተመልሶ መጥቶ እንደሚያጠፋት ዝቶባት እንደአቧራ በኖ እንደ ጢስም ተኖ ጠፋ፡፡ በሰኔ 12 ቀን የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያዘጋጀች ሳለች ሰይጣን ብርሃናዊ መልአክ መስሎ መጣ፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል እንደሆነ ገልጾ የመጀመሪያውን የመሰለ ከንቱ ምክሩን አሰማምሮ አቀረበላት፡፡ አሳቡንም የእግዚአብሔር ፈቃድና አሳብ እንደሆነ አድርጎ ለማሳመን ቅድስት አፎምያም በእግዚአብሔር ኃይል ጸንታ በቅዱስ ሚካኤልም ተራዳኢነት ታምና ‹‹የእግዚአብሔር መልአክ ከሆንክ መንፈሳዊ ማረጋገጫህ የሆነው የመስቀል ምልክት የታለ?›› በማለት በምድራዊ ንጉሥና በጭፍራው መካከል የሚኖርን የጋራ መግባቢያ መንገድ ዋቢ አድርጋ ጠየቀችው፡፡ ለጊዜው ‹‹በእኛ በመላእክት ዘንድ እንዲህ አይደለም›› ብሎ ሊሸነግላትና አቋሟን ሊያስቀይራት ሞከረ። ከቤቷ ያለ የቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ላይ ያለውን ምልክት አብራርታ የእርሱ ግን ከዛ ጋር አንድነት እንደሌለው አረጋገጠችበት፡፡ በመቀጠልም ከቤቷ ላለው ለቅዱስ ሚካኤል ሥዕል እጅ እንዲነሣ ጠየቀችው፡፡ በዚህ ጊዜ መልኩ ወደ ትክክለኛ ሰይጣናዊ ማንነቱ ተለወጠና ጨለማ ለብሶ እየዛተ አነቃት፡፡ ቅድስት አፎምያም የከበረ መልአክ ቅዱስ ሚካኤልን "ድረስልኝ" እያለች በጠራችው ጊዜ መልአኩም ፈጥኖ በመድረስ ከሰይጣን እጅ አዳናት፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ፤ ትምሕርት ዋና ክፍል ፥ ንዑስ ክፍል /ሕትመት እና ሚዲያ/ የተዘጋጀ :: ꔰ #share Contact: https://t.me/finotehiwot1927 .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot .YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w www.finotehiwotsundayschool.com ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ት.ቤት .

ያም በግ ጠባቂ ስለ ወርቁ ስጦታ ደስ በመሰኘት ያን ጐልማሳ ጠርቶ ‹‹ልጄ ባሕራን ሆይ ይህ ክቡር ሰው ለሥራ ጉዳይ ወደ ቤቱ ሊልክህ ይፈልጋልና መልእክቱን አድርስለት እግዚአብሔር በሰላም ያግባህ›› ሲል ጠየቀው፡፡ ልጁም ‹‹እሺ መልካም ነው አባቴ ሆይ ያዘዝከኝን ሁሉ ለመፈጸም ዝግጁ ነኝ›› አለው። ከዚህም በኋላ ያ ባለጸጋ ‹‹ይህችን የመልእክት ደብዳቤ ይዞ ወደ አንተ የመጣውን ስሙ ባሕራን የተባለውን መልእክቷ በደረሰችህ ጊዜ ፈጥነህ ግደለው፤ ገድለህም ሬሣውን ከጉድጓድ ጣለው እኔ በሰላም ተመልሼ እስክመጣ ድረስ ማንም ማን ይህን ምሥጢር አይወቅ›› የሚል ጽሑፍ ለሹሙ ጽፎ አዘጋጀ፤ በአገልጋዩ (በሹሙ)ና በእርሱ መካከል የሚተዋወቁበትን ማኅተም በደብዳቤው ላይ አትሞ ለባሕራን ሰጠው፡፡ ለመንገዱም የሚሆነው ስንቅ ሰጥቶ ላከው። የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ለሰይጣኑ ተገቢውን ቅጣት ሰጥቶ ቅድስት አፎምያን ባረካት፡፡ የዕረፍት ቀኗ በዚህ ቀን መሆኑን ነግሮ ቤቷን እንድታዘጋጅ አዘዛት፡፡ የበዓሉን ዝግጅት አከናውና ሥጋ ወደሙን ተቀብላ ኤጲስ ቆጶሱንና ካህናቱን እንደየመዓርጋቸው ጠርታ በቤቷ አክብራ ተቀበለቻቸው፡፡ ለነዳያንና ለጾም አዳሪዎች በኤጲስ ቆጶሱና በካህናቱ እጅ ገንዘቧን መጽውታ መንገዷን አሳመረች፡፡ ስለ ኃጢአቷ እንዲጸልዩላት ተማፅና በፊታቸው ተንበርክካ ጸለየች፡፡ ባሏ ያሠራላትን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል አቅፋ ስማ ከተማጸነች በኋላ ሰኔ 12 ቀን በሰላም ዐረፈች፡፡ #፭. ቅዱስ ላሊበላን ወደ ሰማያት ማሳረጉን፤ ወደፊት ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን እንደሚያንጽ ጌታችን የነገረውና የሕንጻዎቹን አሠራር ዝርዝር የነገረው በዚሁ እለት ነው፡፡ ባሕራንም መልእክቱን ለማድረስ ዘጠኝ ቀን ተጉዞ የአንድ ቀን ጎዳና ሲቀረው እነሆ ክቡር የሚሆን የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በንጉሥ ጭፍራ አምሳል በፈረስ ተቀምጦ ወደሱ ደረሰና ወዴት እንደሚሄድ ጠየቀው፡፡ ባሕራንም ‹‹ከአንድ ባለጸጋ ሰው የተጻፈ ደብዳቤ ይዤ እርሱን ለማድረስ ዕገሊት ወደምትባል አገር እሄዳለሁ›› አለው። ንዑድ ክቡር የሚሆን ቅዱስ ሚካኤልም "እስኪ የመልእክቱን ደብዳቤ አሳየኝ?" አለው፡፡ ባሕራንም ‹‹ጌታዬ ለማንም አታሳይ ብሎኛል›› አለው፡፡ መልአኩም ‹‹እሺ ያም ባይሆን እንደተጠቀለለ አሳየኝ›› አለው፡፡ ባሕራንም አሳየው፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም በሞቱ ደብዳቤ ላይ እፍ ቢልበት የሞቱን ትእዛዝ አጥፍቶ የሕይወት ትዕዛዝ ጽፎበታል፡፡ በደብዳቤው ላይ የተጻፈውን የሞት መልእክት ደምስሶ ‹‹ከእኔ ከባለጸጋ ዕገሌ የተጻፈ›› ይልና ‹‹ይህን መልእክት ይዞ ለመጣሰው ዕገሊት የምትባለዋን ልጄን አጋቡት (ዳሩለት) በዱር የተሰማራውን ከብቴን ፥ በቤት ያለውን ሀብቴን በጠቅላላው የሚንቀሳቀስና የማይንቀሳቀስ ንብረቴን በሙሉ አውርሼዋለሁና እኔ እስክመጣ ድረስ አትጠብቁ በሄድኩበት ሀገር የምቆይበት ጉዳይ አለኝና፤ በቤቴና በንብረቴ ላይ ሙሉ ሥልጣን ሰጥቼዋለሁና የወደደውን ያደርግ ዘንድ አትከልክሉት ስለዚህም በእኔና በአንተ መካከል የምንተዋወቅበትን ምልክት አድርጌበታለሁ›› የሚል ጽሑፍ ጻፈበት "እንግዲህ ወደ ባለጸጋው ቤት ሂድና ይህን መልእክት አድርስ አለው፤ ባሕራንም ‹‹እሺ ጌታዬ እንዳዘዝከኝ አደርጋለሁ›› ብሎ ጉዞውን ቀጠለና የዚያን የባለፀጋ ቤት እየጠየቀ ከደረሰበት በኋላ ደብዳቤውን ለሹሙ ሰጠው። ያም ሹም ደብዳቤውን ተቀብሎ ሲያነብ የታተመበት ማኅተም ዕውነተኛ መሆኑን ካረጋገጠ በኋላ በቤተ ክርስቲያን ደንብ የባለጸጋውን ልጅ አጋባው፣ የሠርጉንም በዓል እስከ ፵ ቀን ድረስ በታላቅ ደስታ አከበሩ። ከሠርጉም በዓል ፍጻሜ በኋላ ያ ባለጸጋ ሰው ከሄደበት አገር ወደ ሀገሩ ተመልሶ ገባና በቤቱ አካባቢ ሲደርስ የደስታና የዘፈን ድምፅ ስለሰማ "ይህ የምሰማው ድምፅ ምንድነው?" ሲል ጠየቀ፡፡ ሰዎቹም ‹‹ባሕራን የተባለ ጐበዝ ካንተ ዘንድ ልጄን ዳሩለት የሚል ትእዛዝ አምጥቶ ልጅህን አግብቶ በሠርጉ ምክንያት ይዘፍናሉ ይደሰታ፤ እነሆ እየበሉና እየጠጡ በቀንና በሌሊት እየዘፈኑ ሲደሰቱ ፵ ቀን ሆኗቸዋል በመልእክትህም እንዳዘዝከው ገንዘብህን የወንድና የሴት ባሮችህን በጠቅላላው የሚንቀሳቀስና የማይንቀሳቀስ ንብረትህን ሁሉ በሙሉ አስረክበውታል›› አሉት። ያም ባለጸጋ ያህን ቃል በሰማ ጊዜ ከድንጋጤው የተነሳ በታላቅ ቃል በመጮኽ ከመሬት ላይ ተከስክሶ ሞተና ነፍሱን አጋንንት ተረክበው ወደ ሲኦል አወረዷት። ከዚህም በኋላ ባሕራን የተባለ ያ ጐልማሳ የቅዱስ ሚካኤልን በዓል በየወሩ እያከበረ ዝክሩን እየዘከረ ይኖር ጀመር። በዚያን ጊዜ በጉዞ ላይ ሳለ ተገልጾለት የሞቱን መልእክት ወደ ሕይወት የለወጠለት ቅዱስ ሚካኤል እንደሆነም አወቀ ተረዳ። ንዑድ ክቡር የሚሆን የመላእክት ሁሉ አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ያደረገው ተአምር ሊቈጥሩት የማይቻል ብዙ ስለሆነ በኛም ላይ ኃይለ ረድኤቱ አድሮብን ይኑር እስከ ዘላለሙ ድረስ አሜን፡፡ #፬. አፎምያን ያዳነበት ቅድስት አፎምያ ሀገሯ ኪልቅያ ነው፡፡ ባለቤቷ አስተራኒቆስ መስፍነ ኪልቅያ ነበረ፡፡ በየወሩ በ29 ቀን የጌታችንን የልደቱን፣ ወር በገባ በ21 የእመቤታችንንና ወር በገባ በ12 የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያደረጉ ነዳያንን ይጎበኙ ነበር፡፡ ባለቤቷ አስተራኒቆስ ከዚህ ዓለም የሚያርፍበት ጊዜ እንደደረሰ ባወቀ ጊዜ ይሰጡት የነበረውን ምጽዋት እና የሦስቱን በዓላት መታሰቢያ ማድረግ እንዳታስታጕል ከአደራ ጋር አዘዛት፡፡ እርሷም የመልአኩን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል ያሥልላት ዘንድ ባለቤቷን ጠይቃ አሠርቶ ሰጣት፡፡ በከበረ ቦታም አኖረችው፡፡ ባሏ ካረፈ በኋላ ያዘዛትን መንፈሳዊ ሥራ ከወትሮው አስበልጣ መሥራት ቀጠለች፤ ከሀብቷ ከንብረቷ እየሰጠች እየመጸወተች በጾም ፥ በጸሎት ተወስና ትኖር ነበር፡፡ ሰይጣን ለምቀኝነት አያርፍምና ደግ መነኵሴ መስሎ አጋንንትን መነኰሳይያት አስመስሎ መጥቶ ከደጅ ሆኖ አስጠራት፡፡ እርሷም ‹‹ከቤት ገብታችሁ በቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ፊት ጸልዩልኝ›› አለቻቸው፡፡ ሰይጣናቱም ‹‹እኛማ በነግህ ጸልየናል?›› አሏት፡፡ ቀጥሎም ሰይጣን ‹‹...እንደው አንቺ ግን ይህ ሁሉ ጾም ጸሎት ምን ያደርገልሻል? ሀብትሽን ሰጥተሸ መጨረስሽስ ስለምንድን ነው? በዚያ ላይ አንቺ ስትደክሚ የሚደግፍሽ ፥ ስታረጂ የሚጦርሽ ልጅ የለሽም ሁለተኛ ማግባት ኃጢአት መስሎሻልን? እነ አብርሃም እነ ዳዊት ከብዙ ሴቶች ብዙ ልጆች ወልደው የለምን? አሁንም ቤት ሰሪ፥ ጎመን ዘሪ ልጅ ያስፈልግሻልና ባል አግቢ፣ እሺ በይኝ›› አላት፡፡ ቅድስት አፎምያም ‹‹አባ ቆብህ መልካም ነበር ንግግርህ ግን ክፉ ነው፣ አትጹሚ፥ አትጸልዩ ያልከኝ፤ ጌታ ምጽዋትን መጽውቱ ብሎ የለምን? ሁለተኛ ባል አግቢ ማለትንስ ከምን አገኘኸው? ርግቦች እንኳን ባሎቻቸው ከሞቱባቸው ከሌላ ወንድ አይቀርቡም፤ ታዲያ ጥንት በንጽሕና ሊኖር የተፈጠረ ሰው ሁለተኛ አላገባም ቢል ዕዳ ፍዳ ሊሆንበት ነውን?›› ብላ ሞገተችው፡፡ የሰው ልጆች ጠላት የሆነው ሰይጣንም በመልካም አገልግሎት ስትበረታ አይቷታልና ዝም ብሎ ሊተዋት አልወደደም፡፡