en
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Open in Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 327 subscribers, ranking 5 647 in the Religion & Spirituality category and 2 194 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 327 subscribers.

According to the latest data from 17 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -87 over the last 30 days and by -13 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 21.14%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 9.89% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 240 views. Within the first day, a publication typically gains 1 515 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 23.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 18 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

15 327
Subscribers
-1324 hours
-147 days
-8730 days
Posts Archive
እንኳን ለሐዋርያት (የሰኔ) ጾም ፍቺ፤ እንዲሁም ለብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ በዓለ ዕረፍት አደረሳችሁ፡፡ ✤✤ #ብርሃናተ_ዓለም_ጴጥሮስ_ወጳውሎስ_ወሥርዐተ_ማኅሌት_ዘሐምሌ_፭፡፡ ✼ #ሐዋርያው_ቅዱስ_ጴጥሮስ፤ በገሊላ ባሕር ዳርቻ በምትገኘው በቤተሳይዳ ተወለደ፡፡ የአባቱ ስም ዮና የእናቱ ስም ሃውኒን ይባላል፡፡ ከ 5 ዓመቱ ጀምሮ ያደገው በቅፍርናሆም ከተማ ነው የመጀመሪያው ስሙ ስምዖን ሲሆን ይህንንም እናቱ በነገዷ ስም እንዳወጣችለት ይነገራል፡፡ ✼ #ሐዋርያው_ቅዱስ_ጳውሎስ፤ ነገዱ ከዕብራውያን ከብንያም ነገድ ነው አባቱ ዮስአል ሲሆን የተወለደውም በጠርሴስ ከተማ ነው፡፡ ጠርሴስ በንግድ የታወቀች የኬልቅያ ዋና ከተማ ናት፡፡ ሮማውያን በሥራቸው ለሚተዳደሩት ሕዝቦች ሮማዊ ዜግነት ይሰጡ ስለነበር የቅዱስ ጳውሎስ አባት በዜግነት ሮማዊ ነበር፡፡ ይህም ለቅዱስ ጳውሎስ ተላልፎለታል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ  በ15 ዓመት ዕድሜው ወደ ትውልድ ሐገሩ በመመለስ በኢየሩሳሌም ከነበረው የታወቀ የገማልያል ትምህርት ቤት ገባ፡፡ በዚያም የአይሁድን ሕግና ሥርዐት እየተማረ እስከ 3ዐ ዓመቱ ቆየ፡፡  በ3ዐ ዓመቱ የአይሁድን ሸንጐ አባል ሆኖ ተቈጠረ፡፡ ✤ #ለአገልግሎት_አጠራራቸው ✤✼ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በጐልማሳነቱ ከወንድሙ ከእንድርያስ ጋር በገሊላ ባሕር ዓሣ ማሥገር ጀመረ፡፡ ለደቀመዛሙርትነት ሲመረጥ እድሜው 55 ዓመት ሲሆን ወደጌታችን ያመጣውም ወንድሙ እንድርያስ ነው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ለሐዋርያነት ሲጠራ መተዳደሪያው የነበረውን መረቡን ታንኳውን እንዲህም አባቱን ትቶ ጌታውን የተከተለ ሐዋርያ ነው፡፡ በቂሳርያ ከተማ መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ማን ትሉኛላችሁ ብሎ በጠየቀ ጊዜ አንተ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ነህ ብሎ ለአይሁድ ሊቃውንት የተሰወረ ምሥጢረ ተዋሕዶ ገልጦ በመመስከሩ ጌታችን አንተ ጴጥሮስ ነህ ብሎታል ይህን በጽርዕ ቋንቋ «ዐለት» ማለት ነው በአረማይክ ደግሞ ኬፋ ይባላል፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ጌታን ይወድ ነበር፡፡ ፍቅሩ ግን ቅንዓት የተቀላቀለ በመሆኑ ጌታችን ለደቀመዛሙርቱ የሞቱን ነገር ቀድሞ ሲነግራቸው አይሁንብህ በማለት ተከራክሯል፡፡ ማቴ 16፥23 በኋላም ሁሉም በአንተ ቢሰናከሉ እኔ ከቶ አልሰናከልም ብሎ በራሱ ቅንዓት ተማምኖ ተናግሮ ነበር፡፡ ጌታችን ዶሮ ሳይጮህ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ ያለው እንኳን ከአንተ ጋር መሞት እንኳ የሚያስፈልገኝ ቢሆን ከቶ አልክድህም በማለት የተናገረ ሐዋርያ ነው፡፡ (ማቴ 26፥34) ነገር ግን 3 ጊዜ ጌታችንን አላውቀውም ብሎ ካደ፤ ዶሮ በጮኸና አምላኩን መበደሉን እንዳወቀ ከግቢው ወጥቶ አለቀሰ ንስሐ ገባ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ በዕድሜው ታላቅነት በሐዋርያት ዘንድ እንደ አባት ይታይ ስለነበር ጌታ በተለየው ጊዜ ሐዋርያቱን ሊመግብ ወደሚያውቀው ሙያ ዓሣ ወደማስገሩ ተሠማራ ጌታም አስቀድሞ የመረጠው እርሱ ነውና ቢከዳው እንኳን በንስሐ በመመለሱ ንስሐውን መቀበሉን ዛሬም እንደሚወደው ይገልጽለትም ዘንድ በጥብርያዶስ ባሕር ተገለጠለት፡፡ ሦስት ጊዜ ክዶት ነበርና ቀኖና ሰጠው፡፡ አሁን ቅዱስ ጴጥሮስ በራስ መተማመኑ እንዳላዋጣው አውቆ ትወደኛለህ ተብሎ ሲጠየቅ አንተ ታውቃለህ ነበረ መልሱ የራሱ እውቀት የት እንዳደረሰው ያውቃልና ጌታችንም ኀዳጌ በቀል /በቀልን የሚተው/ ነውና ዛሬም እንደሚወደው በንሰሐ ተመልሷልና ዛሬም ለእርሱ የሰጠውን ክብር እንደማያጐልበት ሲነግረው ግልገሎቼን አሠማራ ጠቦቶቼን ጠብቅ በጐቼን አሠማራ በማለት አደራውን አስረከበው፡፡ ዮሐ 21፥15-17 ✼ #ሐዋርያው_ቅዱስ_ጳውሎስ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚያስተምርበት ዘመን ቅዱስ ጳውሎስ በኢየሩሳሌም ስለነበረ በአይሁድ ሸንጐ አባልነት ለ2 ዓመታት በሠራበት ወቅት እምነቱ ቀናተኛ ፈሪሳዊ በመኾኑ ክርስቲያኖችን በማናቸውም አጋጣሚ ይቃወም ነበር፡፡ ቅዱስ እስጢፋኖስ በድንጋይ ተወግሮ በሰማዕትነት ሲያርፍም የወጋሪዎችን ልብስ ይጠብቅ የነበረው እርሱ ነው፡፡  በ32 ዓመት ዕድሜው ከኢየሩሳሌም 223 ኪ.ሜ ርቀት በስተሰሜን በኩል በምትገኘው የደማስቆ ከተማ ብዙ ክርስቲያኖች መኖራቸውን ሲሰማ ወደ ሊቀ ካህናቱ ቀርቦ ክርስቲያኖችን ለማጥፋት የሚያስችለውን የፈቃድ ደብዳቤ ጠይቆ ካገኘ በኋላ ጭፍሮችን አስከትሎ ወደ ደማስቆ አመራ፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ ወደ ከተማዋ ለመድረስ ጥቂት ሲቀረው ነበር ከሰማይ የወረደው ብርሃን አካባቢውን ያለበሰውና ሳዖል፥ ሳዖል ስለምን ታሳድደኛለህ? የሚለውን ድምፅ የሰማው፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስም ጌታ ሆይ ማን ነህ? ብሎ ጠየቀ የምታሳድደኝ እኔ የናዝሬቱ ኢየሱስ ነኝ የመውጊያውን ብረት ብትቃወም ለአንተ ይብስብሃል ሲል መድኀኒታችን ተናገረው፡፡ ያንን በወደቀበት ሆኖ እየተንቀጠቀጠ ጌታ ሆይ ምን አደርግ ዘንድ ትወዳለህ ሲል ጠየቀው ከዚህ በኋላ ተነሥቶ ወደ ደማስቆ እንዲገባ ተነገረው፡፡ የሐዋ 9፥1 የሐዋርያው ዓይኖች ለማየት አልቻሉም ነበር፡፡ እየተመራ ወደ ደማስቆ ገባ ለ3 ቀናት ያህልም እህል ሳይቀምስ ቆየ በዚያች ዕለት እግዚአብሔር አምላክ በደማስቆ ለሚገኘው እና ሐናንያ ለተባለው አባት በራዕይ ተገለጠለት፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም ያለበትን አድራሻ ነገረውና  እንዲያጠምቀው አዘዘው፡፡ ሐናንያ አስቀድሞ የቅዱስ ጳውሎስን ማንነት ያውቃል፡፡ አብዛኞቹ በደማስቆ የሚገኙት ክርስቲያኖች ከኢየሩሳሌም በስደት ጊዜ የመጡ ናቸው፡፡ ያን ስደት ያስነሳው ደግሞ በቅዱስ እስጢፋኖስ ላይ የደረሰው መከራ ነው፡፡ በዚህ በቅዱስ እስጢፋኖስ ሰማዕትነት ደግሞ ዋናው ተዋናይ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ነበርና ነው፡፡ ሐናንያ ቅዱስ ጳውሎስን ካጠመቀውና ካስተማረውም በኋላ ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ዓረብ ሐገር ሄደ፥ ለሦስት ዓመታት በዓረቢያ በረሃ ከቆየም በኋላ ወደ ደማስቆ ከተማ ተመለሰ። በዚያም በነበሩ አይሁድ መካከል በፊት ያሳድደው የነበረውን ኢየሱስ ክርስቶስን መስበክ ጀመረ፡፡ ከዚያ በፊት በፈሪሳዊነቱና ለአይሁድ ሕግ በነበረው ቅንዓት የሚታወቀው ጳውሎስ ዛሬ ወንጌል ሲሰብክ በማየታቸው አይሁድ ተነሡበት፡፡ በዚያም የተነሣ የደማስቆ ክርስቲያኖች በቅርጫት አውርደው ወደ ኢየሩሳሌም ላኩት፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ኢየሩሳሌም ሲደርስ አይሁድ ጳውሎስን እንደሚያውቁት እና እንደለመዱት ሆኖ ስላላገኙት ሊገድሉት ተነሱ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ክርስቲያኖች የቅዱስ ጳውሎስን መመለስ ሊያምኑ አልቻሉም፡፡ በመጨረሻ ግን በርናባስ ወደ ሐዋርያት ዘንድ ወስዶ የጳውሎስን መመለስ በመተረክ እንዲያምኑት አደረጋቸው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በኢየሩሳሌም በድፍረት በማስተማሩ አይሁድ ስለተቃወሙት ከተማዋን ትቶ በቂሳርያ በኩል ወደ ትውልድ ሐገሩ ጠርሴስ ተመለሰ፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በጠርሴስ ከተማ ለ9 ዓመታት ቆይቷል፡፡ ከኢየሩሳሌም ውጭ የአሕዛብ ከተማ በነበረችው በአንጾኪያ የክርስትና ሃይማኖት ተስፋፋ፡፡ ከዚህም በኋላ ሐዋርያው ሦስት ታላላቅ ሐዋርያዊ ጉዞዎችን አድርጓል፡፡ በመጀመሪያው ጉዞው ወደ 2,ዐዐዐ ኪ.ሜ የሚደርስ መንገድ በእግር ተጉዟል፤ ይህም የተከናወነው በ46 ዓ.ም. ነው፡፡ በሁለተኛው ሐዋርያዊ ጉዞው ከ18 በላይ ከተሞችን ሸፍኗል፤ ጉዞውም በ5ዐ ዓ.ም. የተደረገ ነው፡፡  በሦስተኛው ሐዋርያዊ ጉዞው ከ2ዐ በላይ ከተሞችን ሸፍኗል፤ ጉዞውም በ54 ዓ.ም. የተደረገ ነው፡፡ ብዙም ጊዜ በቁም እሥር በብዙም መከራ ሥቃይ እንግልት ያሳለፈ ታላቅ ሐዋርያ ነው፡፡

#ልደተ_ቅዱስ_ዮሐንስ_መጥምቅ_ወሥርዐተ_ማኅሌት፡፡ (ከሰንበት ትምህርት ቤታችን የሰሌዳ መጽሔት ተለቅሞ የተዘጋጀ፡፡) #ልደቱና_ብሥራቱ አባቱ ዘካርያስ (ከአብያ ምድብ የኾነ ሊቀ ካህን ነው)፤ እናቱ ዘካርያስ (ከአሮን ነገድ ነበረች)፤ ሁለቱም የጌታን ትእዛዝና ሥርዓት ሁሉ ጠብቀው ያለ ነቀፋ የሚኖሩ፣ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን ነበሩ፤ ይሁን እንጂ ኤልሳቤጥ መካን በመሆኗ ልጅ አልነበራቸውም፡፡» /ሉቃ.1÷5-7/፡፡ ካህኑ ዘካርያስና ቅድስት ኤልሳቤጥ ልጅ እንዲሰጣቸው እግዚአብሔርን ዘወትር በጸሎት ይጠይቁ ነበር፡፡ አንድ ቀን ዘካርያስ እንደ ብሉይ ኪዳኑ ሥርዐት /ዘጸ.3ዐ÷6-8/ ወደ ቤተ መቅድስ ገብቶ ዕጣን የማጠን ተራ ደርሶት /ዕጣ ወጥቶለት/ ወደ ቤተመቅደስ ሲገባ መልአከ እግዚአብሔር ከዕጣን መሠዊያው /ከዕጣን መሥዋዕት ማቅረቢያው/ በስተቀኝ ቆሞ ታየው፡፡ ዘካርያስም ባየው ጊዜ በፍርሃት ተዋጠ፡፡ መልአኩ ግን «ዘካርያስ ሆይ አትፍራ ጸሎተህ ተሰምቷል፤ ሚስትህ ኤልሳቤጥ ወንድ ልጅ ትወልድልሃለች፤ ስሙንም ዮሐንስ ትለዋለህ፤ በእርሱ ተድላና ደስታ ታገኛለህ ብዙዎቹም በእርሱ መወለድ ደስ ይላቸዋል፤ በጌታ ፊት ታላቅ ይሆናልና» በማለት ብሥራት ከነገረው በኋላ ስለሚወለደው ልጅ አራት ነገሮችን ነገረው /ሉቃ.1÷13-17/፡፡ ሀ. የወይን ጠጅም ሆነ ሌላ የሚያሰክር መጠጥ አይጠጣም፡ ለ. በእናቱ ማኅፀን ሳለ በመንፈስ ቅዱስ ይሞላል፡፡ ሐ. ከእስራኤል ወገን ብዙዎችን ወደ ጌታ ወደ አምላካቸው ይመልሳል፤ መ. ለጌታ የሚገባ ሕዝብ ለማዘጋጀት በኤልያስ መንፈስና ኃይል በጌታ ፊት ይሔዳል፡፡ ዘካርያስ ይህንን ከመልአኩ በሰማበት ወቅት እርሱ ሸምግሎ፥ ሚስቱም አርጅታና የመውለጃ ዕድሜዋ አልፎ በዚያም ላይ መካን ነበረችና «ይህን በምን አውቃለሁ? እኔ ሽማግሌ ነኝ ሚስቴም በዕድሜ ገፍታለች» በማለት ጥርጣሬውን በጥያቄ መልክ አቀረበ፡፡ በዚህን ጊዜ መልአኩ እንዲህ አለው «እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ፡፡ ይህን እነግርህና ይህን የምሥራች አመጣልህ ዘንድ ተልኬያለሁ፤ እነሆ ጊዜውን ጠብቆ የሚፈጸመውን ቃሌን ስላላመንህ ይህ እስከሚፈጸምበት ቀን ድረስ ድዳ ትሆናለህ፤ መናገርም አትችልም» አለው፤ በዚህም መሠረት ዘካርያስ አገልግሎቱን ፈጽሞ ሲወጣ መስማትም ሆነ መናገር አልቻለም ነበር፡፡ መልአኩ እንደነገረውም ሚስቱ ኤልሳቤጥ ፀነሰች፡፡ ይህ ከሆነ ከስድስት ወር በኋላ የቅዱስ ዮሐንስን መፀነስ ለዮሐንስ ያበሠረው መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ከእግዚአብሔር ዘንድ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ጌታችንን እንደምትወልድ አበሰራት፡፡ መልአኩ እመቤታችንን ሲያበስራት ኤልሳቤጥ መፀነስዋንም ነግሯት ነበር፡፡ «... እነሆ ዘመድሽ ኤልሳቤጥ በእርጅናዋ ወራት ወንድ ልጅ ፀንሳለች፤ መካን የተባለችውም ስድስተኛ ወሯን ይዛለች፤ ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለምና» ብሏት ነበር፡፡ እመቤታችንም መልአኩ ስለ ኤልሳቤጥ የነገራትን ለማየት በዚያው ሰሞን ፈጥና ወደ ኤልሳቤጥ ሄደች፡፡ ወደ ዘካርያስም ቤት ገብታ ለኤልሳቤጥ ሰላምታ ስታቀርብላት እጅግ የሚያስደንቅ ነገር ተከሰተ፤ ኤልሳቤጥ የእመቤታችንን ሰላምታ በሰማች ጊዜ በማኅፀኗ ያለው ጽንስ ዘለለ፡፡ ኤልሳቤጥም በመንፈስ ቅዱስ ተሞላች ድምጽዋን ከፍ አድርጋ እንዲህ አለች፡- «አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ፤ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው፡፡ የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል? እነሆ የሰላምታሽ ድምፅ በጆሮዬ በመጣ ጊዜ ጽንሱ በማኅፀኔ በደስታ ዘሏልና፡፡... »፡፡ ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ይህንን አስመልክቶ በድጓው ላይ ባስተማረው ትምህርት «አእሚሮ እምከርሠ እሙ ሰገደ ወልደ መካን ለወልደ ድንግል» «ገና በእናቱ ማኅፀን ሳለ አውቆ የመካኒቱ /የኤልሳቤጥ/ ልጅ ለድንግሊቱ /ለእመቤታችን/ ልጅ ሰገደ» ብሏል፡፡ #የቅዱስ_ዮሐንስ_ልደት (ሉቃ.1÷67-80) ኤልሳቤጥ የመውለጃዋ ቀን ደረሰ፤ ወንድ ልጅም ወለደች፡፡ በስምንተኛውም ቀን ጎረቤቶቿና ዘመዶቿ ሕፃኑን ሊገርዙት መጡ፤ በአባቱም ስም ዘካርያስ ሊሉት ፈለጉ፤ እናቱ ግን ለዘካርያስ በቤተ መቅደስ «የሕፃኑ ስም ዮሐንስ ይባላል» ብሎ ያናገረ በመልአኩ በቅዱስ ገብርኤል አማካኝነት መንፈስ ቅዱስ ገልጦላት «ዮሐንስ መባል አለበት» አለች፡፡ ዘካርያስን ለልጁ ምን ስም ሊያወጣለት እንደሚፈልግ ሲጠይቁት መጻፊያ ሰሌዳ እንዲሰጡት ጠይቆ «ስሙ ዮሐንስ ነው» ብሎ ጻፈ ወዲያውም አንደበቱ ተፈታ፡፡ (ዮሐንስ ማለትም ፍሥሐ ወሐሴት፣ ርኅራኄ ማለት ነው፡፡)፤ እግዚአብሔርንም እያመሰገነ ይናገር ጀመር፡፡ በዚህም ምክንያት ጎረቤቶቹ ሁሉ በፍርሃት ተመሉ፡፡ ነገሩም በይሁዳ አውራጃ ሁሉ ተወራ፡፡ የሰሙትም ሁሉ «ይህ ሕፃን ምን ይሆን?» እያሉ በመገረም ጠየቁ፡፡ ካህኑ ዘካርያስም በመንፈስ ቅዱስ ተመልቶ ስለ ሕፃኑ ስለ ቅዱስ ዮሐንስ ትንቢት ተናገረ /ሉቃ.1÷67-79/ «አንተ ሕፃን ሆይ የልዑል ነቢይ ትባላለህ፤ መንገዱን ልትጠርግ በጌታ ፊት ትሔዳለህና፤ እንደዚሁም የኃጢአታቸው ሥርየት የሆነውን የመዳን ዕውቀት ለሕዝቡ ትሰጣለህ» በማለት ቅዱስ ዮሐንስ የጌታችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መንገድ ጠራጊ እንደሚሆን ማለትም ከእርሱ ቀድሞ የሕዝቡ ልብ ጌታችንን እና ትምህርቱን እንዲቀበል የሚያዘጋጅ ትምህርት እንደሚያስተምር ተናገረ፡፡ የቅዱስ ዮሐንስ መንገድ ጠራጊነት በቅዱስ ገብርኤልና በአባቱ በዘካርያስ ብቻ ሳይሆን ቀድሞም በሌሎች ነቢያት ትንቢት የተነገረለት ነበር፡- ነቢዩ ኢሳይያስ «የዐዋጅ ነጋሪ ድምፅ እንዲህ ይላል «የእግዚአብሔርን መንገድ በምድረ በዳ አዘጋጁ...» /ኢሳ.4ዐ ÷3/ በማለት ተናግሮ ነበር፡፡ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

፯. አዲስጌ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ፤ አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ እንሳሮ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ለሚ → እንሳሮ፡፡ ፰. ፀዶበር ዮሐንስ መጥምቅ፤ አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ መንዝ ፥ ቀያ ገብርኤል፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → መንዝ → ቀያ ገብርኤል፡፡ ፱. አርባ ምንጭ ገረሴ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ፤ (ፈዋሴ ድውያን የሆነ ፈዋሽ ጠበል ያለበት) አድራሻ፤ አርባ ምንጭ ሀገረ ስብከት፥ ገረሴ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. አለም ባንክ አውቶቡስ ተራ → አርባ ምንጭ → ገረሴ (ከአርባ ምንጭ 55 ኪ.ሜ.)፡፡ ፲. ወንጪ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ፤ አድራሻ፤ ደቡብ ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ወንጪ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ ውቶቡስ ተራ → ወንጪ፡፡ ፲፩. ደብረ ዘይት (ቢሾፍቱ) ዳግማዊ ሸንኮራ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ፤ (ፈዋሴ ድውያን ጠበል ያለበት) አድራሻ፤ ደቡብ ሸዋ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ አድአ ወረዳ ቤተ ክህነት ፥ ከታ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ዘይት → ከታ፡፡ ፲፪. ተንታ ደብረ ብርሃን ቅዱስ ሚካኤል፤ (ንጉሥ ሚካኤል በሚያስደንቅ ሁኔታ ያሠሩት) አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት፥ አምባሰል፥ ተንታ ወረዳ፥ ጠዓት ቀበሌ፥ እሜገኝ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ጻድቃኔ፡፡ ፲፫. ሰበታ ፈለገ ዮርዳኖስ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ሰበታ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. አስኮ አውቶቡስ ተራ → ሰበታ፡፡ ፲፬. ሰበታ ፈለገ ዮርዳኖስ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ሰሜን አሜሪካ ሀገረ ስብከት፥ ቨርጂኒያ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ቦሌ አየር መንገድ → አሜሪካ /ቨርጂኒያ/፡፡ አቅጣጫ ምንጭ ዋሊ.. /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

#ሰኔ #፴ ፤ #በዓለ_ልደቱ_ለቅዱስ_ዮሐንስ_መጥምቅ_፡፡ #በመላው_ዓለም_ክብረ_በዓሉ_የሚከበርባቸው_ #፴፰ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ #በአዲስ_አበባ_የቅዱስ_ዮሐንስ_መጥምቅ_በዓለ_ልደት_ክብረ_በዓል_የሚከበርባቸው_ #፳፬ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ (ሌሎች ያልጠቀስናቸው ካሉ ጨምሩበት፡፡) ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ፩. ቦሌ ደብረ ሳሌም ዮሐንስ መጥምቅ (ኋላ መድኀኔ ዓለም ወዮሐንስ መጥምቅ) ቤ/ክ፤ አድራሻው፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ቦሌ መድኀኔ ዓለም፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ቦሌ፤ ፪. ፉሪ ፈለገ ዮርዳኖስ ቅዱስ ዮሐንስና ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ጀሞ 3፥ መስታወት ፋብሪካ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ሜክሲኮ → ጀሞ፡፡ ፫. ደብረ ሰሊሆም መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስና መድኀኔ ዓለም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ በርታ ሰፈረ ሰላም፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(4ኪሎ) → ቃሊቲ፡፡ ፬. ቱሉ አቦ ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቅዱስ ዑራኤልና መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ቱሉ አቦ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ቃሊቲ → ቱሉ አቦ፡፡ ፭. ጎፋ መብራት ኀይል ደብረ መዊዕ ቅዱስ መርቆሬዎስና መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ጎፋ፥ መብራት ኀይል፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ጎፋ መብራት ኀይል፡፡ ፮. ላፍቶ ኢያሪኮ መድኀኔ ዓለም (ለብቻው የቅዱስ ዮሐንስ ሕንፃ ቤ/ክ አለ)፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ቀርሳ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ሜክሲኮ → ኢያሪኮ መድኀኔ ዓለም፡፡ ፯. ቦሌ ቡልቡላ ፍኖተ ሕይወት ማርያምና መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ፤ አድራሻው፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ቡልቡላ ኮንዶሚንየም፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ሳሪስ → ቡልቡላ፤ ፰. ቤተል ጌቴሴማኒ ቅድስት ማርያም ወዮሐንስ ፤ አድራሻው፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ቤቴል፥ መኪና መለማመጃ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ኮልፌ → መኪና መለማመጃ፤ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #እንዲሁም_በድርብነት_፤ ፱. ጉለሌ ሸጎሌ ኪዳነ ምሕረት ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ አዲሱ ገበያ ፥ ቶታል፥ ወደ ዊንጌት በቀለበት መንገገዱ ትንሽ ሄደው፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (አስኮ) → አዲስ ገበያ፡፡ ፲. አንቆርጫ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤልና ቅድስት ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አንቆርጫ፤ ታክሲ፤ ከጊዮርጊስ (4 ኪሎ) (6 ኪሎ) → ፈረንሳይ → አንቆርጫ፡፡ ፲፩. ፈረንሳይ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ፈረንሳይ ፥ ብረት ድልድይ፤ ታክሲ፤ ከጊዮርጊስ (4 ኪሎ) (6 ኪሎ) → ፈረንሳይ → ብረት ድልድይ፡፡ ፲፪. ቦሌ ሰሚት መካነ ሰላም መድኀኔ ዓለም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ሰሚት፥ ወጂ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ሰሚት፡፡ ፲፫. ገዳመ ኢየሱስ፤ አድራሻ፤ ልደታ ክፍለ ከተማ፥ ሆላንድ ኤምባሲ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ኮልፌ አጣና ተራ፡፡ ፲፬. አውግስታ ደብረ ጽዮን ማርያም ቤ/ከ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ አውግስታ፥ ሸሚዝ ፋብሪካ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ጦር ኃይሎች → አውግስታ፡፡ ፲፭. አስኮ ደብረ መድኀኒት መድኀኔ ዓለምና ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ አስኮ፥ አዲስ ሰፈር፤ ታክሲ፤ ከአራዳ (ፒያሳ) → አስኮ አዲስ ሰፈር፡፡ ፲፮. መዝገበ ምሕረት ቅዱስ ፋኑኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ፋኑኤል ሰፈር፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(ከመርካቶ) → ካራቆሬ፡፡ ፲፯. ምዕራፈ ቅዱሳን ፈለገ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስና አቡነ አረጋዊ ገዳም፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ሳሪስ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ሳሪስ ፲፰. ሳሪስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ሳሪስ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ሳሪስ ፲፱. ቀርሳ ፈለገ ብርሃን ቅድስት ልደታ ለማርያምና አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ገላን ኮንዶሚኒየም፥ ቀርሳ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ቃሊቲ → ቀርሳ፡፡ ፳. ኮልፌ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ዊንጌት፥ ጠሮ አራት መንታ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ አራዳ → ዊንጌት፡፡ ፳፩. ካራ አሎ ደብር ቅዱስ ደብረ ቀርሜሎስ መደኀኔ ዓለምና አቡነ ገሪማ ገዳም፤ አድራሻው፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ኮተቤ፥ ካራ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(4 ኪሎ) → ሾላ መገናኛ → ኮተቤ ካራ፤ ፳፪. ምሥራቀ ፀሐይ ገብርኤል፤ አርሴማና አቡነ አዳም ቤ/ክ ፤ አድራሻው፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ መካኒሳ፥ ጀርመን ዐደባባይ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → መካኒሳ /ጀርመን ዐደባባይ/፤ ፳፫. ሰርጢ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻው፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ሰርጢ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ቃሊቲ/አቃቂ → ሰርጢ፤ ፳፬. አቃቂ ፈንታ ደብረ ጽጌ ሩፋኤልና አርሴማ፤ አድራሻው፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ፈንታ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ቃሊቲ/አቃቂ → ፈንታ፤ #እንዲሁም_ ፈዋሴ ድውያን ወገባሬ ተአምራት የሆኑ #ጠበሎቹ፤ መካነ ሰማዕት ደብረ ፍስሓ ቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ (ለገሃር ምድር ባቡር ጣቢያ ጀርባ)፤ ፈዋሽ የፍልውኃ ጠበል በላፍቶ ኢያሪኮ መድኀኔ ዓለም ቤ/ክ አለ፡፡ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከበርባቸው_ጥንታውያን #፲፬ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. ደብረ ቢዘን ዘንባባ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ገዳም፤ (የቅዱሳን መናኸሪያ) አድራሻው፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ተጉለት፤ ትራንስፖርት፤ ከጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ብርሃን → በኩክ የለሽ መስመር የ1 ሰዐት የእግር ጕዞ፤ ወይም፤ ከጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ብርሃን → ይዞሽ አሞራ → የ1 ሰዐት እግር ጕዞ፡፡ ፪. ጎንደር ደብረ ጽጌ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር፡፡ ፫. ሸንኮራ ደብረ መንክራት ቅዱስ ዮሐንስ ፤ (ዮሐንስ ጌታን ሲያጠምቀው በሚስል ሁኔታ ከደረቅ አለት መሃል በተሰቈረ ቀዳዳ የሚፈልቅ አስደናቂ ጠብል ያለበት) አድራሻው፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ምንጃር፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ሞጆ → ሸንኮራ፤ ፬. ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ቤ/ክ፤ (በሸንኮራ ዮሐንስ መስመር መንገድ ዳር ላየይ የሚገኝ) አድራሻው፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ምንጃር፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ሞጆ → ሸንኮራ (ሳማ ሰንበት) መንገድ አጠገብ የሚገኝ፤ ፭. ደብረ አናጕግ ቅዱስ ሚካኤል ወዮሐንስ መጥምቅ ፤ አድራሻው፤ አኵሱም (ማዕከላዊ ትግራይ) ሀገረ ስብከት፥ አኵስም አጠገብ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → አኵስም → አናጕግ፡፡ ፮. መርሐ ቤቴ አሮጋንዳ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ፤ አድራሻው፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ መርሐ ቤቴ → ዓለም ከተማ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → መርሐቤቴ /አሮጋንዳ/፤

ደብራችን ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል አብያተ ክርስቲያናት በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ/መ/ፓ/ጠ/ቤተ ክህነት የትምህርት እና ስልጠና መምሪያ ከ ሰኔ 24-ሰኔ 25 ባካሄደው "
ደብራችን ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል አብያተ ክርስቲያናት በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ/መ/ፓ/ጠ/ቤተ ክህነት የትምህርት እና ስልጠና መምሪያ ከ ሰኔ 24-ሰኔ 25 ባካሄደው "ዝክረ ወንጌል ወዝክረ ሊቃውንት " በተሰኘው መርሐግብር በአ.አ ሀገረ ስብከት ስር ከሚገኙ ገዳማት እና አድባራት የአብነት ትምህርት ቤቶች መካከል የታላቁ ንቡረ እድ በየነ ዐሊ መታሰቢያ የላይ ቤት አቋቋም የአብነት ትምህርት ቤት ውስጥ በሚሰጡ ጉባኤዎች ማለትም ፨ ከ 45 ዓመታት በላይ ወንበር ሳያጥፉ በሚያስተምሩት በታላቁ መዝገበ ብርሃን የኔታ ሙሴ ቦጋለ የደብረ አባይ ቅዳሴ ጉባኤ ቤት ፨ በታላቁ ሊቅ የብሉያት የሐዲሳት የሊቃውንት የፍትሐ ነገሥት እንዲሁም የቅኔው ሊቅ በሆኑት መጋቤ ምስጢር የኔታ ቀፀላ ፈንቴ በሚሰጠው የቅኔ ጉባኤ ቤት ፨ በ ታላቁ የድጓ ባለሙያ ሊቅ የኔታ ጥበቡ የሚሰጠው የዜማ ጉባኤ ቤት ፨ በወጣቱ ሊቅ የታላቁ የደብረ ሊባኖስ ገዳም ፍሬ በሆኑት  የቋቋም መምህር የኔታ ዲበኩሉ በሚሰጠው የላይ ቤት አቋቋም ጉባኤ ቤት አመርቂ ውጤት በማስመዝገቡ እንዲሁም በአቡሻኸር ትምህርት ነጥብ ተቀንሶበት በ አራተኝነት የምስክር ወረቀት ተቀብሏል ።

ሰኔ ፳፬ #አባ_ሙሴ_ጸሊም በሰማዕትነት አረፈ ሰዎች ከገድሉ የተነሣ ይህን ቅዱስ ያደንቁታል እርሱ  አስቀድሞ መንግሥተ ሰማያትን ገፍቷት ነበረና እርሱ በሥጋው  ጠንካራ በሥራውም ኃይለኛ ነበር ይበላና ይጠጣ ይቀማና ያመነዝር ነበር ይገድልም ነበር ማንም ሊቋቋመው አይችልም ነበር። አንድ በግ በአንድ ጊዜ ጨርሶ እንደሚበላና አንድ ቀን ወይን ጠጅ እንደ ሚጠጣ ስለ እርሱ ተነግሮአል። እርሱም ፀሐይን ለሚያመልኩ ሰዎች አገልጋይ ነበረ ብዙ ጊዜም ወደ ፀሐይ እያንጋጠጠ ፀሐይ ሆይ አንተ አምላክ ከሆንክ አነጋግረኝ ይል ነበር ደግሞም በልቡ የማላውቅህ ሆይ ራስህን አሳውቀኝ ይል ነበር። ከዚህም በኋላ በአስቄጥስ ገዳም ያሉ መነኰሳት እግዚአብሔርን ያውቁታል ያዩታልም እያሉ ሲነጋገሩ ሰዎችን ሰማቸው። ያን ጊዜም ተነሣ ሰይፉንም ታጥቆ ወደ አስቄጥስ ገዳም ሔደ በደረሰም ጊዜ አባ ኤስድሮስን አገኘው አባ ኤስድሮስም ፈራው ሙሴ ጸሊምም እውነተኛውን አምላክ ታሳውቁኝና ታስረዱኝ ዘንድ  ወደ እናንተ መጣሁ አለው አባ ኤስድሮስም ወደ አባ መቃርስ ወስዶ አገናኘው። እርሱም ተቀብሎ ሃይማኖትን አስተ ማረው እንዲህም አለው ታግሰህ የማስተምርህን ከጠበቅህ እግዚአብሔርን ታየዋለህ። ከዚህም በኋላ የክርስትና ጥምቀትን አጥምቆ አመነኰሰው ከብዙዎች ገድለኞች ቅዱሳን ይልቅ ብዙና ጽኑዕ ገድልን መጋደል ጀመረ። ሰይጣንም አስቀድሞ ሲሠራው በነበረ በመብልና በመጠጡ በዝሙቱም ይዋጋው ነበረ እርሱም በራሱ ላይ የሚደርስበትን ሁሉ ለአባ ኤስድሮስ ይነግረው ነበር እርሱም አጽንቶ ሊሠራው የሚገባውን ያስተምረው ነበር። ከገድሉ ብዛትም የተነሣ አረጋውያን መነኰሳት በሚተኙ ጊዜ ቤቶቻቸውን በመዞር ውኃ መቅጃዎችን ወስዶ ውኃ መልቶ በየቤታቸው ደጃፍ ያኖር ነበር። ውኃው ከእነርሱ ሩቅ ነበረና እንዲህም እያደረገ በመጋደል ለብዙ ዘመናት ኖረ። ሰይጣንም በእርሱ ቀንቶ በእግሩ ውስጥ አስጨናቂ የሆነ አመታትን መታው ተኝቶም እየተጨነቀ ብዙ ቀን ታመመ ከዚህም በኋላ የመታውና የሚፈታተነው ሰይጣን እንደሆነ ዐውቆ ሥጋው በእሳት ተለብልቦ እንደ ደረቀ ዕንጨት እስቲሆን ድረስ ተጋድሎውንና አገልግሎቱን አበዛ። እግዚአብሔርም ትዕግሥቱን አይቶ ከደዌው ፈወሰው የሰይጣንንም ጦር ከእርሱ አራቀለት የመንፈስ ቅዱስም ጸጋ አደረበት ወደርሱም አምስት መቶ ወንድሞች መነኰሳት ተሰበሰቡ በእነርሱም ላይ አበምኔት ሆነ። ከዚህ በኋላ ቅስና ሊሾሙት መረጡት በቤተ መቅደስም በሊቀ ጳጳሳቱ ዘንድ ባቆሙት ጊዜ ሊቀ ጳጳሳቱም አልፈቀደም ነበር፤ አረጋውያኑንም ይህን ጠቋራ ለምን አመጣችሁት ከዚህ አውጡት አላቸው፤ #እርሱም "መልክህ የከፋ ጠቋራ ሆይ፣ መልካም አደረጉብህ" በማለት ራሱን እየገሠጸ ወጣ ከዚህ በኋላ ዳግመኛ ሊቀ ጳጳሳቱ ጠራውና እጁን በላዩ ጭኖ ቅስና ሾመው እንዲህም አለው ሙሴ ሆይ እነሆ በውስጥም በውጭም ሁለመናህ ነጭ ሆነ። በአንዲትም ዕለት ቅዱሳን አረጋውያን ወደርሱ መጡ በእርሱም ዘንድ ውኃ አልነበረም እርሱም ከበዓቱ ብዙ ጊዜ ወጣ ገባ ይል ነበር ከዚህ በኋላም ብዙ ዝናም ዘንሞ ጒድጓዶችን ሁሉ ሞላ። አረጋውያንም ለምን ብዙ ጊዜ ወጣ ገባ ትል ነበር ብለው ጠየቁት እርሱም እግዚ አብሔርን ውኃ ካልሰጠኸኝ ቅዱሳን አገ ልጋዮችህን ምን አጠጣቸዋለሁ እለው ነበር፤ በቸርነቱም ዝናምን ልኮልን ውኃን አገኘን አላቸው። በአንዲትም ዕለት አባ ሙሴ ከአረጋውያን ጋራ ወደ አባ መቃርስ ሔደ አባ መቃርስም የሰማዕትነት አክሊል ያለው ከእናንተ ውስጥ አንዱን እነሆ አያለሁ አላቸው አባ ሙሴም አባቴ ሆይ በሰይፍ ይገደል ዘንድ አለው የሚል ጽሑፍ አለና ብሎ መለሰ። ከዚህም በኋላ የበርበር ሰዎች መጡ አባ ሙሴም ከእርሱ ጋራ ያሉትን መነኰሳት እነሆ የበርበር ሰዎች ደረሱ መሸሽ የሚፈልግ ይሽሽ አላቸው እነርሱም አባታችን አንተስ አትሸሽምን አሉት እርሱም #በሰይፍ የገደለ በሰይፍ ይገደላል ስለሚለው የእግዚእብሔር ቃል እነሆ ያቺን ቀን ለብዙ ዘመናት ስጠብቃት ኖሬአለሁ አላቸው። ወዲያውኑም የበርበር ሰዎች ገብተው በሰይፍ ገደሉት መሸሽ ስላአልፈለጉ ከእርሱ ጋራ ሰባት መነኰሳትም ተገደሉ አንዱ ግን ከምንጣፍ ውስጥ ተሠወረ የእግዚአብሔርንም መልአክ እየ በእጁም አክሊል ነበር እርሱም ቆሞ ይጠብቅ ነበር። ይህንንም ባየ ጊዜ ከተሠወረበት ወጣ፤ የበርበር ሰዎችም ገደሉት የሰማዕትነ ትንም እክሊል ተቀበለ። ወንድሞች ሆይ ከሀዲና ነፍሰ ገዳይ ቀማኛና ዘማዊ  የነበረውን ለውጣ ደግ አባት መምህርና የሚያጽናና ለመነኰሳትም ሥርዓትን የሠራ ካህን እንዳደረገችው በሁሉም አብያተ ክርሰቲያን ስሙ እንዲጠራ እንዳደረገችው #የንስሐን_ኃይሏን_ተመልከቱ። ሥጋውም በአስቄጥስ ገዳም ደርምስ በተባለ ቦታ ለዘላለም ይኖራል ከእርሱም ብዙዎች ድንቆችና ተአምራት ይታያሉ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። #ሰኔ #፳፬ ፤ #በዓለ_ዕረፍቱ_ለአቡነ_ሙሴ_ጸሊም_፡፡ #በአገራችን_በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የአቡነ_ሙሴ_ጸሊም_በዓለ_ዕረፍት_ክብረ_በዓል_የሚከበርባቸው_ጥንታውያን #፪ (ሌሎች ያልጠቀስናቸው ካሉ ጨምሩበት፡፡) ፩. ግብጽ ሰሜን ምዕራብ ኒትሪያን በረሐ ባራሞስ እመቤታችን ገዳም፤ (የቅዱስ አባ ሙሴ ጸሊምና የመምህሩ የቅዱስ አባ ኤስድሮስ የከበረ ዐፅማቸው በክብር ያረፈበት) አድራሻ፤ ግብጽ ሃገር፥ ሰሜን ምዕራብ ኒትሪያን በረሐ፥ ባራሞስ እመቤታችን ገዳም፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ → ግብጽ → ሰሜን ምዕራብ ኒትሪያን በረሐ፡፡ ፪. ሐመር ቡስካ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ወአቡነ ሙሴ ገዳም፤ አድራሻው፤ ደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት፥ ሐመር፥ ቡስካ ተራራ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. አየር ጤና አውቶቡስ ተራ → አርባ ምንጭ → ሐመር → ቡስካ፤ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም ተምሮ ማስተማር ሰንበት ትምህርት ቤት  ዘመናዊ ስቱዱዮ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ተመረቀ ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም ተምሮ ማስተማር ሰንበት ትምህርት ቤት ዘመናዊ ስቱዱዮ ተዘጋጅቶ የሚተላለፉ ማንኛቸውም ትምህርቶች ፣ መዝሙራት ፣ ቪዲዮዎች  ፣ ቃለ መጠይቆች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ  ክርስቲያን  ዶግማና ቀኖናን የጠበቁ  መሆናቸው ሙሉ የአርትኦት / ኦዲቶርያል ስራዎች/   ከገዳማችንና ከሰንበት ትምህት ቤታችን በተመደቡ አባቶች እና መምህራን አማካኝነት ሲረጋገጥ ብቻ እንዲተላለፍ በማድረግ የሚሰራ ሲሆን በዚህ መሠረት  የቤተ ክርስቲያንን ዶግማና ቀኖና የጠበቁ መንፈሳዊ ጽሑፎችን ፣ ትምህርቶችን እና መዝሙራትን  በማቅረብ ምዕመናን ወደ  ንስሀና ወደ ቅዱስ ቁርባን እንዲቀርቡ ለማድረግ ፣ የቤተ ክርስቲያንን ታሪካዊ ቦታዎች ማስተዋወቅ ፣ የቤተ ክርስቲያን አባቶችንና መምህራንን  የህይወት ተሞክሮ ለትውልዱ በማስተዋወቅ አሰረ ፍኖታቸውን እንዲከተሉ ፣ የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያም ፣ የጻድቃን ሰማዕታት ተጋድሎ እና ከእግዚአብሔር የተሰጣቸውን ጸጋ ለማስተዋወቅ ብቻ እንዲተላለፉ በማድረግ የሚሰራ ሲሆን ፣የቤተክርስትያንን ስርዓቶች ለትዉልዱ ለማስተዋወቅ፣ ትዉልዱ ምንነታቸዉን ተረድቶ እንዲጠቀምባቸዉ እና እንዲጠብቃቸው ፣መስማት ለተሳናቸዉ የቤተክርስትያኒቱ ልጆች በቋንቋቸዉ ተከታታይ ትምህርቶችን እንዲማሩ ለማድረግ፤ የቤተክርስትያናችንን፤ የገዳማችንን እና የሰንበት ት/ቤታችንን መንፈሳዊ እና የልማት ስራዎችን ለምዕመና ይህንን ለትዉልዱ እና ለቤተክርስትያን ጠቃሚነቱ የታመነበትን (ዘመናዊ ስቱዱዮ ) ገንብተን ስራ ለማስጀመር፣ ለዚህ የምረቃ ቀን እንድንበቃ ለረዳን ለመድኃኔዓለም ክብርና ምስጋና ይሁን በማለት  ብፁዕነታቸውን እና የገዳሙን አስተዳደር ጽ/ቤት አመስግነዋል ።

ሰኔ 21  ሰኔ ጐልጐታ ወሕንፀተ ቤተክርስቲያን እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ለቅድስተ ቅዱሳን ለድንግል ማርያም ሰኔ ጐልጐታና ሕንፀተ ቤተ ክርስቲያን (ለመጀመሪያ ጊዜ ቤተ ክርስቲያን ለታነጸበት) ክብረ በዓል በሰላምና በጤና አደረሰን አደረሳችሁ፡፡ ‹‹ሰኔ ጐልጐታ ፤ ችግር የምትፈታታ፡፡›› ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያም በዚህች  ቀን (ሰኔ 21) ልጇን ወዳጇን ጐልጐታ በሚባል ቦታ ላይ እንባዋ እንደ ጅረት እስኪፈስ ድረስ ለኃጥአን ምሕረትን ለምናዋለች:: ጌታችንም ‹‹ስምሽን የጠራውን፤ በቃል ኪዳንሽ ያመነውን ሁሉ እምርልሻለሁ፡፡›› ብሎ ቃል ኪዳን ሰጥቷታል፡፡ ሰኔ ጐልጐታን ተመልከት ✤✤ ሕንፀተ ቤተ ክርስቲያን፤ ሰኔ 21 ከእመቤታችን #33ቱ በዓላት አንዱ ሲኾን፤ ሕንጸተ ቤተክርስቲያን ይባላል፡፡ በሐዲስ ኪዳን የመጀመሪያዋ ቤተክርስቲያን በአምላክ እናት ስም የታነጸችው በዚሁ እለት በሰኔ 20 ቀን ነው፡፡ አናጺውም ደግሞ እራሱ ባለቤቱ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን፤ ቦታው በፊልጵስዩስ ነው፤ ቤተክርስቲያኗ የተሰየመችው ደግሞ በእመቤታችን ስም ነው፤ ጥንተ ነገሩስ (ታሪኩ) እንደምን ነው ቢሉ፤ ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና አምላካችን መደኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርቱን ‹‹ሑሩ ወመሐሩ ኵሎ አሕዛበ፤ አሕዛብን ሁሉ ሒዱና አስተምሩ፡፡›› /ማቴ. 28፥19/ ባላቸው ቃል መሠረት ሐዋርያት በወንጌል ያርሷት ዘንድ በዕጣ ተካፍለዋታል:: የሰው ልጅ ድኅነቱ የሚፈጸመው ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ሲቀበል ነውና (ዮሐ. 6፥ 56) አበው ሐዋርያት ቊርባንን በተመረጡ ሰዎች ቤት እያዘጋጁ ቀድሰው  ያቆርቡ ነበር:: በመጀመሪያ በጽርሐ ጽዮን፣ቀጥሎም በተለያዩ ሰዎች ቤት እንዲህ ይከናወን ነበር፡፡ ለጸሎት ሥራ ደግሞ አንዳንዴ ምኵራበ አይሁድን ይጠቀሙ ነበር:: እየቆየ ሲሔድ ግን ከአሕዛብ ያመኑ ሰዎች ቊጥር እጅጉን በመብዛቱ /በተለይ ቅዱስ ዻውሎስ ያሳመናቸው ለጸሎት እያሉ ወደ ጣዖት ቤት መግባት አመጡ::/ በዚህ ምክንያት መምህራን ሕዝቡን ‹‹ካመናችሁ በኋላ እንዴት ወደ ጣዖት ቤት ትገባላችሁ?›› ቢሏቸው ‹‹እኛ ምን እናድርግ! የምንጸልይበት ቤት የለን››ሲሉ መለሱላቸው:: ነገሩ ሲያያዝ ከደጋጉ ሐዋርያት ዻውሎስና በርናባስ ደረሰ:: ወዲያውኑ አንዳንድ ወንድሞች ቤት ‹‹ለምን አናንጽም?›› ብለው ነበር:: ቅዱስ ዻውሎስ ግን ‹‹ሊቀ ሐዋርያቱ ሳይፈቅድ አይሆንም›› አለ:: (ለዚህ ነው ዛሬም ሊቀ ዻዻስ ካልፈቀደ ቤተክርስቲያን የማይታነጸው፡፡) ከዚያ ቅዱሳን ዻውሎስና በርናባስ ሐዋርያቱ ወዳሉበት ሔደው ነገሩን ለቅዱስ ዼጥሮስ አስረዱ:: ሊቀ ሐዋርያቱ ቅዱስ #ዼጥሮስም ‹‹የጌታችን ፈቃዱመኾኑን እናውቅ ዘንድ ተያይዘን ሱባዔ እንግባ›› ብሎ አዋጅ ነገረ:: በዓለም ያሉ ክርስቲያኖች ሁሉ በአንድ ልብ ሱባዔ ገቡ:: በሱባዔያቸው መጨረሻም ክብር ይግባውና ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በኪሩቤል ጀርባ ላይ ሆኖ እልፍ አእላፍ መላአክትን አስከትሎ በግርማ ወደ እነርሱ ወረደ፤እመቤታችን በቀኙ ነበረች፡፡ ኹሉንም ሐዋርያት በሩቅም በቅርብም ያሉትን ደቀ መዛሙርቱን በደመና ጠቅሶ ፊልጵስዩስ በሚባል ሃገር ሰበሰባቸው፡፡ ከዚያም በስተምሥራቅ ከከተማ ወጣ ወዳለ ሥፍራ ወሰዳቸው፡፡ በዚያም ተራርቀው የነበሩ 3 ደንጊያዎች ነበሩ፡፡ 3ቱንም ድንጋዮችን በተአምራት አቀራርቦ አንሥቶ ጎተታቸው፡፡ ድንጋዮቹም እንደሰም ተለጠጡ፣ እንደ ግድግዳም ሆኑ፡፡ ቁመቱን ወርዱን መጥኖ ለሐዋርያቱ ሰጣቸው፡፡ እነርሱም እሳት እንዳየው ሰም በእጃቸው እየለመለሙ (እየሳቡ) ቁመቱን 24፥ ወርዱን 12 ክንድ አድርገው ዕጽብት፥ ግርምት የምትኾን 3 ክፍል ያላትን የመጀመሪያዋን ቤተክርስቲያን በ52 ዓ/ም ሰኔ 20 ቀን አነጹ፡፡ ዳግመኛም የብርሃን ምሰሶ ወረደ፤ ጌታችንም በሰማያዊቷ ኢየሩሳሌም አምሳያ አድርጎ አነጻት፤ ሁለንተናዋም ተጠናቀቀ፡፡ ከዚህም በኋላ ጌታችን ለሐዋርያቱ ‹‹እንግዲህ እናንተም እንዲህ አድርጋችሁ ሥሩ፡፡›› ብሏቸው ዐረገ፡፡ ✜ በማግስቱ ሰኔ 21 ዕለት ደግሞ ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አእላፍ መላእክትን፣ ሰማያውያን ቅዱሳንን እና እናቱን ቅድስት ድንግል ማርያምን ይዞ ወረደ:: ሐዋርያቱ አብዛኞቹ እዛው ሲጸልዩ አድረው ነበርና ጌታችን ከቅዳሴው በፊት 2 ነገሮችን አሳየ፤ አስቀድሞ ቤተክርስቲያኗን በድንግል እናቱ ስም አክብሮ ሥርዐተ ቤተክርስቲያንን አሳየ:: ቀጥሎ ደግሞ ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስን ከመካከል አቁሞ ‹‹አርሳይሮስ›› ሲል ሾመው:: ይኼውም የዓለም ሁሉ ሊቀ ዻዻሳት (ፓትርያርክ) ማለት ነው:: በዚህ ጊዜ ቅዱሳን መላእክት ‹ ‹‹አክስዮስ››(አክዮስ)እያሉ 3 ጊዜ አሰምተው ጮሁ:: አክዮስ ማለት በግዕዙ ‹‹ይደልዎ›› በአማርኛው ደግሞ ‹‹ይገባዋል፤ ያስምርለት›› እንደ ማለት ነው:: ጌታችን ይህን ከከወነ በኋላ ይቀድስ ዘንድ ጀመረ:: አማናዊት ማኅደሩን ድንግል ማርያምን መንበር አድርጎ፣ ቅዱስ ጴጥሮስ እንደ ተራዳኢ ካህን ቆሞ፣ ቅዱስ እስጢፋኖስ ሠራኢ ዲያቆን ኾኖ፣ ሐዋርያት ድንግልን ከበው፣ መላእክተ ብርሃን በክብራቸው ቆመው ጌታችን ቀድሶ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ለወዳጆቹ አቀበለ:: በዚያች ዕለት በፍጡር አንደበት ተከናውኖ ሊነገር የማይችል ደስታ ተደረገ:: ከቅዳሴ በኋላ ጌታችን ሐዋርያትን አዘዛቸው:: ‹‹ከዚህ ቀን ጀምሮ በመላው ዓለም በእናቴ በማርያም ስም አብያተ ክርስቲያናትን አንጹ፤ ይህችን  እለት የሚያከብራትን አከብረዋለሁ::›› ብሏቸው ከድንግል እናቱና ከመላእክቱ ጋር ዐረገ:: ✤✤ ሥርዐተ ማኅሌቱ እንደየደብራችሁ ይትበሃል ትጠሙበበት ዘንድ የሁለቱንም (የላይ ቤት የግምጃ ቤትና የታች ቤት የበአታን) አብነት አስቀምጠንላችኋል፤ በቢጫ የተቀለመው የላይ ቤት (የግምጃ ቤት) አብነትን ለምትከተሉ አድባራት ሲኾን፤ ሰማያዊ የተቀለመው ደግሞ የታች ቤትን (የበዓታን) የአቋቋም ይትበሃል ለምትጠቀሙ ሲኾን፤ ሁለቱም የላይ ቤቱና ያየታች ቤቱ የሚተባበሩበት ላይ ደግሞ ዘግምጃ ቤት ወዘበዓታ ብለን በፈዛዛ ጥቁር አስቀምጠንላችኋል፡፡ መልካም ማኅሌት፨ ኦ አበው ወእማት አኃው ወአኃት ኢትርስዑነ በጸሎተክሙ (በዘጸለይክዋ በዝንቱ ሥርዐተ ማኅሌት) ለትምህርተ ቤትነ ቀ.ደ.ሰ.መድኀኔዓለም ወደ.ት.ቅ.ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት፡፡ ✼ የድንግል እመቤታችን ልመናዋ ክብሯ፣ ጣዕመ ፍቅሯና በረከቷ በሁላችን ላይ ይደርብን:: /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958