uz
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Kanalga Telegram’da o‘tish

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት analitikasi

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 457 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 5 521-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 192-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 457 obunachiga ega bo‘ldi.

02 Avgust, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 75 ga, so‘nggi 24 soatda esa 4 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 23.81% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 7.58% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 681 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 172 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 25 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 03 Avgust, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 457
Obunachilar
+424 soatlar
-17 kunlar
+7530 kunlar
Postlar arxiv
እንኳን  #ለብርሃን_መልአክ_ከሣቴ_ምሥጢር_ለሆነው #ቅዱስ_ዑርኤል_ሊቀ_መልአክ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ #ሐምሌ ፳፪፤ #በዓለ_ቅዱስ_ዑራ(ር)ኤል_ቅዳሴ_ቤቱ_የሚከበርበትና (ሐምሌ ፳፩ ደግሞ ለዕዝራ ጽዋዕ ልቡና ያጠጣበት ነው፡፡) #ዑራኤል ማለት “ብርሃነ እግዚአብሔር” ማለት ነው። “ዑራኤል ሥዩም ላዕለ ኵሎሙ ብርሃናት፤ #ዑራኤል በብርሃናት ላይ ሁሉ የተሾመ ነው” እንዲሁም “ዑራኤል አሐዱ እመላእክት ቅዱሳን እስመ ዘረዓም ወዘረዓድ፤ ከቅዱሳን መላእክት አንዱ ዑራኤል በመብረቅና በነጎድጓድ የተሾመ ነው” እንዲል፡፡ (ሄኖክ ፮፥፪) ከሊቃነ መላእክት አንዱ መሆኑንና ፍርሃት ረዓድ ላለባቸው ረዳታቸው እንደሆነ የመላእክትን ነገር የተናገረ ሄኖክ ነግሮናል፡፡ “የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሠፍራል” በማለት ነቢዩ ዳዊት እንደተናገረ እግዚአብሔርን በሚፈሩና በሚያከብሩት ሰዎች ጭንቀት ጊዜ በመካከላቸው እየተገኘ ያጽናናቸዋል። (መዝ.፴፫፥፯) ምሥጢር ይገልጥላቸዋል፤ ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ይጠብቃቸዋል። #ቅዱስ_ዑራኤል ምሥጢር ገላጭ ነው። ምሥጢር ማናገር #የመንፈስ_ቅዱስ ሥራ ቢሆንም የተሠወረውን መግለጥ፣ በአዲስ ቋንቋ ማናገር ለመላእክት የተሰጠ ጸጋቸው መሆኑም ግልጽ ነው። በዚህ ሀብትነትም የተወደደ ሥራ ለሚሠሩና እንዲያውቁ ለተፈቀደላቸው ሁሉ #ቅዱስ_ዑራኤል ምሥጢር ይገልጣል፤ #ለዕዝራ_ሱቱዔል የሆነለትም እንዲህ ነው። #መልአኩ_ዑራኤል “አፍህን ክፈት፤ እኔም የማጠጣህን ጠጣ” … ብሎ አእምሮ ለብዎውን ገልጦለታል። (ዕዝ.ሱት. ፲፫፥፴፰) የዚህን ተአምር መታሰቢያ ሐምሌ ፳፪ በየዓመቱ ቤተ ክርስቲያናችን ታከብራለች። ለሄኖክም ምሥጢረ ሰማይንና ዕውቀትንም ሁሉ የገለጠለት እርሱ እንደሆነ በመጽሐፈ ሄኖክ ተጽፏል። (ሄኖክ ፳፰፥፲፫) አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ልቡናውን ያበራለት ይህ መልአክ እንደሆነ ገዳሙ ባሳተመው ገድሉ ላይ ተጽፏል። በዚህ አገልግሎቱም ሊቃውንቱ #ከሣቴ_ምሥጢር ይሉታል። አፋቸውን ከፍተው የምስጋና ቃል ለሚናገሩ ሁሉ ክብርና ጥበቃን ከመላእክት እንደሚቀበሉ ከላይ በተመዘገበው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ለዕዝራ ሱቱዔል የተደረገለትን መረዳት ይገባል። ዕዝራ ለረጅም ወራት እግዚአብሔርን ደጅ ጸንቶ ነበር። የነገሩትን የማይረሳ እግዚአብሔር መልአኩን ላከለት፤ የሰማዩን ምሥጢርም ዐወቀ። ይህ መልአክ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ግብጽ ተራሮች በተሰደደች ጊዜ በመካከላቸው ሁኖ መንገድ ይመራቸው እንደነበር በድርሳነ ዑራኤል ተገልጿል። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቀራንዮ አደባባይ ደሙን በፈቃዱ ሲያፈስም በጽዋዕ የተቀበለው መልአክ እርሱ መሆኑን በዕለተ ዓርብ በሚነበበው ግብረ ሕማም ተጽፏል። ሐምሌ ፳፪ ከሚታሰበው በዓሉ በተጨማሪም ፤ በሊቀ መላእክትነት የተሾመበትን በማሰብ ጥር ፳፪ ቀን፣ ከጌታችን የፈሰሰውን ደም በጽዋዕ የተቀበለበትን ቀን በማሰብ መጋቢት ፳፯ ቀን ይከበራል። የሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል አማላጅነትና ተራዳኢነት አይለየን፤ አሜን! /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

#በአዲስ_አበባ_በኢትዮጵያና_በመላው_ዓለም_ክብረ_በዓሉ_የሚከበርባቸው_ #፳፪ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ (ሌሎች ያልጠቀስናቸው ካሉ አሳውቁን) ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #በአዲስ_አበባ_ክብረ_በዓሉ_የሚከበርባቸው_ #፲፫) #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. ደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤ/ክ፤ አድራሻው፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ካዛንቺስ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ካዛንቺስ፡፡ ፪. ኤረር በር ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ዑራኤል፡፡ አድራሻው፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ኤረር በር፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ገርጂ→ ኤረር በር፤ ፫. አዲስ ሰፈር አንፎ መንበረ ብርሃን ቅዱስ ዑራኤል፣ መጥምቁ ዮሐንስና ልደታ ለማርያም፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ አዲስ ሰፈር፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ኮልፌ → አንፎ፡፡ ፬. ፉሪ ደብረ ገነት ቅዱስ ዑርኤል፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ፉሪ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ኮልፌ → ፉሪ፡፡ ፭. ጎፋ መብራት ሀይል ኮንዶሚኒየም መካነ ብርሃን ቅዱስ ዑራኤል ቤ/ክ አድራሻ፤ ጎፋ መብራት ሀይል ኮንዶሚኒየም ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ጎፋ ካምፕ → ጎፋ መብራት ሀይል ኮንዶሚኒየም ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #እንዲሁም_በድርብነት_፤ ፮. ድልበር መካነ ጎልጎታ መድኀኔ ዓለም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ ቶታል/ድል በር/ (ጎጃም በር)፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → አዲሱ ገበያ → ቶታል፡፡ ፯. አስኮ ደብረ መድኀኒት መድኀኔ ዓለምና ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንየ ክፍለ ከተማ፥ አዲስ ሰፈር፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ አራዳ /ከአቡነ ጴጥሮስ/ → አስኮ፡፡ ፰. አውግስታ ደብረ ጽዮን ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ አውግስታ ሸሚዝ ፋብሪካ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ኮልፌ → አውግስታ ሸሚዝ ፋብሪካ፡፡ ፱. ደብረ ተአምራት ዳግማዊት ጻድቃኔ ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ታቦት ማደርያ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ኮልፌ → ታቦት ማደርያ፡፡ ፲. ቱሉ አቦ ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፤ ቅዱስ ዑራኤልና መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ቱሉ አቦ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → አቃቂ → ቱሉ አቦ፡፡ ፲፩. መካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚከኤል፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ መካኒሳ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → መካኒሳ፡፡ ፲፪. ላፍቶ ኢያሪኮ መድኀኔ ዓለምና መጥምቀ መለኮት ዮሐንስ፤ አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ላፍቶ፡፡ ታክሲ፤ ከፒያሳ → መካኒሳ → ላፍቶ፡፡ ፲፫. ሐመረ ወርቅ ማርያምና አርሴማ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ወርቁ ሰፈር፡፡ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ቃሊቲ፡፡ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #በሃገራችን_በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከበርባቸው_ #፮ #ገጥንታውያን_ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩ መንዝ ዕመጓ ደብረ ቆጵሮስ ኢየሱስ ቅዱስ ዑርኤል ገዳም፤ አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ መንዝ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → መንዝ፡፡ ፪. ግሸን ቅዱስ ዑርኤል፤ አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ግሸን ደብረ ከርቤ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ → ግሸን፡፡ ፫. ጎንደር ደብረ ኀይል ቅዱስ ዑርኤል ወበዓታ፤ አድራሻ፤ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አስኮ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር፡፡ ፬. ደብረ ታቦር አንቀፀ አድህኖ ቅዱስ ዑርኤል፤ አድራሻ፤ ደ. ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ደብረ ታቦር ከተማ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አስኮ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ታቦር፡፡ ፭. የወልዲያ ቅዱስ ዑርኤል ፤ አድራሻ፤ ሰሜን ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ወልዲያ ከተማ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አስኮ አውቶቡስ ተራ → ወልዲያ ፡፡ ፮. ደብረ ብርሃን ደብረ ገነት ቅዱስ ዑርኤል ፤ አድራሻ፤ ሰ. ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ደብረ ብርሃን ከተማ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አስኮ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ብርሃን፡፡ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #ከኢትዮጵያ_ውጭ_የሚከበርባቸው_ #፫ #ገጥንታውያን_ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. ጀርመን ደብረ ኃይል ቅዱስ ዑርኤል ወቅዱስ ያሬድ፤ አድራሻ፤ ጀርመንና አካባቢው ሀገረ ስብከት ፪. ደብረ ብርሃን ቅዱስ ዑርኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አሜሪካ ሜንሶታ ፫. ደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑርኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አሜሪካ ሎሳንጀለስ ካሊፎርኒያ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

ሐምሌ ገብርኤል በዓለ ንግሥ 2017 ዓ.ም /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

ሁለተኛ ቀን ጉባኤ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ። ሉቃ ፩፥፲፱ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/F
+9
እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ። ሉቃ ፩፥፲፱ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958