en
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Open in Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 380 subscribers, ranking 5 588 in the Religion & Spirituality category and 2 193 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 380 subscribers.

According to the latest data from 10 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 43 over the last 30 days and by -3 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 23.36%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 9.42% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 592 views. Within the first day, a publication typically gains 1 449 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 23.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 11 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

15 380
Subscribers
-324 hours
-27 days
+4330 days
Posts Archive
እንኳን ለጥቅምት መድኀኔዓለም ክብረ በዓል (ለመጋቢት 27 ጥንተ ስቅለት ልዋጭ በዓል)ና ለአቡነ መብዓ ጽዮን ክብረ በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡ በሃገራችን ከሚገኙ የመድኀኔዓለም ገዳማትና አድ
+2
እንኳን ለጥቅምት መድኀኔዓለም ክብረ በዓል (ለመጋቢት 27 ጥንተ ስቅለት ልዋጭ በዓል)ና ለአቡነ መብዓ ጽዮን ክብረ በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡ በሃገራችን ከሚገኙ የመድኀኔዓለም ገዳማትና አድባራት ጥቂቶቹ፤ ፤ ስብስብ 1፤ ፠ ለየብቻቸው ያሉት፤ ዋልድባ አበረንታት መድኀኔዓለም ገዳምና ኤልሻማ ደብረ ማኅቶት መድኀኔዓለም ቤ.ክ. ፠ አንድ ላይ ያሉት፤ ✤1. ዋልድባ አበረንታት መድኀኔዓለም ገዳም፤ ✤2.ላሊበላ መድኀኔዓለም ✤3. ጎንደር መንበረ መንግሥት መድኀኔዓለም ✤4. መንዳባ አቡነ ያሳይ መድኀኔዓለም፤ ጣና ✤5. ሽረ እንዳሥላሴ መድኀኔዓለም ወመስቀል ክብራ ✤6. ቆላድባ መድኀኔዓለም፤ ጎንደር ከተማ አጠገብ ✤7.ቦሌ ደብረ ሳሌም መጥምቁ ዮሐንስ፤ (የመድኀኔዓለም ታቦት በድርብ አለ) ✤ 8.ድሬዳዋ መድኀኔዓለም ✤9.ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም

#በየቀኑ_ምግብ_ስንመገብ_የምናስባቸው_ታላቁ_አባት_ዛሬ_ዓመታዊ_ክብረ_በዓላቸው_ነው፡፡ ምግብ ተመግበን ‹‹ስብሐት ካልን›› በኋለ ‹‹#በእንተ_አቡነ_አቢብ_ብለን የምናስባቸው፡፡ ✤✤ ሰው ቢረሳ ቢረሳ ምግቡን አይረሳምና በእንተ(ስለ) አባ ቡላ ብሎ በሚመገብ ጊዜ ያሰበውን ማርልኝ ብለው ታላቅ ቃል ኪዳንን መድኀኔዓለም የሰጣቸው አባት ናቸው፡፡ በዚህም ኹል ቀን /ከተመገብን ‹‹ስብሐት ካልን›› በኋላ ስለ አባ ቡላ/አቢብ/ ብለን የምናዘክረው ታላቅ አባት ነው/ **** እንኳን ለታላቁ ቅዱስ አባት አባ ቡላ (አቡነ አቢብ) በዓለ ዕረፍት በሰላም አደረሳችሁ፡፡ ✤ አቡነ አቢብ በሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ በነገሠ ዘመን የነበረ፤ እንደ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰማዕት የኾነና 3ት ጊዜ ሞቶ 3 ጊዜ የተነሣ (በተጋድሎ ሕይወቱ 10ር ጊዜ ሞቶ የተነሣ) ታላቅ ሰማዕተ ጽድቅ ነው፤ በሃገራችን በኢትዮጵያ በስማቸው 3ት ታላላቅና ጥንታዊ ገዳማት አሏቸው፡፡ ✣✣ #የስሙ_ትርጓሜ፣ ልደቱ፣ ጥምቀቱና እድገቱ፤ ቡላ ማለት አቢብ ማለት ነው፤ ቡላ ማለት ትርጓሜውም የእግዚአብሔር አገልጋይ ማለት ሲኸን፤ አቢብ ማለት የብዙዎች አባት፥ የመልካም ሥራ ኹሉ ባለቤት ማለት ነው፡፡ ገድሉ አብ ክቡር፤ ወትሩፈ ትጋህ አባ ቡላ ዘውእቱ አቢብ መክብበ ኵሉ ሠናያት (የተከበረ አባት፥ በትሩፋት የተጋ፥ የመልካም ነገሮች ኹሉ አባት) ይለዋል፡፡ አቡነ አቢብ የተወለደው በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ አካባቢ በሮም ሉፊ ከሚባል አውራጃ የካቲት 16 ነው የተወለደው፤ ወላጆቹ ቅዱስ አብርሃምና ቅድስት ሐሪክ ሲባሉ እጅግ ጽኑዕ ክርስቲያኖች ነበሩ፤ ልጅም አልነበራቸውም፤ በዘመነ ሰማዕታት በመክስምያኖስ ዘመን ስደት በሆነ ጊዜ በስደት በበረሃ ሳሉ በመልአክ ብሥራት ወለፉት፤ ቅዱሱ ሲጸነስም ማንም ሳይተክለው የበቀለው ዛፍ ላይ መልአኩ በሮማይስጥ ቋንቋ "ቡላ ገብሩ ለእግዚአብሔር: ወቅዱሱ ለአምላከ ያዕቆብ: ዘየኀድር ውስተ ጽዮን" (‹‹ቡላ የእግዚአብሔር አገልጋይ በጽዮንም አድሮ የሚኖር የያዕቆብ ፈጣሪ ያከበረው›) የሚል የብርሃን ጽሑፍ ጽፎበት ወላጆቹ ዐይተዋል:: ቅዱሱ የተወለደው በዘመነ ሰማዕታት በመኾኑ ለ1 ዓመት ሳይጠመቅ ከቆየ በኋላ እመቤታችን ለሮሙ ሊቀ ዻዻሳት አባ ሰለባስትርዮስ ውደ በረሃ ወርዶ እንዲያጠምቀው አዘዝችው፤ ሊያጠምቀው ሲምል ሕፃኑ ተነስቶ እጆቹንም ዘርግቶ "አሐዱ አብ ቅዱስ: አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውዕቱ መንፈስ ቅዱስ …." ብሎ አመስግኖ ተጠመቀ:: ከሰማይም ሕብስትና ጽዋዕ ወርዶላቸው ሊቀ ዻዻሳቱ ቀድሶ ሁሉንም አቆረባቸው:: የሕፃኑ ወላጆች "ለልጃችን ስም አውጣልን" ቢሉት "ቡላ" ብሎ ሰየመው:: እነርሱም በዛፉ ላይ የተገለጸውን ምሥጢሩን ያውቁ ነበርና አደነቁ:: ✣✣ #ሰማዕትነት_ ውላጆቹ ገና የ10 ዓመት እድሜ ላይ እንዳለ ድንገት ሕዳር 7 ቀን ተከታትለው ዐረፉ፡፡ ቅዱሱን ሕፃንም ጎረቤቶች ማሳደግ ጀመሩ፤ ሃገረ ገዢውም ለጣዖት ስገዱ ብሎ አዋጅ ባስነገረ ጊዜ በሕፃን አንደበቱ አምልኮተ ክርስቶስን ሰበከ:: በዚህ የተበሳጨ መኮንኑ ስቃያትን አዘዘበት፤ ትላልቅ ችንካሮችን ቸንክረው በጅራፍ ገረፉት፥ በዘንግ ደበደቡት:፥ ቆዳውን ገፈፉት፥ በመጋዝ ቆራርጠውም ጣሉት በሾተሎችና በጦሮች መካከል አድርገው በመንኮራኩር ውስጥፈጩት፡፡ ነገር ግን ኀይለ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበርና ከሞት ተነሳ፡፡ ዳግመኛም መኮንኑ የሕፃኑን ሰውነቱን አሥሮ በመሬት ላይ እንዲጎትቱት አዘዘ አሁንም ግን መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል መጥቶ አዳነው፣ ያለ ምንም ጉዳት ፍጹም ጤነኛ አደረገው፡፡ ቅዱስ ቡላ ዳግመኛም ወደ ሌላ ከሃዲ መኰንን ዘንድ ሄዶ እርሱንም ከነአምልኮ ጣዖቱ ገሠጸው፡፡ ያም ከሃዲ መኰንን ብዙ ካሠቃየው በኋላ ሚያዝያ 18 ቀን ራሱን በሰይፍ አስቆረጠው፤ ነገር ግን አሁንም ለ2ኛ ጊዜ ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ከሰማይ ወርዶ ቅዱስ ቡላን ከሞት አስነሣው፡፡ ወደ አንድ ገዳምም ወስዶ የምንኵስና ልብስንና አስኬማን በመስቀል ምልክት አለበሰውና ‹‹ከቅዱሳን ጻድቃን አንድነት ትሆን ዘንድ እግዚአብሔር አዞሃል›› አለው፡፡ አባ ቡላም ከአንድ ደረቅ ተራራ ላይ ወጥቶ በታላቅ ተጋድሎ መኖር ጀመረ፡፡ ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ በነገሠ ጊዜ ሳያውቅ በመንገድ ሊያልፍ ሲል መልአኩ መጥቶ እንዲሰግድለት አድርጓል፡፡ ✣✣ #ገዳማዊ_ሕይወቱና_ተጋድሎው_ ቅዱስ ቡላ ሰማዕትነቱን ከፈጸመ በኋላ ቅዱስ ሚካኤል በአክሊላት አክብሮ ወስዶ በገነት አኖረው:: ከሰማዕታትም ጋር ደመረው:: በዚያም ቡላ ቅዱስ ጊዮርጊስን ተመልክቶ ተደነቀ:: መንፈሳዊ ቅንዐትን ቀንቷልና "እባክህን ወደ ዓለም መልሰኝና ስለ ፍቅርህ እንደ ገና ልጋደል" ሲል ጌታን ለመነ:: ጌታችን ግን "ወዳጄ ቡላ! እንግዲህስ ሰማዕትነቱ ይበቃሃል:: ሱታፌ ጻድቃንን ታገኝ ዘንድ ግን ፈቃዴ ነውና ሒድ" አለው:: ቅዱስ ሚካኤልም የቅዱስ ቡላን ነፍስ ከሥጋው ጋር አዋሕዶ: ልብሰ መነኰሳትንም አልብሶ ግብጽ በርሃ ውስጥ አኖረው:: አባ ቡላ ወደ በርሃ ከገባ ጀምሮ ዐርብ ዐርብ የጌታችን የመድኀኔ ዓለምን ሕማማት እያሰበ ራሱን ያሰቃይ ገባ:: ራሱን ይገርፋል: ፊቱን በጥፊ ይመታል: ሥጋውን እየቆረጠ ለአራዊት ይሰጣል: ከትልቅ ዛፍ ላይ ተሰቅሎ ወደ ታች ይወረወራል:: ሌላም ብዙ መከራዎችን የጌታን ሕማማት እያሰበ ይቀበላል:: ጌታችንም ስለ ክብሩ ዘወትር ይገለጥለት ነበር፤ የሚታየውም እንደ ተወለደ፥ እንደ ተጠመቀ፥ እንደ ተሰቀለ፥ እንደ ተነሳ፥ እንዳረገ እየሆነ ነበር፡፡ ስለ ጌታ ፍቅርም ብለው፤ ✤ ምንም ነገር ሳይቀምስ፤ መዝሙረ ዳዊትን ጥራዝ እስከ ጥራዝ (15ውን መዝሙራት) እየጸለየ ለ42 ዓመታት ጹሟል:: ✤ በአንዲት ዕለትም የጌታችንን መከራውን አስበው ሰይፍ አምጥተው ስለቱን ወደላይ አቁመው በአንጻሩ ከተከሉት በኋላ ናላው ፈሶ እስኪያልቅ ድረስ አንድ ዓመት በራሱ ተዘቅዝቆ ኑሯል፤ ‹‹ወኀልቀ ናላሁ›› እንዲል ገድሉ፡፡፡፡ ✤ ፊታቸውን እየጸፉ ሥጋቸው ተቆራርሶ እስኪወድቅ ድረስ ጀርባቸውን ሰባት መቶ ጊዜ እየገረፉ ኖሩ፡ ✤ ከረጅም እንጨት ላይ በመውጣት ከዚያ ላይ ራሱን ወደታች ሁልጊዜ ይወረውር ነበር፤ ጦርም ሰክቶ ከላይ ይወድቅበት ነበር፤ ነገር ግን ጦሩ እየተጣመመ አይገድለውም ነበር፤ በአንዲት ቀንም ከረጅም ዛፍ ላይ በተወረወረ ጊዜ ሰይጣን በረታበትና ገደለው፡፡ በአንዲት ቀንም ከረጅም ዛፍ ላይ በተወረወረ ጊዜ ሰይጣን በረታበትና ገደለው፡፡ ነገር ግን ጌታችን ተገልጦለት ከሞት አስነሣውና ‹‹ከእንግዲህ ስምህ ቡላ አይሁን አቢብ (ሃቢብ) ተባል እንጂ የብዙዎች አባት ትሆናለህ›› አለው፡፡ "እስከ ይቤሎ አምላክ ቃለ አኮቴት ማሕዘኔ፤ ረሰይከኑ ለባሕቲትከ ኩነኔ፤ ዘመጠነዝ ታጻሙ ነፍስከ በቅኔ፡፡" እንዲል::

✣✣ #በዓለ_ዕረፍቱ_ አቡነ አቢብ ታላቁ ዕብሎይን ጨምሮ በርካታ ደቀ መዛሙርትን አፈራ:: ከእመቤታችን ጋርም ዕለት ዕለት እየተጨዋወተ ዘለቀ:: በተጋድሎ ሕይወቱም ከ10 ጊዜ በላይ ሙቶ ተነስቷል:: በዚህች ቀን ሲያርፍ ገዳሙ በመላእክት ተሞላ:: እመቤታችንም ከእልፍ አእላፍ ቅዱሳን መላእክት ጋራ መጥታ ‹‹የእኔና የልጄ ወዳጅ አቢብ ሆይ! ሰላምታ ይገሃል›› አለቻቸው፡፡ በዚህም ጊዜ ከበድናቸው ቃል ወጥቶ ‹‹የሰማይና የምድር ንግሥት እመቤቴ ሆይ! ሰላምታ ይገባሻል›› አላት፡፡ እመቤታችንም በከበሩ እጆቿ ዳሰሰቻቸውና ከሞት አስነሣቻቸው፡፡ ሰው ቢረሳ ቢረሳ ምግቡን አይረሳምና በእንተ(ስለ) አባ ቡላ ብሎ በሚመገብ ጊዜ ያሰበውን ማርልኝ ብለው የለመኑትን ልመና አምላካችን ተቀብሎላቸው ዛሬም ድረስ፤ ወደፊትም በዚህ በቃል ኪዳናቸው የሚያስምሩ ሆነዋል፤ ጌታችንም ከድንግል እናቱ ከእልፍ አእላፍ ቅዱሳን መላእክት ጋራ መጥቶ ልዩ የሆኑ አክሊላትን የሚያበሩ ልብሶችንም ይዞ መጥቶ ተገለጠላቸውና ‹‹ወዳጄ አቢብ ሆይ! ወደማያልቅ ተድላ ደስታ ደስ አሰኝህ ዘንድ ወደ እኔ ልወስድህ መጣሁ፣ ስምህን ለሚጠራ፣ መታሰቢያህን ለሚያደርግ እኔ ኃጢአቱን አስተሠርይለት ዘንድ በራሴ ማልኩልህ፣ ወይም በስምህ ለተራቆተ የሚያለብሰውን፣ ለተራበ የሚያጠግበውን፣ለተጠማ የሚያጠጣውን፣ የገድልህን መጽሐፍ የሚጽፈውን የሚያነበውንና የሚሰማውን፣ በጸሎትህም የሚታመኑትን ሁሉ እስከ ዐሥር ትውልድ እምራቸዋለሁ፤ አቅም ቢያጣ 'አምላከ አቢብ ማረኝ' ብሎ 3 ጊዜ በዕለተ ዕረፍትህ የሚለምነኝን፤ በስምህ እንኳን ቁራሽ የሚበላውን ሁሉ እምርልሃለሁ" የሚል ድንቅ ቃልኪዳን ሰጣቸውና አቅፎ ቢስማቸው ቅድስት ነፍሳቸው ከሥጋቸው ተለየች፡፡ የመላእክትን ዝማሬ እያሰማቸው በደረቱ አቅፎ ወደ ሰማያዊት ኢየሩሳሌም ወሰዳቸው፡፡ በዚሁ ዕት መታሰቢያ የሚደረግላቸው አባ ዕብሎይም የአቡነ አቢብ ደቀ መዝሙር ናቸው፤ የአቡነ አቢብና የአባ ዕብሎይ በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን፡፡ ‹‹ሰላም ለዝክረ ስምከ ዘተጸውዓ እምቅድም፤ በመርኅበ ቤቱ ለአብ ኀበ ዘበቈለ ኦም፡፡ አቢብ አቡየ ዝክረ ስምከ ጥዑም፤ በዘሊተ ሥጋሁ ወበዘዚአየ አጽም፤ ተጽሕፎ ይትረከብ በሐዳስ ዓለም፡፡›› /መልክአ አቡነ አቢብ ቀዳማይ/ /ምንጭ፤ የቃል ትምህርት በላስታ ላሊበላ አበው፤ ገድለ አቡነ አቢብ፤ የዲ.ን ዮርዳኖስና ከገድላት አንደበት ገጽ/ /ይህንን ታሪክ ከቦታው ድረስ ሂዶ ከገድሉና ከሌሎችም ጽሑፎች አቀነባብሮ ያዘጋጀልን ወንድማችንን አምላከ አቡነ አቢብ ወዕብሎይ በረድኤት በጤና ይጠብቅልን፡፡/ #ስዕሉ_፤ ✤✤ የአቡነ አቢብ ቤ.ክ በሃገራችን የሚገኝባቸው ቦታዎች፤ ✣ ላሰታ ዳሪያ አቡነ አቢብ፡፡ ከ1500ዓመታት በላይ ያስቈጠረ፤ ከደረቅ ዐለት ላይ ፈዋሽ ጠበል የሚፈልቅበት፤ ላስታ ዳሪያ አቡነ አቢብ ዋሻ ቤ.ክ.፤ ከላስታ ላሊበላ በቅርብ የሚገኝ ሲኾን፤ አፄ ካሌብ ከመንገሳቸውና በላስታ አካባቢ የሚገኙትን ውቅር አብያተ ክርስቲያናት (ቂርቆስ፣ ዐርባዕቱ እንሰሳ፣ ብልብላ ጊዮርጊስ፣…) ከመፈልፈላቸውም 7 ዓመት ቀድሞ በአባ ሳዊሮስ (ታውረስ?) አማካኝነት በተዓምራት በሰይፍ ነው የገመሱት፡፡ በአቡነ አቢብ ቤ.ክ ውስጥ ብዙ ተዓምራቶች ሲኖሩ ማንኛውንም የጆሮ በሽታ የሚያድን ሴቴ ጭረት የሚባል ቄጠማ ነው፤ በመቅደሱ ውስጥ ከደረቅ ዓለት (ድንጋይ) ላይ የሚወጣ ተዓምራታዊ ጸበል አለ፡፡ በቅርቡ ምዕመናኑ ሁሉ ገብቶ እንዲያየው ተደርጓል፡፡ ………5ት አባቶና 1 እማሆይ አገልጋይ ብቻ ያሉት ገዳም፤ ቅዳሴ የሚቀደሰው በየወሩ በ25፣ በፍልሰታ በዓል፣ በሰንበት /በ15ቀን አንዴ፤ ከጃሮ ሚካኤል ጋር በፈረቃ/ ይቀደሳል፡፡……. በልደት ወደ ላሊበላ የምትሔዱ ምዕመናን፣ የጉዞ ማኅበራት ከላሊበላ በቅርብ ስለሚገኝ ተባርካችሁ ኑ፡፡ ✣ አቡነ አቢብ (ጎንደር አርማጭሆ ከደብረ መጕና አቡነ አብሳዲ ገዳም አጠገብ) ✣ አቡነ አቢብ (ጎጃም ዳንግላ አካባቢ)፡፡

#ጸሎተ_ምሕላ_ ከሰኞ - እሑድ (ከቅምት 24 -30) ለ፯ት ቀናት በማኅበረ ሥላሴ አባቶቻችን ጾም፣ ጸሎት፣ ስግደት፣ ጸሎተ ምሕላ በታዘዘው መሠረት በደብራችን በቀጨኔ ደብረ ሰላም እንዲሁም በምስካየ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም አዳራሽ #ከጥቅምት_24 - ጥቅምት 30 #ከምሽቱ_12- 1 ሰዐት የምሕላ ጸሎት ስለሚደርስ ሁላችሁም እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ የቀ.ደ.ሰ መድኀኔዓለም ወደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት፨

#ከጥቅምት_24-30 #ጾም (እስከ 9 ሰዐት)፣ ጸሎት፣ ምሕላ፣ ስግደት፡፡ #እንኳን_ሰዉ_ከብቱ_ሥርዐት_ካለው_ድንቅና_ዕፁብ_የሆነው_የማኅበረ ሥላሴ ገዳም አበው አዘዋል፡፡
+4
#ከጥቅምት_24-30 #ጾም (እስከ 9 ሰዐት)፣ ጸሎት፣ ምሕላ፣ ስግደት፡፡ #እንኳን_ሰዉ_ከብቱ_ሥርዐት_ካለው_ድንቅና_ዕፁብ_የሆነው_የማኅበረ ሥላሴ ገዳም አበው አዘዋል፡፡

ሥርዐተ ማኅሌት ዘወርኀ ጽጌ (‹ዘላይ ወዘታች› ቤት) (፪ኛ ዙር ዓመት፤ ፬ኛ ሳምንት፥ዘጥቅምት ፳፫) በዓለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰማዕት፡፡ ✤፠ ልዩ አዋጅ ዘወርኃ ጽጌ ✤ ፠  ማኅሌቱ ሥርዐት የላይ ቤት
+5
ሥርዐተ ማኅሌት ዘወርኀ ጽጌ (‹ዘላይ ወዘታች› ቤት) (፪ኛ ዙር ዓመት፤ ፬ኛ ሳምንት፥ዘጥቅምት ፳፫) በዓለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰማዕት፡፡ ✤፠ ልዩ አዋጅ ዘወርኃ ጽጌ ✤ ፠  ማኅሌቱ ሥርዐት የላይ ቤት (የጎንደር መካነ ነገሥት ግምጃ ቤት ማርያም አብነት) እና የታች ቤት (የጎንደር ደብረ ኀይል ዑራኤል ወደብረ ጥበብ በዓታ ለማርያምን አብነት) የሚያደርግ ሲኾን፤ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ የማኅሌት ቁመትም የላይ ቤትን አብነት የተከተለ ሲኾን፤ የዚቁ ወረብ ግን የደብሩን የራሱን(የሸዋን) የተከተለ ነው፤  የላይ ቤት ቁመት የሚቆሙ አድባራት ዘግምጃ ቤት የሚለውን እንዲከተሉ፤ የታች ቤትን ቁመት የሚቆሙ አድባራት ዘበዓታ የሚለውን እንዲከተሉ እያሳሰብን፡፡ የዚቁ ወረብን ግን የቀጨኔ ደብረ ሰላም የቤቱን ቀለም አስቀድመን ቀጥሎ ደግሞ ዓዲ (ወይም) በማለት የጎንደርን ስላስቀመጥነው እንደ ደብራችሁ ይትበሃል መርጣችሁ እንድትጠቀሙበት ኹሉንም አስቀምጠነዋል፡፡

#ዝክረ_ሰማዕታት_ #ጥቅምት_16 #ከጸሎተ_ምሕላ_ወደ_ጸሎተ_ፍትሐት_ በሰሞኑን በቤተክርስቲያንና በምዕመናን ላይ በደረሰው ጥፋትና ግድያ ምክንያት ሕይወታቸውን ላጡ ምዕመናን ነገ እሑድ ጥቅምት 16/2
+3
#ዝክረ_ሰማዕታት_ #ጥቅምት_16 #ከጸሎተ_ምሕላ_ወደ_ጸሎተ_ፍትሐት_ በሰሞኑን በቤተክርስቲያንና በምዕመናን ላይ በደረሰው ጥፋትና ግድያ ምክንያት ሕይወታቸውን ላጡ ምዕመናን ነገ እሑድ ጥቅምት 16/2012 ዓ.ም. በመላው በሃገራችንና በዓለም በሚገኙ አብያተ ክርስቲያኖችንና ጸሎተ ምሕላ እንዲካሄድ ቅዱስ ሲኖዶስ አዘዘ፡፡ *በተለይም በአ/አ ከቅዳሴ መልስ ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ #4#ኪሎ_በመንበረ_ጸባዖት_ቅድስት_ሥላሴ_ቤ.ክ. ብፁዓን ወቅዱሳን ፓትርያርኮች ፥ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትና ኤጲስ ቆጶሳት፤ የታላላቅ ገዳማት አበምኔቶችና አባቶች በተገኙበት ጸሎተ ፍትሐት ይከናወናል፡፡ **ስለሆነም በዕለቱ ምዕመናን የተዋሕዶ ልጆች በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት በመገኘት ሰማዕታቱን በጸሎት እንድናስብ ቅድስት ቤ/ን ታሳስባለች፡፡ ***ስለ ቤተ ክርስቲያን ሲሉ እስከ ሞት የታመኑ የታረዱላት የባሌ ሮቤ ሰማዕታት ክርስቲያኖችም ትናንት በታረዱለት በሙሽራው በቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ንግሥ በዓል በቤተ ክርስቲያኑ ቀብራቸው ተፈጽሟል፡፡ ዘመነ ጽጌንና ፍሬ የሆኑትን ሰማዕታት፤ ወርኃ ጥቅምትና እንደ ማር ለቤተ ክርስቲያን ጣፋጭ የሆኑላትን፥ እንደ ሰምም ሆነው የበሩላትን፤ ሙሽራው ገብረ ክርስቶስንና ስለ ቤተ ክርስቲያን ብለው ሙሽራ ሆነው የተሰየፉትን ፥ በገብረ ክርስቶስ ላይ ውሾች እንደቧጨሩትና ስለ ገብረ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ሲሉ በዱላ የተቧጨሩትን፥ የተደበደቡትን …… ሌሎችንም እያስማማችሁና እያመሣጠራችሁ ፠ ባለቅኔ መምህራን ቅኔ ተቀኙላቸው፤ ፠ ባለ ግጥም ገጣምያን ግጥሙን ሰድሩላቸው፤ ፠ ባለ ሥነ ጽሑፍ ጸሓፍያን ጽሑፍ ጻፉላቸው፤ ፠ ባለ ድርሰት ደራስያን ድርሰት ድረሱላቸው፤ የቤተ ክርስቲያን ልጆች በክብር በሰማዕትነት አርፈዋልና፡፡ የአባቶቻችን አምላክ በምሕረቱ ይለመነን፤ ስለ አባቶቻችን ብሎ እርሱ ፍርዱን ይስጥ፨