en
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Open in Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 396 subscribers, ranking 5 565 in the Religion & Spirituality category and 2 183 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 396 subscribers.

According to the latest data from 28 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 15 over the last 30 days and by 5 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 21.32%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 10.24% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 282 views. Within the first day, a publication typically gains 1 576 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 17.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 29 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

15 396
Subscribers
+524 hours
+287 days
+1530 days
Posts Archive
እንኳን ለጥንተ ትንሣኤ እና ለጌታቸን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ፅንሰት በሰላም አደረሳቹህ #እግዚአብሔር_ዓለምን_ከፈጠረበት_ጥበቡ_ይልቅ_ከድንግል_ማርያም_ሰው_ሆኖ_ዓለምን_ያዳነበት_ጥበቡ_ይበልጣል፡፡ ምክንያቱም፤ ፠ እግዚአብሔር ዓለምን የፈጠረበት ጥበቡ፤ 7ቱ ዕለታትን፣ 20ው ዓለማትን፣ 22ት ሥነ ፍጥረታትን ካለመኖር ወደ መኖር፤ ከፈጠራቸውም ላይ አሻሽሎ አስገኘ ፠ ዓለምን ያዳነበት ጥበብ፤ሰማይና ምድር የማይወስኑት፤ ከጽርሐ አርያም በላይ ጠፈሩ፥ ከበርባሮስ በታች መሠረቱ፥ ለአድማስና ለናጌብ ዳርቻቸው የኾነ አምላክ በአጭር ቁመትና በጠባብ ደረት ለሰው ልጅ ቤዛ ለመሆን ወደ ፈጠረው ምድር በፈጠረው አካል ላይ የሰማይ ዙፋኑን ሳይለይ መጥታል #ብስራትና ፅንሰት በአንድ ዕለት ነው የተከናወኑት፡፡ #ኢየሱስ ክርስቶስ በማህፀነ #ማርያም የተፀነሰው ልክ ቅዱስ #ገብርኤል ‹‹ ትፀንሺያለሽ ›› ሲላት እርሷም “ይኩነኒ በከመ ትቤለኒ” ‹‹ እንደቃልህ ይደረግልኝ ›› ብላ በተቀበለች ጊዜ የእግዚአበሔር ቃል በማህፀነ ድንግል ማርያም ተፀነሰ፡፡ አብ አፀናት መንፈስቅዱስ አነፃት ወልድ በተለየ አካሉ ከሥጋዋ ስጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ተዋሐደ (ሉቃ 1፤33)፡: እመቤታችን እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም ንጽሕት መቅደሱ ናትና ፤ ነገሩን አስቀድማ ጠንቅቃ ትወቅ ሲል ቅዱስ ገብርኤልን ልኮታል ( ሉቃ ፩፥፳፮ -፳፷) ብስራቱን የነገራት መጋቢት 29 ቀን በዕለተ እሁድ ከቀኑ ሦስት ሰዓት ላይ ነው፡:ቅዱስ ገብርኤልም ብርሃናዊ መልአክ መሆኑን ለማጠየቅ እና የሥላሴ ማደርያ መኾኗን ለማስረዳት 3 ጊዜ ተመላልሷል ፡፡ ሉቃ 1 ፥33 ማቴ 18፥ 16 #ሊቀ_መላእክት ቅዱስ ገብርኤልም በደስታ ተውጦ ለመላእክት ጉባኤ “በቅድስት ድንግል ማርያም የይሁንታ ቃል ምክንያት ዓለም ዳነች” ብሎ የምስራች አላቸው፡፡ ነቢዩ ሕዝቅኤል “… በዙፋኑም አምሳያ ላይ እንደ ሰው መልክ አምሳያ ነበረ” (ሕዝ.1፡26) ብሎ እንደገለጠው እግዚአብሔር አምላክ ለመላእክት በሰው ምሳሌ ተገልጦ ይታያቸው ነበር እንጂ እርሱን ገጽ በገጽ አያዩም ነበር፡፡ ነገር ግን ቅዱስ ገብርኤል የፀንሰቱን ነገር ለመላእክት በነገራቸው ጊዜ ፈጣሪያቸው እግዚአብሔር ቃል ሰው በመሆን በአካል ሊያዩት እንደተቃረቡ ተረድተው ከዚህ በፊት ተሰምቶ የማያውቅ ታላቅ የሆነ የደስታ ዝማሬ ዘመሩ፡፡ በዚያን ጊዜ ቅዱሳን መላእክት ደስታቸው ድርብ ነበር፡፡ የመጀመሪያው ደስታቸው የሰው ልጆች መዳን ሲሆን ሁለተኛው ግን አምላካቸውን በጠባብ ደረት በአጭር ቁመት ተወስኖ ለማየት በመብቃታቸው ነበር፡፡ ቅዱስ ገብርኤል ለማብሰር የተመረጠውም #_1 #በማብሠር የታወቀ ስለሆነ(መሳ 13) ሊቃ 1 #_2 #የስሙ ትርጓሜ ሥራውን ስለሚገልጽ ፡፡ ገብር ሰው ማለት ሲሆን ኤል ደሞ አምላክ ማለት ነው ስለዚህ አምላክ ወሰብእ ማለት ነው (አምላክም ሰውም) ስለዚህ የአምላክ ሰው የመሆንን ምሥጢር እንዲያበስር ተልኳል ፡፡ #_3.#ሳጥናኤል አምላክ እኔ ነኝ ብሎ መላእክትን ባሸበራቸውጊዜ ‹‹ነቁም በበህላዌነ እስከ ነአምሮ ለአምላክነ (የፈጠረን ይህ አይደለምና ፈጣሪያችንን እስክናውቅ ድረስ በያለንበት እንጽና ) ብሏል፡፡ ይህን ያለበት አንደበቱ የአምላክን ሥጋዌ ለእመቤታቸን ለመንገር አብቅቶታል :: ይህ በቅዱስ ገብርኤል ብሥራት አምላክ በማኅፀነ ማርያም ያደረበትን የፅንሰቱን በዓል ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በታላቅ ድምቀት በማኅሌት፣ በቅዳሴ፣ በትምህርት መጋቢት ፳፱ ቀን ስታስብ ከጌታችን ዘጠኙ ዐበይት በዓላት ውስጥ አንደኛውና የመጀመሪያው አድርጋ ታስበዋለች፡፡ ይህ በዓል በፆም ወቅት ሰለሚውል መጋቢት 29 ቅዱስ አበው በሰሩልን ሥርዓት መሠረት ልዋጭ በዓሉን ታኀሣሥ 22 ብሥራቱን በድምቀት እናከብረዋለን ፡፡ ፍትሐ ነ አነድምታ አ.15 #ጥንተ ትንሣኤ «ትንሣኤ» የሚለው ቃል የግእዝ ቋንቋ ነው፡፡ መገኛ ቃሉም «ተንሥአ» = ተነሣ የሚለው ግስ ሲሆን፡፡ «ትንሣኤ» ማለት = መነሣት፥ አነሣሥ፥ ሐዲስ ሕይወት ማግኘት ማለትን ያመለክታል፡፡ ጌታችን በመስቀል ላይ ተሰቆል በሥጋ ከሞተበት ቀን መጋቢት 27 ፤ ሦስተኛው ቀን መጋቢት 29 ነውና ይህች ዕለት ቅድስት ትንሣኤው ውሎባታል በከበረች ልዩ የሆነች ትንሣኤው የዓለም ድኀነት ሆነ ፡፡ በረቀቀ ጥበቡ በዚህች ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሥቷል ፡፡ የጽንሰቱ በዓል ተደርቦባት ነው እንጂ ልናስበው የሚገባ ትልቅ ዕለት ነው :: /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ፤ ትምሕርት ዋና ክፍል ፥ ንዑስ ክፍል /ሕትመት እና ሚዲያ/ የተዘጋጀ :: #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w, .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem

#መጋቢት_28 #ጻድቅ _ንጉሥ_ቆስጠንጢኖስ_ዕረፍቱ_ነው ፡፡ እናቱ ዕሌኒ አባቱ ቊንስጣ ይባላሉ ፡፡ አባቱ ቊንስጣ አረማዊ ቢሆነም በልቡ ግን ይቅርታን እና ርኀራኀን የተሞላ ነበር ፡፡ ዕሌኒን ካገባ ቦኃላ ቆስጠንጢኖስን ወለዱ ፡፡ ቆስጠንጢኖስ ማለት ዠንጉርጉር ማለት ነው ይህም ነበር ይተባለው እርሷ ክርስቲያን በሏ ደግሞ አረማዊ ሰለሆነ ነው ፡፡ እናቱ ቅድስት ዕሌኒ ይቅርታን እና ርኀራሄን በልቡ እንዲኖር ዘውትር ታስተምረው ነበር ፡፡አባቱ አርፎ መንግስቱን ከተረከበ በኃላ ክርስቲያኖች ላይ የተጫኑትን ክፉ አገዛዞች አስወገደ፡፡ ስለደረሰባቸውም መከራ ተክዞ ሲያስብ በ 6 ሰዓት ላይ እንደ ከዋክብት የሆነ #መስቀል ታየው በላዩ ላይም በዮናኒ ቋንቋ #ኒኮስጣጣን የሚል ጽሑፍ ነበረበት ትርጉሙም #በዚህ_ጠላትህን_ድል_ታደርጋለህ ማለት ነው፡፡ እናቱ ቅድስት ዕሌኒ መስቀሉን ስትፈልግ ሰራዊቱን በመላክ ፣ ሃብት በመስጠት እና በመሳሰሉት ረድቷል ፣ ታሳትፏል ፣ አፋልጓል ፡፡ለተጨማሪ ( መስከረም 17 እና መጋቢት 10 የፃፍናቸውን ያንብቡ ) በስሙ #ቊስጠንጥንያ (Constantinople) የተባለችም ከተማም ገንብቷል በውስጣም #የእመቤታንን ቅድስት ድንግል ማርያምን ስም ፣ በአግያና ስም ፣ በሶፋያ ስም ታላቅ ቤተ ክርስቲያን ሰርቷል ፡፡በእነርሱም ውስጥ #አጽመ ቅድሳንን እያፈላለገ ያኖር ነበር፡፡ አምላክን ደስ ካሰኝ ቦኀላ ተጋድሎውን ፈጽሞ በኒቆምድያ ከተማ ታሞ አረፈ፡፡ ወደ ቊስጠንጥንያ መልሰው በከበሩ ሐዋርያት ቤተ መቅድስ በምስጋና አኑረውታል ፡፡ የፃድቃን ነገሥታት በረከታቸው ይደርብን አሜን! /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ፤ ትምሕርት ዋና ክፍል ፥ ንዑስ ክፍል /ሕትመት እና ሚዲያ/ የተዘጋጀ :: #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w, .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem

መድኀኔዓለም ሆይ፤ ክቡር ልዑል ለሚኾን ጉሮሮህ ሰላም እላለሁ፡፡ በገመድ እየሳቡ ለጎተቱት ክሳድህም ሰላም እላለሁ፡፡ ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ በቀራንዮ አደባባይ የተሰቀልከው ለሰው ልጅ ድኅነት እንደመኾ
+7
መድኀኔዓለም ሆይ፤ ክቡር ልዑል ለሚኾን ጉሮሮህ ሰላም እላለሁ፡፡ በገመድ እየሳቡ ለጎተቱት ክሳድህም ሰላም እላለሁ፡፡ ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ በቀራንዮ አደባባይ የተሰቀልከው ለሰው ልጅ ድኅነት እንደመኾኑ መጠን፤ ስለ እናትህ ስለ ድንግል ማርያም ብለህ ምሬሃለሁ ይቅር ብዬሃለሁ በለኝ፤ ከአንተ በቀር ቸር ይቅር ባይ የለምና፡፡

#ስድስተኛው_ሳምንት ገብርኄር ይባላል፡፡ ገብርኄር ማለት ታማኝ አገልጋይ ማለት ነው፡፡ በዚህ ሳምንት ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለኄር (ስለታማኝ) አገልጋይ ያስተማረው ትምህርት ይነገራል ፡፡ ይኸውም ማቴ 25፥14-30 ላይ ይገኛል፡፡ (ይህም ክፍል ጌታችን በማቴዎስ ወንጌል በምሳሌ ካስተማራቸው ትምህርቶች አንዱ ነው)፡፡ ወደ ሌላ አገር የሚሄድ ሰው ባሮቹን ጠርቶ ያለውን ገንዘብ እንደ ሰጣቸው እንዲሁ ይሆናልና፤ ለእያንዳንዱ እንደ ዐቅሙ፡ ለአንዱ #አምስት መክሊት፥ ለአንዱ #ሁለት፥ ለአንዱም #አንድ ሰጠና ወደ ሌላ አገር ወዲያው ሄደ፡፡ መክሊት የወርቅ መለኪያ (መስፈሪያ) ነው፡፡ #፭ት መክሊትም የተቀበለው ሄዶ ነገደበት ሌላም ፭ት አተረፈ፡፡ እንዲሁም #፪ት የተቀበለው ሌላ ፪ት አተረፈ ፡፡ #፩ድ የተቀበለው ግን ሄዶ ምድርን ቆፈረና የጌታውን ገንዘብ ቀበረ፡፡ ከብዙ ዘመንም በኋላ የእነዚያ ባሮች ጌታ መጣና ተቈጣጠራቸው፡፡ #፭ት መክሊት የተቀበለውም ቀረበና፤ ‹‹ጌታ ሆይ ፭ት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ ሌላ ፭ት መክሊት አተረፍሁበት›› አለ፡፡ ጌታውም፦ ‹‹መልካም አንተ በጎ ታማኝም ባሪያ (ገብር ኄር)፤ በጥቂቱ ታምነሃል በቡዙ እሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ፡፡›› አለው፡፡ #፪ት መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፡፡ ‹‹ጌታ ሆይ ፪ት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ ሌላ ፪ት መክሊት አተረፍሁበት፡፡›› አለ፡፡ ጌታውም፡፡ መልካም፡ ‹‹ አንተ በጎ ታማኝም ባሪያ (ገብር ምዕመን) በጥቂቱ ታምነሃልና በብዙ እሾምሃለሁ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው፡፡ #፩ድ መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፡፡ ‹‹ጌታ ሆይ ካልዘራህባት የምታጭድ፥ ካልበተንህበትም የምትሰበስብ፥ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ፤ ሌቦች እንዳይሠርቁኝ አታላዮች እንዳይቀሙኝ፤ ሄጄም መክሊትህን በምድር ቀበርሁት፤ መክሊትህ እነሆ›› አለው፡፡ ጌታውም መልሶ እንዲህ አለው፡- ‹‹አንተ ክፋና ሃኬተኛ ባሪያ (#ገብር_ሀካይ) ካልዘራሁበት እንደማጭድ ፥ ካልበተንሁበትም እንድሰበስብ ታውቃለህን? ስለዚህ ገንዘቤን ለለዋጮች አደራ ልትሰጠው በተገባህ ነበር፤ እኔም መጥቼ ያለኝን ከትርፉ ጋር እወስደው ነበር፡፡ ስለዚህ መክሊቱን ውሰዱበት ፲ር መክሊትም ላለው ስጡት፤ እሱን ደግሞ ወደ ዘለዓለም ሐዘንና መከራ ወዳለብት ወደ ጨለማው አውጥታችሁ ጣሉት›› አላቸው፡፡ ላለው ሁሉ ይሰጠዋልና ይበዛለትማል፤ ከሌለው ግን ያው ያለው እንኳ ይወስድበታል፡፡ አገልጋዮችም ይህንን ክፉ አገልጋይ ወደ ጨለማው አውጥተው ጣሉት፡፡ በዚህ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል፡፡ † መክሊት የተባለ ጸጋ ስጦታ ሲሆን፤ እግዚአብሔር ለእያንዳንዳችን የተለያየ ስጦታ ሰጥቶናል፤ በተሰጠንም ስጦታ ልናገለግልበት ያስፈልጋል፡፡ † በተጨማሪ መክሊት ቃለ እግዚአብሔር ነው፤ የሰማነውን ቃለ እግዚአብሔር ለመተግበር እየበረታን ለሌላው ማሰማት ይገባናል፤ ከእኛ የሚጠበቀው ማሰማቱ ብቻ ነው፤ በልቡናው አድሮ ሥራ የሚያሠራ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ነውና፡፡ እኛም በሃይማኖት ጠንክረን በምግባር በርትተን ታማኝ ባርያ ልንሆን ይገባል፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w, .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem

እንኳን ለአምላካችንና ለመድኀኒታችን፤ ለፈጣሪያችንና ለአዳኛችን መድኀኔ ዓለም ጥንተ ስቅለት ክብረ በዓል አደረሳችሁ፥ አደረሰን፡፡ #ጥንተ_ስቀለት #ክርስቶስ_የተሰቀለው መጋቢት ፳፯ ቀን #ከሆነ _እንደገና_በሌላ_ጊዜ_በዓለ_ስቅለትን_ማክበር_ለምን_አስፈለገ? #ጥንተ_ትንሣኤ #ጥንተ_ስቀለት የጥንተ ስቅለቱ የመታሰቢያ በዓል በሚከበርበት በመጋቢት ፳፯ ቀን ሰማያዊ አምላክ ስለ ሰው ልጆች ፍቅር ሲል ልዩ ልዩ ጸዋትወ መከራዎችን የተቀበለበትና በሞቱ ሞትን ሽሮ የአዳምን ዘር ሁሉ ከሞት ሞት ያዳነበት፣ ለዓለሙ ሁሉ ፍቅሩን የገለጠበት፣ በመስቀል ላይ ባፈሰሰው ደሙም ዓለምን ነፃ ያወጣበት፣ ሕማማተ መስቀልን በትዕግሥት ተቀብሎ ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ሥጋው #በገዛ_ፈቃዱ የለየበት የስቅለቱና የሞቱ መታሰቢያ የሚከበርበት ቀን በመሆኑ ጥንተ ስቅለት ተብሎ ይጠራል፡፡ በዓሉም በዓለ መድኃኔዓለም እየተባለ በየዓመቱ #በመድኃኔዓለም ስም በታነጹ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ታቦተ ሕጉ ወጥቶ ይከበራል ፡፡ የመጋቢት ጽንሰት ( ብሥራት ) ታሕሣስ 22 እንደሚከብረሁ ሁሉ ማለት ነው ፡፡ ፠#ክርስቶስ የተሰቀለው መጋቢት ፳፯ ቀን ከሆነ እንደገና በሌላ ጊዜ በዓለ ስቅለትን ማክበር ለምን አስፈለገ? ክርስቶስ የተሰቀለው በዕለተ ዓርብ ሲሆን ከመቃብር የተነሣውም በዕለተ እሑድ በመሆኑ #ስቅለት ከዕለተ ዓርብ፣ #ትንሣኤም ከዕለተ እሑድ፣ #ዕርገት ደግሞ ከዕለተ ሐሙስ እንዳይወጡ፤ ሌሎቹም በዓላትና አጽዋማት በተወሰነላቸው ቀን እንዲውሉ ማድረግ ይቻል ዘንድ የቀድሞ አባቶችና ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ሰባት አዕዋዳት አዘጋጅተው እና ቀምረው ሁሉም ሥርዓቱን ጠብቆ ድርጊቱ በተፈጸመበት ቀን እንዲከበር የወሰኑ በመሆኑ ነው፡፡ በዚህም በዲሜጥሮስ ቀመር መሠረት ጥንተ ስቅለቱ መጋቢት ፳፯ ቀን በየዓመቱ እየታሰበ በዓለ ስቅለቱ ደግሞ ከሰሙነ ሕማማቱ ጋር በዓመት አንድ ጊዜ በዕለተ ዓርብ በጾምና በጸሎት እንዲሁም በአክፍሎትና በስግደት እንዲከበር በማድረግ ሕግና ሥርዓት ስለሠሩ በዚሁ መሠረት ይፈጻማል:: #ከዘጠኙ ዓበይት በዓላት አንዱ የሆነው የጌታችን #የጽንሰቱ_በዓል በታላቅ ድምቀት የሚከበርበት ቀን ከመሆኑ የተነሣ በዓሉን በዓል ተጭኖት ነው እንጂ ፫ኛው ቀን መጋቢት ፳፱ኝም ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ የተነሣበት #ጥንተ_ትንሣኤ በመሆኑ እንደ ጥንተ ስቅለቱ ሁሉ ጥንተ ትንሣኤውም ከበዓለ ጽንሰቱ ጋር አብሮ የሚታሰብ መሆኑን ልንዘነጋው አይገባንም፡፡ #በኢትዮጵያ_በዋነኛነትና_በግንባር_ቀደምትነት_የስቅለት_በዓል_የሚከበርበት #ታላቁ ገዳም #ዋልድባ (ዋሊ)፡፡ #142 ዓመታትን ያስቈጠረው ጥንታዊው የጮቢ ደብረ መድኀኒት መድኀኔ ዓለም፡፡ በ1868ዓ.ም. የተመሠረተ፡፡ በምዕራብ ሸዋ ዞን በጀልዱ ወረዳ በጮቢ የሚገኝ፡፡ #በሃገራችን ከሚገኙ የመድኀኔዓለም ገዳማትና አድባራት ጥቂቶቹ፤ ፤ ዋልድባ አበረንታት መድኀኔዓለም ገዳምና ኤልሻማ ደብረ ማኅቶት መድኀኔዓለም ቤ.ክ. ፠ አንድ ላይ ያሉት፤ ✤1. ዋልድባ አበረንታት መድኀኔዓለም ገዳም፤ ✤2.ላሊበላ መድኀኔዓለም ✤3. ጎንደር መንበረ መንግሥት መድኀኔዓለም ✤4. መንዳባ አቡነ ያሳይ መድኀኔዓለም፤ ጣና ✤5. ሽረ እንዳሥላሴ መድኀኔዓለም ወመስቀል ክብራ ✤6. ቆላድባ መድኀኔዓለም፤ ጎንደር ከተማ አጠገብ ✤7.ቦሌ ደብረ ሳሌም መጥምቁ ዮሐንስ፤ (ቦሌ የመድኀኔዓለም ታቦት ) ✤ 8.ድሬዳዋ መድኀኔዓለም ✤9.#ቀጨኔ_ደብረ_ሰላም_መድኀኔዓለም ✤ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም ቤተ ክርስቲያን፤ ፤ የ 110 ዓመታት ዕድሜ ያለው ጥንታዊ የኢያሱ ደብር፡፡ ‹‹በወርቅ ወበዕንቊ ሥርጉት ደብረ ሰላም፤ ወነገሥት ይትቀነዩ ለኪ›› ይህችን ደብረ ሰላምን በመጀመሪያ አቤቶ ኢያሱ /አልጋ ወራሽ ልጅ ኢያሱ/ (ክፍለ ያዕቆብ) በሐምሌ 26 ቀን 1903 ዓ.ም. መሠረታት፤ ንግሥት ዘውዲቱ አሁን ያለውን ሕንፃው ቤ.ክ ጥቅምት 27 ቀን 1913 ዓ.ም አስፈጸመች፡፡) የብዙ ሊቃውንት መፍለቂያ፤ የላይ ቤት አቋቋም፣ የተክሌ ዝማሜና የሸዋና የራሱ የደብሩ ቀለም እንደ ወንዝ የሚፈስባት፤ ታሪካዊ ቅርሶችን የያዘ ቤተ መዘክር (Museum)ና ቤተ መጻሕፍት የሚገኙበት፤ ስዕለት ሰሚ ታቦታት ያሉበት፤ 4ት የሚጠጉ ፈዋሽ ጠበሎች የሚገኙበት፡፡ ጽዶቹ ሳይቀሩ በ72 አርድዕት ቅዱሳን አምሳያ የተተከሉበት፤ በቀድሞ ዘመን መዐዛ ቅዳሴ የተሰኘው የአባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ቅዳሴ በወርኃ ጽጌ የሚቀድስበት፤ 3 ጳጳሳትን ያፈራ፣ ……. ደብር ነው፡፡ ✣ ለደብረ ሰላም ይደልዋ ስብሐት፤ እስመ በውስቴታ ኀደረ መድኀኔዓለም (በደብረ ሰላም በውስጧ መድኀኔዓለም ስላደረ ምስጋና ይገባታል፡፡) 10 #መናገሻ_ጋራ_መድኀኔዓለም፤ ግማደ መስቀሉ ያረፈበት፤ ቀድሞ የቅዳሴ ቤቱን ታላቁ አባት አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ (ቀድሞ የልደታ ቤ.ክ) በአካል በመገኘት በመስቀሉ የባረከው፤ በድርሳነ ራጕኤል ላይ የተገለጸና ቅዱስ ራጕኤል የማይለየው፤ በአረማዊው ግራኝ ወረራ ጊዜ ቤተ ክርስቲያኑ ካህናቱን መነኮሳቱንና ምዕመናኑን እንደያዘ በምድር ውስጥ ገብቶ የተሰወረበት በሥጋ ዕረፍተ ሞት ያልተገቱ ሥውራን ግሩማን አበው የሚኖሩበት "ዛቲ ይእቲ አምባ ማርያም መካነ ክብሮሙ ወጸሎቶሙ ለቅዱሳን ወለነገሥታተ ኢትዮጵያ በሐ በልዋ ተሳለምዋ ጊሱ ሐቤሃ ኢትርሐቁ እምኔሐ" ብለው አበው ያወደሷት የጸሎት የአርምሞና የትኅርምት ቦታ፡፡ 11. #ገዳመ_አባ_ጽጌ_ድንግል (መድኀኔዓለም ቤ.ክ)፤ ማኅሌተ ጽጌ የተደረሰበት ወሎ፤ ወግዲ፤ ወለቃ ወንዝ አጠገብ፤ የበረሃው ዕንቊ ገዳም፤ አባ ጽጌ ድንግል የፈለፈሉት ባለ 3 መቅደስ እጅግ ሰፊ ዋሻ ቤ.ክ፡፡ 12. #ደብረ_ቀራንዮ_መድኀኔዓለም ቤ.ክ፥ አዲስ አበባ፤ በአዲስ አበባ ከተመሠረተ ከ1826 ዓ.ም ጀምሮ ፍልሰት ሳያጋጥመው በመቆየቱ፤ የመጀመሪያው የአዲስ አበባ ቤ.ክ፡፡ (ነገር ግን በመሃል ፍልሰት እያጋጠማቸው እንጂ በአዲስ አበባ ከ1600 ዓመታት በፊት ደብረ ኤረር፣ የካ ዋሻ ተክለሃይማኖትና /ኋላ የካ ሚካኤል/ በአብርሃ ወአጽብሃ ዘመን፤ እንዲሁም እንጦጦ ኪዳነ ምሕረት በአልአሜዳ ዘመነ መንግሥት መመሥረታቸውን ልብ ይሏል) #በዓለም አቀፍ ደረጃ በዋነኛነትና በግንባር ቀደምትነት የስቅለት በዓል የሚከበርባችው ፪ቱ ታላላቅ ገዳማት ፩ኛ. ኢየሩሳሌም ዴር ሡልጣን ፪ኛ. #ዋልድባ (ዋሊ)፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w, .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem