en
Feedback
Bisratfm101.1

Bisratfm101.1

Open in Telegram

Bisrat FM 101.1 is a radio station established by Oyaya Multimedia. Journalist Messele Mengistu, is the owner of Oyaya Multimedia and who remained in the hearts of the Ethiopian radio listeners for the past 10 years, has just realized his long time dream

Show more
6 627
Subscribers
-524 hours
-257 days
-9530 days
Posts Archive
ሰኔ 30፤2018 - ሙትአንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል ገዳም ለጀመረው የልማት ፕሮጀክት ከ63 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ማግኘቱን አስታወቀ የሙትአንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የገጠመውን መጠለያ
+1
ሰኔ 30፤2018 - ሙትአንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል ገዳም ለጀመረው የልማት ፕሮጀክት ከ63 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ማግኘቱን አስታወቀ የሙትአንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የገጠመውን መጠለያ የማጣት ችግር ለመቅረፍና ራሱን ለማስቻል በጀመረው የልማት ፕሮጀክት ገዳሙ ባለፉት ሁለት ዓመታት ከስድስት ወራት ውስጥ ባከናወናቸው የገቢ ማሰባሰብ ሥራዎች ከ63 ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብ እና የዓይነት ድጋፍ ማግኘት መቻሉን የአስተዳደሩ ተወካዮች ገልጸዋል። የገዳሙ አስተዳደር እንደገለፀው በተለያዩ የቴሌቪዥን ዘጋቢ ፕሮግራሞች እና በማኅበራዊ ሚዲያ አማካኝነት በተደረገው ሰፊ የገቢ ማሰባሰብ ጥረት 52 ሚሊዮን 640 ሺህ ብር በጥሬ ገንዘብ፣ 11 ሚሊዮን 320 ሺህ ብር የሚገመት የዓይነት ድጋፍ መሰብሰቡ ነዉ የተገለፀዉ። ይህ የተገኘው ድጋፍ የልማት ፕሮጀክቱን የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ምዕራፎች ከ65 በመቶ በላይ ለማሳካት ያስቻለ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የእናቶች በዓት እና የእንግዳ ማረፊያ ግንባታ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ እናቶች አገልግሎት ማግኘት መጀመራቸው ተገልጿል። ከ160 በላይ ገዳማውያን የሚገኙበት ይህ አንድነት ገዳም ከተፈጥሮአዊ እና ሰው ሠራሽ ችግሮች ጋር ተያይዞ ገዳማውያኑ ከብርድና ከዝናብ የሚከላከል መጠለያ አጥተው በከፍተኛ ችግር ውስጥ ይገኙ እንደነበር ተገልጿል። በአሁኑ ወቅት ምዕመናን የሚገኙበት የሐዋርያት ጾም (የሰኔ ጾም) የበረከት ወቅት በመሆኑ፣ የተጀመረው የልማት ሥራ ሙሉ በሙሉ ፍጻሜ እንዲያገኝ ሕዝበ ክርስቲያኑ የጀመረውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርቧል። በሰመሀር አለባቸው #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #Ethiopia የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat101

ሰኔ 30፤2018 - ያልታከመ የማህፀን ኢንፌክሽን መካንነትን ሊያስከትል ይችላል ተባለ በባክቴሪያ ፣በፈንገስ እና በቫይረስ አማካኝነት የሚከሰት የሴቶች የመራቢያ አካል ወይንም የማህፀን ኢንፌክሽን ህ
ሰኔ 30፤2018 - ያልታከመ የማህፀን ኢንፌክሽን መካንነትን ሊያስከትል ይችላል ተባለ በባክቴሪያ ፣በፈንገስ እና በቫይረስ አማካኝነት የሚከሰት የሴቶች የመራቢያ አካል ወይንም የማህፀን ኢንፌክሽን ህክምና ካላገኘ እና በተደጋጋሚ የሚከሰት ከሆነ መካንነትን ሊያስከትል እንደሚችል ከብስራት ሬዲዮ ጋር ቆይታ ያደረጉት የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ታዘባቸዉ ዉዴ ገልፀዋል። የማህፀን ወይንም ብልት አካባቢ የሚከሰት ኢንፌክሽን በርካታ ሰዎችን ከሚያጠቁ የኢንፌክሽን አይነቶች መካከል ዋነኛዉ መሆኑ ተገልጿል ።ለማህፀን ኢንፌክሽን አጋላጭ የሚሆኑ በርካታ ምክንያቶች መኖራቸዉን የሚገልፁት ዶክተር ታዘባቸዉ በግብረ ስጋ ግንኙነት የሚተላለፉ እንደ ክላሚዲያ እና ጎኖሪያ ያሉ ባክቴሪያዎች ዋነኞቹ መሆናቸዉን አስገንዝበዋል ። በአብዛኛዉ መካንነትን ሊያስከትሉ የሚችሉትም በባክቴሪያ አማካኝነት የሚከሰቱ ኢንፌክሽኖች ናቸዉ። የማህፀን ኢንፌክሽን ከመከሰቱ አስቀድሞ መከላከል ዋነኛዉ መፍትሄ መሆኑን ዶክተር ታዘባቸዉ ገልፀው ብልት አካባቢ የማሳከክ ፣የመቁሰል ፣የሆድ ህመም እና ሽንት በሚሸናበት ወቅት የማቃጠል ስሜት ሲኖር ወደ ጤና ተቋም በመሄድ ምርመራ ማድረግ እና ህክምና ማግኘት ተገቢ ነዉ ብለዋል ። በመባ ወርቅነህ #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #Ethiopia የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat101

ሰኔ 30፤2018 - የፈረንሳይ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በፓራጓይዋ ሴናተር ላይ ክስ መስርቷል! የፖራጓይ ሴናተር ሴሌስቴ አማሪያ በኪሊያን ምባፔ ላይ የሰነዘረችዉ የዘረኝነት አስተያየት መነጋጋሪያ ሆኗል
ሰኔ 30፤2018 - የፈረንሳይ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በፓራጓይዋ ሴናተር ላይ ክስ መስርቷል! የፖራጓይ ሴናተር ሴሌስቴ አማሪያ በኪሊያን ምባፔ ላይ የሰነዘረችዉ የዘረኝነት አስተያየት መነጋጋሪያ ሆኗል ። ፈረንሳይ በአለም ዋንጫ ጥሎ ማለፍ ፓራጓይን 1ለ0 አሸንፋ ከውድድሩ ካስወጣታቻት በኋላ ነበር ነገሩ የተፈጠረው። ፈረንሳዊ ለመምሰል የሚጣጣር ቅኝ የተገዛ ካሜሩናዊ ቂመኛ በአቋራጭ የበለጸገ ትዕቢተኛ ነዉ። ልክ እንደ ቡድኑ በጨዋታው በሙሉ ተጨንቆ እና በፍርሃት ተውጦ ነበር አንድም ጎል እንኳን ማግባት አልቻሉም በዕድል ብቻ ነው ያሸነፉት ብላለች። ብዙዎቻችን የፖራጎይን ቡድኑን የምንወቅስበት ብቸኛው ነገር ጨዋታው ሲጠናቀቅ ምባፔን ፊቱን በጥፊ አለመምታታቸው ነው። ይህን የምለው የእግር ኳስ አድናቂ እንኳን ሳልሆን ነው ስትል አነጋጋሪ አስተያየት ሰጥታለች ጨዋታው ከተጠናቀቀ በኋላ የፓራጓዩ ግብ ጠባቂ ኦርላንዶ ጊል ወደ ምባፔ በመቅረብ ሰላም ለማለት ቢሞክርም በጨዋታው ወቅት በደረሰበት ከባድ አጨዋወትና ትንኮሳ ተበሳጭቶ ስለነበር ምባፔ ሰላም ሳይለው ሄዷል እንዲሁም ከጨዋታው በኋላ ምባፔ ለጋዜጠኞች በሰጠው አስተያየት የፓራጓይን አጨዋወት አስቀያሚነት ገልፆ ነበር ። አሁን ላይ የፈረንሳይ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በፓራጓይዋ ሴናተር ላይ ክስ መስርቷል ​በኪሊያን ምባፔ ላይ የተሰነዘረውን የዘረኝነት ጥቃት ተከትሎ የፈረንሳይ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (FFF) ጠንካራ እርምጃ መውሰዱን በይፋ አስታውቋል! የወጣው ይፋዊ መረጃ እንደሚያመለክተው የፈረንሳይ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በፈረንሳዩ ኳስ ኮከብ ኪሊያን ምባፔ ላይ ዘረኛ እና አድሎአዊ አስተያየት በሰነዘረችዉ የፓራጓይዋ ሴናተር ሴሌስቴ አማሪላ ላይ ይፋዊ የህግ ክስ መመስረቱን አስታውቋል። ​ፌዴሬሽኑ በተጫዋቾቹ ላይ የሚሰነዘሩ ማናቸውንም የዘረኝነት ጥቃቶች እንደማይታገስና እስከ መጨረሻው በህግ እንደሚፋለም በውሳኔው አሳይቷል። ✍️ አዲስ መሀመድ #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #sports የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat10

ሰኔ 30፤2018 - በቀጣይ 5 ዓመታት 1.5 ሚሊዮን ቤቶች ይገነባሉ ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለጹ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በቀጣይ አምስት ዓመታት 1.5 ሚሊዮን ቤቶችን ለመገንባት መታቀ
ሰኔ 30፤2018 - በቀጣይ 5 ዓመታት 1.5 ሚሊዮን ቤቶች ይገነባሉ ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለጹ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በቀጣይ አምስት ዓመታት 1.5 ሚሊዮን ቤቶችን ለመገንባት መታቀዱን ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡት ማብራሪያ ባለፉት ሰባት ዓመታት 1.2 ሚሊዮን ቤቶች መገንባታቸውን ጠቅሰው በቀጣዩ አምስት ዓመታት ተጨማሪ 1.5 ሚሊዮን ቤቶች እንደሚገነቡ ተናግረዋል። እንደ ገለጻቸው የቤቶቹ ግንባታ በመንግሥት፣ በግል ዘርፍ ተሳትፎ እና በሌሎች የአጋርነት መንገዶች የሚከናወን ሲሆን ለዚህም የሚያግዝ ፖሊሲ ተዘጋጅቶ በካቢኔ መፅደቁን አስታውቀዋል። በተጨማሪም የኮንስትራክሽን ግብዓት የሚያመርቱ ፋብሪካዎች ምርት መጀመራቸውን፣ዘርፉን የሚደግፉ የሰው ኃይል ስልጠናዎች እየተሰጡ መሆናቸውን እና በከተማና በገጠር የቤት ግንባታ እንቅስቃሴዎች መጀመራቸውን ገልጸዋል። የቤት ፋይናንስ ተደራሽነትን ለማሳደግ የሞርጌጅ ስርዓት እየተዘጋጀ መሆኑንም ጠቁመው፣ ዜጎች ቤት በቀጥታ መግዛት ባይችሉም በረጅም ጊዜ ክፍያ ከገቢያቸው ጋር በሚጣጣም መንገድ ባለቤት እንዲሆኑ መንግሥት በተለያዩ አማራጮች ላይ እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል። በሳምራዊት ስዩም #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #Ethiopia የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat101

ሰኔ 30፤2018 - የፓራጓይ ሴናተር ምባፔ ፈረንሳዊ እንደሆነ ያስመስላል እንጂ ቅኝ የተገዛ ካሜሮናዊ ማለቷን ተከትሎ ተቃውሞ ገጠማት የፓራጓይ ሴናተር ሴሌስቴ አማሪላ ኪሊያን ምባፔ ላይ ያስተላለፉት
+1
ሰኔ 30፤2018 - የፓራጓይ ሴናተር ምባፔ ፈረንሳዊ እንደሆነ ያስመስላል እንጂ ቅኝ የተገዛ ካሜሮናዊ  ማለቷን ተከትሎ ተቃውሞ ገጠማት የፓራጓይ ሴናተር ሴሌስቴ አማሪላ ኪሊያን ምባፔ ላይ ያስተላለፉት የዘረኝነት ንግግር ከፍተኛ ቁጣን ቀስቅሷል። "ወይዘሮ ሴሌስቴ አማሪላ፣ እፕንቺ እጅግ የተናቅሽ ሴት ነሽ፤ ለያዝሽውም ቦታ አትመጥኝም" ሲሉ ምባፔ በኤክስ ገፁ ላይ ጽፏል። ከፓራጓይ እና ፈረንሳይ ጨዋታ መጠናቀቅ በኃላ ሴናተሯ ምባፔን አስቀያሚ በማለት “ ሙሉ ጨዋታውን ተረብሾ እና ፈርቶ ነው የጨረሰው “ ብላለች። ኪሊያን ምባፔ በበኩሉ “ የፓራጓይን ህዝብ አትወክይም ፣ በግንዛቤ ማነስ እና ባልተገደበ የዘረኝነት ዝንባሌሽ ምክንያት፣ መላው ዓለም የፓራጓይን ሩጫ እና በዚህ የዓለም ዋንጫ ያሳዩትን ታሪካዊ ጥረት ረስቶታል" ሲል አክሏል። የሴናተሯ አስተያየ በፈረንሳይ ቁጣ ቀስቅሷል፤ የአገሪቱ የስፖርት ሚኒስትር ማሪና ፌራሪ “አሳፋሪ እና ተቀባይነት የሌላቸው” ሲሉ ገልጸዋቸዋል።የፈረንሳይ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አምበላቸው ላይ የደረሰውን የስም ማጥፋት ተከትሎ ጉዳዩን ወደ ሚመለከተው የህግ አካል መወሰዱን አሳውቋል። የፓራጓይ የውጪ ጉዳይ ሚንስቴር መንግስትን ወክሎ የሴናተሯ ጉዳይ ውስጥ እንደሌለበት በኤክስ የማህበራዊ ትስስር ገፅ አጋርቷል። በስምኦን ደረጄ #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #sports የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat10

ሰኔ 30፤2018 - የመጨረሻው ዓለም ዋንጫ 🐐 #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #sports የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞ
+3
ሰኔ 30፤2018 - የመጨረሻው ዓለም ዋንጫ 🐐 #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #sports የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat10

ሰኔ 30፤2018 - የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ የስራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባውን በዛሬው ዕለት እያካሄደ ይገኛል ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ ከምክር ቤት አባላት ለሚነሱላቸው ጥያቄዎች
ሰኔ 30፤2018 - የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ የስራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባውን በዛሬው ዕለት እያካሄደ ይገኛል ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ ከምክር ቤት አባላት ለሚነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ  ይሰጣሉ። በምክር ቤት አባላት ከተነሱ ጥያቄዎች መካካል 👉 የመድኃኒት  አቅርቦት የህክምና የመሳሪያዎች እጥረት ለመቅረፍ ምን አይነት እርምጃዎች እየተወሰደ ይገኛል 👉  ከግብጽ ከሱዳን እና ከኤርትራ ጋር ያሉ የዲፕሎማሲያዊ ስትራቴጂ እንዲብራራ ተጠይቋል 👉 የሰሜን ኢትዮጵያ  ጦርነት ጠባሳ ሳይሽር አሁንም በተለያዩ አካባቢዎች  የእገታ እና ግድያዎች እየተባባሱ ይገኛሉ 👉በጋዜጠኞች በሚዲያዎች ላይ ያሉ እክሎች ዜጎች አማራጭ ድምጽ እንዳያሰሙ አድርጎቸዋል 👉የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ  የኑሮ ውድነቱ   ነዋሪዎች መቋቋም አቅቷቸዋል  👉 በየጊዜው በፓርላማ የሚጸድቁ ብድሮች ለምን በሪፖርቱ  ላይ አልተካተቱም 👉የ12 ኛ ክፍል  58.7 የማለፍ ምጣኔ የትምህርት ጥራት  መውደቁን የሚያመላክት እየሆነ ነው ለምን  በዚህ ውስጥ አልፈው ለሚመረቁ ተማሪዎች የስራ እድል የለም 👉 የሰብዓዊ ቀውሶች ትኩረት እየተሰጣቸው አደለም ለምን ? በጦርነት እና በረሃብ  የተፈናቀሉ ዜጎች  ቁጥር ቀላል የሚባል አደለም #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #Ethiopia የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat101

ሰኔ 30፤2018 - እስራኤል 'የሰፈራ አብዮት' እንደምትጀምር የሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣን ተናገሩ የእስራኤል የፋይናንስ ሚኒስትር ቤዛልል ስሞትሪች እስራኤል "የሰፈራ አብዮት" ብለው የሚጠሩትን ጀም
ሰኔ 30፤2018 - እስራኤል 'የሰፈራ አብዮት' እንደምትጀምር የሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣን ተናገሩ   የእስራኤል የፋይናንስ ሚኒስትር ቤዛልል ስሞትሪች እስራኤል "የሰፈራ አብዮት" ብለው የሚጠሩትን ጀምራለች ሲሉ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል፣ ይህዉ እንቅስቃሴ በዌስት ባንክ ብቻ የተወሰነ እንዳልሆነ አክለዋል።   "ዜና አለኝ፡ አብዮቱን በሰፈራ ጀምረናል። እንዲሁም ኔጌቭ እና ገሊላ እንደርሳለን" ሲሉ የቀኝ ክንፍ ሚኒስትሩ በኢንስታግራም ላይ ጽፈዋል።እነዚህ አስተያየቶች የተሰጡት የእስራኤል ካቢኔ ሐሙስ ዕለት በማዕከላዊው የዌስት ባንክ 13 አዳዲስ ሰፈሮችን ለማቋቋም ዕቅድ ካፀደቀ በኋላ ነው።   በሌላ በኩል የአይሁድ ሕዝብ ፖሊሲ ​​ተቋም ባደረገው አዲስ የሕዝብ አስተያየት ጥናት 60 በመቶ የሚሆኑት እስራኤላውያን በእስራኤል ውስጥ የእርስ በርስ ጦርነት ሊጀምር የሚችል “ተጨባጭ እና እውነተኛ” አደጋ እንዳለ ያምናሉ።ጥናቱ እንዳመለከተው 79 በመቶ የሚሆኑት እስራኤላውያን ባለፈው ዓመት የማህበራዊ ሁኔታዉን “መጥፎ” ብለው ሲመድቡ 49 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ ስለወደፊቱ ተስፋ ቢስ እንደሆኑ ተናግረዋል።   በጥናቱ መሠረት 52 በመቶ የሚሆኑት እስራኤላውያን ጠቅላይ ሚኒስትርን ወይም ሌላ ከፍተኛ የፖለቲካ ሰውን ኢላማ ያደረገ የፖለቲካ ግድያ “ከፍተኛ ዕድል” እንዳለ ያምናሉ። የጥናቱ ማዕከል ፕሬዝዳንት ዬዲዲያ ስተርን ለእስራኤሉ ናሽናል ኒውስ እንደተናገሩት ሕዝቡ ውስጣዊውን ልዩነት እንደ ዋና ጠላቱ አድርጎ ይመለከተዋል፣ እናም አንድነትን እና መተማመንን ለማጎልበት የረጅም ጊዜ የድርጊት መርሃ ግብር በአስቸኳይ ያስፈልገናል። በስምዖን ደረጄ #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #Ethiopia የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat101

ሰኔ 30፤2018 - ቻይና የሚሳኤል ሙከራ ማድረጓን ተከትሎ ከአውስትራሊያ፣ ኒውዚላንድ እና ጃፓን ትችት ቀረበባት ቻይና በፓስፊክ ውቅያኖስ ውስጥ ውሃማ አካል ላይ የወደቀ የኑክሌር ሰርጓጅ መርከብን
ሰኔ 30፤2018 - ቻይና የሚሳኤል ሙከራ ማድረጓን ተከትሎ ከአውስትራሊያ፣ ኒውዚላንድ እና ጃፓን ትችት ቀረበባት   ቻይና በፓስፊክ ውቅያኖስ ውስጥ ውሃማ አካል ላይ የወደቀ የኑክሌር ሰርጓጅ መርከብን ሚሳኤል ሙከራ ማድረጓን መንግስታዊዉ ዢንዋ የዜና ወኪል ዘግቧል፣ ይህ እርምጃዋ ከጃፓን፣ አውስትራሊያ እና ኒውዚላንድ ትችት እና ስጋት አስከትሏል።የቻይና የባህር ኃይል ሰኞ ዕለት በደቡብ ፓስፊክ ውስጥ ካሉት የኑክሌር ኃይል ባላቸው ሰርጓጅ መርከቦቿ የረጅም ርቀት ባላስቲክ ሚሳኤልን ፈትሾታል ሲል ዢንዋ አክሏል፡፡   ሙከራው የቻይና ዓመታዊ ወታደራዊ ስልጠና "መደበኛ ዝግጅት" ሲሆን በማንኛውም የተለየ ኢላማ ላይ ያተኮረ አልነበረም።የአውስትራሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፔኒ ዎንግ ቻይና ወደ ፓስፊክ ውቅያኖስ የባህር ላይ የሚሳኤል ሙከራ ለማድረግ እቅድ እንዳላት ማሳወቋን አረጋግጠዋል ነገር ግን እርምጃው ለክልሉ "አለመረጋጋት" እንደሆነ ተናግረዋል።"አውስትራሊያ ይህ የታቀደ ሙከራ ቻይና በፈጣን ወታደራዊ ግንባታ አውድ ውስጥ መሆኑን ግልፅ አድርጋለ  ሲሉ ዎንግ በፊጂ ዋና ከተማ ሱቫ በተደረገ የዜና ኮንፈረንስ ላይ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።   የጃፓን መንግስት ስለ ሚሳኤል ማስወንጨፊያ አስቀድሞ ማሳወቂያ እንደደረሰው እና ቻይና በድጋሚ እርምጃዋን እንድታጤን አሳስቧል።"የቻይና ጦር እንቅስቃሴ እየጨመረ በመምጣቱ ከፍተኛ ስጋት እንዳለን ገልጸናል" ሲል የጃፓን መንግስት አስታዉቋል። የኒውዚላንድ መንግስት የታቀደው ማስወንጨፊያ ከተከናወነ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ እንደተነገረው ተናግሯል።ኒውዚላንድ ይህንን እርምጃ ተቀባይነት የሌለው እና አሳሳቢ እንቅስቃሴ አድርጋ ትቆጥረዋለች ብሏል። በስምዖን ደረጄ #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #Ethiopia የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat101

ሰኔ 30፤2018 - የኢራን መሪዎች ከጥፋታቸዉ ካልተማሩ እንደምትገድላቸዉ እስራኤል ዛተች 👉 አሜሪካ የቤት እንስሶቿን ከቴል አቪቭ እንድታስወግድ ቃል ገብታለች ካልሆነ ፈጣን አጸፋ አለዉ ስትል ኢራ
ሰኔ 30፤2018 - የኢራን መሪዎች ከጥፋታቸዉ ካልተማሩ እንደምትገድላቸዉ እስራኤል ዛተች 👉 አሜሪካ የቤት እንስሶቿን ከቴል አቪቭ እንድታስወግድ ቃል ገብታለች ካልሆነ ፈጣን አጸፋ አለዉ ስትል ኢራን ተደምጣለች     የእስራኤል የመከላከያ ሚኒስትር ሀገራቸው እስራኤልን “ለማጥፋት እቅድ” በመምራት አሊ ኻሜኔይን እንደገደለች እና እንደዚህ አይነት ድርጊቶችን ለማስተዋወቅ የሚሞክር ማንኛውንም የኢራን መሪ “እንደምታጠፋ” በድጋሚ ዝተዋል።ሚኒስትሩ ኢዝራኤል ካትዝ በቴህራን በሚካሄደዉ የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ በሰነዘሩት አስተያት ላይ ይህንኑ ተናግረዋል፡፡ ካትዝ እስራኤል በማንኛውም ጊዜ እና ማንኛውንም ስጋት ለመከላከል ዝግጁ መሆኗን አክለዋል።   ካትዝ ቀደም ሲል የካሜኔይ ልጅ እና ተተኪው ሞጅታባ “ለሞት ምልክት ተደርጎበታል” ሲሉ መናገራቸዉ ከቴህራን ተቃውሞ አስነስቷል። የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ ትራምፕ “አሜሪካ የቤት እንስሶቿን ከቴል አቪቭ እንድታስወግድ ቃል ገብታለች” ሲሉ አክለዋል፣ “በሕዝባችን እና በአመራራችን ላይ የሚሰነዘር ማንኛውም ስጋት ፈጣን እና ኃይለኛ ምላሽ ያገኛል” ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡   ባለፈው ሳምንት መጨረሻ የተጀመረው እና በቀጣይ ቀናትም የሚካሄደው የቀድሞው የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሜኒ የስንብት እና የቀብር ሥነ ሥርዓት በመቶ ሺህዎች እየታደሙበት ቀጥሏል።ኻሜኒ ከአብዮታዊዋ እስላማዊት ሪፐብሊክ ኢራን መሪነታቸው በተጨማሪ በሺዓ እስልምና እምነት ተከታዮች ከፍተኛ ተሰሚነት ያላቸው መሪ ነበሩ።የቀድሞው መሪ የስንብት ሥነ ሥርዓት ከኢራን በተጨማሪ በኢራቅ ውስጥ ይከናወናል፡፡ በስምዖን ደረጄ #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #Ethiopia የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat101

ሰኔ 30፤2018 - ከስደት ተመላሽና ጥቃት የደረሰባቸውን ወገኖች ሕይወት እየመለስን ነው — ዶ/ር አበራ አደባ ​ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ከ240 ሺህ በላይ ለሆኑ ከስደት ተመላሽ፣ በሰው ዝውው
+3
ሰኔ 30፤2018 - ከስደት ተመላሽና ጥቃት የደረሰባቸውን ወገኖች ሕይወት እየመለስን ነው — ዶ/ር አበራ አደባ ​ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ከ240 ሺህ በላይ ለሆኑ ከስደት ተመላሽ፣ በሰው ዝውውር ለተጎዱና ጥቃት ለደረሰባቸው ዜጎች መጠለያ፣ የሕክምና፣ የስነ-ልቦና እና የሙያ ስልጠና ድጋፍ በመስጠት ወደ መደበኛ ሕይወታቸው የመለሰው አንጋፋው ሀገር በቀል ድርጅት አጋር ኢትዮጵያ በአማራ ክልል አገልግሎቱን ይበልጥ ለማስፋፋት የሚያስችለውን ታሪካዊ የስምምነትና የርክክብ ፊርማ በባህር ዳር ከተማ ተፈራርሟል። ​ተቋሙ ላለፉት 8 ዓመታት በባህር ዳር ከተማ በኪራይ መጠለያ ውስጥ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ ቢሆንም፣ አሁን ግን የአማራ ክልል ሴቶች፣ ሕፃናትና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ከጤና ቢሮ ጋር በመተባበር ያስገነባውን ዘመናዊ ባለብዙ አገልግሎት ሕንፃ (ሴፍ ሀውስ) በይፋ ተረክቧል። ​የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዳይሬክተር ዶ/ር አበራ አደባ እንደገለጹት፣ በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ፣ በኦሮሚያ እና በአማራ ክልል በሚገኙ ማዕከላት አማካኝነት አገራዊ ግዳጅን እየተወጡ ሲሆን፣ በቀጣይም ማዕከላቱን ራሳቸውን ወደቻሉ የማኅበራዊ ኢንተርፕራይዞች ለመለወጥ ስልታዊ ዕቅዶች አሏቸው። በመጨረሻም ዋና ሥራ አስፈጻሚው ለተደረገላቸው ከፍተኛ እምነት የክልሉን መንግሥት አመስግነው፣ ድርጅቱ “በትልቅ ማለም፣ በትንሹ መጀመር፣ አሁኑኑ ለተግባር መንቀሳቀስ!” በሚለው መርሁ መሠረት የተጣለበትን አደራ በታማኝነት እንደሚወጣ አረጋግጠዋል። #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #Ethiopia የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat101

ሰኔ 30፤2018 - የስልጤ ዞን ፍትህ መምሪያ ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ የተመዘበረ የመንግስት ገንዘብ ማስመለሱን አስታወቀ የስልጤ ዞን ፍትህ መምሪያ በ2018 የበጀት ዓመት ባከናወነው የተቀናጀ የሕ
ሰኔ 30፤2018 - የስልጤ ዞን ፍትህ መምሪያ ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ የተመዘበረ የመንግስት ገንዘብ ማስመለሱን አስታወቀ   የስልጤ ዞን ፍትህ መምሪያ በ2018 የበጀት ዓመት ባከናወነው የተቀናጀ የሕግ ማስከበር ሥራ ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ የተመዘበረ የመንግሥት ገንዘብ ማስመለሱን አስታውቋል።በዚህም በምርመራ መዛግብት አፈጻጸም ታይቶ የማይታወቅ ስኬት ማስመዝገቡን የመምሪያው ኃላፊ አቶ ሬድዋን ኑሪ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡   በፍትሐ ብሔር የሙስና ፣የታክስ እና ኢኮኖሚ ወንጀሎች ተመዝብሮ የነበረ ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የመንግሥት እና የሕዝብ ገንዘብ በሕግ አግባብ ተጣርቶ ወደ መንግሥት ካዝና እንዲመለስ ተደርጓልለ፡፡እንዲሁም በዓመቱ ለዐቃቤ ሕግ የቀረቡ የወንጀል ምርመራ መዛግብትን በማጥራት እና ውሳኔ በመስጠት ሂደት ተቋሙ ከምንጊዜውም  በተሻለ መልኩ በሁሉም መዛግብት ላይ ፈጣን እና ሕጋዊ ውሳኔ መስጠት ችሏል።   በተጨማሪም በንቃተ ህግ ሥራ ዘርፍ  በሁሉም የማስተማሪያ ዘዴዎች ከ 730 ሺህ በላይ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች የሕግ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ መሰራቱን አስረድተዋል።እንዲሁም ከሰነድ ማረጋገጥ እና የጠበቆች ክትትል ሥራ፣ ከሕገ ወጥ የሠዎች ዝውውር ወንጀል መከላከል እና ከሴቶች እና ሕፃናት ጥቃት ጋር ተያይዞ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን በተሰሩ ስራዎች በርካታ ለውጦች መምጣታቸውን ኃላፊው ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።   በሰመሀር አለባቸው #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #Ethiopia የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat101

ሰኔ 30፤2018 - ውድ የብስራት ሬዲዮ አድማጮች የ facebook ገጻችን like, share እና Comment በማድረግ ሃሳብ አስተያየታችሁን አካፍሉን። በ-#አለም_ዋንጫ የ-#ስዊዘርላንድ እና #ኮ
ሰኔ 30፤2018 - ውድ የብስራት ሬዲዮ አድማጮች የ facebook ገጻችን like, share እና Comment በማድረግ ሃሳብ አስተያየታችሁን አካፍሉን። በ-#አለም_ዋንጫ የ-#ስዊዘርላንድ እና #ኮሎምቢያ-ን ጨዋታ #ቪቫ_ስፖርት ይዘውላችሁ ይቀርባሉ። ማነኛውንም ሃሳብ አስተያየት አድርሱን። መልሰን ወደ እናንተ አናደርሳለን። ምሽት ከ4:00-7:00 ሰዓት ይጠብቁን! በመላው #ዓለም በዩቲዩብ ገፃችን ይጠብቁን። 👇👇👇 https://www.youtube.com/@Bisrat_Fm_101.1 የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat101fm TikTok: https://www.tiktok.com/@bisrat.fm

ሰኔ 30፤2018 - ውድ የብስራት ሬዲዮ አድማጮች የ facebook ገጻችን like, share እና Comment በማድረግ ሃሳብ አስተያየታችሁን አካፍሉን። በ-#አለም_ዋንጫ የ-#አርጀንቲና እና #ግብ
ሰኔ 30፤2018 - ውድ የብስራት ሬዲዮ አድማጮች የ facebook ገጻችን like, share እና Comment በማድረግ ሃሳብ አስተያየታችሁን አካፍሉን። በ-#አለም_ዋንጫ የ-#አርጀንቲና እና #ግብጽ-ን ጨዋታ #ቲፎዞ ይዘውላችሁ ይቀርባሉ። ማነኛውንም ሃሳብ አስተያየት አድርሱን። መልሰን ወደ እናንተ አናደርሳለን። ምሽት ከ12:00-4:00 ሰዓት ይጠብቁን! በመላው #ዓለም በዩቲዩብ ገፃችን ይጠብቁን። 👇👇👇 https://www.youtube.com/@Bisrat_Fm_101.1 የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat101fm TikTok: https://www.tiktok.com/@bisrat.fm

ሰኔ 30፤2018 - የፖርቹጋል አሰልጣኝ ሮቤርቶ ማርቲኔዝ ከሀላፊነታቸው ለቀቁ ! የፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሮቤሮቶ ማርቲኔዝ ከጨዋታው በኋላ ከሀላፊነታቸው ለቀዋል። “ ይሄ የመጨረሻ ጨዋታዬ
ሰኔ 30፤2018 - የፖርቹጋል አሰልጣኝ ሮቤርቶ ማርቲኔዝ ከሀላፊነታቸው ለቀቁ ! የፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሮቤሮቶ ማርቲኔዝ ከጨዋታው በኋላ ከሀላፊነታቸው ለቀዋል። “ ይሄ የመጨረሻ ጨዋታዬ ነው የፖርቹጋል ህዝብን አመሰግናለሁ “ ሲሉ አሰልጣኝ ሮቤርቶ ማርቲኔዝ ተናግረዋል። የዛሬው ጨዋታ በአለም ዋንጫው የፖርቹጋል ምርጥ ጨዋታ ነው ” ሲሉ ሮቤርቶ ማርቲኔዝ ተናግረዋል። ሮቤርቶ ማርቲኔዝ " ወደ ፖርቹጋል የመጣሁት አለም ዋንጫ ለማሸነፍ ነው የቻልኩትን አድርጊያለሁ መቆየቴ ጥቅም የለውም "ብለዋል። የአሰልጣኙን ስንብት ተከትሎ  ሆርጌ ጄሱስ አዲሱ የፖርቹጋል አሰልጣኝ ይሆናሉ ተብሏል። ከፖርቹጋል የዜና ወኪል ኤ ቦላ የወጡ ዘገባዎች እንደሚያሳዩት ጄሱስ የውል ዝርዝሮችን ለማጠናቀቅ እና የሹመት ሂደቱን ለማጠናቀቅ ከፖርቹጋል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጋር ይገናኛሉ። ልምድ ያላቸው አሰልጣኙ በአሁኑ ጊዜ በፖርቱጋል፣ በብራዚል እና በሳዑዲ አረቢያ በተሳካ የክለቡ የስራ ዘመናቸው የሚታወቁ ሲሆን ብሄራዊ ቡድኑን ለመምራት የፌዴሬሽኑ ተመራጭ ምርጫ ሆነዉ ብቅ ብለዋል። ✍️ አዲስ መሀመድ #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #sports የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat10

ሰኔ 30፤2018 - የክርስቲያኖ ሮናልዶ የዓለም ዋንጫ ጉዞ አብቅቷል! ስፔን የፖርቹጋልን ህልም በ16ቱ ዙር ነጥቃለች። ክርስቲያኖ ሮናልዶ የዓለም ዋንጫን የማሸነፍ ህልሙ በ16ቱ ዙር ፖርቱጋል በደረ
ሰኔ 30፤2018 - የክርስቲያኖ ሮናልዶ የዓለም ዋንጫ ጉዞ አብቅቷል! ስፔን የፖርቹጋልን ህልም በ16ቱ ዙር ነጥቃለች። ክርስቲያኖ ሮናልዶ የዓለም ዋንጫን የማሸነፍ ህልሙ በ16ቱ ዙር ፖርቱጋል በደረሰባት አሳዛኝ የ 1-0 ሽንፈት በስፔን ተገቷል ። የጨዋታውን ብቸኛ ጎል በ91ኛው ደቂቃ የአርሰናሉ ተጫዋች ሚኬል ሜሪኖ ከተጠባባቂ ወንበር ተነስቶ አስቆጥሯል ። የ41 ዓመቱ ሮናልዶ በእግር ኳስ ትልቁን ሽልማት የማሸነፍ ህልሙ አሁን አብቅቷል። ስፔን በዚህ ወድድር ምንም ጎል ሳይቆጠርባት ጉዞዋን ቀጥላለች። ✍️አዲስ መሀመድ #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #sports የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat10

ሰኔ 29፤2018 - ጀደን ሳንቾ ማንችስተር ዩናይትድን እንደሚለቅ ተነግሯል! እንግሊዛዊው የማንችስተር ዩናይትድ የመስመር አጥቂ ጄደን ሳንች ማንችሰተር ዩናይትድን በነፃ እንደሚለቅ ተገልጿል። የተጨዋ
ሰኔ 29፤2018 - ጀደን ሳንቾ ማንችስተር ዩናይትድን እንደሚለቅ ተነግሯል! እንግሊዛዊው የማንችስተር ዩናይትድ የመስመር አጥቂ ጄደን ሳንች ማንችሰተር ዩናይትድን በነፃ እንደሚለቅ ተገልጿል። የተጨዋቹ ኮንትራት በዚህኛው ወር የተጠናቀቀ ሲሆን ማንችስተር ዩናይትድ ኮንትራቱን ለማደስ ፍቀደኛ አለመሆኑን ተከትሎ ክለቡን በነፃ የሚለቅ ይሆናል። አሁን ላይዐ የሳውዲ እና የአሜሪካ ክለቦች ፕሮፖዛል ያቀረቡ ቢሆንም ጀደን ሳንቾ ግን ከአውሮፓ ውጪ ወደ ሌሎች ክለቦች የመሔድ ፍላጎት እንደሌለው ተገልጿል። ✍️በአህመዲን ከማል #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #sports የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat10

ሰኔ 29፤2018 - በስሪ ላንካ እስር ቤት በተከሰተ ግጭት ቢያንስ 19 ሰዎች ተገደሉ በስሪላንካ በሚገኝ አንድ እስር ቤት በተከሰቱ ግጭቶች ቢያንስ 19 ሰዎች መሞታቸውን እና ከ100 በላይ ሰዎች መ
ሰኔ 29፤2018 - በስሪ ላንካ እስር ቤት በተከሰተ ግጭት ቢያንስ 19 ሰዎች ተገደሉ በስሪላንካ በሚገኝ አንድ እስር ቤት በተከሰቱ ግጭቶች ቢያንስ 19 ሰዎች መሞታቸውን እና ከ100 በላይ ሰዎች መቁሰላቸውን የመገናኛ ብዙሃን ዘገባዎች አመልክተዋል።እሁድ ዕለት ከዋና ከተማዋ ኮሎምቦ በስተሰሜን 35 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምትገኘው ኔጎምቦ በሚገኘው እስር ቤት ዓመፅ መከሰቱን እና ሰኞ ዕለትም እንደቀጠለ ፖሊስ አስታዉቋል፡፡ የሆስፒታሉ ዳይሬክተር ፑሽፓ ጋምላት ሰኞ ዕለት ለኤኤፍፒ የዜና ወኪል እንደተናገሩት የኔጎምቦ ሆስፒታል የአራት የእስር ቤት ጠባቂዎች እና የ15 እስረኞች አስከሬንን ተቀብሏል።ከ100 በላይ የቆሰሉ እስረኞች ወደ ሆስፒታል መግባታቸውን ተናግረዋል። የአካባቢው ሂሩ ቲቪ በግጭቱ ቢያንስ 20 ሰዎች መሞታቸውን ደረሰኝ ባለዉ መረጃ መሰረት ዘግቧል።የፖሊስ ቃል አቀባይ ቻንዳና ሄራት በእስር ቤቱ ውስጥ በተከሰቱት ግጭቶች እና ሞት መከሰቱን አረጋግጠዋል፣ ተጨማሪ ዝርዝር መረጃዎችን ከመስጠት ግን ተቆጥበዋል፡፡ የግጭቱ ምክንያት ግን ግልጽ አይደለም። በስምዖን ደረጄ #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #Ethiopia የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat101

ሰኔ 29፤2018 - ዶናልድ ትራምፕ ፊፋ የፍሎሪያን ባሎጉን ቀይ ካርድን እንዲገመግመው መጠየቃቸውን አረጋገጡ! የአሜሪካው ፕሬስዳንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ የፍሎሪያን ባሎጉን ቀይ ካርድ በተመለከተ
ሰኔ 29፤2018 - ዶናልድ ትራምፕ ፊፋ የፍሎሪያን ባሎጉን ቀይ ካርድን እንዲገመግመው መጠየቃቸውን አረጋገጡ! የአሜሪካው ፕሬስዳንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ የፍሎሪያን ባሎጉን ቀይ ካርድ በተመለከተ ለፊፋ ፕሬስዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ መጠየቃቸውን በይፋ ተናግረዋል። አሜሪካ በ16 ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ቦስኒያን ሁለት ለባዶ ባሸነፈችበት ጨዋታ ላይ የአሜሪካ ብ/ቡድን ተጨዋች የሆነው ባሎጉን በቀይ ካርድ በዕለቱ ጨዋታ ከሜዳ መውጣቱ ይተወሳል። ይህንን ተከትሎ ፊፋ የባሎጉንን ቀይ ካርድ ማንሳቱን ከገለፀ በሗላ በቤልጂየሙ ጨዋታ መሳተፍ እንደሚችልም ይፋ አድርጓል። ይህንን በተመለከተ የአሜሪካ ተፅኖ በፊፋ ላይ ከባድ የእምነት ማጣት ከማስከተልም ባለፈ መነጋጋሪያ ሆኗል። ዶናልድ ትራምፕ ለዚህ ምላሽ የሰጡ ሲሆን'' ከቀይ ካርዱ ጋር በተያያዘ ለጂያኒ ኢንፋንቲኖ ቀይ ካርዱን እንደገና እንዲገመግሙት ጠይቄዋለሁ፤ እሱ የተከበረ ሰው ነው ካሉ በኋላ እኛ የአለም ዋንጫውን እንድናዘጋጅ የጠየቅኩት እኔ ነኝ ያኔ ባይደን ተኝቶ ነበር ሲሉ አስገራሚ ምላሽ ሰጥተዋል። በሌላ መልኩ የፊፋን ውሳኔ የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ፍፁም ያልተገባ ሲል የተቃወመ ሲሆን የቤልጂየም እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጉዳዮን ወደ ስፖርት ገላጋይ ፍርድ ቤት (ካስ) እንደ ሚወስደው ገልጿል። ✍️በአህመዲን ከማል #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #sports የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat10

ሰኔ 29፤2018 - ሳንድሮ ቶናሊ በይፋ የቶትንሐም ተጨዋች ሆኗል! ጣሊያናዊው የኒውካስትል ዩናይትድ የመሐልሜዳ ተጨዋች ሳንድሮ ቶናሊ ቶትንሐም ሆትሰፐርን በይፋ መቀላቀሉ ተገልጿል። ሳንድሮ ቶናሊ ቶ
ሰኔ 29፤2018 - ሳንድሮ ቶናሊ በይፋ የቶትንሐም ተጨዋች ሆኗል! ጣሊያናዊው የኒውካስትል ዩናይትድ የመሐልሜዳ ተጨዋች ሳንድሮ ቶናሊ ቶትንሐም ሆትሰፐርን በይፋ መቀላቀሉ ተገልጿል። ሳንድሮ ቶናሊ ቶትንሐም ሆትሰፐርን በ6 ዓመት ኮንትራት የተቀላቀለ ሲሆን ቶትንሐም ለተጨዋቹ ዝውውር ቋሚ 92.5 ሚሊዮን ፓውንድ የዝውውር ሂሳብ እንዲሁም 7.5 ሚሊዮን ፓውንድ በጥቅማጥቅም መልኩ እንደሚከፍልም ተዘግቧል። ከፍሪሚያው በሗላ ሳንድሮ ቶናሊ አሰተያየቱን የሰጠ ሲሆን ''ከአሰልጣኝ ዲዜርቢ ጋር ለሁለት ሰዓት ያክል ስለክለቡ አጨዋወት፣ ስለ ደጋፊዎቹ፣ ስለ ስታዲየሙ እና ሌሎች ጉዳዮች ከተነጋገርን በሗላ ቶትንሐም ሆትሰፐርን ለመቀላቀል ወስንኩ'' ሲል ተደምጧል:: ✍️በአህመዲን ከማል #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #sports የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat10