en
Feedback
Bisratfm101.1

Bisratfm101.1

Open in Telegram

Bisrat FM 101.1 is a radio station established by Oyaya Multimedia. Journalist Messele Mengistu, is the owner of Oyaya Multimedia and who remained in the hearts of the Ethiopian radio listeners for the past 10 years, has just realized his long time dream

Show more
6 632
Subscribers
+224 hours
-147 days
-9730 days
Posts Archive
ሐምሌ 1፤2018 - “የግብጽ ተጫዋቾች ሁሉንም ነገር አደርገዋል እያንዳንዱ ዉሳኔ ለአርጀንቲና ጠቃሚ ነበር" የሪያል ማድሪዱ አሰልጣኝ ጆዜ ሞሪኒሆ ከአርጀንቲናና ግብጽ ጨዋታ በኋላ አስተያየታቸዉን ሰ
ሐምሌ 1፤2018 - “የግብጽ ተጫዋቾች ሁሉንም ነገር አደርገዋል እያንዳንዱ ዉሳኔ ለአርጀንቲና ጠቃሚ ነበር" የሪያል ማድሪዱ አሰልጣኝ ጆዜ ሞሪኒሆ ከአርጀንቲናና ግብጽ ጨዋታ በኋላ አስተያየታቸዉን ሰተዋል:- "በእግር ኳስ እየሆነ ያለዉ ነገር ያሳዝናል የአርጀንቲና የመጀመሪያዉ ጎል መቆጠር አልነበረበትም እንዴት በቫር ሳይታይ ጨዋታዉ እንዲቀጥል ትፈቅዳለህ ጨዋታዉ መቆም ነበረበት ሌላም ጥያቄ አለኝ የአርጀንቲና የመጀመሪያ ጎል ኦፍሳይድ ነበር ግብጽ ግን ጎል አስቆጥራ በቫር ታይቶ ተሽሯል ተመሳሳይ ዉሳኔ በዳኛዉ በኩል አልተመለከትኩም" "ቫር ፍትሀዊነትን እንጂ ግራ መጋባትን ማምጣት የለበትም የግብጽ ተጫዋቾች ሁሉንም ነገር አደርገዋል ለሀገራቸዉ እስከ መጨረሻዋ ደቂቃ ድረስ ተፋልመዋል ጥሩም ተጫዉተዋል ማንም እሄንን አልጠበቀም እኔ ለእነሱ ትልቅ ክብር አለኝ እዉነት መናገር ካለብኝ የዳኝነት ዉሳኔዉ ግን ብዙ የሚያነጋግሩ ጉዳዮች አሉት እኔ ብቻ ሳይሆን ሁሉም ሰዉ ተመልክቶታል" "ሜሲ ሁሌም ሜዳ ላይ ካለ ጎል አለ ተጫዋቾቹ ለሜሲ ይጫወታሉ እያንዳንዱ ዉሳኔ ለአርጀንቲና ጠቃሚ ነበር የስካሎኒ ቅያሬዎች ስኬታማ ነበሩ እኔ ግን ለግብጽ ተጫዋቾች የበለጠ ክብር አለኝ አርጀንቲና የ2026ቱን የአለም ዋንጫ ለማሸነፍ ሁሉም ነገር አላት" ሲሉ ጆዜ ሞሪኒሆ ግልጸዋል። በ-ሙሉቀን ሙጨ ⚽️ #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #sports የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat10

ሐምሌ 1፤2018 - ለፈርኦኖቹ ደማቅ አቀባበል ይደረጋል "ኮርተንባችኋል" የግብፅ ፕሬዝዳንት አብድል ፈታህ አል ሲሲ ብሔራዊ ቡድኑ በአለም ዋንጫ ያሳየዉን ብቃት ተከትሎ መልእክታቸዉን አስተላልፈዋል:
+1
ሐምሌ 1፤2018 - ለፈርኦኖቹ ደማቅ አቀባበል ይደረጋል "ኮርተንባችኋል" የግብፅ ፕሬዝዳንት አብድል ፈታህ አል ሲሲ ብሔራዊ ቡድኑ በአለም ዋንጫ ያሳየዉን ብቃት ተከትሎ መልእክታቸዉን አስተላልፈዋል:- አስደናቂ አጨዋወት ማድረግ ችላችኋል ባሳካችሁት ነገር ሁላችንም ኮርተንባችኃል ቀጣዩ ጊዜ ከዚህ የተሻለ ይሆናል ብለን እናስባለን በሜዳ ላይ ሁሉንም ነገር አደርጋችኋል ጀግኖቻችን እናመሰግናለን በግብፅ የእግር ኳስ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ታሪክ ስላስመዘገባችሁ ሁላችንም በጣም ደስተኞች ነን በማለት አልሲሲ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። የግብፅ ብሔራዊ ቡድን ወደ ሀገር ቤት ሲመለስ ህዝባዊ አቀባበል እንደሚደረግለት እየተነገረ ይገኛል ከወዲሁም በካይሮ እና በተለያዮ የግብጽ ከተሞች ዝግጅት በመደረግ ላይ ነዉ ብሔራዊ ቡድኑ ካይሮ አየር ማረፊያ ሲደርስ የጀግና አቀባበል እንደሚደረግለት የሀገሪቱ ስፖርት ሚኒስቴር አሳዉቀዋል። የግብፅ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ ታሪካዊ ተጫዋች የነበረዉ ሞሀመድ አቡ ታሪካ ከጨዋታው በኃላ አስተያየቱን ሰቷል:- "የተጫወትነው ከፊፋ ከሜሲ እና ከዳኛው ጋር ነው እሄንን ጉዳይ ሁሉም የስፖርት ቤተሰብ ተመልክቷል የሚያበሳጭ ዉጤት ተመዝግቧል ዳኛዉ እና አወዳዳሪዉ አካል የሰሩትን ያዉቃሉ ሜሲ ታላቅ ተጫዋች ነዉ እመኑኝ አርጀንቲና ያለ ሜሲ አለም ዋንጫ ማሸነፍ አትችልም ነበር ለግብጽ ተጫዋቾች ክብር አለኝ ግን ሽንፈቱ ያማል" ሲል አቡታሪካ ተናግሯል። በ-ሙሉቀን ሙጨ ⚽️ #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #sports የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat10

ሐምሌ 1፤2018 - “ሜሲ ሁሉንም አሸንፏል ነገር ግን አሁንም ይፈልጋል" ስዊድናዊዉ ኢንተርናሽናል የቀድሞ ታላቅ ተጫዋች የነበረዉ ዝላታን ኢብራሂሞቪች ሼፊክ ሜሲን በተመለከተ አስተያየቱን ሰቷል:-
ሐምሌ 1፤2018 - “ሜሲ ሁሉንም አሸንፏል ነገር ግን አሁንም ይፈልጋል" ስዊድናዊዉ ኢንተርናሽናል የቀድሞ ታላቅ ተጫዋች የነበረዉ ዝላታን ኢብራሂሞቪች ሼፊክ ሜሲን በተመለከተ አስተያየቱን ሰቷል:- "ሜሲ የማያቋርጥ ጥረት ዉስጥ ይገኛል አሁንም እያየነዉ ነዉ ሜሲ ሁሉንም አሸንፏል ነገር ግን አሁንም ይፈልጋል እያንዳንዱ ጨዋታ ለእሱ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ ማየት ተችላላችሁ ይህንን አለም ዋንጫ አስቀድሞ እንዳሸነፈ አስታዉሱ" "ብዙ ዋንጫዎችን ብዙ ባሎንድኦርን የአመቱ የፊፋ ምርጥ ተጫዋችነትን ሁሉንም ነገር አሸንፏል እዚህ ቁጭ ብየ እሱ ፍጹም የተለየ ተጫዋች ነዉ እያልኩ ነዉ ከሌሎች ሰዎች የሚለይበት ብዙ ነገሮች አሉት ግን አሁንም ዋንጫ ለማሳካት ይፈልጋል አሁንም ይፈልጋል እና እሄ ነገር እዉነት አስደናቂ ነዉ" "አርጀንቲና በጨዋታዉ ግብጽን ለማሸነፏ የግለሰቦች ብቃት እንዳለ ሆኖ ቡድኑ መጀመሪያ ላይ 2-0 ቢመራም ተመልሰዉ ማሸነፍ እንደሚችሉ ያዉቁ ነበር እድሎችን ሲፈጥሩ ተመልክተናል የሜሲ የአመራርነት ብቃት የጨዋታዉን ስሜት ቀይሮታል በአንጻሩ የግብጽ ተጫዋቾች ወደ ኋላ ተመለሱ" "አርጀንቲና አሁንም የአለም ዋንጫዉን ለማሳካት አቅሙ አላት መሪዉ ሜሲ ነዉ የእሱ ፍላጎት የተለየ ነዉ ከመቼዉም ጊዜ በላይ የበለጠ ጠንካራ ሆኖ ቀጥሏል የሜሲ የአስተሳሰብ ደረጃ ሌሎች የቡድኑ ተጫዋቾችን ያነቃቃል" ሲል ዝላታን ሀሳቡን አጋርቷል። በ-ሙሉቀን ሙጨ ⚽️ #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #sports የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat10

ሐምሌ 1፤2018 - “ከዚህ በኋላ አለም ዋንጫ ዉድድርን አላይም" የግብጽ ብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ የሆኑት ሆሳም ሀሰን በአርጀንቲና ሽንፈትን ካስተናገዱ በኋላ በተለያዮ ጉዳዮች ዙሪያ አስተያየታቸ
ሐምሌ 1፤2018 - “ከዚህ በኋላ አለም ዋንጫ ዉድድርን አላይም" የግብጽ ብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ የሆኑት ሆሳም ሀሰን በአርጀንቲና ሽንፈትን ካስተናገዱ በኋላ በተለያዮ ጉዳዮች ዙሪያ አስተያየታቸዉን ሰተዋል። "የፊፋ ሰዎች አርጀንቲና በአለም ዋንጫዉ እንዲቀጥል ፈለገዋል እዉነታዉ እሄ ነዉ ዉጤቱ በሜዳ ዉስጥ ባለዉ ዉስጣዊ ምክኒያቶች ተጽእኖ አሳድሯል ሜሲ በዉድድሩ እንዲቆይ ተፈልጎ ይሆናል እኛ መከራ ደርሶብናል ዳኛዉን ኢ- ፍትሀዊ ነህ ብየ ነግሬዋለሁ ዉሳኔዎቹ ትክክል አልነበሩም ለማንኛዉም እኔ ከዚህ በኋላ የአለም ዋንጫ ዉድድርን አላይም ጨዋታዉ እና ዉጤቱ በእጃችን ነበር አዳዲስ ነገሮች ሜዳ ላይ ተከስተዋል ሁሉም ሰዉ አይቶታል ስለዚህ እያንዳንዱን ነገር መናገር አልፈልግም" "እኛ ግን እንደ ቡድን በሜዳ ላይ አርጀንቲናን በልጠን ተጫዉተናል መጀመሪያም ለማጥቃት ነበር አስበን ወደ ሜዳ የገባነዉ ከዳኛዉ ስህተት ዉጭ በሁሉም ነገሮች ምርጥ ነበርን የአርጀንቲና ተጫዋቾች ግራ እንዲጋቡ ማድረግ ችለናል አፍሪካን አረብን የሀገራችንን ደጋፊዎች ለማስደሰት ተቃርበን ነበር ግን አልቻልንም" የግብጹ አጥቂ ሞስታፋ ዚኮ በበከሉ "ጨዋታዉን እንደገና ማየት ከባድ ነዉ መጥፎ እድል ነዉ ጨዋታዉ በእጃችን ነበር ነገር ግን አንዳንድ ነገሮች በሜዳዉ ላይ ተከሰቱ ሁለተኛዉ ጎል ለምን እንደተሻረ አላዉቅም ለዚህ ምንም ምክኒያት አይታየኝም የተጫወትነዉ ከአለም ሻምፒዮኖቹ ከአርጀንቲና ብሄራዊ ቡድን ጋር ነዉ ብንሸነፍም ባሳየነዉ ነገር ኩራት ይሰማናል ባለፉት 1ዐ ደቂቃዎች ስህተቶችን ሰርተናል የዳኝነቱ ጉዳይ ስህተት እንደነበር ሁሉም አይቷል ለቀጣይ ጥሩ ነገሮች ይኖራሉ አሁንም ምርጥ ቡድን አለን" ሲል ዚኮ ተናግሯል። በ- ሙሉቀን ሙጨ ⚽️ #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #sports የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat10

ሐምሌ 1፤2018 - “እዚህ የተገኘነዉ ዋንጫ ለማሸነፍ ነዉ" የአርጀንቲና ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ የሆኑት ሊዮኔል ስካሎኒ ከድራማዊዉ ጨዋታ በኋላ ሀሳባቸዉን ማጋራት ችለዋል:- "ይቅርታ አሁን በጣም
ሐምሌ 1፤2018 - “እዚህ የተገኘነዉ ዋንጫ ለማሸነፍ ነዉ" የአርጀንቲና ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ የሆኑት ሊዮኔል ስካሎኒ ከድራማዊዉ ጨዋታ በኋላ ሀሳባቸዉን ማጋራት ችለዋል:- "ይቅርታ አሁን በጣም ስሜታዊ ነኝ ምን አይነት ቡድን እንዳለኝ የተመለከታችሁ ይመስለኛል ምን ማለት እንዳለብኝ አላዉቅም ወንድሜ አሁን መሄድ አለብኝ ም/ም ስሜታዊ ነኝ" ሲሉ ገልጸዋል። የማሸነፊዋን ጎል ማስቆጠር የቻለዉ ኤንዞ ፈርናዴዝ በበኩሉ:- "ይህ ቡድን ተስፋ የማይቆርጥ ስብስብ ነዉ ያለን በካታር ዋንጫዉን ካሸነፍን አራት አመታት አልፈዋል አሁን በሌላ ዋንጫ ለመደሰት እዚህ ተገኝተናል ሁሉም ነገር አለን አሁንም አንድ ብቻ አላማ አለን ስሜቱ ከባድ ነዉ አንድ ነገር ማወቅ ያለባችሁ እዚህ የተገኘነዉ ዋንጫ ለማሸነፍ ነዉ ማድረግ እንችላለን 3ኛዋን ጎል በማስቆጠሬ ኩራት ተሰምቶኛል" "የላዉታሮ ኳስ ጥራት ነበረዉ እኔም ተጠቀምኩበት ጥሩ ቡድን እና ምርጥ አሰልጣኝ አለን የምንሰራዉን እናዉቃለን ስለ ሜሲ ምን ማለት ይቻላል እሱ የተለየ ነዉ ከባድ ጨዋታ ነበር እኛ እንደ ቡድን ሁሌም ቢሆን ተነሳሽነት አለን እንቀጥላለን የዳኛዉ ፊሽካ እስካልተነፋ ድረስ መፋለማችንን አናቋርጥም ሜሲን ስናየዉ በፍጹም ተስፋ አንቆርጥም" ሲል ኤንዞ ፈርናዴዝ አስተያየቱን ሰቷል። በ-ሙሉቀን ሙጨ ⚽️ #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #sports የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat10

ሐምሌ 1፤2018 - ከግብፅ እና አርጀንቲና ጨዋታ በሗላ ከኮሎምቢያ እና ከስዊዘርላንድ ጨዋታ በፊት የፊፋ ፕሬዝዳንት ኢንፋንቲኖ የግብፅ ማልያን ሲያዉለበልቡ ተስተዉለዋል የግብፁ አሰልጣኝ ኦሳም ሀሰን
ሐምሌ 1፤2018 - ከግብፅ እና አርጀንቲና ጨዋታ በሗላ ከኮሎምቢያ እና ከስዊዘርላንድ ጨዋታ በፊት የፊፋ ፕሬዝዳንት ኢንፋንቲኖ የግብፅ ማልያን ሲያዉለበልቡ ተስተዉለዋል የግብፁ አሰልጣኝ ኦሳም ሀሰን ሜሲን እና አርጀንቲናን ለማቆየት ፍትህ አጉድለዋል አለም የተመለከተዉ ነዉ ግብፅ በልጣ ነበር ነገር ግን ለቢዝነሳቸዉ ብለዉ እኛን አስቀሩን ብሏል ሩብ ፍፃሜ አርጀንቲና ከስዊዘርላንድ ይገናኛሉ በፍራኦል ረቡማ #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #sports የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat10

ሰኔ 30፤2018 - ሜሲ ታሪክ መስራቱን ቀጥሏል! ሊዮኔል ሜሲ በአንድ የፊፋ የዓለም ዋንጫ ዉድድር ስምንት ጎሎችን ያስቆጠረ ሁለተኛው የአርጀንቲና ተጫዋች ሆኗል ይህም በ1930 ጊለርሞ ስታቢሌ ያስመ
ሰኔ 30፤2018 - ሜሲ ታሪክ መስራቱን ቀጥሏል! ሊዮኔል ሜሲ በአንድ የፊፋ የዓለም ዋንጫ ዉድድር ስምንት ጎሎችን ያስቆጠረ ሁለተኛው የአርጀንቲና ተጫዋች ሆኗል ይህም በ1930 ጊለርሞ ስታቢሌ ያስመዘገበውን የረጅም ጊዜ ሪከርድ አስመዝግቧል ። ሜሲ በአትላንታ በተካሄደው የ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ የ16ቱ ዙር ጨዋታ አርጀንቲና ከግብፅ ጋር ባደረገችው ጨዋታ 83ኛዉ ደቂቃ ላይ የአቻነት ጎል አስቆጥሯል ። ካፒቴኑ ከስታቢሌ ጋር በብሔራዊ ቡድኑ ሪከርድ መዝገብ ውስጥ እንዲሳተፍ አስችሎታል። ስቴቢል በ1930 በኡራጓይ በተካሄደው የመጀመሪያ ውድድር ስምንት ጎሎችን በማስቆጠር ለ96 ዓመታት በአንድ የዓለም ዋንጫ ውድድር ላይ የአርጀንቲና ከፍተኛ ጎል አስቆጣሪ ሆኖ ቆይቶ ነበር። ✍️አዲስ መሀመድ #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #sports የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat10

ተጠናቀቀ አርጀንቲና 3-2 ግብፅ ⚽️ ሮሜሮ ⚽ ኢብራሂም ⚽️ ሜሲ ⚽️ ዚኮ ⚽️ ኢንዞ ፈርናንዴዝ
ተጠናቀቀ አርጀንቲና 3-2 ግብፅ  ⚽️ ሮሜሮ         ⚽ ኢብራሂም ⚽️ ሜሲ           ⚽️ ዚኮ ⚽️ ኢንዞ ፈርናንዴዝ

85 ' አርጀንቲና 2-2 ግብፅ ⚽️ ሮሜሮ ⚽ ኢብራሂም ⚽️ ሜሲ ⚽️ ዚኮ
85 ' አርጀንቲና 2-2 ግብፅ ⚽️ ሮሜሮ ⚽ ኢብራሂም ⚽️ ሜሲ ⚽️ ዚኮ

82 ' አርጀንቲና 1- 2 ግብፅ ⚽️ ሮሜሮ ⚽ ኢብራሂም ⚽️ ዚኮ
82 ' አርጀንቲና 1- 2 ግብፅ ⚽️ ሮሜሮ ⚽ ኢብራሂም ⚽️ ዚኮ

ሰኔ 30፤2018 - በሊባኖስ ክርስቲያኖች በአብላጫ በሚኖሩበት ስፍራ ከእስራኤል ጋር መቀላቀል ይፈልጋሉ ሲሉ ኔታንያሁ ያደረጉትን ንግግር ውድቅ አደረጉ በሊባኖስ ደቡባዊ ድንበር ላይ የሚገኙ የክርስት
ሰኔ 30፤2018 - በሊባኖስ ክርስቲያኖች በአብላጫ በሚኖሩበት ስፍራ ከእስራኤል ጋር መቀላቀል ይፈልጋሉ ሲሉ ኔታንያሁ ያደረጉትን ንግግር ውድቅ አደረጉ በሊባኖስ ደቡባዊ ድንበር ላይ የሚገኙ የክርስትና እምነት ተከታዮች በብዛት በሚገኙባቸው መንደሮች የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ እስራኤልን ለመቀላቀል እንደሚፈልጉ የሰጡትን አስተያየት ውድቅ አድርገዋል። ከሊባኖስ ድንበር ክልል ውስጥ ካሉ መንደሮች የመጡ ከንቲባዎች፣ ቀሳውስት እና የማህበረሰብ መሪዎች ለአናዶሉ የዜና ወኪል እንደተናገሩት ለሊባኖስ ማንነታቸው ቁርጠኛ መሆናቸውን ቀጥለዋል። “የድንበር መንደር ነዋሪዎች ለሊባኖስ መንግሥት እና ለሕጋዊነቱ ቁርጠኛ ሆነው ቀጥለዋል፣ እናም የእስራኤል ጥቃት ያስከተለውን አስቸጋሪ ሁኔታ ቢያስወግድም ከዚህ አቋም ፈቀቅ ብለው አያውቁም” ሲሉ የክርስቲያን ድንበር መንደሮችን የሚወክሉ ማዘጋጃ ቤቶች በጋራ ባወጡት መግለጫ ተናግረዋል። የማዘጋጃ ቤቶቹ ነዋሪዎች “በብሔራዊ ንብረታቸው ይኮራሉ፣ ሊባኖስን እንደ ትውልድ አገራቸው አጥብቀው ይይዛሉ፣ እናም አቋማቸውን ለማዛባት ወይም ምንም ግንኙነት ለሌላቸው አጀንዳዎች ለመጠቀም የሚደረጉ ማናቸውንም ሙከራዎች ውድቅ ያደርጋሉ” ብለዋል። እሁድ ዕለት ኔታንያሁ በቴሌቪዥን በተደረገ ቃለ ምልልስ በደቡባዊ ሊባኖስ የሚገኙ በርካታ የክርስቲያን መንደሮች ከሂዝቦላህ ጥበቃ ለማግኘት ከእስራኤል እንዲዋሃዱ ጋር ጠይቀዋል ሲሉ መናገራቸው ይታወሳል። በስምዖን ደረጄ #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #Ethiopia የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat101

ሰኔ 30፤2018 - ሊዮኔል ሜሲ በአንድ የዓለም ዋንጫ ሁለት የፍፁም ቅጣት ምቶችን የሳተ የመጀመሪያው ተጫዋች ሆኗል! ሊዮኔል ሜሲ በፊፋ የዓለም ዋንጫ ታሪክ ከግብፅ ጋር ባደረገው ጨዋታ ፍፁም ቅጣት
ሰኔ 30፤2018 - ሊዮኔል ሜሲ በአንድ የዓለም ዋንጫ ሁለት የፍፁም ቅጣት ምቶችን የሳተ የመጀመሪያው ተጫዋች ሆኗል! ሊዮኔል ሜሲ በፊፋ የዓለም ዋንጫ ታሪክ ከግብፅ ጋር ባደረገው ጨዋታ ፍፁም ቅጣት ምት ከሳተ በኋላ በአንድ ውድድር ላይ ሁለት የፍፁም ቅጣት ምቶችን የሳተ የመጀመሪያው ተጫዋች ሆኗል ። የአርጀንቲናው ካፒቴን በ16ቱ ዙር ጨዋታ ግብፃዊው ግብ ጠባቂ ሞስታፋ ሾቤር ጥረቱን አድኖታል በምድብ ጨዋታ ከኦስትሪያ ጋር ባደረገው ጨዋታም የፍፁም ቅጣት ምት ስቷል ምንም እንኳን በዚያ ጨዋታ ሁለት ጎሎችን ማስቆጠር ቢችልም። ሜሲ አሁን በዓለም ዋንጫ ጨዋታዎች ከስምንት የፍፁም ቅጣት ምቶች ውስጥ አራቱን ሳይጠቀም የቀረ ሲሆን የመጨረሻው የፍፁም ቅጣት ምቱ ያልተፈለገ የውድድር ዘመን ሪከርድ አስመዝግቧል። የስምንት ጊዜ የባሎንዶር አሸናፊው ለአርጀንቲና በ197 ጨዋታዎች 73 ጎሎችን እና 33 አሲስቶችን አስመዝግቧል። ✍️አዲስ መሀመድ #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #sports የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat10

ሰኔ 30፤2018 - አርጀንቲና 19 የዓለም ዋንጫ ቅጣት ምቶችን ያገኘች የመጀመሪያዋ ሀገር ሆነች! አርጀንቲና በ16ቱ ዙር ከግብፅ ጋር ባደረገችው ጨዋታ የፍፁም ቅጣት ምት ካገኘች በኋላ በፊፋ የዓለ
ሰኔ 30፤2018 - አርጀንቲና 19 የዓለም ዋንጫ ቅጣት ምቶችን ያገኘች የመጀመሪያዋ ሀገር ሆነች! አርጀንቲና በ16ቱ ዙር ከግብፅ ጋር ባደረገችው ጨዋታ የፍፁም ቅጣት ምት ካገኘች በኋላ በፊፋ የዓለም ዋንጫ ታሪክ 19 ቅጣት ምቶችን ያገኘች የመጀመሪያዋ ሀገር ሆናለች ። ፍፁም ቅጣት ምቱ አርጀንቲና ከዚህ በፊት በዓለም ዋንጫ ጨዋታዎች 18 የቅጣት ምት በማግኘት ሪከርዱን የተጋራችው ስፔንን እንድትበልጥ አድርጓታል። ሊዮኔል ሜሲ ፍፁም ቅጣት ምት ቢመታም የግብፁ ግብ ጠባቂ ሞስታፋ ሾቤር ኳሱን አድኖታል። የአርጀንቲናዉ ካፒቴን አሁን ስምንት የዓለም ዋንጫ ፍፁም ቅጣት ምቶችን መቷል ከነዚህ ዉስጥ አራት ፍፁም ቅጣት ምቶችን ሲያስቆጥር ጊዜ አራት ጊዜ ደግሞ ስቷል። ✍️ አዲስ መሀመድ #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #sports የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat10

ሰኔ 30፤2018 - ግብፅ የመጀመሪያውን አጋማሽ ያሲር ኢብራሂም ባስቆጠራት ግብ አርጀንቲናን 1-0 እየመራች ወደ እረፍት መውጣት ችላለች ሊዮናል አንድሬስ ሜሲ አርጀንቲና ያገኘችውን የፍፁም ቅጣት ሳ
ሰኔ 30፤2018 - ግብፅ የመጀመሪያውን አጋማሽ ያሲር ኢብራሂም ባስቆጠራት ግብ አርጀንቲናን 1-0 እየመራች ወደ እረፍት መውጣት ችላለች ሊዮናል አንድሬስ ሜሲ አርጀንቲና ያገኘችውን የፍፁም ቅጣት ሳይጠቀምበት ቀርቷል። #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #sports የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat10

ሰኔ 30፤2018 - አርሰናል ግብ ጠባቂ ሊያስፈርም ነው! አርሰናል ግብ ጠባቂ ኢላን ሜስሊየርን ከሊድስ ዩናይትድ ከለቀቀ በኋላ ለማስፈረም ከጫፍ ደርሰዋል ። የ26 አመቱ ተጫዋች ባለፈው የውድድር ዘ
ሰኔ 30፤2018 - አርሰናል ግብ ጠባቂ ሊያስፈርም ነው! አርሰናል ግብ ጠባቂ ኢላን ሜስሊየርን ከሊድስ ዩናይትድ ከለቀቀ በኋላ ለማስፈረም ከጫፍ ደርሰዋል ። የ26 አመቱ ተጫዋች ባለፈው የውድድር ዘመን መጨረሻ ላይ ከኤልላንድ ሮድ ከለቀቀ በኋላ በነፃ ዝውውር ላይ የሚገኝ ሲሆን ይህም በዮርክሻየር ክለብ ውስጥ ለሰባት አመታት የዘለቀውን ቆይታ አጠናቋል። ሜስሊየር በሊድስ ቆይታው 215 ጨዋታዎችን አድርጓል እና ለአምስት ተከታታይ የውድድር ዘመናት የክለቡ የመጀመሪያ ምርጫ ግብ ጠባቂ ሆኖ በክለቡ ራሱን አሳይቷል ። ይሁን እንጂ አስቸጋሪ በሆነው የ2024/25 የውድድር ዘመን ሜስሊየር በተከታታይ ወጥነት በሌላቸው ብቃቶች ምክንያት በዋና አሰልጣኝ ዳንኤል ፋርኬ ስር ቋሚ ቦታውን አጥቷል። ለሊድስ የመጨረሻ ጨዋታውን ያደረገው በመጋቢት 2025 ከስዋንሲ ሲቲ ጋር ባደረጉት ጨዋታ 2-2 በሆነ አቻ ውጤት ሲጠናቀቅ ነው። ዘገባው ሜስሊየር ወደ ኤሚሬትስ ስታዲየም የሚያደርገውን ዝውውር ከማጠናቀቁ በፊት የሕክምና ምርመራ ሊያደርግ እንደሆነ ይገልጻል። አርሰናል የዝውውር ክፍያ ሳይከፍሉ ከፍተኛ የፕሪሚየር ሊግ ልምድ ያለው ግብ ጠባቂ የመጨመር እድል ካገኙ በኋላ በፍጥነት እርምጃ ወስደዋል። የሜስሊየር መምጣት ከፍተኛ ደረጃ የተሰጠው የእንግሊዝ ከ21 አመት በታች ግብ ጠባቂ ቶሚ ሴትፎርድ የወደፊት ዕጣ ፈንታ ላይ ተጽዕኖ ሊያሳድር ይችላል ተብሏል። ✍️አዲስ መሀመድ #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #sports የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat10

ሰኔ 30፤2018 - በወላይታ ሶዶ ከተማ የ14 ሰዎችን ኤቲኤም ካርድ የሰረቀው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ በወላይታ ሶዶ ከተማ የኤቲኤም (ATM) ካርድ በመቀየር የማጭበርበር ወንጀል ለመፈጸም የሞከረ
ሰኔ 30፤2018 - በወላይታ ሶዶ ከተማ የ14 ሰዎችን ኤቲኤም ካርድ የሰረቀው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ በወላይታ ሶዶ ከተማ የኤቲኤም (ATM) ካርድ በመቀየር የማጭበርበር ወንጀል ለመፈጸም የሞከረው ግለሰብ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል ።የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነትና ገጽታ ግንባታ ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር አሸናፊ ኃይሌ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለጹት በወላይታ ሶዶ ከተማ አንድ የባንክ ደንበኛ ከኤቲኤም ማሽን ገንዘብ ለማውጣት ሲሞክር ማሽኑ ችግር አጋጥሞት ነበር። በወቅቱ በአቅራቢያው የነበረው ተጠርጣሪ ዳንኤል ደሳለኝ “ካርዱን ስጠኝ፣ በፀጉሬ ጠርጌ እሰጥሃለሁ” በሚል የማታለያ ዘዴ ካርዱን ተቀብሎ ወስዷል።በሰዓቱም የሚስጥር ቁጥሩን (PIN) ሲያስገባ በመመልከት ካርዱን ጠርጎ የመለሰ በማስመሰል ሌላ የተቀየረ የኤቲኤም ካርድ ሰጥቶ ዋናውን ካርድ ይዞ ለማምለጥ ሞክሯል።የደረሰውን ጥቆማ ተከትሎ ፖሊስ ባደረገው ፈጣን ክትትል ተጠርጣሪውን እጅ ከፍንጅ በመያዝ ቁጥጥር ስር አውሏል። ፖሊስ ምርመራውን በማስፋት በፍርድ ቤት በተሰጠ የብርበራ ትዕዛዝ በተጠርጣሪው የተጎጂውን ካርድ ጨምሮ 14 የተለያዩ ሰዎች የኤቲኤም ካርዶችን ይዞ መገኘቱ ተገልጿል።ፖሊስ ህብረተሰቡ ከኤቲኤም ማሽኖች ገንዘብ በሚያወጣበት ጊዜ የሚስጥር ቁጥሩን ለሌላ አካል እንዳያሳይ በማሽኑ አጠቃቀም ላይ ችግር ካጋጠመውም ከማያውቀው ሰው እርዳታ ከመጠየቅ ይልቅ የባንኩን ባለሙያዎች ወይም የጥበቃ አካላትን ብቻ እንዲያነጋግር አሳስቧል። በሳምራዊት ስዩም #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #Ethiopia የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat101

ሰኔ 30፤2018 - በአሽሙር ሰደበኝ በማለት የቢራ ብርጭቆ ወርውሮ አንድ አይን ያጠፋው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ በምስራቅ ባሌ ዞን ጊኒር ከተማ አስተዳደር በአሽሙር ሰደበኝ በማለት የቢራ መጠጫ ብርጭ
ሰኔ 30፤2018 - በአሽሙር ሰደበኝ በማለት የቢራ ብርጭቆ ወርውሮ አንድ አይን ያጠፋው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ በምስራቅ ባሌ ዞን ጊኒር ከተማ አስተዳደር በአሽሙር ሰደበኝ በማለት የቢራ መጠጫ ብርጭቆ በመወርወር አንድ አይን ያጠፋው ግለሰብ በእስራት መቀጣቱ ተገልጿል።የጊኒር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ፅ/ቤት ኃላፊ ኢንስፔክተር ኢብራሂም አቡበከር ለብስራት ሬዲዮ እንደገለጹት ተከሳሽ እስራኤል ተስፋዬ፣ የግል ተበዳይ ደግሞ አብረሃም ካሳዬ ይባላል። ሁለቱ ወጣቶች ነሃሴ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ላይ በጊኒር ከተማ አጋምሳ ቀበሌ በአንድ ግሮሰሪ ውስጥ ከተገናኙ በኋላ ድርጊቱ መፈጸሙን ገልጸዋል።ተከሳሽና የግል ተበዳይ በግሮሰሪ ውስጥ እየተጫወቱ ሳለ አለመግባባት መፍጠራቸውን የገለጹት ሃላፊው የግጭታቸው መንስዔ ተከሳሽ በአሽሙር ሰድቦኛል የሚል ነው ብለዋል ።የሚጠጣበትን የቢራ ብርጭቆ በመወርወር የግራ አይኑ ብሌን እንዲፈስ ማድረጉን ነግረውናል። ፖሊስም በወቅቱ የደረሰውን ጥቆማ መሰረት አድርጎ ተከሳሹን በቁጥጥር ስር በማዋል የምርመራ መዝገቡን በሰውና በህክምና ማስረጃ በማጠናከር ለአቃቢ ህግ ልኳል።አቃቢ ህግም ከፖሊስ የቀረበውን የምርመራ መዝገብ ተመልክቶ ታስቦ የሚፈፀም ከባድ የአካል ጉዳት ክስ መስርቷል።የአቃቢ ህግን ክስ ሲከታተል የቆየው የጊኒር ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ እስራኤል ተስፋዬ አስፈላጊ ከሆኑ የሰውነት ክፍሎች ላይ በሚታይ ስፍራ ጉዳት ማድረሱ ተነግሯል። በተጎጂው ሰውነትና አእምሮ ላይ የማይሽር ጠባሣ በማሳረፉ በሁለት ዓመት ከሶስት ወራት እስራት እንዲቀጣ ተወስኖበታል በማለት ኢንስፔክተር ኢብራሂም አቡበከር ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ገልፀዋል። በኤደን ሽመልስ #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #Ethiopia የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat101

ሰኔ 30፤2018 - ቻይና 325 ሚሊዮን ዶላር ጉቦ የተቀበሉትን የመንግስት ባለስልጣን በሞት እንዲቀጡ ወሰነች በምስራቅ ቻይና የሚገኝ አንድ ፍርድ ቤት ለ30 ዓመታት ከ2.2 ቢሊዮን ዩዋን ወይም 32
ሰኔ 30፤2018 - ቻይና 325 ሚሊዮን ዶላር ጉቦ የተቀበሉትን የመንግስት ባለስልጣን በሞት እንዲቀጡ ወሰነች በምስራቅ ቻይና የሚገኝ አንድ ፍርድ ቤት ለ30 ዓመታት ከ2.2 ቢሊዮን ዩዋን ወይም 325 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ ጉቦ የወሰዱ የቀድሞ የከተማው ባለስልጣን በሞት ፍርድ እንዲቀጡ ተወስኖባቸዋል። ከ1993 እስከ 2023 በናንጂንግ ከተማ በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ ያገለገሉት ያንግ ዩሊን በማጭበርበር፣ ስልጣን አላግባብ በመጠቀም እና በገንዘብ ማዘዋወር ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው ተገኝተዋል። የ69 ዓመቱ አዛውንት ገንዘብ እና ውድ ንብረቶችን በመቀበል ባለሀብቶች የምህንድስና ኮንትራቶችን፣ የመሬት ዝውውርን እና ፋይናንስን እንዲያገኙ ለመርዳት መስራታቸውን የመንግስት ሚዲያዎች ዘግበዋል።ያንግ ላይ ምርመራው የተደረገው ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ በወታደራዊ እና ከፍተኛ ደረጃ ባላቸው የባንክ ዘርፎች ላይ ባስጀመሩት የፀረ-ሙስና ዘመቻ አካል ነው። በናንጂንግ አብዛኛውን የስራ ዘመናቸውን ያሳለፉት ያንግ እጅግ ከባድ ወንጀሎችን ፈጽመዋል። ይህው ድርጊታቸው “በመንግስት እና በህዝቡ ጥቅም ላይ እጅግ ከባድ ኪሳራ አስከትሏል” ሲል በቻንግዙ ከተማ የሚገኝ ፍርድ ቤት አስታውቋል። በስምዖን ደረጄ #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #Ethiopia የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat101

ሰኔ 30፤2018 - ሙትአንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል ገዳም ለጀመረው የልማት ፕሮጀክት ከ63 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ማግኘቱን አስታወቀ የሙትአንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የገጠመውን መጠለያ
+1
ሰኔ 30፤2018 - ሙትአንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል ገዳም ለጀመረው የልማት ፕሮጀክት ከ63 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ማግኘቱን አስታወቀ የሙትአንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የገጠመውን መጠለያ የማጣት ችግር ለመቅረፍና ራሱን ለማስቻል በጀመረው የልማት ፕሮጀክት ገዳሙ ባለፉት ሁለት ዓመታት ከስድስት ወራት ውስጥ ባከናወናቸው የገቢ ማሰባሰብ ሥራዎች ከ63 ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብ እና የዓይነት ድጋፍ ማግኘት መቻሉን የአስተዳደሩ ተወካዮች ገልጸዋል። የገዳሙ አስተዳደር እንደገለፀው በተለያዩ የቴሌቪዥን ዘጋቢ ፕሮግራሞች እና በማኅበራዊ ሚዲያ አማካኝነት በተደረገው ሰፊ የገቢ ማሰባሰብ ጥረት 52 ሚሊዮን 640 ሺህ ብር በጥሬ ገንዘብ፣ 11 ሚሊዮን 320 ሺህ ብር የሚገመት የዓይነት ድጋፍ መሰብሰቡ ነዉ የተገለፀዉ። ይህ የተገኘው ድጋፍ የልማት ፕሮጀክቱን የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ምዕራፎች ከ65 በመቶ በላይ ለማሳካት ያስቻለ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የእናቶች በዓት እና የእንግዳ ማረፊያ ግንባታ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ እናቶች አገልግሎት ማግኘት መጀመራቸው ተገልጿል። ከ160 በላይ ገዳማውያን የሚገኙበት ይህ አንድነት ገዳም ከተፈጥሮአዊ እና ሰው ሠራሽ ችግሮች ጋር ተያይዞ ገዳማውያኑ ከብርድና ከዝናብ የሚከላከል መጠለያ አጥተው በከፍተኛ ችግር ውስጥ ይገኙ እንደነበር ተገልጿል። በአሁኑ ወቅት ምዕመናን የሚገኙበት የሐዋርያት ጾም (የሰኔ ጾም) የበረከት ወቅት በመሆኑ፣ የተጀመረው የልማት ሥራ ሙሉ በሙሉ ፍጻሜ እንዲያገኝ ሕዝበ ክርስቲያኑ የጀመረውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርቧል። በሰመሀር አለባቸው #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #Ethiopia የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat101

ሰኔ 30፤2018 - ያልታከመ የማህፀን ኢንፌክሽን መካንነትን ሊያስከትል ይችላል ተባለ በባክቴሪያ ፣በፈንገስ እና በቫይረስ አማካኝነት የሚከሰት የሴቶች የመራቢያ አካል ወይንም የማህፀን ኢንፌክሽን ህ
ሰኔ 30፤2018 - ያልታከመ የማህፀን ኢንፌክሽን መካንነትን ሊያስከትል ይችላል ተባለ በባክቴሪያ ፣በፈንገስ እና በቫይረስ አማካኝነት የሚከሰት የሴቶች የመራቢያ አካል ወይንም የማህፀን ኢንፌክሽን ህክምና ካላገኘ እና በተደጋጋሚ የሚከሰት ከሆነ መካንነትን ሊያስከትል እንደሚችል ከብስራት ሬዲዮ ጋር ቆይታ ያደረጉት የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ታዘባቸዉ ዉዴ ገልፀዋል። የማህፀን ወይንም ብልት አካባቢ የሚከሰት ኢንፌክሽን በርካታ ሰዎችን ከሚያጠቁ የኢንፌክሽን አይነቶች መካከል ዋነኛዉ መሆኑ ተገልጿል ።ለማህፀን ኢንፌክሽን አጋላጭ የሚሆኑ በርካታ ምክንያቶች መኖራቸዉን የሚገልፁት ዶክተር ታዘባቸዉ በግብረ ስጋ ግንኙነት የሚተላለፉ እንደ ክላሚዲያ እና ጎኖሪያ ያሉ ባክቴሪያዎች ዋነኞቹ መሆናቸዉን አስገንዝበዋል ። በአብዛኛዉ መካንነትን ሊያስከትሉ የሚችሉትም በባክቴሪያ አማካኝነት የሚከሰቱ ኢንፌክሽኖች ናቸዉ። የማህፀን ኢንፌክሽን ከመከሰቱ አስቀድሞ መከላከል ዋነኛዉ መፍትሄ መሆኑን ዶክተር ታዘባቸዉ ገልፀው ብልት አካባቢ የማሳከክ ፣የመቁሰል ፣የሆድ ህመም እና ሽንት በሚሸናበት ወቅት የማቃጠል ስሜት ሲኖር ወደ ጤና ተቋም በመሄድ ምርመራ ማድረግ እና ህክምና ማግኘት ተገቢ ነዉ ብለዋል ። በመባ ወርቅነህ #BisratNews #BisratFm #BisratRadio #Ethiopia የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ… Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400 Website: https://www.bisrattv.com/ Telegram: https://t.me/Bisrat101fm YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB Twitter: https://twitter.com/Bisrat101