Bisratfm101.1
Open in Telegram
Bisrat FM 101.1 is a radio station established by Oyaya Multimedia. Journalist Messele Mengistu, is the owner of Oyaya Multimedia and who remained in the hearts of the Ethiopian radio listeners for the past 10 years, has just realized his long time dream
Show more6 570
Subscribers
No data24 hours
+37 days
+230 days
Posts Archive
6 570
ጳጉሜን 2፤2018 - የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለ840 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ፡፡
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት መጪውን አዲስ ዓመት አስመልክቶ የይቅርታ መስፈርቱን ላሟሉ 840 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ ማድረጉን አስታውቋል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እንዳስታወቁት ይቅርታ የተደረገላቸው ታራሚዎች በማረሚያ ቤት ቆይታቸው መልካም ሥነ-ምግባር ያሳዩ ሲሆን በሕግ የተደነገጉ የይቅርታ መስፈርቶችን ማሟላታቸው በክልሉ የይቅርታ ቦርድ ተጣርቶ ቀርቧል።
ታራሚዎቹ በመደበኛ የይቅርታ ሕግ እና ተጨማሪ መስፈርቶች መሠረት ይቅርታ የሚያስገኙ ሁኔታዎችን ያሟሉ መሆናቸውም ተገልጿል።
ይቅርታ ከተደረገላቸው ታራሚዎች መካከል 56ቱ ሴቶች ሲሆኑ 784 ቱ ደግሞ ወንዶች ናቸው።ታራሚዎቹ በማረሚያ ቤት የቆዩ ፣የጤና ችግር የነበረባቸው ፣በዕድሜ የገፉ፣ እንዲሁም ከተፈረደባቸው የእስራት ጊዜ አንድ ሦስተኛ ወይም ከግማሽ በላይ የሆነውን የቅጣት ጊዜ ያጠናቀቁ መሆናቸው ታውቋል።
የይቅርታው ተጠቃሚ የሆኑ የሕግ ታራሚዎች የይቅርታን እሴት ተላብሰው ሰላም ወዳድ፣ ለሕግ ተገዥና አምራች ዜጋ በመሆን የበደሉትን ህብረተሰብ በማገልግል ሊክሱ ይገባል ተብሏል።
ማኅበረሰቡም ይቅርታ የተደረገላቸው ታራሚዎች በጥፋታቸው ተፀፅተውና ታርመው የወጡ መሆኑን በመረዳት ወደ መልካም እና አምራች ኑሮ እንዲመለሱ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል።
በሳምራዊት ስዮም
#BisratNews #BisratFm #BisratRadio #Ethiopia
የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…
Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101
6 570
ጳጉሜን 2፤2018 - በኢትዮጵያ ከ46 በመቶ በላይ የሚሆኑ ወጣቶች በሱስ ተጠቂ መሆናቸው ተነገረ::
በኢትዮጵያ የወጣቶች የሱስ ተጠቃሚነት በከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን በቅርቡ የተደረገ አንድ ሀገራዊ ጥናት አመላክቷል።
በጥናቱ መሰረት ከ15 እስከ 24 በሚሆን የዕድሜ ክልል ዉስጥ የሚገኙ ወጣቶች የሱስ ተጠቂ መሆናቸዉ ተረጋግጧል ሲሉ በቅዱስ ጳዉሎስ ሆስፒታል የአእምሮ ህክምና ስፔሻሊስት የሆኑት ዶክተር አስካለማሪያም ቢክስ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል ።
እንደ ዶክተር አስካለማሪያም ገለፃ በወጣቶች ዘንድ የአልኮል ተጠቃሚነት ሱስ ከፍተኛዉን ድርሻ ይይዛል ። ሲጓራ እና ጫትን ጨምሮ ለማስታገሻነት በጥንቃቄ የሚወሰዱ መድኃኒቶችን ወጣቶች ለሱስ እንደሚጠቀሙበት ተገልጿል ።
ወጣቶች ራሳቸዉን ከሱስ ለመጠበቅ እርስ በእርስ መረዳዳት ፣ጊዜያቸዉን ትርጉም ባላቸዉ ነገሮች ላይ ማሳለፍ ፣ስፖርት መስራት እና በሌሎች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ መሳተፍ እንዳለባቸዉ ተነግሯል።የሱስ ተጠቂነት የሚያስከትለው ጫና ቀላል አለመሆኑን የሚያስረዱት ስፔሻሊስቷ ተጋላጭ የሆኑ ሰዎች ለራሳቸዉ ቅድሚያ በመስጠት ህክምና ማድረግ እንዳለባቸዉ አስገንዝበዋል ።
ሱስ በአካል እንዲሁም በአእምሮ ላይ የሚያሳድረዉን ተፅዕኖ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል ተገንዝቦ ከመፈረጅ ይልቅ በዙሪያው ያሉ የሱስ ተጠቂዎች የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ ይኖርበታል ተብሏል ።
በመባ ወርቅነህ
#BisratNews #BisratFm #BisratRadio #Ethiopia
የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…
Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101
6 570
ጳጉሜን 2፤2018 - በቦንጋ ከተማ የተሰረቁ ሞባይሎችን የገዙ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ
.
በቦንጋ ከተማ የተሰረቁ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን በተለይም ሞባይሎችን የገዙና የተቀበሉ ግለሰቦች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን የቦንጋ ከተማ ፖሊስ አስታውቋል።
የቦንጋ ከተማ ወጣቶች ያለአግባብ እየታሰሩ ነው በሚል በማህበራዊ ትስስር ገጾች የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑንና ዓላማውም ወንጀል የፈጸሙ ግለሰቦች በህግ እንዳይጠየቁ ለማድረግ እንደሆነ ፖሊስ ገልጿል።
የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለፁት በከተማው የስርቆት ወንጀል ተፈጽሞ የተሰረቁ ሞባይሎችን የሚገዙ፣ የሞባይል ይለፍ ቃል የሚጠልፉ እና ከህገወጥ የስርቆት ተግባር ፈጻሚዎች ጋር ግንኙነት ያላቸው አምስት ግለሰቦች በመረጃ እንዲለዮ ተደርጓል።
በሞባይል ጥገና ስራ የተሰማሩ አራት ግለሰቦችም በቁጥጥር ስር ውለዋል።አንደኛው ተጠርጣሪ መሰወሩ የተገለፀ ሲሆን በቁጥጥር ስር ለማዋል ፖሊስ በክትትል ላይ ይገኛል ሲሉ ኢንስፔክተሩ ጨምረው ገልፀዋል።ተጠርጣሪዎቹ የተሰረቁ ሞባይሎችን የይለፍ ቃል በመክፈትና በውስጣቸው ያሉ መረጃዎችን በማጥፋት ገንዘብ ሲቀበሉ እንደነበር ተነግሯል።
ፖሊስ በተጨማሪም የተሰረቁ ዕቃዎችን የሚገዙ፣ የሚረከቡና የሚያጓጉዙ ግለሰቦች እንዲሁም ባለሦስት እግር ባጃጅ ተሽከርካሪዎች በመኖራቸው ህብረተሰቡ እነዚህን ሕገወጥ ተግባራት ለመከላከልና ወንጀለኞችን ለሕግ ለማቅረብ ከፖሊስ ጋር እንዲተባበር ጥሪ አቅርቧል።
በሳምራዊት ስዮም
#BisratNews #BisratFm #BisratRadio #Ethiopia
የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…
Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101
6 570
ጳጉሜን 2፤2018 - ትራምፕ አዲሱ የሜክሲኮ ግዛት መጠሪያ ስም እንዲቀየር ሃሳብ አቀረቡ
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የቦታዎችን ስም የመቀየር ዘመቻቸው እሁድ ዕለት ያልተጠበቀ አዲስ ኢላማ ያገኘ ሲሆን፣ የአዲሷ ሜክሲኮ ግዛት ስም ወደ ኒው አሜሪካ (አዲሷ አሜሪካ) ቢቀየር የሚል ሃሳብ አቅርበዋል።
በግዛቷ አስተዳዳሪ ወዲያውኑ ውድቅ የተደረገው ይህ የትራምፕ ሃሳብ የቀረበው፣ ከጎረቤት ካናዳ ጋር ባለው የንግድ ጦርነት መሃል የኦንታሪዮ ሀይቅ ስም ወደ አሜሪካ ሀይቅ እንዲቀየር ትእዛዝ በፈረሙ በቅርብ ቀናት ውስጥ ነው።ሪፐብሊካኑ ፕሬዝዳንት በማህበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት ብዙ ሰዎች የአዲሷ ሜክሲኮ ስም ወደ አዲሷ አሜሪካ ቢቀየር የሚል ሃሳብ አቅርበዋል።
ይህም አቅም ላላት ግዛትና ለህዝቦቿ እጅግ የላቀ ዝና የሚያጎናጽፍና ውብ ይሆናል፤ እኔ በጣም ወድጄዋለሁ ብለዋል። ዋይት ሀውስም የአዲሷ ሜክሲኮ ግዛት ስም ላይ ሜክሲኮ የሚለው ተሰርዞ በቦታው አሜሪካ የሚል የተቀመጠበትን ምስል መልሶ አጋርቷል።
አንዳንድ የአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን ዘገባዎች እንደሚጠቁሙት ይህ ሃሳብ መነሻው የኢንተርኔት የፈጠራ ወሬ ሳይሆን አልቀረም። የግዛቷ አስተዳዳሪ ሚሼል ሉሃን ግሪሻም ለፎክስ ኒውስ በሰጡት አስተያየት የስሙ ጉዳይ ለድርድር የሚቀርብ አይደለም፤ አሜሪካ ሀገር ሆና ከመመስረቷ በፊትም ቢሆን የኛው ስም ነበር ብለዋል።
አስተዳዳሪዋ አክለውም ፕሬዝዳንቱ የአሜሪካውያንን ትኩረት እንደ ነዳጅ ዋጋ መናር ካሉ አጣዳፊ ጉዳዮች ለማስወጣት ይፈልጋሉ ብለዋል። ትራምፕ ባለፈው ሳምንት ከኢራን ጋር ያለው ጦርነት በቀጠለበት ወቅት የሆርሙዝ ሰርጥ ስም ወደ ትራምፕ ሰርጥ እንዲቀየር ሃሳብ አቅርበው የነበረ ቢሆንም፣ ከሰዓታት በኋላ ግን ስለ እቅዱ እውነተኛ እንዳልነበሩ ጠቁመዋል።
ፕሬዝዳንቱ እ.ኤ.አ በ2025 ወደ ዋይት ሀውስ በተመለሱበት የመጀመሪያ ቀን የሜክሲኮ ባሕረ ሰላጤን ስም ወደ የአሜሪካ ባሕረ ሰላጤ የቀየሩ ሲሆን፣ ይህም እርምጃ በሜክሲኮ በኩል ውድቅ ተደርጎ ነበር። በተመሳሳይ ካናዳም የኦንታሪዮ ሀይቅን ስም የመቀየር ጥረቱን ውድቅ አድርጋዋለች።
ሰላማዊ ነጋሲ
#BisratNews #BisratFm #BisratRadio #Ethiopia
የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…
Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101
6 570
ጳጉሜን 2፤2018 - ለአዲስ አመት ከ4 ሺህ በላይ የእርድ እንስሳትን እንደሚያቀርብ የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት አስታወቀ
የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የዘንድሮውን የአዲስ አመት በዓል አስመልክቶ በዛሬው እለት ለመገናኛ ብዙሀን ባለሙያዎች መግለጫ ሰጥቷል።
የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ዋና ሥራ አስኪያጅ ኮማንደር አህመድ መሀመድ ለብስራት ሬድዮ እንደገለፁት ተቋሙ በመጪው የአዲስ ዓመት በዓል 4 ሺህ 500 የቁም የእንስሳትን እርድ ለማከናወን ዝግጅት አጠናቋል።
ከእነዚህም መካከል ከ3 ሺህ በላይ በሬዎች እና ከ1 ሺህ 500 በላይ በግና ፍየሎች እርድ እንደሚከናወን ተገልጿል።
የከተማዋ ነዋሪዎችም በግና ፍየልን በ300 ብር፣ እንዲሁም በሬዎችን ደግሞ በ2ሺ 100 ብር የቄራ የእርድ አገልግሎት ማግኘት እንደሚችሉ ነው የተጠቀሰው። ሕብረተሰቡ ጥራታቸውና ደህንነታቸው የተጠበቁ ሥጋዎችን እንዲያገኝ ወደ ቄራዎች ድርጅት መምጣት እንደሚገባው ጥሪ ቀርቧል።
በበዓሉ የአቅርቦት እጥረት እንዳይኖር እና ያልተገባ የዋጋ ጭማሪን ለመከላከል በአዲስ አበባ በሚገኙ የሸማቾች ኅብረት ሥራ ማኅበራት ሥጋ ቤቶች 1 ኪሎ የበሬ ሥጋ 1 ሺህ 200 ብር ሆኖ ለሽያጭ እንደሚቀርብ ተቋሙ ገልጿል።
በቅድስት ደጀኔ
#BisratNews #BisratFm #BisratRadio #Ethiopia
የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…
Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101
6 570
+1
ጳጉሜን 2፤2018 - የአሜሪካ ልዑካን ሩሲያ እና ዩክሬንን ለማስታረቅ ያደረጉትን ውይይት ቀጥለዋል፡፡
የአሜሪካውያን ልዑካን ስቲቭ ዊትኮፍ እና ጃሬድ ኩሽነር በሞስኮ ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላዲሚር ፑቲን ጋር ካደረጉት የሶስት ሰዓታት ውይይት በኋላ ኪየቭ ገብተዋል።
ዋሽንግተን አራት ዓመታትን ያስቆጠረውን የሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት ለማስቆም በምታደርገው ጥረት አካል የሆነው ይህ ጉዞ፣ ልዑካኑ በፖላንድ በኩል በየብስ በመጓዝ እሁድ ዕለት የዩክሬን መዲና መድረሳቸውን ያሳያል።
በሞስኮ የነበራቸው ቆይታ ምንም አይነት ይፋዊ ስምምነት ሳይደረግበት የተጠናቀቀ ቢሆንም፣ የክሬምሊን ባለስልጣናት ውይይቱን «ገንቢ እና ግልጽ» ሲሉ ገልጸውታል።
ፕሬዝዳንት ፑቲን ሩሲያ ግቦቿን እንደምትመታ እና የግጭቱ መሰረታዊ መንስኤዎች መፈታት እንዳለባቸው ለልዑካኑ ማሳሰባቸው ተሰምቷል።
በዚህ የדיፕሎማሲ ጥረት ሳቢያ ሩሲያ እና ዩክሬን ለሶስት ቀናት በየመዲኖቻቸው ላይ ጥቃት ላለመፈጸም ቃል መግባታቸው ተገልጿል። የአሜሪካ ልዑካን ዛሬ እሁድ ከዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዜሌንስኪ ጋር ይገናኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በሚኪያስ ጸሀዬ
#BisratNews #BisratFm #BisratRadio #Ethiopia
የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…
Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101
6 570
ጳጉሜን 2፤2018 - የ አውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የ 2026/27 የውድድር ዘመን ነገ ምሽት መካሄዱን ይጀመራል።
በዚህ ሳምንት በሚደረጉ ሁሉም የሻምፒየንስ ሊግ የመጀመሪያ ጨዋታዎች በኔፓል የተፈጥሮ አደጋ ለደረሰባቸው የህሊና ፀሎት እንደሚደረግላቸው ተነግሯል።
በዚህም መሰረት ከሁሉም ጨዋታዎች በፊት ተጎጂዎች ለአንድ ደቂቃ በዝምታ እንደሚታሰቡ ዩኤፋ በመረጃው ያስታወቀ ሲሆን ''ብቻችሁን አይደላችሁም " የሚል የድጋፍ የፅሁፍ መልዕክት እንደሚተላለፍ ተገልጿል።
እንደመረጃዎች ዘገባ ከሆነ በአስከፊው የጎርፍ አደጋ የበርካታ ሰዎች ህይወት ማለፉ ይታወሳል። የአውሮፓ እግርኳስ ማህበረም ይህንን ታሳቢ በማድረግ ለተጎጂዎች የህሊና ፀሎት እንዲደረግ ማድረጉ እግርኳስ ከሜዳ ባሻገር የሰባውነት እሳቤን ያካተተ ስለመሆኑ ያሳየ ነው ተብሏል።
✍️በአህመዲን ከማል
#BisratNews #BisratFm #BisratRadio #sports
የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…
Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101
6 570
ጳጉሜን 2፤2018 - ፓዮኔር ዳያግኖስቲክ ሴንተር ለተከታታይ አምስት ቀናት የሚቆይ ነፃ የሲቲ ስካን አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡
ፓዮኔር ዳያግኖስቲክ ሴንተር የአዲስ ዓመት በዓልን ምክንያት በማድረግ ከጳጉሜ 1 እስከ 5ቀን 2018 ዓ.ም ለተከታታይ አምስት ቀናት የሚቆይ ነፃ የሲቲ ስካን ምርመራ አገልግሎት ለህብረተሰቡ መስጠት መጀመሩን አስታውቋል፡፡
ፓዮኔር ዳያግኖስቲክ ሴንተር መስራች እና ስራ አስፈጻሚ አቶ ብሩክ ፋቃዱ ለብስራት ሬድዮ እንደተናገሩት ለሁለት አስርተ ዓመታት ያህል ከኢትዮጵያ የጤና ሥርዓት ጋር በመሆን እየሠራ ይገኛል በእነዚህ ዓመታት ሁሉ መሠረታዊ መርሀችን አንድ ነው፤ ትክክለኛ፣ ጥራት ያለውና በወቅቱ የሚሰጥ የምርመራ አገልግሎት በማቅረብ ሐኪሞች ታካሚዎቻቸውን በተሻለ ሁኔታ እንዲያግዙ ማድረግ ብለዋል፡፡
ድርጅቱ የማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ያዘጋጀው ይህ ነፃ የምርመራ እድል በተመረጡ ቅርንጫፎች የሚሰጥ ሲሆን፣ አገልግሎቱን ማግኘት የሚፈልጉ የህብረተሰብ ክፍሎች በ9485 የጥሪ ማዕከል ደውለው መመዝገብ ይችላሉ። የነፃ አገልግሎቱ የምርመራውን ክፍያ ብቻ የሚሸፍን ሲሆን፣ከህክምና ጋር ተያያዥነት ያላቸው የፍጆታ ቁሳቁሶች ወጪዎችን እንደማያካትት ተገልጿል።
ለአስራ ዘጠኝ ዓመታት ያህል በኢትዮጵያ በምስል የተደገፈ የህክምና ምርመራ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየውና የISO ጥራት ማረጋገጫ ያለው ፓዮኔር ዳያግኖስቲክ ሴንተር፤ በአዲስ አበባ በሚገኙ 6 እና በጅጅጋ እንዲሁም በቡታጅራ በሚገኙ 2 ቅርንጫፎቹ ዘመናዊ የምርመራ አገልግሎቶችን እየሰጠ ይገኛል።
ይህ የነጻ አገልግሎት የሚሰጠው ሀሌሉያ ሆስፒታል እና በቤተዛታ ሆስቢታሎች በሚገኙ ቅርንጫፎች መሆኑም ተነግራል፡፡
#BisratNews #BisratFm #BisratRadio #Ethiopia
የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…
Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101
6 570
ጳጉሜን 2፤2018 - ከማረሚያ ቤት ከተፈታ በሦስተኛ ቀኑ የአምቡላንስ ተሽከርካሪ ቁልፍ የሰረቀው ግለሰብ በጽኑ እሥራት ተቀጣ።
ከዚህ ቀደም በተጣለበት የፍርድ ውሳኔ መሠረት በማረሚያ ቤት ቆይታ የእስር ጊዜውን አጠናቆ በወጣ በሦስተኛው ቀን በድጋሚ በስርቆት ወንጀል የተከሰሰው አቶ ያሬድ ገብረሚካኤል የተባለው ግለሰብ መሆኑ የአክሱም ከተማ ፖሊስ አስታውቋል።
የማዕከላዊ ዞን ዓቃቤ ሕግ ቢሮ እንዳስታወቀው ተከሳሹ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀመው፣ ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ.ም በዓድዋ ከተማ በሚገኝ አንድ ሆስፒታል ያለችን እህቱን ለመጠየቅ የመጓጓዣ ገንዘብ እንደሌለው በመግለጽ በዓድዋ ከተማ ቀይ መስቀል ማህበር አምቡላንስ ተሳፍሮ በመጓዝ ላይ በነበረበት ወቅት ነው።
ግለሰቡ በተሳፈረበት አምቡላንስ ውስጥ ተቀምጦ የነበረውን የተሽከርካሪውን ቁልፍ ሰርቆ ከተሰወረ በኋላ በጸጥታ አካላት በተደረገ ክትትል በአክሱም ከተማ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተሰምቷል።የአክሱም ከተማ ፖሊስ ወንጀል ፈፃሚዉን እጅ ከፍንጅ ይዞ በቁጥጥር ስር በማዋሉ አስፈላጊውን ማጣራት በማጠናቀቅ መዝገቡን ለዓቃቤ ሕግ አቅርቧል።
ጉዳዩን ሲከታተል የቆየው የአክሱም ከተማ ፍርድ ቤትም ነሐሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት የቀረበበትን የሰነድ እና የሰው ማስረጃ መርምሮ ግለሰቡ በተከሰሰበት የስርቆት ወንጀል ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ በ6 ዓመት ከ6 ወር ጽኑ እሥራት እንዲቀጣ ወስኖበታል።
በሰብል አበበ
#BisratNews #BisratFm #BisratRadio #Ethiopia
የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…
Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101
6 570
ጳጉሜን 2፤2018 - አዲዳስ ከእስራኤል ወታደር ጋር ባካሄደው የማስታወቂያ ዘመቻ ተቃውሞ ቀረበበት።
የስፖርት ትጥቅ አምራቹ አዲዳስ ከቀድሞ የእስራኤል ወታደር ጋር ያካሄደውን የማስታወቂያ ዘመቻ ተከተሎ ከደንበኞች ለቀረበበት ተቃውሞ እና የሰፊ ማዕቀብ ጥሪዎች ተጋልጧል።
ኩባንያው "ሲንግል ሹ ሰርቪስ" የተሰኘውን የነጠላ ጫማ አገልግሎቱን ለማስተዋወቅ በጋዛ ውጊያ ወቅት እግሩን ያጣውን የቀድሞ የእስራኤል ወታደር ሻሌቭ ቢቶንን ማሳተፉ ነው ተቃውሞውን ያስነሳው።
የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች እና የሶሻል ሚዲያ ተጠቃሚዎች ኩባንያው የእስራኤልን ጦር ይደግፋል ሲሉ የከሰሱ ሲሆን፣ ታዋቂውን ተዋናይ ጃቪየር ባርዴምን ጨምሮ በርካቶች በምርቱ ላይ ማዕቀብ እንዲጣል ጥሪ አቅርበዋል።ተቃዋሚዎቹ በጋዛ በሺዎች የሚቆጠሩ ፍልስጤማውያን እና ህፃናት ለከባድ አካል ጉዳት በተዳረጉበት አሰቃቂ ሁኔታ ውስጥ፣ ኩባንያው የቀድሞ የእስራኤል ወታደርን ለዘመቻው መምረጡ ተገቢ አይደለም ብለዋል።
አዲዳስ በ23 የአውሮፓ ሀገራት ያስተዋወቀው ይህ አገልግሎት ለአካል ጉዳተኞች የሚሰጥ ቢሆንም፣ አብዛኛው ተቃውሞ ያተኮረው ኩባንያው በወሰደው ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ ምርጫ ላይ መሆኑ ተገልጿል።
ሰላማዊ ነጋሲ
#BisratNews #BisratFm #BisratRadio #Ethiopia
የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…
Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101
6 570
ጳጉሜን 2፤2018 - ሃኪም ዚያች ወደ ቦታፎጎ ለማቅናት ተስማማ!
የቀድሞ የቼልሲው የመስመር አጥቂ ወደ ብራዚሉ ክለብ ቦታፎጎ ለማቅናት በቃል ደረጃ መስማማቱ ተገልጿል። ሞሮኳዊው ኢንተርናሽናል ከብራዚሉ ክለብ ጋር የሁለት ዓመት ኮንትራት ለመፈረም መስማማቱ የተገለፀ ሲሆን በቀጣይ ፊርሚያውን እንደሚያሮርም ለክለቡ ቅርብ የሆኑ መረጃዎች ዘግበዋል። 33 ዓመቱ ላይ የደረሰው ዚያች ቦታፎጎን በነፃ ዝውውር ይቀላቀላል ተብሎ ይጠበቃል።
✍️በአህመዲን ከማል
#BisratNews #BisratFm #BisratRadio #sports
የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…
Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101
6 570
ጳጉሜን 2፤2018 - ውድ የ-#መሴ_ሪዞርት አድማጮች አዲሱን የ facebook ገጻችን like, share እና Comment በማድረግ ሃሳብ አስተያየታችሁን አካፍሉን።
የመወያያ ነጥቦች፦
👉በህመማቹ ጊዜ ከጎናችሁ የቆመው ማነው?
👉ሰርግና ሞት አንድ ነው :ከሰርጌ በፊት በፍፁም ያልነው ነገር ምነድን ነው?
👉ውሳኔዎቻችሁ ምን አስከትለባችሁ?
በመላው #ዓለም በዩቲዩብ ገፃችን ይጠብቁን። 👇👇👇
https://www.youtube.com/@Bisrat_Fm_101.1
#BisratNews #BisratFm #BisratRadio #Messe_resort #መሴ_ሪዞርት
የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…
Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101fm
TikTok: https://www.tiktok.com/@bisrat.fm
6 570
ጳጉሜን 2፤2018 - ለምርጫዉ እንደሚወዳደሩ ተሰምቷል
የፊፋዉ ፕሬዝደንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ በቀጣይ በሚደረገዉ ምርጫ እንደሚወዳደሩ አሳዉቀዋል። ተቃውሞ የበረታባቸው ኢንፋንቲኖ ዳግም ለፕሬዝዳንትነት እንደሚወዳደሩ መግለጻቸዉን ተከትሎ ብዙዎች ቁጣቸዉን እየገለጹ ይገኛል ተብሏል።
ጂያኒ ኢንፋንቲኖ አለም ዋንጫውን የተወሰነ ድርሻ ወደ ግል ለማዞር ባደረጉት ሙከራ ምክንያት ከፍተኛ ጫና ዉስጥ ይገኛሉ ነገር ግን ለሚቀጥለዉ ምርጫ ዝግጁ መሆናቸዉን አረጋግጠዋል የአዉሮፓ እግር ኳስ ማህበር ፕሬዝደንቱን አሌክሳንደር ሴፈሪንን ጨምሮ በርካታ የቀድሞ እግር ኳስ ተጫዋቾች ኢንፋንቲኖ ስልጣናቸዉን እንዲለቁ ለወራት ጥያቄ ሲያቀርቡ ቢቆዮም ጣሊያናዊዉ ሰዉ በድጋሚ እወዳደራለሁ ማለታቸዉ ብዙዎችን አስገርሟል።
የፊፋዉ ቃል አቀባይ እንደገለጹት "ኢንፋንቲኖ ከ 2016 ጀምሮ ፊፋን እየመሩ ነዉ አሁንም የተቀየረ ነገር የለም ፕሬዝደንቱ ሀሳባቸዉን አልቀየሩም ለምርጫዉ ዝግጁ መሆናቸዉን ልነግራችሁ እፈልጋለሁ በ 2027ቱ ምርጫ ኢንፋንቲኖ ተወዳዳሪ ናቸዉ" ሲሉ ሀሳባቸዉን ገልጸዋል።
በ-ሙሉቀን ሙጨ ⚽️
#BisratNews #BisratFm #BisratRadio #sports
የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…
Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101
6 570
ጳጉሜን 2፤2018 - “የጀመርነዉ አዲስ ምእራፍ አለ"
የቼልሲዉ አሰልጣኝ ዣቪ አሎንሶ ከትናትናዉ ጨዋታ በኋላ ሀሳቡን አጋርቷል:-
"ጨዋታው የተለያዩ የጨዋታ ደረጃዎች ነበሩት በጥሩ ሁኔታ ጀምረን ነበር ከዚያም ለ15 ደቂቃ ያህል እነሱ በጣም ጫና ፈጠሩብን ወደ ኋላ ተጠግተን ተከላከልን እና ኳሱን ለማግኘት ተቸገርን 15 ደቂቃዎቹ ከባድ ሆነዉብናል ጨዋታው በጣም ተቀራራቢና ከባድ እንደነበር ገልጽ ነዉ"
"ለእነሱ ምንም ጥቅም እንዳንሰጥ ከፍተኛ ትኩረት ያስፈልገን ነበር በሁለተኛው ጎል ላይ ግን የተሻለ ማድረግ እንችል ነበር ይህ የጨዋታው አካል ነው፣ መቀበል አለብን እነሱ ከፍተኛ ደረጃ ያለው ቡድን ናቸዉ እስከመጨረሻው ተጋድለን ቀጠልን ቡድኑ እስከመጨረሻው ለመታገል ትልቅ ፍላጎት አሳይቷል"
"ለማሸነፍ እና በተቻለ መጠን ጥሩ ሁኔታ ለመወዳደር እፈልጋለሁ። ዛሬ ከመጀመሪያው ደቂቃ ጀምሮ ወደ ኋላ ተጠግተን ለመከላከል አልፈለግንም በፕሬሲንግ ውስጥ እኛ ተዋናዮች መሆን ፈልገን ነበር ብዙ ትክክለኛ ነገሮችን አድርገናል ነገር ግን ማሻሻልና ከስህተቶቻችን መማር ያለብን ነገሮችም አሉ"
"ከቼልሲ ጋር የጀመርነው አዲስ ምዕራፍ አለ አሁን ገና ሶስተኛ ጨዋታችን ነው ማሸነፍ ፈልገን ነበር በእውነቱ ብዙም አልራቅንም መፎከካር ችለናል ካይሴዶን በተመለከተ የረጅም ጊዜ ጉዳት አይደለም ግን ስጋቱን መገምገም አለብን። ለቀጣይ ጨዋታ ራሳችንን እናዘጋጅ ሽንፈቱ ግን ሊያመን ይገባል" ሲል አሎንሶ ሀሳቡን አጋርቷል።
በ- ሙሉቀን ሙጨ ⚽️
#BisratNews #BisratFm #BisratRadio #sports
የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…
Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101
6 570
ጳጉሜን 2፤2018 - “ጨዋታዉ ለተመልካቾች አስደናቂ ነበር"
የአርሰናሉ አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ቼልሲን 2-1 ካሸነፉ በኋላ አስተያየታቸዉን ሰተዋል:-
"በዉጤቱ በጣም ደስተኛ ነኝ ካይ ሀቨትዝና ማርቲን ኦዴጋርድ ጨዋታዉን እንድናሸንፍ አግዘዉናል አጀማመራችን ጥሩ አልነበረም ጎል ተቆጥሮብን ነበር ግን በቶሎ ምላሽ ሰተናል ከመጀመሪያዉ ደቂቃ ጨምሮ እስከ መጨረሻዉ ድረስ ጨዋታዉ ለተመልካቾች አስደናቂ ነበር የምናጠቃበት መንገድ ጥሩ ነዉ ደጋፊዎችም ከእኛጋ ነበሩ ብዙ የጎል እድሎችን ፈጥረናል"
አሁንም ማሻሻል ያሉብን ነገሮች አሉ እያሸነፍን መቀጠል እንችላለን ቼልሲዎች እዉነተኛ ተፎካካሪ ነበሩ ጥንካሪያቸዉንም አሳይተዋል። ኦዴጋርድ በእግር ኳስ እየተደሰተ ነዉ የግል ህይወቱ የተረጋጋ ነዉ ዛሬ ድንቅ ነበር ጨዋታዉን መቀየር ችለናል ፕሪሚየር ሊጉ በጣም ከባድ ይሆናል ም/ም በሊጉ ጠንካራ ቡድኖች አሉ በየሳምንቱ እንደዚህ አይነት ከባድ ፈተናዎች ያጋጥሙናል ለሁሉም ነገር ዝግጁ መሆን አለብን የቡድኔ እንቅስቃሴ የተለየ ነበር ሞስኬራ የጡንቻ ችግር ነው የገጠመው በቀጣይ ወደ ጨዋታ እንዲመለስ እገዛን ይፈልጋል"
"በተጫዋቾቼ ብቃት ኩራት ተሰምቶኛል አሁንም ጠንካራ መሆን አለብን በኤሚሬትስ ደጋፊዎቹ ሲደሰቱ ማየት ተልቅ ስሜት አለዉ ዞሊስ የተለየ ተጫዋች ነዉ የሚሰራዉን ያዉቃል እዉነት ለመናገር ጥሩ ዝዉዉር አደርገናል ለእያንዳንዱ ጨዋታ ትኩረት መስጠት ይጠበቅብናል" ሲል ሚኬል አርቴታ ገልጿል።
በ- መሉቀን ሙጨ ⚽️
#BisratNews #BisratFm #BisratRadio #sports
የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…
Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101
6 570
ጳጉሜን 1፤2018 - በሸኖ ከተማ አቅራቢያ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ6 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ 18 ሰዎች ቆሰለዋል።
በሸኖ ከተማ አስተዳደር ኦንቱ ቀበሌ፣ አዳ ሀሮ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በደረሰ ከባድ የትራፊክ አደጋ የስድስት ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ፣ በ18 ሰዎች ላይ ደግሞ የአካል ጉዳት መድረሱን የአካባቢው የትራፊክ ደህንነት አስታውቋል።
የሸኖ ከተማ አስተዳደር የትራፊክ ደህንነት ማረጋገጫ ክፍል ኃላፊ ረዳት ኢንስፔክተር አዲሱ መርጋ እንደገለጹት አደጋው የደረሰው የሰሌዳ ቁጥሩ 3-A04933 አ.አ የሆነ ኤፍኤም የህዝብ ማጓጓዣ ተሽከርካሪ ባስ ከአዲስ አበባ ወደ ደሴ ሲጓዝ ከሚፈቀደው የፍጥነት ወሰን በላይ በማሽከርከሩ ምክንያት የተፈጠረ አደጋ ነው ብለዋል።
በአደጋው ሕይወታቸው ካለፉት 6 ሰዎች መካከል 2 ወንዶች እና 4 ሴቶች እንደሚገኙበት ታውቋል። በተጨማሪም ጉዳት ከደረሰባቸው 18 ተጓዦች 12 ወንዶች እና 6 ሴቶች ውስጥ 13ቱ ከባድ እና መካከለኛ አደጋ የገጠማቸው ሲሆን፣ አምስቱ ደግሞ ቀላል ጉዳት አጋጥሟቸዋል።
የሟቾች አስከሬን በህብረተሰቡና በትራፊክ ፖሊስ አባላት ትብብር ወደ ሸኖ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የተወሰደ ሲሆን፣ ተጎጂዎችም በዚሁ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል።
ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው ተሳፋሪዎች ለተሻለ ህክምና ወደ ሌሎች ከፍተኛ ሆስፒታሎች የተላኩ ሲሆን፣ አነስተኛ ጉዳት የደረሰባቸው ደግሞ ጉዟቸውን ወደ ደብረ ብርሃን እና አዲስ አበባ መቀጠላቸውን ተገልፅዋል።
በአብዛኛ አገር አቅዋራጭ ከፍተኛ አውቶብሶች የሰውን ሕይወት ጭነው በግዴለሽነት የሚያደርሱት አደጋ በመበራከቱ አሽከርካሪዎች ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ረዳት ኢንስፔክተር አዲሱ መርጋ ጨምረው ገልፀዋል።
#BisratNews #BisratFm #BisratRadio #Ethiopia
የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…
Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101
6 570
ጳጉሜን 1፤2018 - 🔴🆚🔵 መድፈኞቹ ከሰማያዊዎቹ ተናፋቂው የለንደን ደርቢ ትንቅንቅ!
የሰሜን ለንደኑ አርሰናል እና የምዕራብ ለንደኖቹ ቼልሲዎች ፉክክር እንደ ዩሮፒያኖቹ አቆጣጠር ከ1907 ጀምሮ የሰነበተ ነው።
ሁለቱ ክለቦች ሲገናኙ መታዘብ የምንችለው የ90 ደቂቃ እግር ኳስ ብቻ ሳይሆን ይህ ከመቶ ዓመታት በላይ የተሻገረ የለንደን ባለቤትነትን ለመቀራመት የሚደረግ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ ለሶስት ነጥቦች ሆነ መረሀ ግብር ለማሟያ የሚዘጋጅ አይደለም።
የአርሰናል እና የቼልሲ የመጀመሪያ የሊግ ጨዋታ የተካሄደው እ.ኤ.አ. ቅዳሜ,ኖቨምበር, 9, 1907 ነበር። በወቅቱ መድፈኞቹ አሁን በምናውቀው ስማቸው እንኳ አይጠሩም ነበር። በ1913 በሰሜን ለንደን ከመክተማቸው አስቀድሞ በእንግሊዟ መናገሻ ደቡብ ምስራቅ አቅጣጫ በምትገኘው ዎልዊች በተሰኘች ቦታ ላይ ሰፍረው የነበረ ሲሆን መጠሪያቸውም ዎልዊች አርሰናል ይባል ነበር።
በዚያ ታሪካዊ የመጀመሪያ ጦርነት ቼልሲ 2–1 በሆነ ውጤት ድል መንሳት ቻለ፤ ሁለቱንም የቼልሲ ጎሎች ጆርጅ ሂልስደን አስቆጥሮ የዚህን ረጅም የታሪክ ጅማሮ 55,000 የሚጠጉ ደጋፊዎች ፊት በድል አበሰረ።
ሁለቱ ባላንጣዎች 215 ጊዜ ሲገናኙ ታሪክ ለመድፈኞቹ ታደላለች። አርሰናሎች 87 ጊዜ ድልን ሲጎናፀፉ፣ ቼልሲዎች በ66 ይከተላሉ። ቀሪውን 62 ጨዋታ በመከባበር በአቻ ውጤት ቋጭተዋል።
የደርቢውም ዋና ተዋናይ አይቮሪኮስታዊው የቼልሲ ፊት አውራሪ ዲድየር ድሮግባ ይሰኛል። በዚህ ግለት በማይለየው ድግስ ላይ 13 ጊዜ ኳስን ከመረብ ጋር ማዋሀድም ችሏል። ይህም የደርቢው የምንጊዜም ከፍተኛ ጎል አስቆጣሪ ያደርገዋል።
ታሪክን እንዲ በትንሹ ከዳሰስን ወደ ተጠባቂው የሰንበት አመሻሹ ጨዋታ እንጓዝ። በኤምሬትስ የሚደረገው ፍልሜያ ከቀድሞ ሳይቀዘቅዝ እንደተዋበ ሁለቱን የከተማ ተቀናቃኞች ሊያገናኝ ከደጃችን ቆሟል።
የአርሰናል ተልዕኮ ግልጽ ነው። ያሳለፋትን ጣፋጭ የውድድር ዓመት ዘንድሮም ማስቀጠል። በተስፋ ለ2 አስርት አመታት ሲጠብቁት የነበረውን ክብር ዳግም ለመጎናፀፍ አርቴታና ሰራዊቱ መድፋቸውን በቀሪው 19ኙ ክለቦች ላይ ከወዲው ቀስረዋል።
በዝውውር ገበያው ወደ ቡድናቸው የቀላቀሏቸው ተጫዋቾች ከወዲሁ አመርቂ እንቅስቃሴያቸውን ማሳየታቸው ለእሁዱም ጨዋታ እንዲጠበቁ ያደርጋቸዋል።
በሊጉ በተጫዋችነት ለመርሲ ሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል ተጫውቶ ያለፈው ዣቢ አሎንሶ በአሰልጣኝነት እንግዳ ወዳሎነበት መድረክ ሲመለስ መንገዶች አልጋ በአልጋ የሆኑለት ይመስላሉ። የመክፈቻ ጨዋታዎቹን ማሸነፍ የቻለው ስፔናዊ ከበስተ ጀርባ አንዳች ችግር ቢጤ መሸፈን እንደሚኖርበት በርካቶች ያምናሉ።
የክረምቱ ፈራሚዎችም ከመድፈኞቹ ጋር በሚኖራቸው ጨዋታ ስማቸውን በወርቃማ ቀለም ለማፃፍ የማይፈነቅሉት ድንጋይ፣ የማይወጡት ተራራ አይኖርም።
እኛስ በእሁዱ የለንደን ደሪቢ ምን እንጠብቅ?
የመድፈኞቹን የተኩስ ጬኸት ወይስ የሰማያዊዎቹን የድል ዝማሬ?
✍️ በአቤኔዘር አዳነ
#BisratNews #BisratFm #BisratRadio #sports
የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…
Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101
6 570
ጳጉሜን 1፤2018 - 🔵🆚🔴የመርሲሳይዱ ኤቨርተን ከቀያይ ሰይጣኖቹ በሂል ዲኪንሰን የሚያደርጉት ትንቅንቅ!
የሁለቱ ክለቦች ምስረታ እንደ ዩሮፒያኖቹ አቆጣጠር 1878 ላይ የነበረ ሲሆን፣ የዛሬው ጨዋታ በርካታ አስደሳች ታሪኮችን ይዞ መጥቷል። የኤቨርተን አሰልጣኝ ዴቪድ ሞይስ ከማንቺስተር ዩናይትድ ጋር ሲገናኝ ሁሌም ትኩረት የሚስብ ነው። በተጨማሪም ብሩኖ ፈርናንዴዝ ከኤቨርተን ጋር ባደረጋቸው ጨዋታዎች 11 የጎል ተሳትፎዎች አሉት። ይህም ከዴቪድ ቤካም እና ከራያን ጊግስ ጋር እኩል በመሆን ይመራል።
ይህ በሁለቱ ክለቦች መካከል የሚደረገው 214ኛው ጨዋታ ሲሆን፣ ዩናይትድ በፕሪሚየር ሊጉ ታሪክ ከሌላ ክለብ በበለጠ ኤቨርተንን አሸንፏል።
ዌይን ሩኒ ሁለቱንም ክለቦች በትልቅ መንገድ ያገናኛል። በኤቨርተን ተጫዋችነቱን ከጀመረ በኋላ ወደ ዩናይትድ በመሄድ የክለቡ የምንጊዜም ከፍተኛ ጎል አስቆጣሪ መሆን ቻለ።
ዴቪድ ሞይስም ሁለቱንም ክለቦች ያሰለጠነ አሰልጣኝ ነው። ሰር አሌክስ ፈርጉሰንም በኤቨርተን ላይ አስደናቂ የድል መዝገብ ነበራቸው።
ታሪክን እንዲህ በትንሹ ካነሳን አይቀር ሂል ዲኪንሰን ወደተዘጋጀው ድግስ እንለፍ።
🔰 ማንቺስተር ዩናይትድ በአሰልጣኙ ማይክል ካሪክ እየተመራ በሊጉ የመክፈቻ ጨዋታውን በኤምኬኤም ስቴድየም በሃል ሲቲ ሽንፈትን ካስተናገደ በኃላ ኤፕስዊችን በአንበላቸው ብሩኖ ፈርናንዴዝ ሶስት ጎሎች በመታገዝ መርታት ችሏል።
ዛሬም በሚደረገው ጨዋታ ፖርቹጋላዊው በጥሩ አቋሙ ላይ መገኘቱ ለቀያይ ሰይጣኖቹ የደስታ ዜና ሆኗል።
ከፊት መስመር ደግሞ ቤንጃሚን ሼሽኮ የዩናይትድን የጎል ችግር ለመፍታት ትልቅ ተስፋ የተጣለበት ተጫዋች ነው። ማቲያስ ኩኛ፣ ማርከስ ራሽፎርድ እና ብራየን ምቡሞም የጥቃቱን አቅም ሊያሳድጉ የሚችሉ የፊት መስመር ተጠባቂ ተጫዋቾች ናቸው።
🔵 ኤቨርተን በበኩሉ በሊጉ ጅማሬው ፓላስን በማሸነፍ እና ከቦርንማውዝ አቻ በመለያየት በሊጉ 10ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል።
የዛሬውን መረሃግብር ማን በአሸናፊነት ያጠናቅቅ ይሆን?
የመርሲ ሳይዱ ኤቨርተን ወይስ የላንክሻየሩ ዩናይትድ?
መልሱን አብረን የምናይ ይሆናል።
✍️ በአቤኔዘር አዳነ
#BisratNews #BisratFm #BisratRadio #sports
የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…
Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101
6 570
+2
ጳጉሜን 1፤2018 - ካቮድ ኮመርሻል ለደንበኞቹ ዘመናዊ የኤሌክትሪክ መኪኖችንና የፈርኒቸር ምርቶችን የሽልማት ዕጣ አወጣ
ካቮድ ኮመርሻል ሪል እስቴት ባለፉት ዘጠኝ ወራት ሲተገብር የቆየውን የደንበኞች ማበረታቻ የሽልማት መርሃ ግብር የማጠቃለያ ዕጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓት አከናውኗል።
በዚህ ወቅት የካቮድ ኮመርሻል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ የምወድህ ታደሰ እንደገለፁት ፣ የእጣ ማዉጣት መርሀ-ግብሩ ፍትሃዊ፣ ታማኝ እና ግልጽ በሆነ መልኩ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ጋር በመተባበር ተከናውኗል።
በገዟቸው የሱቅ መለያ ኮድ (Shop Code) እና በሳይቱ ኮድ አማካኝነት ደንበኞች በዕጣው እንዲካተቱ ተደርጓል ያሉት ዋና ስራ አስፈፃሚው ካቮድ ኮሜርሻል የንግድ ቦታዎችን ከመገንባት ባለፈ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ በጎ ተፅዕኖ የመፍጠር አላማ እንዳለው አመልክተዋል።
ካቮድ ኮመርሺያል የወደፊት የንግድ እይታውን የሚያንጸባርቅ “አራዳው ነጋዴ” የተሰኘ አዲስ የማርኬቲንግ እንቅስቃሴ ይፋ ያደረገ ሲሆን ይህም የዛሬን ውሳኔ ከነገው ስኬት ጋር በማገናዘብ ረጅም ርቀት ማየት የሚችል፣ የንግድ ቦታዎችን በጥበብ የሚመርጥ እና የወደፊት ተስፋውን የሚገነባ ብልህ ነጋዴን የሚወክል መሆኑ ተገልጿል።
በመርሃ ግብሩ ይፋ የተደረጉት የ1ኛ እና 2ኛ ዕጣ ሽልማቶች ዘመናዊ የኤሌክትሪክ መኪኖች ናቸው።
1ሚሊዮን ብር የሚያወጡ የኦቪድ ፈርኒቸር ምርቶች ደግሞ በሶስተኛ እጣ የተካተቱ የሽልማት አይነቶች መሆናቸው በመርሀግብሩ ላይ ተገልጿል።
ከ4ኛ እስከ 10ኛ ዕጣ ያሉ የሽልማት አይነቶች ደግሞ የተለያየ ዋጋ ያላቸው የፈርኒቸር ምርቶችን ያካትታሉ።
ቅድስት ደጀኔ
#BisratNews #BisratFm #BisratRadio #Ethiopia
የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…
Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101
6 570
ጳጉሜን 1፤2018 - ውድ የብስራት ሬዲዮ አድማጮች የ facebook ገጻችን like, share እና Comment በማድረግ ሃሳብ አስተያየታችሁን አካፍሉን።
በ-#ጣልያን_ሴሪ_ኤ የ-#ዩቬንቱስ እና #ኤሲሚላን-ን ጨዋታ #ቪቫ_ስፖርት ይዘውላችሁ ይቀርባሉ።
ማነኛውንም ሃሳብ አስተያየት አድርሱን። መልሰን ወደ እናንተ አናደርሳለን።
ምሽት ከ3:00-6:00 ሰዓት ይጠብቁን!
የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…
Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=61577130725400
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101fm
TikTok: https://www.tiktok.com/@bisrat.fm
