6 918
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
6 918
ያሳዝናል‼
========
✍ ጋዛን ከዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ጋር ያገናኝ የነበረው ብቸኛው የጀዋል ካምፓኒ ዓለም አቀፉ የኢንተርኔት ገመድ በጽዮናዊያኑ ቦምብ መመታቱን ተከትሎ ጋዛዊያን ድምፃቸው ታፍኖ ያለ ማቋረጥ ከ3 ሰዓታት በላይ የቆዬ እጅግ ዘግናኝ የቦምብ ጥቃት እየዘነበባቸው ነው።
በተጨማሪም በባህርም፣ በአየርም፣ በምድርም እሳት እየዘነበባቸው ነው።
ጠብቃ ጠብቃ እስራኤል ከሰሞኑ የከፋውን ጭፍጨፋ ዛሬ በጨለማ ጀምራለች።
ከ40 ሺህ በላይ ታማሚዎች የሚገኙበትን ዋነኛውን አልሺፋ ሆስፒታልንም አጋይታለች።
አንድም ፈለስጢናዊ በህይዎት ማየት አትፈልግም።
አምቡላንሶች እንኳ ወደ ሟቾችና ቁስለኞች ዘንድ በማምራት ማንሳት አልቻሉም።
እስራኤል ወንጀሏና የምትፈጽመው ዘግናኝ ጥቃት ተቀርፆ በሚዲያ እንዳይወጣባት ድምጿን አጥፍታ እየጨረሰች ነው።
በጘ-ዝ'ዛ ታሪክ ይቀር የማይለው የጦር ወንጀልና የዘር ማፅዳት ጭፍጨፈሰ እየተፈጸመ፤ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ አሁንም በዝምታ ላይ ነው።
በጣም ነው የሚያሳዝነው!
6 918
----
ኢራቅ ሰሞኑን ኢራቅ የዓለምን ሕዝብ ስታስደንቅ ነው የዋለችው፡፡ የዓለም ሚዲያዎች እስከ አሁን ስለእርሷ እያወሩ ነው፡፡ የዚህን መንስኤ ለማወቅ ካሻችሁ ከዚህ በታች ያለውን ፎቶግራፍ ማየት አለባችሁ፡፡
----
ፎቶው በቅርቡ በተጠናቀቀው የቀጠር የዓለም ዋንጫ ወቅት የተነሳ ከመሰላችሁ ተሳስታችኋል፡፡ ይህ ፎቶ የተነሳው ዐርብ ዕለት ነው፡፡ ቦታው ደግሞ የኢራቅ ሶስተኛዋ ትልቅ ከተማ የሆነችው በስራ ናት፡፡
አዎን! ኢራቅ 25ኛው የባሕረ ሰላጤ ሀገራት የእግር ኳስ ዋንጫ ውድድር አዘጋጅ ናት፡፡ ዝግጅቱ ባለፈው ዐርብ የኢራቅ መሪዎች፣ የባሕረ-ሰላጤው ሀገራት ከፍተኛ የመንግሥት ተወካዮች፣ ስምንቱን የባሕረ-ሰላጤ ሀገራት የወከሉ ብዙ ስፖርተኞች እና ብዙ ሺህ ሕዝብ በተገኘበት በበስራ ከተማ ትልቁ ስቴዲየም እጅግ በደመቀ ሁኔታ ተከፍቷል፡፡ ስፖርተኞቹ በሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት ውድድራቸውን ያካሄዳሉ፡፡
-----
ለሃያ ዓመታት በአሜሪካ አውዳሚ መሣሪያዎች በተከፈተባት ወረራ፣ እርሱን ተከትሎ በተፈጠረው ጦርነት፣ በሽብር፣ በፍንዳታ፣ በአንጃዎች የእርስ በእርስ ውጊያ፣ በእልቂት፣ በሕዝብ መፈናቀል እና በISIS ጽንፈኞች ትርምስ ስትናጥ የከረመችው ኢራቅ ከችግሯ ሁላ አገግማ ይህንን ትልቅ ውድድር ለማዘጋጀት መብቃቷ በጣም አስደሳች ነገር ነው፡፡ ይህቺ ታላቅና ጥንታዊት ሀገር ለወደፊቱም አሁን በጀመረችው የተሐድሶ ጉዞ ተራምዳ እንደ ጥንቷ ባቢሎኒያ እና እንደ አባሲድ ኸሊፎች መቀመጫዋ “በግዳድ አል-ሸምሲያ” እንድታንጸባርቅ መልካሙን ሁሉ እንመኝላታለን፡፡
------
አፈንዲ ሙተቂ
6 918
የሕዳሴ ግድብ 3ኛው ዙር ውኃ ሙሌት በስኬት ተጠናቅቋል፡፡
ዓባይ ላይ ግድብ ለመገንባት ስንነሳ ወንዙን የራሳችን ብቻ የማድረግ ፍላጎት አድሮብን እንዳልሆነ ከመጀመሪያውም ስንናገር ነበር፡፡ እኛ ማግኘት የሚገባንን ጥቅም እናግኝ ስንል ልክ እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ ሌሎቹ የዓባይ ሥጦታዎች - ሱዳንና ግብጽ ከወንዙ በየድርሻቸው እንደሚጠቀሙበት እያሰብን ጭምር ነው፡፡ እውነትን ይዘን ተነስተን፣ በገዛ ሐቃችን ገንብተን፣ በቃላችን መሠረት፣ ማንም ላይ ጉዳት ሳናደርስ እነሆ 3ኛውን ዙር ውኃ ሙሌት በታሰበው ጊዜ ማጠናቀቅ ስለቻልን የዓባይ ልጆች ሁሉ እንኳን ደስ ያለን!!
የዓባይ ወንዝ ለሺህ ዘመናት ሦስቱን ሀገራት አስተሳስሮ እንዳኖራቸው ሁሉ÷ በእሱ ላይ የተገነባው ግድብ ከሌሎች ጎረቤቶቻችንም ጋር በትብብር እንድንኖር ያስችለናል፡፡ ግድቡ ደለል የሚያስቀር በመሆኑ በጎርፍ ምክንያት በታችኛው ተፋሰስ ሀገራት የሚወድመውን ሀብትና የሚጠፋውን የሰው ሕይወት ቁጥር እንደሚቀንስ ይታወቃል፡፡ ከዚህ ባለፈ ግድቡ የሚያመነጨውን ኤሌክትሪክ - በኃይል ምንጭነት፣ በውኃው አናት ላይ የሚነጠፈውን ውብ ገጽታ -በመዝናኛነት፣ በውኃው ጉያ የሚሰግሩትን አሳዎች - በምግብነት ከጎረቤቶቻችንና ከዓለም ጋር እንጋራዋለን፡፡
6 918
የማክሮ ኢኮኖሚ ኮሚቴ ስብሰባችንን አካሂደናል። ባለፈው ዓመት የሚያበረታታ የወጪ ንግድ አፈጻጸም፣ ቀጥተኛ የውጭ ሙዓለ ነዋይ ፍሰት መጨመር ታይቷል። ባለፉት ሁለት ወራት የዋጋ ግሽበት መቀነስ፣ ከፍተኛ የአረንጓዴ ዐሻራ ክንውን፣ የበጎ ፈቃደኝነት ተግባራት፣ የሬሚታንስ ጭማሪ እና በቴክኖሎጂ የታገዘ የሥራ ክንውን የተመዘገቡበት እንደ ሆነ አረጋግጠናል። በዚህ ዓመት የተገኙ ስኬቶችን አጠናክሮ መቀጠል በእጅጉ አስፈላጊ ነው።
Our macroeconomic committee meeting today confirmed remarkable export performance this past year; better FDI flows; decreased inflation past two month;
optimal green legacy, volunteer activities, remittance and automation performance. It is key we build and expand on this year’s achievements.
6 918
Ethiopia 🇪🇹 has just completed the 3rd round filling of the Grand Ethiopia Renaissance ( GERD) Dam successfully.
The greatest dam in Africa is near completion (reached over 85%).
The water is now overflowing and moving downward to Sudan 🇸🇩 and Egypt 🇪🇬.
Sudanese & Egypt brothers and sisters should take care of floodings.
#GERD #Africa
6 918
«እናንተ የምትጣሉት ለኮብራ መኪና ለወንበር እንጂ ለዲን አይደለም። እምቢ ካላችሁ ይሄንኑ ቃል ለህዝበ ሙስሊሙ እናገርባችኋለሁ!
ወጣቱን አታባሉት። አብዛሃኞቻችሁ ዱኒያ ላይ የመኖሪያ ጊዚያችሁን ጨርሳችኋል።ታሪክ አበላሽታችሁ ወደ አኺራህ አትሂዱ!»
6 918
ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ዋና ፕሬዝዳንት ተደርገው ተሹመዋል። ከስራቸውም ሁለት ምክትሎች ተመርጠዋል።
6 918
በሀገራችን የሕክምና አገልግሎት ለማሳደግ እየተደረገ ያለው ጥረት ለውጥ እያሳየ ነው። የአዲስ አበባ ከተማ የግሉ ዘርፍ ሙአለ ንዋይ እንዲያፈስስ በማስቻል አዲስ የኩላሊት እጥበት ሕክምና ማዕከልን እውን ማድረጉ በጤና አጠባበቅ ሥርዓታችን ላይ የሚታዩትን በርካታ ስብራቶችን የሚጠግን እመርታ ነው። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በሞያቸው ሀገራቸውን ለማገልገል ያደረጉትን ጥረት እያደነቅኩ፣ ሌሎችም ተመሳሳይ ጥረቶችን እንዲያበዙ አበረታታለሁ።
Efforts being undertaken to enhance medical care within our nation are encouraging. The Addis Ababa City’s demonstration of a new dialysis facility through drawing private sector investments is key in addressing the many breakages in our health care system. While appreciating Ethiopians living abroad that have mobilised professionally in service of their country, I encourage many others to multiply such endeavours.
6 918
Repost from Ahmedin Jebel - አሕመዲን ጀበል
«አላህ ሽቶብኝ ነው እንጂ እኔ ስልጣን አልፈልግም።»
❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄
ሙፍቲ ሐጅ ዑመር እድሪስ አልፎ አልፎ ሚዲያ ባለበት ሕዝባዊ ስብሰባዎችም ሆነ መግለጫ ላይ ከሚያነሷቸው ነጥቦች አንዱ ስልጣንና ዱንያዊ ጥቅማ ጥቅምን እንደማይፈልጉ የሚገልጹባቸው ቃላቶች ይገኙባቸዋል። የዱንያዊው ጥቅም ጉዳይ ለጊዜው በይደር ይቆየኝና ስልጣን እንደማይፈልጉ ከሚገልጹባቸው መካከል «አላህ ሽቶብኝ ነው እንጂ እኔ ስልጣን አልፈልግም» ከሚለው ጋር በተያያዘ ጥቂት ልበል።
በቅርበት የማያውቃቸው ሰው "ታዲያ ስልጣን የማይፈልጉ ከሆነ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት (መጅሊስ) በይፋ ከተመሠረተበት እስከ ዛሬ (ከመጋቢት 4 ቀን 1968 እስከ 2014 ግንቦት) መንግስታት ሲቀያየሩ ጭምር ቦታ እየቀያየሩና እየተመሳሰሉ እንዴት መጅሊስ ዉስጥ ለ46 ዓመታት በስልጣን ላይ መቆየት ቻሉ?" የሚል ጥያቄ በአዕምሮው ሊያጭርበት ይችላል።
ሙፍቲ የመጅሊስ ምርጫ ጉዳይ ሲነሳ ምርጫ ከተደረገ ከስልጣን እንደሚለቁ ስለሚያውቁ አጀንዳውን ለማዳፈን በተደጋጋሚ የሚያቀርቡት ማስፈራሪያ ከመጅሊስ ስልጣን ከተነሱ «መጅሊስ ለሁለት ይከፈላል» የሚለው ዛቻ ነው። ለሁለት ሲከፈል እሳቸው የአንዱ ክፋይ መሪ ሆነው እንዲቀጥሉ ሲባል ማለት ነው።
መጀመሪያ ዑለሞችና የቦርድ አባላት ሲመረጡ የመጅሊስ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ። ለስድስት ወራት በተባለው የሽግግር ጊዜ የተሰጣቸውን ኃላፊነት በአግባቡ ሳይወጡ 3 ዓመት አለፋቸው። ቆይተው ደግሞ በግልጽና በይፋ የተሰጠ ኃላፊነት ሆኖ ሳለ አንዴ «ስድስት ወር ብሎ ነገር የለም። ቋሚ ነን»፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ «እንደ ፓትሪያርኩ አንዴ ተመርጫለሁ እስከ ሕይወት ፍጻሜ ድረስ አልወርድም» ማለት ጀመሩ።
በኢትዮጵያ ሙስሊሞች ተቋማዊ ለውጥ የጋራ ኮሚቴ ሥር የመጅሊስ መተዳደሪያ ደንብን እንዲያዘጋጅ ተሰይሞ የነበረው የነበረው ኮሚቴ መተዳደሪያ ደንቡን ለዋናው ኮሚቴው ሲያቀርብ የሚመረጠው ዋና ሙፍቲ በንቃት ሕዝበ ሙስሊሙን ለማገልገል እንዲችል «እድሜው ከ40 ያላነሰና ከሰማንያ ያልበለጠ» የሚለው ነጥብ ሲጠቀስ ከሐጅ ዑመር ተቃውሞ ገጠመው። «ከሰማንያ ያልበለጠ የሚለው የእድሜ ገደቡ ይነሳ» አሉ። ይህም ስልጣናቸውን ለማስጠበቅ መሆኑ ግልጽ ነው።
ቀጥሎም ሌላኛው መስፈርት «ዐረብኛ ቋንቋ መናገር፣ መጻፍና ማንበብ መቻል አለበት» የሚለው ነጥብ ጋር ሲደረስም «የሀገራችን ብዙ ዑለሞች ዐረብኛ መናገር ስለማይችሉ የዐረብኛ ቋንቋ መስፈርቱ ይቅር» ብለው ተቃወሙ። በኋላ ስረዳ እሳቸው «ይህ መስፈርት እኔ እንዳልመረጥ ሆነ ብላችሁ ያስገባችሁት ነው» ብለው መተዳደሪያ ደንቡን በአሉታዊ ጎኑ ማየት መጀመራቸውን ተረዳሁ።
ለስድስት ወራት ከ26 ዑለማና ቦርድ ጋር የጊዜያዊ መጅሊስ ፕሬዝዳንት ሆነው ሲሾሙም አንዱ በጊዜው እንዲሰሩ በይፋ የተቀመጠው በባለሞያዎች የተዘጋጀው ረቂቅ መተዳደሪያ ደንብ ላይ ተጨማሪ ዉይይት በማድረግ ማፅደቅ ቢሆንም ባለፉት 3 ዓመታት አንዴ እንኳን ዞር ተብሎ ሳይታይ ያ መተዳደሪያ ደንብ ተትቶ ሌላ ተዘጋጅቶ በቅርብ ጊዜ ለውይይት ቀረበ።በእርሳቸው መሪነትም ዉይይት ተደረገበት።በመጨረሻም በአብላጫ ድምፅ ጸደቀ።
መጅሊስ በ1968 ሲመሠረት በመተዳደሪያ ደንቡ ምርጫ እንደሚደረግ በግልጽ እንደሚደነግግ የሚያውቁና መተዳደሪያ ደንቡ ላይ የፈረሙ፣ በተደጋጋሚ ጊዜም በመጅሊስ ምርጫ ላይ የተሳተፉ ነበሩ። ሌላው ቀርቶ በ2005 ሕዝበ ሙስሊሙ በፌደራል ጉዳይ አማካኝነት በየቀበሌ ተደረገ በተባለው ምርጫ እንኳን በመራጭም ሆነ በተመራጭነት የተሳተፉ ነበሩ። ሆኖም እርሳቸው ለጊዜያዊነት ተብሎ ለስድስት ወር የመጅሊስ ፕሬዝዳንት ሲሆኑ ከቦታው ላለመነሳት አንዴ «በእስልምና ምርጫ የለም» ሲሉ፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ «የክርስቲያኖች ፓትሪያርክ አንዴ ከተመረጠ በሕይወት እስካለ ሌላ ምርጫ አይደረግም። የኛም እንደዚህ ቢሆን ጥሩ ነው» የሚል ሐሳብ አመጡ። ይህም ተቀባይነት ሲያጣ በሕዝባዊ ምርጫ እሳቸው መሪ ሆነው እንደማይመረጡ ሲረዱ «ዑለማ ዑለማን ይመርጣል እንጂ ሕዝቡ ምርጫው አይመለከተውም፞። የሚመርጡትን ዑለሞች ደግሞ እኛ እንመርጣቸዋለን። የመረጥናቸው ዑለሞች ደግሞ መሪዎቻቸውን ይመርጣሉ» የሚል አቋም አራመዱ።
ሐጅ ዑመር እድሪስ ከ1968 እስከ 1985 ለ18 ዓመታትም የመጅሊስ ጠቅላላ ጉባኤ አባል፣ ከ1985-1986 ድረስ የመጅሊስ ሊቀመንበር (ፕሬዝዳንት) አማካሪ ሆነው አገለገሉ። በየካቲት 14 ቀን 1987 በአንዋር መስጂድ ግርግርና በመንግስት ጥቃት 10 ሙስሊሞች በመንግስት የጸጥታ አካላት ከተገደሉ በኋላ ሕዝቡን እንዲያረጋጉና የኢድ ሰላት አስተባባሪ ኮሚቴ አባል እንዲሆኑ ተደረገ።
በ1988 ከቢሾፍቱ ከተማ መንግስት ለርሱ ቅርብ የሆኑ ሰዎችን ሰብስቦ የመጅሊስ አመራር ሲመርጥ ሐጅ ዑመር እድሪስም በድጋሚ የመጅሊስ ጠቅላላ ጉባኤና የዑለማ ምክር ቤት አባል ሆነው ተመረጡ። እስከ 1992 ድረስም በዚያው ቆዩ።
ከ1993 እስከ ሚያዚያ 2001 የአዲስ አበባ መጅሊስ ፕሬዝዳንት፣ ከሚያዚያ 2001 እስከ መስከረም 2005 የፌደራል መጅሊስ መስጊድና አውቃፍ ዘርፍ ኃላፊ፣ ከ2005 እስከ 2010 የፌደራል መጅሊስ የጠቅላላ ጉባኤው አባል፣ የመስጊድና አውቃፍ ዘርፍ ኃላፊ፣ እንዲሁም የዑለማ ምክር ቤት አባል ሆነው ቆዩ።
ጠቅላይ ሚኒስተር ዶ/ር አብይ ወደ ስልጣን ሲመጡ ህዝበ ሙስሊሙና የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴው በመጅሊስ ጉዳይ ጥያቄ ሲያቀርብ መጀሊስን በመወከል ከጠቅላይ ሚ/ሩ ጋር ከቀረቡት መካከል ነበሩ። ከ2010 ሰኔ 26 እስከ ሚያዚያ 23 2011 ድረስ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ባቋቋሙት የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ተቋማዊ ለውጥ የጋራ ኮሚቴ ላይ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰብሳቢ ተደርገው ተሾሙ።
በሚያዚያ 23/2011 የጊዜያዊ መጅሊስ ፕሬዝዳንት ተደርገው ለ6 ወራት ተሹመው በሕገ ወጥ መንገድ ከ3 ዓመታት በላይ ቆዩ። ከሰሞኑ ደግሞ የመጅሊስ ጠቅላላ ጉባኤ ሐጅ ዑመር እድሪስንና ምክትላቸውን ዶ/ር ጄይላንን ጨምሮ አራት ዑለሞችን ከአመራርነት አንስቶ ወደ ፈትዋ ዘርፍ መደባቸው።
ተቋሙ ከተመሠረተ ጀምሮ ላለፉት 46 ዓመታት በተለያዩ ኃላፊነቶች በአመራር ወንበር ላይ የነበሩት ግለሰብ ተቋሙ በዚህ ሁሉ ዘመኑ ለሕዝበ ሙስሊሙ ተገቢውን አገልግሎት ባለመስጠቱ ይቅርታ ጠይቀው በራሳቸው ፈቃድ ሊሰናበቱ ይገባቸው ነበር። ዕድሜያቸው 90 ሞልቷል። በፈትዋ ክፍል በሙፍቲነት እንዲያገለግሉ ሲወሰን በእምቢተኝነት ሕዝበ ሙስሊሙን ወደ መክፈል ድረስ የሚያደርሰው የስልጣን ፍቅር እንዴት ስር ቢሰድ ነው አቅል እስከ ማሳት የሚያደርሰው?
ከ3 ሳምንታት በፊት የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች የመንግስታዊ ተቋማት ሪፎርምን እንዲገበኙ ተሰናድቶ በነበረው ጉብኝት ማጠናቀቂያ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመሩት ስብሰባ ላይ 120 የምንሆን ሙስሊሞች ተገኝተን ነበር። ስለመጅሊስ ምርጫ አጀንዳ ሲነሳ ግን በተለያዩ መድረኮች «አላህ ሽቶብኝ ነው እንጂ እኔ ስልጣን አልፈልግም» ያሉትን ንግግር ተቃርነው ዛቻ ጀመሩ። ያው በተለመደው የሱፊያ ካባ ስር ሆነው «ደም ይፈሳታል እንጂ አልለቅም» ሲሉ በግልጽ ተናገሩ። ኢናሊላሂ ወኢናኢለይሂ ራጂኡን!
6 918
በመላው ዓለም የምትገኙ ኢትዮጵያውያን እና #የኢትዮጵያ ወዳጆች የ #ወደሀገርቤት እንግባ ጥሪን እንድትቀላቀሉ እንጋብዛለን።
1 ሚሊየን ሰዎች በሀገር ቤት በታኅሣሥ 29፣ 2014 ዓ.ም.
Itoophiyaanonni fi michuuwwan #Itoophiyaa guutuu addunyaatti argamtan waamicha #BiyyattiHaagallu jedhutti akka makamtan isin afeerra.
Mudde 29/2014 tti namoota miliyoona 1 gara biyyaatti.
Ethiopians and friends of #Ethiopia around the world, join the #GreatEthiopianHomeComing Challenge
1 million by January 7, 2022
6 918
የኢትዮጵያ ሕዝብ በሁሉም መስክ ተባብሮ ሲነሣ ውጤቱ ድል ነው። በግንባር፣ በዲፕሎማሲ፣ በኢኮኖሚ፣ በኮሙኒኬሽን፣ በስንቅ ዝግጅት፣ ዘማች በመከባከብ፣ ጸጥታ በማስከበር፣ተፈናቃዮችን በመደገፍ. በሁሉም ግንባሮች ለዘመታችሁ ሁሉ እንኳን ደስ አላችሁ!
Uummanni Itoophiyaa gama hundaan tumsee yoo ka'e bu'aansaa injifannoodha. Warri gama addawwan waraanaatiin, dippiloomaasiidhaan, dinagdeedhaan, koominikeeshinii, galaa qopheessuu, warra duulan kunuunsuu, nageenya kabachiisuufi buqqaatota deeggaruudhaan duultan hundi baga gammaddani!
6 918
“ኢትዮጵያ” የሚለውን የነጻነት ስም የማስጠበቅ የታሪክ አደራ አለብን!
ውድ የሀገሬ ልጆች፣
የተከበራችሁ የኢትዮጵያ ወዳጆች፣
ኢትዮጵያ በልጆቿ ጀግንነትና መሥዋዕትነት ክብሯንና ነጻነቷን አስጠብቃ የኖረች ሀገር ናት። ይሄን ወዳጅም ጠላትም ያውቀዋል። ድንበሯን ሊደፍሩ የሞከሩ አይበገሬ ክንዷን አይተዋል። ሊያስገብሯት የቋመጡ አቀርቅረው ተመልሰዋል። ክህደት ለፈጸሙባት ተገቢውን ትምህርት መስጠት፣ ከጀርባ የወጓትን አይቀጡ ቅጣት መቅጣትን ታውቃለች። ለሺህ ዘመናት የተጎናጸፈችው ነጻነትና ሉዓላዊ ክብር በችሮታ የተገኘ አይደለም። ያለ ዋጋ ነጻነትን አጽንቶ መጠበቅ አይቻልምና፤ ኢትዮጵያ የሚለው የነጻነት ስም የደም ዋጋ ተከፍሎበታል፣ ብርቱ ጀግኖች ሞተውለታል።
በታሪክ የምናውቃቸው አባቶቻቸው በአስተዳደርና በርእዮተ ዓለም ይለያያሉ፤ ለመብት፣ ለፍትሕና ለእኩልነት በነበራቸው አመለካከት ይለያያሉ። ለኢትዮጵያ የግዛት አንድነት፣ ነጻነትና ሉዓላዊነት ባላቸው ቦታ ግን ልዩነት አልነበራቸውም። በቋንቋ፣ በብሔርና በጎሳ ብዝኃነት ቢኖራቸውም የአልደፈርም-ባይ ቆራጥነታቸው አንድ ያደርጋቸዋል። የግል ፍላጎታቸው የቱንም ያህል የተራራቀ ቢሆን፣ የጋራ ጠላት ሲመጣ ኢትዮጵያዊነት ከግላዊነታቸው በላይ ይቀመጣል።
ድሮም ሆነ ዛሬ የእያንዳንዳችን ፍላጎት፣ የሁላችንም ሕይወት ከኢትዮጵያ በታች ነው። እኛ ኖረን ኢትዮጵያ ከምትሞት እኛ ሞተን ኢትዮጵያ እንድትኖር እንፈልጋለን። የሁላችንም የሆነች፣ ነጻነትና ፍትሕ የሰፈነባት፣ በገናናነቷና በነጻነቷ በዓለም አደባባይ የምትጠራ ሀገር እንድትኖረን ምኞታችን ነው። ለኢትዮጵያ ትልቅ በመመኘት፤ ሀገራችን አንገቷ ቀና እንዲል በመፈለግ፤ ባለፉት ሦስት ዓመታት ዐቅማችን የፈቀደውን ሁሉ አድርገናል። ፖለቲካችን ከመገዳደል ወደ መተጋገል እንዲቀየር ታግለናል። ኢትዮጵያ የሁላችን ናት ብለን በሰው ሀገር የሚንከራተቱት ሁሉ እንዲገቡ ለማድረግ ሞክረናል። ካለፈው በጎውን ወስደን ጥፋቱን በይቅርታ ለማረም ተንቀሳቅሰናል። “በፍቅር እንደመር፣ በይቅርታ እንሻገር” ብለን አዲስ ምዕራፍ ከፍተናል። የመለያየትና የጥላቻን ግንብ አፍርሰን የመደመርና ኅብረ ብሔራዊ ወንድማማችነት ድልድይን ልንገነባ ቃል የገባነውን ወደ ተግባር ለመተርጎም ዐቅማችን የፈቀደውን አድርገናል።
ኢኮኖሚው እንዲያገግምና መዋቅራዊ ለውጥ እንዲያመጣ፤ የዳኝነት ሥርዓታችን እንዲሻሻል፣ የሰብአዊ መብት አያያዛችን እንዲስተካከል፤ የውጭ ግንኙነት መርሐችን ጎረቤት ተኮር እንዲሆን ታግለናል። በዚህ መካከል እንደ ሰው በርትተናል። እንደ ሰውም ደክመናል። እንደሰው አልምተናል፣ እንደ ሰውም አጥፍተናል። በኢትዮጵያ ኅብረ ብሔራዊ አንድነት፣ በኢትዮጵያ ክብርና በኢትዮጵያ ታላቅነት ግን ለአፍታም አዘንብለን አናውቅም።
ኢትዮጵያ የምታጓጓ ሀገር ናት። ከትናንትናዋ ይልቅ ነገዋ ታላቅ ነው። መከራ ማለፍ ነባር ችሎታዋ ነው። ይሄንን የገጠመንን መከራም እናልፈዋለን። ኢትዮጵያ ማሸነፏ አይቀርም። አሁን ኢትዮጵያን ለመታደግ የመጨረሻውን ፍልሚያ የምናደርግበት ጊዜ ላይ ነን። ጠላቶቻችን በውጭና በውስጥ ተቀናጅተው ዘምተውብናል። በአንድ በኩል ታሪካዊ ጠላቶቻችን በራሷ ፈቃድና በራሷ መንገድ ብቻ የምታድግ ኢትዮጵያ ላለማየት የጥፋት በትር ሰንዝረዋል። ኢትዮጵያ አፍሪካዊ በሆነ መንገድ ከተነሣች፣ ተነሥታም ካሸነፈች፣ ከዚህ በኋላ ለማንም የማትመለስ ትሆናለች። ይሄን አፍሪካዊ መንገድ ለማደናቀፍ ሁሉንም ዓይነት የክፋት መሣሪያዎች አሰልፈዋል። የውጭና የውስጥ ጠላቶቻችን የእነርሱን ብርታት በኢትዮጵያ ድካም ላይ ለመገንባት ተነሥተዋል። የኢትዮጵያ ፍላጎት ይዞ ማለፍ እንጂ ጥሎ ማለፍ አልነበረም፤ ለዚህ ነው የውጭ ግንኙነት ፖሊሲያችን በዋናነት ጎረቤት ተኮር እንዲሆን ያደረግነው፤ ይህ ትግል የመላ ጥቁር ሕዝቦች ትግል ነው። ኢትዮጵያ አንበርክኮ ጥቁር ሕዝብን ለማሳፈርና አዲሱን የቅኝ ግዛት ቀንበር ለመጫን የሚደረግ ሤራ ነው።
ጥቁር ሕዝቦች የራሳችን ታሪክ፣ ባህል፣ ማንነትና ክብር እንዳይኖረን ሆን ተብሎ የሚደረግ አንገት የማስደፋት ትግል ነው። ይህ በኢትዮጵያ ላይ የተከፈተ ዘመቻ፣ ኢትዮጵያን በማንበርከክ ጥቁር ሕዝቦች የነጻነትና የአሸናፊነት አርአያ እንዳያገኙ የተከፈተ ዘመቻ መሆኑን ላስታውሳችሁ እወዳለሁ። ለጥቁር ሕዝብ ክብርና ልዕልና ስትሉ፣ በፓን አፍሪካ መንፈስ፣ ሁላችሁም ጥቁር ሕዝቦች፣ ከኢትዮጵያ ጋር እንድትቆሙ ጥሪ አቀርብላችኋለሁ።
በመጨረሻም ይህ ትግል የሁሉም ኢትዮጵያዊ ትግል ነው። ልጆቻችን ሀገር እንዲኖራቸው የሚደረግ ትግል ነው። ልጆቻችን ክብርና ነጻነትን ለብሰው፣ በዓለም አደባባይ በኩራት ቀና ብለው እንዲሄዱ የሚደረግ ትግል ነው። በዓለም ላይ በክብር የምንጠራበት ስም እንዲኖረን የሚደረግ ትግል ነው። መኖር ወይም አለመኖራችንን የሚወስን ትግል ነው። ያለ ጥርጥር ግን እናሸንፋለን። ኢትዮጵያን ጠርቶ መሸነፍ ፈጽሞ የማይታሰብ ነው።
ጊዜው ሀገርን በመሥዋዕትነት መምራት የሚያስፈልግበት ጊዜ ነው። ከእንግዲህ እኔ መከላከያን በግንባር ሆኜ ለመምራት ከነገ ጅምሮ ወደ ትግሉ ሜዳ እዘምታለሁ። ታሪክ ከሚያደንቃቸው የኢትዮጵያ ልጆች አንዱ ለመሆን የምታስቡ ሁሉ ለሀገራችሁ ስትሉ ዛሬውኑ ተነሡ፤ ግንባር ላይ እንገናኝ፡፡ የእኛ መዝመት የሚፈጥረውን ክፍተት ከግንባር የቀሩት በሙሉ ዐቅማቸው ሸፍነው ይሠራሉ፡፡ በግንባር ያልተሰለፉ የክልልና የፌደራል አመራሮች ከመቼውም ጊዜ በላይ የልማትና አስተዳደር ሥራዎችን በሙሉ ዐቅማቸው ይከውናሉ።
ጎልማሶች በዘዴና በብልሃት አካባቢያቸውን እየጠበቁ፣ አረጋውያን እናትና አባቶች በጸሎት እየተጉ፣ ሁሉም ሰው ተባብሮ የኢትዮጵያን አሸናፊነት ያረጋግጣል። ከዚህ በኋላ በሩቁ ተቀምጠን ተቺና አራሚ የምንሆንበት ጊዜ አይደለም። መደረግ ያለበትን እኛው ራሳችን እናድርገው። ለኢትዮጵያ ከእኛ በላይ ከየትም አይመጣም። ኢትዮጵያ የሚለው ስም የአሸናፊዎች ስም ነው፤ የነጻነት ምልክት ነው። አልጠራጠርም፣ የእኔ ትውልድ ለአሸናፊ ስሙና ለነጻነት ምልክቱ የሚጠበቅበትን ዋጋ ከፍሎ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን በክብር መዝገብ ላይ በወርቅ ብዕር ያትማል።
አመሰግናለሁ!!
ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትሩር!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ኅዳር 13፣ 2014 ዓ.ም
6 918
"ይኼ ጊዜ ችግሮች ተደራርበው የመጡበት የፈተና ጊዜ ነው!
ፈተናው እስኪያልፍ ሁሉም ሰው መፈተኑ አይቀርም። ችግሮቻችን አፋጣኝ መፍትሄ አግኝተው ወደ መደበኛ ኑሮ እስክንመስ ሁላችንም አኗኗራችንን ለፈተና ጊዜ እንዲስማማ አድርገን መቆየት አለብን።
እንደ ሰላሙ ጊዜ ነገሮች አልጋ በአልጋ እንዲሆኑ መጠበቅ የሰላሙን ጊዜ ያርቀዋል እንጂ ፈጽሞ አያቀርበውም።
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የታወጀውም የመከራውን ጊዜ ለማሳጠርና የመፍትሔውን ጊዜ ለማቅረብ ነው።
ስለዚህ ዜጎች ወቅቱ እንደሚጠይቀው በመሆን፣ አዋጁ የሚያዝዛቸውን መመሪያዎች በማክበር፣ የሕግ አስከባሪ አካላት ሥራቸውን በቅልጥፍና እንዲያከናውኑ በመተባበር እና አስፈላጊውን እገዛ በማድረግ ሁሉም የበኩሉም ሚና እንዲወጣ ጥሪዬን አቀርባለሁ።"
ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ
6 918
ከፍተኛ የህወሓት አመራሮች እርምጃ ተገደሉ።
መከላከያ ሰራዊት አቶ ስዩም መስፍንን ጨምሮ ሌሎች የህወሓት አመራሮች መደምሰሳቸውን አሳውቋል።
አመራሮቹ በተከዜ ወንዝ ዳርቻ አካባቢ ተደብቀው እንደነበር እና ከነ ጠባቂዎቻቸው እና ከወታደራዊ አመራሮቻቸው ጋር እንደተደመሰሱ ሀገር መከላከያ ገልጿል።
የተደመሰሱት አመራሮች ፦
1. አቶ ስዩም መስፍን - የቀድሞው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩ እንዲሁም ውጊያውን የመሩና ሰራዊቱ ከቦታ ቦታ እንዳይንቀሳቀስ ያዘዙ፣ በመጨረሻም በመከላከያ ሰራዊቱ ላይ ውጊያ እንዲከፈት ትዕዛዝ የሰጡ፣
2. አቶ አስመላሽ ወልደስላሴ - የህወሓት ከፍተኛ የፖለቲካ አመራር የነበሩ
3. አቶ አባይ ፀሃዬ - የህወሓት ከፍተኛ የፖለቲካ አመራር የነበሩ
4. ኮሎኔል ኪሮስ ሀጎስ - ከመከላከያ የከዱ ከነጥበቃዎቻቸው ተደምስሰዋል።
በሌላ በኩል በቁጥጥር ስር የዋሉ ወታደራዊ እንዲሁም የክልል አመራሮች ፦
1. ኮሎኔል ገብረመስቀል ገብረ ኪዳን - ከመከላከያ የከዱ
2. ኮሎኔል ፍስሃ ብርሃኔ - ከመከላከያ የከዱ፤
3. ኮሎኔል ዘረአብሩክ ታደሰ - ከመከላከያ የከዱ፤
4. ኮማንደር ገብረኪዳን አስገዶም - የልዩ ሀይል ክፍለ ጦር አዛዥ የነበሩ
5. አቶ መብራህቶም ክንዴ ሀይሉ - የክልሉ ውሃ ስራዎች ድርጅት ፋይናንስ ሀላፊ የነበሩ በቁጥጥር ስር ውለዋል።
የሀገር መከላከያ ሰራዊት ኃይል ስምሪት መምሪያ ሀላፊ ብርጋዴር ጀነራል ተስፋዬ አያሌው ፣ አሁንም የተደበቁ የህወሓት ቡድን አባላት በሰላማዊ መንገድ እጅ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል።
6 918
I am pleased to endorse Professor Hirut Woldemariam, #Ethiopia ’s Candidate for
# AU Commissioner of Education, Science, Technology & Innovation. Having served in my Cabinet as Minister for the Ministry of Science and Higher Education and currently serving as my Social Sector Advisor, Professor Hirut is an exceptional candidate for the post.
6 918
የኢጋድ አባል ሀገራት መሪዎች የህግ ማስከበር እርምጃዎቻችንን ህጋዊነት እውቅና መስጠታቸው እንዲሁም ኢትዮጵያን ለመደገፍ ቁርጠኝነታቸውን ገለፁ
