አርባ ምንጭ ዪኒቨርስቲ
Open in Telegram
Official Arbaminch University ® ማስታወቂያዎችን እና ወቅታዊ መረጃዎችን በፍጥነትና በጥራት! ሀሳቦች እና እንዲተላለፍላችሁ የምትፈጉት ነገር ካለ በ @newneway @Fika_Amare @miko1122 @ADA1249 ላይ ያግኙን፡፡ AMU Info ...... እውነተኛ እና ፈጣን መረጃ ይደርሶታል፡፡ ።።ከተማሪ ለተማሪ።።: Arba_Minch_university
Show moreThe country is not specifiedEducation52 928
3 063
Subscribers
+624 hours
+307 days
+4030 days
Posts Archive
3 063
ዶ/ር ዳምጠው ዳርዛ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ሆነው በድጋሚ ተሾሙ
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲን ላለፉት ዓመታት በፕሬዝደንትነት ሲመሩ የቆዩት ዶ/ር ዳምጠው ዳርዛ የመጀመሪያ ዙር የሹመት ዘመን መጠናቀቅን ተከትሎ 13 ተፎካካሪዎች የተሳተፉበት ይፋዊ ፕሬዝደንታዊ ምርጫ ተካሂዶ በድጋሚ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ሆነው ተሹመዋል፡፡
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ትምህርት ሚኒስቴር ታኅሣሥ 06/2015 ዓ/ም በቁጥር 1/158/898/15 በጻፈው የሹመት ደብዳቤ በመንግሥት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሪፎርም ዕቅድ መሠረት አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ራስ ገዝ ሆኖ መልሶ እስኪደራጅና አዲስ ፕሬዝደንት በዓለም አቀፍ ውድድር እስኪቀጠር ድረስ ዶ/ር ዳምጠው ዳርዛ ከታኅሣሥ 15/2015 ዓ/ም ጀምሮ በድጋሚ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ሆነው መሾማቸውን በመግለጽ ዩኒቨርሲቲው ተልዕኮውን ያሳካ ዘንድ የተጣለባቸውን ከባድ ኃላፊነት በትጋት እንዲወጡ አሳስቧል፡፡
ዶ/ር ዳምጠው ዳርዛ እጅግ ፈታኝ በሆነው ጊዜ ውስጥ የዩኒቨርሲቲውን ሰላማዊ መማር ማስተማር ከፌዴራልና ከአካባቢው መንግሥት ጋር በቅንጅት በመሥራት ማስቀጠል መቻላቸው ይታወሳል፡፡
የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
@amucampus
@amucampus
3 063
#ወላይታ_ሶዶ_ዩኒቨርሲቲ
የመውጫ ፈተናን በኦላይን መስጠት የሚያስችል መተግበሪያ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ መምህራን መበልጸጉ ተገለጸ።
በዩኒቨርሲቲው ኢንፎርማቲክስ ትምህርት ቤት መምህራን የለማው መተግበሪያ፤ WSU E–learning and Online Exam System ተብሎ ይጠራል።
አዲስ የለማው ሶፍትዌር ኩረጃን ለማስቀረት ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው መተግበሪያውን ያለሙ ባለሙያዎች አስተባባሪ ሀብታሙ ፋንታ (ዶ/ር) ገልጸዋል።
ሶፍትዌሩ ጥቅል የፈተና ባንክ፣ የአሳይመንት ምድብ፣ ሞጁል፣ መጽሐፍት እና የመውጫ ፈተና ክፍሎችን እንደያዘ ተናግረዋል።
የመውጫ ፈተናን በተሳካ መልኩ ለመስጠት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመሰረተ ልማት ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ ትምህርት ሚኒስቴር አቅጣጫ ማስቀመጡ ይታወቃል።
👉tikvahuniv
@amucampus
@amucampus
3 063
ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎች በሙሉ
የዩኒቨርሲቲው አመራር አካላትና መምህራን በቀን 01/4/2015 ዓ/ም ሰፊ ውይይት ካካሄዱ በኋላ ከሰኞ (ታኅሣሥ 03/2015 ዓ/ም) ጀምሮ የመማር ማስተማር ሥራውን በተሟላ ደረጃ ለመቀጠል ከስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡ በመሆኑም ሁሉም መምህራን እና ተማሪዎች በትምህርት ክፍለ ጊዜያችሁ መሠረት በመማር ማስተማር ሥራው ላይ እንድትገኙ ዩኒቨርሲቲው ከአደራ ጭምር ይገልጻል፡፡
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
@amucampus
@amucampus
3 063
🕯አሳዛኝ ዜና
አርቲስት ታሪኩ ብርሀኑ (ባባ) በድንገተኛ ህመም ዛሬ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
ለቤተሰቦቹ፣ለወዳጆቹ እንዲሁም ለአድናቂዎቹ በሙሉ መፅናናትን እንመኛለን።
ነብስ ይማር 🙏
@amucampus
@amucampus
3 063
ውድ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲና የዚህ ቻናል ተከታታዮች በሙሉ በተለያዩ በውስጥ ችግር ምክንያት መረጃ ለናንተ ማድረስ ካቆምን ሰንበትበት ማለታችን አይዘነጋም ሆኖም የውስጥ ችግሮቻችንን በመፍታት በድጋሜ እናትን ለማገልገል ዝግጅታችንን ጨርሰን መረጃ ይዘን መተናል ሰለ አስተያየታቹና አክብሮታቹ ከልብ እያመሰገንን ሀሳብ አስተያየት ለመስጠት @newneway ላይ አድርሱን።
@amucampus
@amucampus
3 063
ለአርባምንጭ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች እና ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ ፤ እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ ።
የደመራ በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶድክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምዕመናን ዘንድ ልዩ ትኩረት የሚሰጠው ክብረ በዓል ነው። የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ስቅለተ መስቀል ለማግኘት የንግስት ኢሌኒን እና የልጇ የንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ድካም ፤ የአረጋዊው የኪራኮስ አድራሻ ጠቋሚነት እና የአይሁዳውያን የመስቀል ጠላትነት ሁሉ በጥቅሉ አብሮ የሚታሰብ እንደሆነ ይታወቃል ።
በየዓመታቱ የሚፈራረቁ በዓላት እርስ በርሳችን ያለንን መስተጋብር የሚያጠናክሩ ፣ አንዳችን ለአንዳችን ያለንን ወዳጅነት አጉልተው የሚያደረጁ አጋጣሚዎች ናቸው ። ከእነኝህ መሀል ደግሞ የመስቀል ደመራ ዋነኛው ነው። በተለይም የዚህ ዘመን ተማሪዎች ሁላችንም በጋራ ፣ በትዝታ ሰረገላ የኋሊት የተጓዝን እንደሆን ፣ የመስቀል በዓል ከልጅነት ዘመናችን ጋር በእጅጉ የተቆራኘ ነው። ከደመራ መልስ ቧሃላ ቡድን መስርተን ፣ ዱላ ይዘን ፣ ሆያ ሆዬ አውጪ ፣ ገንዘብ ያዥ መድበን በውድቅት ጨለማ የመስቀል መገኘቱን ብስራት እያዜምን እንዞራለን ። ከማይረሱ የልጅነት ትውስታችን መሀል ይህ በዓል የመጀመሪያ ስፍራ የሚሰጠው ነው።
በዓሉን እንደልጅነታችን የምንሰባሰብበት ፣ ባልደፈረሰ ፍቅር ፣ ባላደፈ ልቦና የምንቀራረብበት ፣ የተራቡ ጠግበው ፣ የተጠሙ ረክተው ፣ የተራራቁት ሁሉ ተሰብስበው የምናከብረው በዓል እንዲሆን እንመኛለን።
በድጋሚ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ !
የአርባምንጭ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች ህብረት ❗
3 063
የአርባምንጭ ዩንቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ ❗
ተማራቂዎቻችን የአስራዎቹን ዓመታት የድካም ፍሬ ልትቀበሉ ፣ ለታጫችሁት ልዩ ቀን እንኳን በሠላም እና በጤና አደረሳችሁ ። በብዙ ውጣ ወረድ ውስጥ አልፋችሁ ፣ ድካሙን በትጋት ፣ ፈተናውን በፅናት በመወጣት ለዛሬ ቀን በመብቃታችሁ ሁላችሁም ዘንድ የተፈጠረውን የሀሴት ስሜት እንጋራው ዘንድ ተሰይመናል ። ይህ ዕለት ከተመራቂ ተማሪዎች በበለጠ ደግሞ ለአስመራቂ ቤተሰብ ትልቅ ቁምነገር እንዳለው ገሀድ ነው።
አስመራቂ ቤተሰቦችንም እንኳን ደስ አላችሁ ።
መመረቅ አቀበቱ ከተወጣ ወዲህ ከተስፋ አውላላ የሚደረስ የዕድሜ ሰገነት ነው። ልጅነት በልፋት የተባጀበት ፣ ወጣትነት በፅኑ ልፋት የተደከመበት የእውቅና ውጤት ነው ፤ ምርቃት :: ተማሪዎቻችን በዩኒቨርስቲ ቆይታቸው ያሳዩትን ሠላም ወዳድነት ፣ ያዳበሩትን ሀገራዊ እሴት ፣ በፅኑ ያጎለበቱትን የአብሮነት ስሜት ፤ ነገም በሚሰማሩበት የስራ መስክ እንደሚደግሙት የአርባምንጭ ዩንቨርስቲ የተማሪዎች ህብረት በፅኑ ያምናል ።
የዛሬ ምርቃት ለበለጠ ሀገራዊ ኃላፊነት ፣ ለተሻለው ትውልዳዊ አደራ እንዳጫቸው ተማራቂዎቻችን እንደሚገነዘቡ እናምናለን ። በምትሄዱበት ሁሉ ቸር ይገጥማችሁ ዘንድ እየተመኘን ፤ በድጋሚ ለተመራቂ ተማሪዎች እና ቤተሰቦች ፣ ለመምህራን ፣ ለዩንቨርስቲ አመራር አካላት እና ለመላው የአርባምንጭ ዩንቨርስቲ ማህበረሰብ እንኳን ደስ አላችሁ ።
Haashshu Ufayssi Gidides !
የአርባምንጭ ዩንቨርስቲ የተማሪዎች ህብረት ❗
3 063
Repost from Arba Minch University Students`Union
የአርባምንጭ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ ።
አሮጌው ሄዶ በአዲስ ሲተካ ፣ ክረምቱ አልፎ ዘመን ሲፈካ በአደይ በተዋበ ውብ መሬት አዲሱን ዓመት ለመቀበል እንሰናዳለን። የአሮጌው ዓመት መጥፎ አጋጣሚዎቻችን ተረስተው ፣ ወደትዝታ መዝገብ የሚሰፍሩበትን ፤ የአዲሱን ዓመት በአዲስ የህይወት ምዕራፍ የምንጀምርበት ወርሃ መስከረም ሲጠባ ከአውዳመት ማግስት ውጥኖቻችን የበዙ ናቸው ። አዲስ ዓመት ደግሞ ለተማሪዎች ሲሆን ልዩ ትዝታ ይኖረዋል ። የክረምቱን ጭጋግ በዕረፍት አሳልፈን ፣ በፀደይ መባቻ የትምህርት መርሐ ግብራችን የምንጀምረበት ልዩ የሆነ የትዝታ ሰነዳችን ነው።
በዚሁ ዑደት የምንጓዝበት የህይወት መንገድ በብዙ ውጣ ውረዶች እና አባጣ ጎርባጣዎች የተሞላ ነውና ፤ የታከተ መንፈሳችንን አድሰን ለአዲሱ የትምህርት ዘመን የምንዘጋጅበት መጪው ዓመት ይሁንልን ። 2015 ዓ.ም ለዩንቨርስቲያችን ተማሪዎች ፣ መምህራን ፣ አመራሮች ፣ ባጠቃላይ ለዩንቨርሲቲው ማህበረሰብ እና ለመላው የሀገራችን ህዝብ የፍስሐ ፣ የሠላም እና የብልጽግና ይሆን ዘንድ የአርባምንጭ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች ህብረት ይመኛል ❗
መልካም አዲስ ዓመት !!
3 063
የሀዘን መግለጫ
😭😭😭😭😭😭😭😭
ዳዊት ይልማ ይባላል 08 ባች አርባምንጭ ዪኒቨርስቲ CIVIL ምህንድስና ተማሪ ነበር በጣም ትሁት እና ታታሪ ልጅ ነበር😭
3 063
በድጋሚ የወጣ የነባር የክረምት መርሃ-ግብር ተማሪዎች ጥሪ ጊዜ ማሻሻያ ማስታወቂያ
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የ2014 ዓ/ም የነባር የክረምት መርሃ-ግብር ትምህርት የምዝገባና የትምህርት መጀመሪያ ጊዜ አስመልክቶ በቴሌቪዥን፣ በዩኒቨርሲቲው ድረ ገጽና ማኅበራዊ ትስስር ገጾች ምዝገባ ሐምሌ 11-12/2014 ዓ/ም እንዲሁም ትምህርት የሚጀምርበት ጊዜ ሐምሌ 13/2014 ዓ/ም መሆኑን ማስተዋወቁ ይታወቃል፡፡
ይሁን እንጂ ከትምህርት ሚኒስቴር በ27/10/2014 ዓ/ም በተጻፈ ደብዳቤ በኮቪድ - 19 እና በሰሜኑ በተከሰተው ጦርነት ምክንያት የአጠቃላይ ትምህርት ተማሪዎች መደበኛ የትምህርት መርሃ-ግብር በተቀመጠለት ጊዜ ባለመጠናቀቁ የ2014 ዓ/ም የክረምት የመምህራንና የት/ቤት አመራሮች ደረጃ ማሻሻያ ትምህርት ከሐምሌ 20/2014 ዓ/ም እስከ መስከረም 10/2015 እንዲካሄድ ስለተገለጸ በዚሁ አግባብ ማሻሻያ በማድረግ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የምዝገባ ጊዜ ሐምሌ 20-21/2014 ዓ/ም እንዲሁም ትምህርት የሚጀመርበት ጊዜ ሐምሌ 22/2014 ዓ/ም መሆኑን በድጋሚ ያሳውቃል፡፡
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
@amucampus
@amucampus
3 063
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዬች በሙሉ እንኳን ለ1443ኛው የኢድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችው በዓሉ የሰላም , የደስታ , የብልግና ,የስኬት እና የፍቅር ይሁንላችው!
መልካም በዓል ለሁላችን 🙏
@amucampus
@amucampus
3 063
የ 2014 ተመራቂ ተማሪዎች እንኳን አደረሳቹ👏👏
Congra🎓🎓🎓🎓🎓
Especially dmoo
Oly
Bela
Eshu
Yoni
Abdu(2)
Rahwi
Fodi
Josi
Bebi
Mita
Heli
Elu
Shemsi
Eku
Jem
Tedi
Becho
Ayu
Rich
Elif
.....
.....
.....
.....
G 5 (Mechanical)🎓🎓🎓🎓🎓
3 063
#ArbaMichUniversity
አርባ ምንጭ የኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 2 ሺህ 540 ተማሪዎች ያስመርቃል።
ተመራቂዎቹ ከመጀመሪያ እስከ 3ኛ ዲግሪ በመደበኛ፣ በክረምት፣ በማታ፣ በሳምንት መጨረሻ እና በተከታታይ መርሃ ግብር ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።
ከዩኒቨርሲቲው 35ኛ ዙር ተመራቂዎቹ መካከል 657ቱ ሴቶች መሆናቸው ተገልጿል፡፡
የተማሪዎች የምረቃ ስነ ስርዓት ነገ ሰኔ 25/2014 ዓ.ም እና እሁድ ሰኔ 26/2014 ዓ.ም ይከናወናል።
@tikvah university
3 063
Congratulations 🙏!
ዩኒቨርሲቲያችን የ2014 ዓ.ም የተማሪዎች የምረቃ ስነ-ስርዓት ሰኔ 25/2014 ዓ.ም እንደሚከናወን አሳውቋል ።
@amucampus
@amucampus
@newneway
3 063
ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ ዲግሪ የክረምት መርሃ-ግብር ተማሪዎች በሙለ
የ2014 ዓ.ም የክረምት ትምህርት ምዝገባ ሐምሌ 4-5/2014 ዓ.ም ስለሚካሄድ በተጠቀሱት ቀናት
በየካምፓሶቻችሁ ተገኝታችሁ እንድትመዘገቡ እየገለጽን ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ የሚመጣ ተማሪን
ዩኒቨርሲቲው የማያስተናግድ እንዲሁም ይህ ማስታወቂያ የግብርና ሳይንስ ኮሌጅ ተማሪዎችን
የማይመለከት መሆኑን ያስታውቃል፡፡
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተከታታይና ርቀት ትምህርት ኮሌጅ
@amucampus
@amucampus
