en
Feedback
𝐉𝐨𝐮𝐫𝐧𝐞𝐲 𝐓𝐨 𝐈𝐬𝐥𝐚𝐦🪸

𝐉𝐨𝐮𝐫𝐧𝐞𝐲 𝐓𝐨 𝐈𝐬𝐥𝐚𝐦🪸

Open in Telegram

#ሚዛናዊነት_እና_ሁለንተናዊነት #ህልም_ትጋት_ስኬት اقْرَأْ بِاسْمِ رَبِّكَ الَّذِي خَلَقَ አንብብ በዚያ (ሁሉን) በፈጠረው ጌታህ ስም ትውልድ ሚገነባው በእውቀት ነው። እውቀትን ምናገኝበት ዋናኛው መንገድ ደሞ በማንበብ ነው።

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified

📈 Analytical overview of Telegram channel 𝐉𝐨𝐮𝐫𝐧𝐞𝐲 𝐓𝐨 𝐈𝐬𝐥𝐚𝐦🪸

Channel 𝐉𝐨𝐮𝐫𝐧𝐞𝐲 𝐓𝐨 𝐈𝐬𝐥𝐚𝐦🪸 (@ahlu_al_quran1) is an active participant. Currently, the community unites 11 656 subscribers, ranking in the Other category.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 11 656 subscribers.

According to the latest data from 08 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -617 over the last 30 days and by -28 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 7.40%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 3.74% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 863 views. Within the first day, a publication typically gains 436 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 12.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
#ሚዛናዊነት_እና_ሁለንተናዊነት #ህልም_ትጋት_ስኬት اقْرَأْ بِاسْمِ رَبِّكَ الَّذِي خَلَقَ አንብብ በዚያ (ሁሉን) በፈጠረው ጌታህ ስም ትውልድ ሚገነባው በእውቀት ነው። እውቀትን ምናገኝበት ዋናኛው መንገድ ደሞ በማንበብ ነው።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 09 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Other category.

11 656
Subscribers
-2824 hours
-537 days
-61730 days
Posts Archive
«ተመኘሁ... አገባሁ، ተመኘሁ... ወለድኩ، ነገር ግን ህይወት አልበቃ አለችኝ!»🥲 አንዲት ሴት እንዲህ አለች፦ ተመኘሁ... ማግባትን ተመኘሁ—እናም አገባሁ—ነገር ግን ቤቴ ባዶና በዝምታ የታፈነ ነበር። ስለዚህ ተመኘሁ... ልጆች መውለድን ተመኘሁ—እናም ወለድኩ። ሆኖም፣ ብዙም ሳይቆይ፣ የቤቱ ግድግዳዎች እንኳ አሰለቹኝ። ስለዚህ ተመኘሁ... ስራ ማግኘት ተመኘሁ—እናም አገኘሁ—ከዚያም የራሴ ቤት መኖር ዋናው ምኞቴ ሆነ። ከብዙ ትግል በኋላ፣ በመጨረሻ ያንን ቤት ባለቤት ሆንኩ፤ ነገር ግን ልጆቼ አድገው ነበር። ስለዚህ ተመኘሁ... ሲያገቡ ማየትን ተመኘሁ—እናም አገቡ። ነገር ግን ከስራ እና ከችግሮቹ ሰልችቶኝ ነበር፤ ስራው አድካሚ ሆኖብኝ ነበር። ስለዚህ ተመኘሁ... ጡረታ ወጥቼ እረፍት ማድረግን ተመኘሁ—እናም አደረግኩ—ነገር ግን ልክ ከትምህርት እንደተመረቅኩበት ጊዜ ሁሉ ብቻዬን ቀረሁ። ሆኖም፣ ከትምህርት ስመረቅ ህይወትን በጉጉት እጠብቅ ነበር፤ አሁን ግን ከእርሷ እየራቅኩ ነው። ግን አሁንም ምኞቶች አሉኝ... ስለዚህ ተመኘሁ... ቁርአንን በቃሌ ለመያዝ ተመኘሁ፤ ነገር ግን የማስታወስ ችሎታዬ አላገዘኝም... ስለዚህ ተመኘሁ... ለአላህ ብዬ ለመጾም ተመኘሁ፤ ነገር ግን ጤንነቴ አልፈቀደልኝም... ስለዚህ ተመኘሁ... የለሊት ሶላትን ለመስገድ ተመኘሁ፤ ነገር ግን እግሮቼ ክብደቴን መሸከም አቃታቸው... ስለዚህ፤ ህመም ከመምጣቱ በፊት የጤንነትህን፣ እርጅና ከመምጣቱ በፊት የወጣትነትህን እድል ተጠቀምበት፤ እንዲሁም ስለ ዓለማዊ ሲሳይህ (ስለ ኑሮህ) የሚኖሩህ ሀሳቦች ከመጪው ዓለም (ከአኺራ) ጉዳይ እንዳያዘናጉህ ተጠንቀቅ ​#የህይወት_ትምህርት#

ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን የወንድማችን ኡስታዝ አሕመዲን ጀበል ወላጅ እናት ወደ አኼራ ሄደዋል:: የእናታችን ስርዓተ ቀብርም ነገ ቅዳሜ ከዝሁር ሰላት ቡኃላ ሰናተል ጀናዛ ተሰግዶባቸው በኮልፌ የሙስሊሞች መካነ መቃብር የሚፈፀም ይሆናል:: አላህ ይዘንላቸው፣ ማረፊያቸውንም በጀነተል ፊርዶስ ያድርግላቸው ለኡስታዝ አህመዲን ጀበል እና ለመላው ቤተሰቦቹ አላህ ሰብሩን ይወፍቃችሁ🤲

🩶የታሪክ እዳ🩶               ✍ፀሐፊ - አል -ዓረብ ኢብን ሙሀመድ ክፍል 2⃣፡     ​የሁለቱ እጣ ፈንታ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሻገረው በአካባቢው በተደረገ አንድ ትልቅ የበጎ አድራጎት እና የማህበረሰብ ድጋፍ መድረክ ላይ ነበር። አንዋር ወጣቶችን አስተባብሮ የወላጅ አልባ ህፃናትን ሲረዳ፣ አስማእ ደግሞ ከእናቷ ጋር ሆና የምግብና የልብስ እርዳታዎችን ታዘጋጅ ነበር። በዚያ ስራ መካከል በመከባበር የተሞላ እይታ አልፎ አልፎ ይተያዩ ነበር፣ አንዋር የሷን ሃያእ፣ አስማእ ደግሞ የሱን ትህትና ከርቀት አስተዋሉ፤ በሁለቱም ልብ ውስጥ ሃላል የሆነ የጋብቻ ምኞት ተተከለ።      ​ሆኖም አንዋር ሽማግሌዎችን ወደ አስማእ አባት ቤት በላከበት ወቅት፣ ያልታሰበ ትልቅ መሰናክል ተደቀነ። የአቶ ከማል(የአስማእ አባት) ምላሽ ከባድ እና የጠነከረ ነበር—ምክንያቱም የአንዋር አባት እና አቶ ከማል ከበርካታ አመታት በፊት በንብረት እና በመሬት ወሰን ምክንያት የደረሰባቸው ጥልቅ የድሮ ቂም እና ጸብ በመካከላቸው ነበረ።      ​አቶ ከማል ፊታቸውን አኮሳትረው፡ "የዚያን ሰው ልጅ በቤቴ ደጃፍ አላሳልፍም። የቤተሰባችንን ስም ያጎደፈ፣ መብታችንን የበላ ሰው ልጅ እንዴት ተደርጎ የልጄ አጋር ይሆናል!? ይኸ ጉዳይ እዚሁ አብቅቷል" ሲሉ ጥያቄውን በፅኑ ውድቅ አደረጉት።         ​አስማእ በክፍሏ ውስጥ ሆና ይህን ሰበብ ስትሰማ ልቧ በሐዘን ተሰበረ። የወላጆቹ የድሮ ቂም በሁለቱ ንጹህ መፃኢ እድል ላይ እንደ ግድግዳ መደቀኑን ስትረዳ፣ የልቧ ትግል ጀመረ። በአንድ በኩል የወላጅ አባቷን ትእዛዝ ማክበር፣ በሌላ በኩል ደግሞ በአላህ ፍራቻ ላይ የተመሰረተው ንጹህ የሃላል ህልሟ በድሮ ቂም ምክንያት ሲመክን ማየት... የውስጥ ጦርነቷ እዚህ ላይ ተጀመረ።        ​የአቶ ከማል ውሳኔ በአካባቢው ከተሰማ በኋላ፣ በአንዋር እና በአስማእ መካከል ያለው የርቀት አጥር ይበልጥ እየጎላ መጣ። አንዋር የአባቱን የድሮ ቂም እና የቀደመ አለመግባባት በሱ ትከሻ ላይ ተጭኖ ሲመለከት፣ ልቡ በከባድ ህመም ተሞላ። ሆኖም፣ ይፋዊ በቀል ወይም የቃላት ጭቅጭቅ ውስጥ ከመግባት ይልቅ፣ ወደ ሌሊቱ ተሃጁድ ሶላቱ ተመለሰ።      ​በአንድ ወቅት ወዳጁ ፉአድ ከአንዋር ጋር በመስጂድ ውስጥ ተቀምጦ ሳለ፣ "አንዋር፣ የአቶ ከማል የቆየ ቂም ላንተ የማይገባህ በደል ነው። ሽማግሌዎችን ደግመህ አትልክም?" ሲል ጠየቀው።     ​አንዋር ረጅምና ከባድ ምሬት አውጥቶ፣ አይኖቹን ወደ መሬት ደፍቶ እንዲህ አለ፡ "ፉአድ፣ የሰው ልብ በእጁ ያለው አላህ ብቻ ነው። አቶ ከማልም ቢሆኑ የልጃቸውን መልካም እድል የሚፈልጉ አባት ናቸው። እኔ በአባቴ ስህተት ወይም በሰው ቂም ምክንያት አላህን የሚያስቆጣ አካሄድ አልከተልም። አላህ በቁርዓኑ 'ታገሱ፣ አላህ ከታጋሾች ጋር ነውና' ብሏል። የኔ ድርሻ ሰብር ማድረግና በሃላል መንገድ ላይ መፅናት ብቻ ነው።" ​በሌላ በኩል አስማእ በክፍሏ ውስጥ ሆና በከባድ የህሊና ጦርነት ውስጥ ነበረች። የወላጅ አባቷን ፍላጎት ማክበር የእስልምና ትልቅ ትእዛዝ መሆኑን ታውቃለች፤ ሆኖም አባቷ ያነሱት ምክንያት በእስልምና አስተምህሮ ፍትሃዊ እንዳልሆነ እና በወላጆች የድሮ ቂም ምክንያት ንጹህ ጥያቄን ማኮላሸት ተገቢ እንዳልሆነ ትረዳለች። እናቷ ወደ ክፍሏ ገብታ ስትሰቃይ ስታያት፣ "ልጄ... የአባትሽን ልብ ለማለስለስ ሞክሬ ነበር፣ ነገር ግን የድሮው ቁስል አልተጠገነም። አላህ ሌላ መልካም ነገር ያዘጋጅልሻል" አለቻት።      ​አስማእ በእንባ የተሞሉ አይኖቿን ወደ እናቷ አዞራ፡ "እናቴ፣ እኔ የአባቴን ትእዛዝ አልጥስም። ነገር ግን በልቤ ውስጥ ያለውን አላህ የሚያውቀውን ንጹህ አላማ በድሮ ቂም ምክንያት አለውጠውም። አላህ የፃፈልኝን ቀደር በፀጋለመቀበል ዱዓ አደርጋለሁ" አለች። ክፍል  3⃣ ይቀጥላል....

🩶የታሪክ እዳ🩶 ክፍል 2️⃣ ከምሽቱ 2:30 ...ይቀጥላል አላችሁ ወይ????
🩶የታሪክ እዳ🩶  ክፍል 2️⃣    ከምሽቱ 2:30 ...ይቀጥላል አላችሁ ወይ????

የጁመዓ ቀን ሱናወች 🧼 ገላን መታጠብ : ንጹህ ልብስ መልበስ እና ሽቶ መጠቀም። ​📖 ሱረቱል ካህፍን መቅራት: በዕለቱ ወይም በሌሊቱ አጠናቆ መቅራት። ​✨ ሶለዋት ማብዛት: በነቢዩ (ﷺ) ላይ ሶለ
የጁመዓ ቀን ሱናወች
🧼 ገላን መታጠብ : ንጹህ ልብስ መልበስ እና ሽቶ መጠቀም። ​📖 ሱረቱል ካህፍን መቅራት: በዕለቱ ወይም በሌሊቱ አጠናቆ መቅራት። ​✨ ሶለዋት ማብዛት: በነቢዩ (ﷺ) ላይ ሶለዋት ማውረድ። ​🕌 ወደ መስጊድ በማለዳ መሄድ: ኹጥባ ሳይጀመር በጊዜ መገኘት። ​👂 ኹጥባን በፅጥታ ማዳመጥ: ኢማሙ ሲናገር ጭጭ ብሎ ማዳመጥ። ​🤲 ዱዓ ማብዛት: በተለይ ከዐስር በኋላ እስከ መግሪብ ባለው ጊዜ። https://t.me/ahlu_Al_quran1

ያጀመዓ ሸር እናድርገው 👇 https://t.me/ahlu_Al_quran1

🩶የታሪክ እዳ🩶               ✍ፀሐፊ - አል -አረብ ኢብን ሙሀመድ ክፍል 1⃣፡         ​በከተማዋ ሰሜናዊ ጫፍ በሚገኘው የቁርዓን ማዕከል ውስጥ የአንዋር ድምፅ ማታ ማታ የመስጂዱን ግድግዳዎች ይሞላ ነበር። አንዋር ገና በወጣትነቱ ቁርዓንን ሙሉ በሙሉ በልቡ ያጠናቀቀ፣ በስነ-ምግባሩ እና በእፍረቱ በአካባቢው ህዝብ ዘንድ በእጅጉ የሚከበር ወጣት ነው። በቀን በትንሽ ንግዱ ደክሞ ወጥቶ የሚገባ፣ በሌሊት ደግሞ በተሃጁድ ሶላት ከአላህ ጋር የሚነጋገር፣ የዱንያ ውበት ያላታለለው ጠንካራ የኢማን ባለቤት ነበር። ሆኖም፣ በውስጡ ማንም የማያውቀው፣ ወደ አላህ ብቻ የሚያሰማው ጥልቅ የብቸኝነት እና የጽናት ትግል ነበረው።       ​በሌላ በኩል፣ በውበትና በስነ-ስርዓቷ የምትታወቀው አስማእ በቤቷ ቅጥር ግቢ ውስጥ የራሷ የሆነ እውነተኛ የመንፈስ አለም ነበራት። አስማእ የእስልምናን እውቀት በጥበብ የምትሰበስብ፣ በእፍረቷ የተሸፈነች፣ እንድሁም በፅናት የተሞላች ሴት ናት። አባቷ አቶ ከማል በአካባቢው ትልቅ ግምትና ተሰሚነት ያላቸው አባት በመሆናቸው፣ አስማእ ያደገችው በጥብቅ ሃይማኖታዊ ስነ-ስርዓት እና በቤተሰብ ክብካቤ ውስጥ ነበር። በልቧ ውስጥ የአላህን ፍራቻ ያነገሰችው አስማእ፣ ህይወቷን ሙሉ በሙሉ ለዲኗ እና ለቤተሰቧ ታዛዥ በማድረግ ታሳልፍ ነበር።       ​እነዚህ ሁለት የተለያዩ አለማት ውስጥ የሚኖሩ ነፍሳት፣ ሳያውቁት በመንፈሳዊ ጥንካሬያቸው እና በአላህ ፍራቻቸው አየር ላይ ሳይቀር የተሳሰሩ ይመስሉ ነበር። ሳይተያዩ እና ሳይነጋገሩ፣ ሁለቱም በየራሳቸው አቅጣጫ ከአላህ ዘንድ መልካም እና ሃላል የሆነን የህይወት አጋር በዱዓቸው ይለምኑ ነበር። ክፍል  2⃣  ይቀጥላል....

🩶የታሪክ እዳ🩶 ክፍል 1⃣ ዛሬ ከምሽቱ 2:30 ... ይጀመራል።
🩶የታሪክ እዳ🩶  ክፍል 1⃣  ዛሬ  ከምሽቱ 2:30 ... ይጀመራል።

🩶የታሪክ እዳ🩶 ክፍል 1⃣ ዛሬ ከምሽቱ 2:30 ... ይጀመራል።
🩶የታሪክ እዳ🩶 ክፍል 1⃣ ዛሬ ከምሽቱ 2:30 ... ይጀመራል።

ወንዶች ቢያንስ ላለመመታት sport ስሩ 😁
ወንዶች ቢያንስ ላለመመታት sport ስሩ 😁

📖 የቁርኣን ብርሃን ወደ ቤትዎ! 📖 ​ቁርኣን መቅራትና፣ ማስተካከል ይፈልጋሉ? እንግዲያውስ ይህ ዕድል እንዳያመልጥዎ! ​ልዩ የቁርኣን መቅሪያ የቴሌግራም ግሩፕ ተዘጋጅቶ ይጠብቅዎታል። ወደ ግሩፑ በመቀላቀል የቁርኣን ጉዞዎን ዛሬውኑ ይጀምሩ! ​👉 አሁኑኑ ሊንኩን ተጭነው ይቀላቀሉ፡ https://t.me/Ahlul_Quran_2

🖤የታሪክ እዳ 🖤 ክፍል 1 ከምሽቱ 2:30... ይለቀቃል።
🖤የታሪክ እዳ 🖤 ክፍል 1 ከምሽቱ 2:30... ይለቀቃል።

“ከርሱ ጋር ለስራ በደረሰ ጊዜም “ልጄ ሆይ! እኔ በህልሜ የማርድህ ሆኜ አይቻለሁ፤ (እስቲ አንተም ነገሩን) ተመልከት፡፡ “ምን ይታይሃል” አለው፡፡ (ልጁም) አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ፈጽም፤ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ አለ" እንደዚህ የተባባሉት ማን እና ማን ናቸው?

📖 የቁርኣን ብርሃን ወደ ቤትዎ! 📖 ​ቁርኣን መቅራትና፣ ማስተካከል ይፈልጋሉ? እንግዲያውስ ይህ ዕድል እንዳያመልጥዎ! ​ልዩ የቁርኣን መቅሪያ የቴሌግራም ግሩፕ ተዘጋጅቶ ይጠብቅዎታል። ወደ ግሩፑ በመቀላቀል የቁርኣን ጉዞዎን ዛሬውኑ ይጀምሩ! ​👉 አሁኑኑ ሊንኩን ተጭነው ይቀላቀሉ፡ https://t.me/Ahlul_Quran_2

📌ቁርአን ሸር ያልተደረገ ምን ሸር ይደረጋል ያጀመዓ??   📢 ቻናላችንን ይቀላቀሉ፡- Telegram👉 🔗 https://t.me/ahlu_Al_quran1 Tiktok 👉 tiktok.com/@ahlul_quran_official

አላህ ያሰባችሁትን ያሳካላችሁ! ከጭንቀት ይገላግላችሁ!

ለሌሎችም እናጋራ ያጀመዓ👇 https://t.me/ahlu_Al_quran1

አንድ ሷሊሕ ሰዉ እንዲህ ይላሉ:- «የሰዎች ነገር እጅግ በጣም ይገርማል። ከአካል ሞት ይልቅ የቀልብ ሞት የጠና/የከፋ ሆኖ ሳለ፧ አካሉ ለሞተ ሰዉ ሲያለቅሱ ልቡ ለሞተ (ለጨለመ) ግን አያለቅሱም።» ያ አላህ ከልብ ድርቅና ጠብቀን፤ አንተን አብዝተን እንድናወሳ ወፍቀን። اللهم أحيي قلوبنا وارزقنا الثبات على طاعتك       

ልባችንን በቁርአን እናርጥብ