𝐉𝐨𝐮𝐫𝐧𝐞𝐲 𝐓𝐨 𝐈𝐬𝐥𝐚𝐦🪸
#ሚዛናዊነት_እና_ሁለንተናዊነት #ህልም_ትጋት_ስኬት اقْرَأْ بِاسْمِ رَبِّكَ الَّذِي خَلَقَ አንብብ በዚያ (ሁሉን) በፈጠረው ጌታህ ስም ትውልድ ሚገነባው በእውቀት ነው። እውቀትን ምናገኝበት ዋናኛው መንገድ ደሞ በማንበብ ነው።
Show more📈 Analytical overview of Telegram channel 𝐉𝐨𝐮𝐫𝐧𝐞𝐲 𝐓𝐨 𝐈𝐬𝐥𝐚𝐦🪸
Channel 𝐉𝐨𝐮𝐫𝐧𝐞𝐲 𝐓𝐨 𝐈𝐬𝐥𝐚𝐦🪸 (@ahlu_al_quran1) is an active participant. Currently, the community unites 11 659 subscribers, ranking in the Other category.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 11 659 subscribers.
According to the latest data from 07 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -620 over the last 30 days and by -16 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 7.11%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 3.65% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 831 views. Within the first day, a publication typically gains 426 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 12.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“#ሚዛናዊነት_እና_ሁለንተናዊነት
#ህልም_ትጋት_ስኬት
اقْرَأْ بِاسْمِ رَبِّكَ الَّذِي خَلَقَ
አንብብ በዚያ (ሁሉን) በፈጠረው ጌታህ ስም
ትውልድ ሚገነባው በእውቀት ነው።
እውቀትን ምናገኝበት ዋናኛው መንገድ ደሞ በማንበብ ነው።”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 08 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Other category.
Data loading in progress...
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 08 September | 0 | |||
| 07 September | 0 | |||
| 06 September | 0 | |||
| 05 September | 0 | |||
| 04 September | +9 | |||
| 03 September | +59 | |||
| 02 September | 0 | |||
| 01 September | 0 |
| 2 | ይህ ሰው መጥፎ ሰው ነው…‼
~
📌ታላቁ ዓሊም ኢማም አህመድ ኢብኑ ሀንበል፤ ስለ ዊትር ሶላት ክብደት ሲናገሩ የተናገሩት ንግግር ልብን በድንጋጤ የሚሞላ፣ የሰውነትን ፀጉር የሚያቆም ነው። እንዲህ አሉ፡-
📚قال الإمام أحمد: « من ترك الوتر عمدا فهو رجل سوء ولا ينبغي أن تقبل له شهادة»
«ዊትርን ሆን ብሎ የተወ ሰው፤ እርሱ መጥፎ ሰው ነው። ምስክርነቱም ሊቀበል አይገባም!»
ይህ ንግግር ዝም ብሎ የተወረወረ አይደለም! እስቲ ቆም ብለን እናስተውል። ዊትር እንደ አምስቱ ወቅት ሶላቶች ግዴታ አይደለም፤ ጠንካራ ሱና እንጂ። ነገር ግን ኢማሙ አህመድ ይህንን ሱና ያጓደለን ሰው "መጥፎ ሰው" ብለው ፈረጁት። በሸሪዓው ፍርድ ቤት ቀርቦ ጉዳይ ቢያስፈጽም እንኳ "ምስክርነቱ ተቀባይነት የለውም" በማለት የሰውየውን ታማኝነት አጠራጣሪ አደረጉት። ለምን?
ምክንያቱም ዊትር የቀንህ መዝጊያ፣ የሌሊትህ ብርሃን፣ ከጌታህ ጋር ያለህ ትስስር ማጠንከሪያ ገመድ ነው። ይህንን ብርሃን ሆን ብሎ ያጠፋ ሰው፤ የልቡ መድረቅ ምልክት ነውና።
ጉዳዩ የደቂቃዎች ነው። ቢደክምህ እንኳ አንድ ረከዓም ቢሆን ከሰገድክ ዊትርን አገኝተሃል። አንድ ረካዓ! አንዲት ረካዓ ብቻ እኮ ናት። ግን ክብደቷ ሚዛን ይደፋል። ይህቺን አጭር ሶላት ለመስገድ የሰነፈ ሰው፣ እንዴት ታላቅ አማኝ ተብሎ ይመሰክርለታል? እንዴትስ ታማኝነቱ ይረጋገጣል? ከፈጣሪው ጋር ያለውን ቀጠሮ ያቃለለ ሰው፣ ከሰዎች ጋር ባለው ጉዳይ እንዴት ይታመናል? የኢማሙ አህመድ ንግግር ሚስጥር ይሄው ነው።
መጥፎ ሰው ከመሆን አላህ ይጠብቀን። አላህ ያግራልን!
https://t.me/ahlu_Al_quran1 | 259 |
| 3 | የተውበት መስፈርቶች
በህይወታችን ብዙ ጊዜ ወንጀሎችን እንፈፅማለን። አላህ ያደለው በወንጀሉ አላህ ፊት እንዳይጠየቅ ተውበት ማድረግን ያስባል። ግን ስንቱ ነው ተውበቱ መስፈርቶችን የሚያሟላ እንዲሆን የሚጨነቀው? እራሳችንን በሚገባ ጠይቀን እናውቃለን?! ለመሆኑ መስፈርቶቹን ምን ያህሎቻችን በሚገባ እንለያቸዋለን? ለማያውቁ ጥቆማ፣ ለሚያውቁ ማስታወሻ ይሆን ዘንድ እጠቅሳለሁ። የተውበት መስፈርቶች ስድስት ናቸው። እነሱም:–
① ኢኽላስ: – አላህን ብቻ በማሰብ ሊፈፀም ነው። አንድ ሰው ወንጀልን የሚቶወው ዱንያዊ ጥቅሞችን አስቦ ከሆነ የመጀመሪያውን የተውበት መስፈርት ዘንግቷል።
② ወንጀሉን ማቆም:– አንድ ሰው የሚፈፅመውን ወንጀል ባላቋረጠበት ሁኔታ "ቶብቻለሁ" ቢል ቀልድ ነው የሚሆነው። ስለዚህ ተውበት ያሰበ ሰው ጥፋቱን በቀጠሮ ሳይሆን ቀጥታ ሊያቆም ይገባል።
③ ወደ ጥፋቱ ዳግም ላይመለሱ ቁርጠኛ ውሳኔ ላይ መድረስ። አንድ ሰው ከወር ቡሀላ እንደሚመለስ እያሰበ ረመዳን ሊገባ ሲል አንድን ወንጀል ቢተው መስፈርት ስላላሟላ ተውበት አድርጓል ማለት አይቻልም።
④ በወንጀሉ መፀፀት። ሰውየው ሲፈፅመው በቆየው ወንጀል ላይ ደንታ ቢስ ከሆነ ተውበቱ የሐቂቃ አይደለም። ፀፀቱ "ሰው ምን ይለኛል" ወይም "ክብሬ ጎደፈ" በሚል ሳይሆን የጌታውን ህግ በመጣሱ ሊሆን ይገባል። ለምሳሌ ብዙ ሰዎች ዝሙት ፈፅመው ጌታቸው ዘንድ ካለው ሂሳብ ይልቅ ዱንያ ላይ ያለው የሰው ወሬ ሲያስጨንቃቸው ይፀፀታሉ። እንዲህ አይነት ፀፀት የተውበትን መስፈርት አያሟላም። ይልቅ ከዛሬው የበዛ ህዝብ ፊት ነገ በአኺራ መዋረድ ከመምጣቱ በፊት ትክክለኛውን ፀፀት እዚሁ ልናስገኝ ይገባል።
⑤ ተውበቱ ወቅቱን የጠበቀ መሆን። ይህም ሞት አፋፍ ላይ ከመድረሱ በፊት እና ፀሀይ በመጥለቂያዋ ከመውጣቷ በፊት መሆኑ ነው።
⑥ ወንጀሉ የሰው ሐቅ መግፋት ከሆነ ሐቁን ሊመልስ ወይም ይቅርታውን ሊያገኝ ይገባል።
https://t.me/ahlu_Al_quran1 | 42 |
| 4 | 🩶የታሪክ እዳ🩶 ክፍል 6️⃣ ከምሽቱ 2:30 ...ይቀጥላል
አላችሁ ወይ???? | 276 |
| 5 | 📖 የቁርኣን ብርሃን ወደ ቤትዎ! 📖
ቁርኣን መቅራትና፣ ማስተካከል ይፈልጋሉ? እንግዲያውስ ይህ ዕድል እንዳያመልጥዎ!
ልዩ የቁርኣን መቅሪያ የቴሌግራም ግሩፕ ተዘጋጅቶ ይጠብቅዎታል። ወደ ግሩፑ በመቀላቀል የቁርኣን ጉዞዎን ዛሬውኑ ይጀምሩ!
👉 አሁኑኑ ሊንኩን ተጭነው ይቀላቀሉ፡
https://t.me/Ahlul_Quran_2 | 296 |
| 6 | 🩶የታሪክ እዳ🩶
✍ፀሐፊ - አል -ዓረብ ኢብን ሙሀመድ
ክፍል 5⃣፡
ከጥቂት ቀናት በኋላ የአንዋር ንጹህነት ተረጋገጠ፤ ሰኢድ ያዘጋጀው የሀሰት ማስረጃ ተቃውሞ ገጥሞት አንዋር ከእስር ተፈታ። ሆኖም፣ ይህ ክስተት በአንዋር እና በአስማእ መካከል ያለውን አጥር አላፈረሰውም። ይልቁንም፣ የሁለቱ መንገድ ይበልጥ የተራራቀ እና ውስብስብ ወደሆነ አዙሪት ውስጥ ገባ።
አንዋር ከእስር ከተፈታ በኋላ፣ በሰፈሩ ውስጥ የነበረውን አየር እና የአስማእ አባት አሁንም በውስጣቸው የሚመላለሰውን የቆየ የቤተሰብ ኩራት ተመለከተ። አባቷ አቶ ከማል ከህመማቸው ቢሻሉም፣ በአካባቢው ህዝብ ፊት የነበራቸው ትዕቢትና የቀደመው የቂም ጥላ ሙሉ በሙሉ አልተወገደም ነበር። አንዋርም ቢሆን፣ የአስማእ አባት ሙሉ በሙሉ ሳይወዱና ሳይፈቅዱ፣ ወይም በአስገዳጅ ሁኔታ ውስጥ ሆነው ልጃቸውን እንዲሰጡት አልፈለገም።
"እኔ የሷን እጅ የምፈልገው በአላህ ወገንተኝነት፣ በደስታና በሃላል መንገድ ነው" አለ አንዋር ለወዳጁ ፉአድ። "በአባቷ ድካም ወይም በችገራቸው አጋጣሚ ተጠቅሜ እሷን ማግኘት አልፈልግም። አላህ ካልፃፈው፣ የሰው ልጅ ጥረት ብቻውን አያገናኘንም።"
በዚያው ሳምንት አንዋር አንድ ከባድ ውሳኔ ወሰነ። በከተማው ውስጥ ያለው ውጥረት እና የመንፈስ እወካ ከዲን ትምህርቱ እና ከልቡ እረፍት እያራቀው ስለመጣ፣ ለአንድ አመት ያህል ወደ ሌላ ሩቅ ክፍለ ሀገር ሄዶ የቁርዓን ትምህርቱን ይበልጥ ለማጥናት እና ንግዱን ለማስፋፋት አቀደ።
ዜናው ወደ አስማእ ዘንድ ሲደርስ፣ ልቧ በከባድ ድንጋጤ ተመታ። አንዋር ከአካባቢው ሊርቅ እንደሆነ ስታውቅ፣ ህይወቷ ሙሉ በሙሉ የጨለመ ያህል ተሰማት። ነገር ግን፣ በአላህ ቀደር ላይ ያላትን ጥልቅ እምነት አጥብቃ ያዘች።
አንዋር ከመነሳቱ በፊት በመስጂዱ በር ላይ ቆሞ ወደ አስማእ ቤት አቅጣጫ ለረጅም ጊዜ ተመለከተ—ምንም አይነት ስሜታዊ ቃል ሳይለዋወጡ፣ ሳያዩት እና ሳታየው፣ ሁለቱም ልቦች ግን በአንድ አላህ ፊት በእምነትና በሰብር ታስረው ነበር።
አንዋር ረጅም መንገድ ለመጓዝ ተነሳ፤ አስማእ ደግሞ በቤቷ ውስጥ ሆና የቀናትና የወራት ፈተናዎችን ለመጋፈጥ ተዘጋጀች...
አንዋር ከተማዋን ትቶ ወደ ደቡባዊው የሀገሪቱ ክፍል ከተጓዘ ወራት ተቆጠሩ። አዲሱ አካባቢ አረንጓዴማና ጸጥታ የሰፈነበት ቢሆንም፣ በልቡ ውስጥ ያለው የመንፈስ ትግል ግን አልቆመም። በቀን በዚያ ከሚገኙ ታላላቅ ኡለማዎች ዘንድ የቁርዓንና የሐዲስ ትምህርቱን ይከታተላል፤ ማታ ማታ ደግሞ በትንሿ ክፍሉ ውስጥ ለብቻው ሆኖ በተሃጁድ ሶላት ይቆማል።
ርቀት የስሜት መጥፋትን ሳይሆን፣ የእውነተኛ ፍቅርንና የኢማንን ጥንካሬ የሚያረጋግጥ ማጣሪያ ሆነበት። አንዋር አስማእን የሚያስባት እንደ ዱንያ ምኞት ሳይሆን፣ ወደ አላህ የሚያቀርበው የመንፈስ አደራ አድርጎ ነበር።
በአንድ አርብ ምሽት፣ ከአስታዋሽ ኡስታዙ ጋር ተቀምጦ ሳለ፣ ኡስታዙ የአንዋርን የፊት መለወጥ አስተውለው እንዲህ አሉት፡ "አንዋር ልጄ... በልብህ ውስጥ ትልቅ ፈተና እንዳለ እመለከታለሁ። ነገር ግን እወቅ፤ አላህ አንድን ነገር ካራቀብህ፣ ልብህ ወደ እሱ ብቻ እንዲጠጋ ስላሰበ ነው። የሰው ልጅ የሚፈልገውን ነገር ከአላህ ፍላጎት አስቀድሞ ሲመኝ ይፈተናል።"
አንዋር እንባውን እየተቆጣጠረ፡ "ኡስታዜ... እኔ የምፈራው አላህ በፃፈልኝ ቀደር ላይ ልቤ እንዳያመፅ ነው። በሩቅ ሆኜ ለሷ የማደርገው ዱዓ ይበልጥ ወደ አላህ የሚያቀርበኝ ከሆነ፣ ይህ ርቀት ለኔ ራህመት ነው" ሲል መለሰ።
በሌላ በኩል አስማእ በቤቷ ውስጥ የምታሳልፈው ጊዜ በስውር ህመም የተሞላ ነበር። የአንዋር ከአካባቢው መራቅ በሰፈሩ ውስጥ ያለውን ወሬ ቢያስቆመውም፣ በቤቷ ውስጥ ግን ትልቅ ባዶነት ፈጥሮ ነበር። አስማእ በየቀኑ ቁርዓን ስታቀራ፣ ድምጿ ውስጥ ያለው ጥልቅ ሀዘንና ጽናት እናቷን ሳይቀር ያሳስባት ነበር።
እናቷ በአንድ ወቅት ወደ ክፍሏ ገብታ፡ "ልጄ... እስከ መቼ ነው በዚህ ሁኔታ ውስጥ የምትኖሪው? እሱ እኮ ርቆ ሄዷል፤ " አለቻት።
አስማእ በብስለትና በረጋ ድምፅ፡ "እናቴ፣ እኔ ሰብር እያደረግኩ ያለሁት ለአንድ ሰው ብዬ አይደለም። አላህ ለኔ የፃፈልኝን ቀን እየጠበቅኩ ነው። አላህ የዘጋውን በር በሰው ሀይል መክፈት አይቻልም፤ እሱ የከፈተውን ደግሞ ማንም ሊዘጋው አይችልም" አለች።
ክፍል 6⃣ ይቀጥላል.... | 520 |
| 7 | 🩶የታሪክ እዳ🩶 ክፍል 4⃣ ከምሽቱ 2:30 ...ይቀጥላል
አላችሁ ወይ???? | 470 |
| 8 | ያጀመዓ ሸር እናድርገው 👇
https://t.me/ahlu_Al_quran1 | 463 |
| 9 | ሳተነቡ አትለፋት 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
😭😭
♥አንዴ አንድ ሠው ወደ ነብዩ (ሶለሏሁ አለይሂ ወሰለም)ዘንድ ይሔድና መሥጅዳቸው አጠገብ ይቆማል፡ነብዩም (ሶለሏሁ አለይሂ ወሰለም) ሠግደው ሢወጡ አዩት ከዛ አንተ ወጣት ምነው? ለምን ቆምክ ?ብለው ጠየቁት፡፡✍✍እሱም የአላህ መልክተኛ የአላህ ሠላም ባንተ ላይ ይሁን አላቸው እሳቸውም ባንተም አሉት፡፡ከዛ ይህ ወጣት የቆመበትን
ችግር ይነግራቸው ጀመር፡፡አላቸው እናቴ በጣም ትወደኝ ነበር በጣም ከመውደዷ የተነሣ የማገባት ሤት እሷ መረጠችልኝ ፤ሚሥት ባገባሁ በሁለተኛ አመት ከባለቤቴ አልተሥማሙም ይጣላሉ እኔ እናቴን እቆጣት ጀመር የመጀመሪያ ልጄና ሚሥቴ ይዜ ከእናቴ ራቅ ወዳለ ስፍራ ሔድኩ በእናቴ ተናደድኩ ላያት አሥጠላችኝ እሧ ላላይ ወሠንኩ ከተወሰነ ጊዜ በሗላ ልጄ ሞተ ባለቤቴ እናትህ ነች ልጄ የገደለችብኝ ትለኛለች እኔም
እውነት ሖኖ ታየኝ እናቴ የባሠ ጠላሗት 😭😭😭😭😭በመንገዴ እንዳላያት ነገርኳት አሥፈራራሗት ከጊዜ በሗላ ነገር ግን እናቴ በድንገት በጣም ታመመች ልጠይቃት ብመጣ እንዳላያት ተከለከልኩ እናቴ ጣረሞት ይዟት እንኳ ልጄ ትላለች እኔ ግን ..😭😰😰😰😰.....♥የአላህ መልክተኛ (ሶለሏሁ አለይሂ ወሰለም)አለቀሱ 😢😢😢😢 እያለቀሱም ይሰሙታል ሚስቴ ጥላኝ ሔደች አላቸው፡፡ እሱም ያለቅስ ጀመር በል ዝምበል አሉት መላክተኛው ንግግሩ አቋርጠው
😭አሁን እናት አለች ወይስ ሞተቸ? አሉት እሱም ሞተች አላቸው ወየውልህ አሉት ላንተ የተቀጣጠለች እሳት አንዷ ፍም የዱንያ ውሐ ሑሉ አያጠፋውም አሉት እሱም ከዚህ ቅጣት መዳኛ መንገት ጠየቃቸው! እሳቸውም እናትህ ቀስቅሳትና አፉ ትበልህ አሉት 🌺ያ አላህ ውድ ወንድሞችና እህቶቼ ሠው ከሞተ በሗላ ማነው ሚቀሰቅሰው? ???
☑️ታድያ እናታች ሣትለየን ካሁኑኑ ለምን አፉታ አንጠይቃትም &?ለምን አናሥደሥታትም
👉የሥንቶቻችን እናት በኛ ታዝናለች ራሣች እንጠይቅ♥ አላህ ሕደያው ይስጠን፡፡
✅✅ይህ ወጣት እናቱ አፉ እስካላለችው ድረስ ጀነት ይቅርና የቀብር ሠላም አያገኝም አሉ፡፡
❤️❤️እናታች አላህ እረጅም እድሜ ይስጣት
እኛም የናታችን ፍቅር ይስጠን
የሞቱትንም አላህ ይማራቸዉ 🤲🤲🤲
"ወደ መልካም ነገር ያመላከተ ሰው የሰራ ሰውን አጅር ያህል ያገኛል" ረሱል (ﷺ)
ያጀመዓ ሸር እናድርገው 👇
https://t.me/ahlu_Al_quran1
| 613 |
| 10 | 🔔ያ ጀምአ ነገ ሰኞ ነው💭💭
የቻለ ይፁም ያልቻለ 🔸
ጨርሱት ✍ | 208 |
| 11 | 📚👉 ለማዘዝና ዋጋ ለማወቅ ከታች ባለው አድራሻ ያናግሩን።
ለማዘዝ👇
t.me/Fatumma_123
👉የዋሳፕና የመስመር ቁጥር
0536504651
📖ሁሉም የሳኡዲ ከተሞች እናደርሳለን | 224 |
| 12 | 📚👉 ለማዘዝና ዋጋ ለማወቅ ከታች ባለው አድራሻ ያናግሩን።
ለማዘዝ👇
t.me/Fatumma_123
👉የዋሳፕና የመስመር ቁጥር
0536504651
📖ሁሉም የሳኡዲ ከተሞች እናደርሳለን | 98 |
| 13 | 🩶የታሪክ እዳ🩶
✍ፀሐፊ - አል -ዓረብ ኢብን ሙሀመድ
ክፍል 4⃣፡
ከዚያ ክስተት በኋላ አቶ ከማል በከፍተኛ የህሊና ውጥረት እና ህመም ውስጥ ወደቁ። በሰፈሩ እና በዘመድ አዝማድ ፊት ያዩትን እፍረት ማሰቡ ጤናቸውን አበላሸው፤ ቀናት ሳያልፉም በቤት ውስጥ በፅኑ ታመው አልጋ ላይ ወደቁ።
በእነዚያ አስቸጋሪ ቀናት ውስጥ የአስማእ ቤተሰብ ድጋፍ የሚያስፈልገው ነበር። ሰኢድ የተባለው ሰው የተጋለጠበትን እፍረት ለመበቀል በአቶ ከማል ንግድ እና ስም ላይ የተለያዩ መሰናክሎችን መፍጠር ጀመረ። የሰፈሩ ሰው በሙሉ ከአባቷ ርቆ በቆመበት በዚያ ጨለማ ጊዜ፣ አንድ ያልተጠበቀ እጅ ከጀርባ ሆኖ ይደግፋቸው ነበር።አንዋር!።
አንዋር በምስጢር፣ አባቱ እንዳያውቁ እና የአቶ ከማል ክብር እንዳይነካ በማድረግ፣ የቤተሰቡን አስፈላጊ የቤት ውስጥ ፍላጎቶች እና የህክምና ወጪዎች በታማኝ ወዳጁ በፉአድ በኩል ያደርስ ነበር። አንዋር ይህን ያደረገው ከአስማእ አባት ምስጋና ፈልጎ ወይም የድሮውን ቂም ለማብረድ ሳይሆን፣ ለአላህ ብሎ እና የአንድን ሙስሊም አባት ክብር ለማስጠበቅ ነበር።
አስማእ አባቷን እያስታመመች ሳለች፣ የምታገኛቸው እርዳታዎች እና ድጋፎች ከየት እንደሚመጡ መጠራጠር ጀመረች። ፉአድ ወደ ቤታቸው ይመላለስ የነበረ ቢሆንም፣ ከጀርባው ያለው እውነተኛ ሰው ማን እንደሆነ በግልጽ አልተናገረም ነበር።
በአንድ እሁድ ምሽት፣ አቶ ከማል ከህመማቸው በትንሹ ተሻሽለው ከተቀመጡበት፣ ወደ አስማእ ተመልከተው በእንባ የተሞላ ድምጻቸው፡ "ልጄ... እኔ በኩራትና በድሮ ቂም ታውሬ ህይወትሽን ልበታትን ነበር። አላህ ግን እውነተኛውን ሰው እና አታላዩን አሳየኝ" አሏት።
በዚያው ምሽት ግን፣ ሰኢድ በበቀል ስሜት ተሞልቶ በአንዋር ንግድ እና ስም ላይ ትልቅ የሃሰት ውንጀላ በማዘጋጀት ለፖሊስ አቤቱታ አቀረበ...
ሰኢድ ያዘጋጀው የሀሰት ውንጀላ በአካባቢው ሲወራ፣ የአንዋር ስም ለመጀመሪያ ጊዜ በጥያቄ ምልክት ውስጥ ገባ። በአንዋር ትንሽ ንግድ ቤት ውስጥ የሃራም ንብረትና የተከለከሉ እቃዎች ተገኝተዋል የሚል ወሬ በሰፈሩ ህዝብ ዘንድ በፍጥነት ተሰራጨ።
በዚያች ምሽት አንዋር በፖሊስ ጣቢያ ቅጥር ግቢ ውስጥ በብቸኝነት ተቀምጦ ሳለ፣ ልቡ ከሳሾቹ ላይ የጥላቻ ስሜት አልያዘም። ይልቁንም፣ አላህ የፈተነበትን መንገድ እያሰበ በሱጁድ ላይ ሆኖ ለረጅም ጊዜ አለቀሰ።
"ያ ረብ..." አለ አንዋር ድምፁ በቅሬታ ሳይሆን በስግደት እየተንቀጠቀጠ፣ "ይህ የኔን ስም ለማደፍረስ የተደረገ ሴራ ቢሆንም፣ ባንተ ዘንድ ያለው እውነታ አይቀየርም። ልቤን ከበቀልና ከቁጣ ጠብቅልኝ፤ ይህን ፈተና ደግሞ ወደ አንተ የምቀርብበት ሰበብ አድርግልኝ።"
በሌላ በኩል አስማእ የአንዋርን መታሰር ስትሰማ፣ በክፍሏ ውስጥ ያለው አየር ሁሉ የጠበበባት ያህል ተሰማት። አንዋር ለእሷ አባት ያደረገውን ምስጢራዊ ድጋፍ ከፉአድ አንደበት በከፊል ተረድታ ስለነበር፣ የሱ ንጹህነት በእሷ ልብ ውስጥ ከማንም በላይ ግልጽ ነበር።
አስማእ በዚያች ምሽት ለተሃጁድ ሶላት ስትቆም፣ በህይወቷ ውስጥ አይታው የማታውቀውን ጥልቅ የልብ ትግል አስተናገደች። በአንድ በኩል ለንጹሁ ወጣት የሚሰማት ጥልቅ መከባበርና የሃላል ፍቅር፣ በሌላ በኩል ደግሞ ከቤቷ ሳትወጣ፣ ከእሱ ጋር ሳትነጋገር፣ ጉዳዩን ሙሉ በሙሉ ወደ መለኮታዊው ዳኛ የማቅረብ ግዴታ ነበረባት።
እሷ የምታውቀው አንድ ትልቅ እውነት ነበር፡ እውነተኛ ፍቅር በእጅ በመጨባበጥ ወይም በንግግር ሳይሆን፣ በሌሊት ሶላት ላይ ለአንድ ሰው በምስጢር በሚደረግ ዱዓ ነው የሚገለጸው።
ከ 50 ❤ በኋላ ...
ክፍል 5⃣ ይቀጥላል.... | 622 |
| 14 | 🩶የታሪክ እዳ🩶 ክፍል 3️⃣ ከምሽቱ 2:30 ...ይቀጥላል
አላችሁ ወይ???? | 533 |
| 15 | #የነቢዩ ﷺ ፍቅር 💔🥺
አንድ ወጣት ከመስጂደ ነበዊ አጠገብ በፖሊሶች ተያዘ፡ ምንም ሳይናገር እጆቹን ወደ ኋላ በካቴና አሰሩት
#ወጣቱም እያለቀሰ፦
«ምን አድርጌ ነው? ሌባ አይደለሁም፡ ወንጀለኛም አይደለሁም… ለምን ትወስዱኛላችሁ?» አለ፡፡
አንድ አዛውንትም ሁኔታውን በሩቅ ይከታተሉ ነበርና ወደ ፖሊሶቹ ጠግተው፦
«ልጅየውን አውቀዋለሁ፡ ሁልጊዜ በነቢዩ ﷺ ረውዳ ፊት ለፊት ተቀምጦ እያለቀሰ ዱአ ሲያደርግ እየዋለሁ፡ ምን አድርጎ ነው የምትወስዱት?» ሲሉ ጠየቁ፡፡
ፖሊሶቹም፦ «አልፎበታል፤ ከአልጄሪያ የመጣ ሰው ነው፡፡ ለ6 ዓመታት ህጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ ሳይኖረው መዲና ውስጥ ኖሯል፡፡ ወደ ሀገሩ ለመመለስ ብዙ ጊዜ ሞክረናል፤ ግን ሁልጊዜ አምልጦ እንደገና ከመስጂደ ነበዊ እናገኘዋለን» አሉ።
#ወጣቱም እንባውን እያፈሰሰ፦
«ልሰርቅም፤ አልዘረፍኩም፤ ማንንም አልጎዳሁም፡፡ እዚህ የመጣሁት የአላህን መልእክተኛ ﷺ ሰላምልል ብቻ ነው፡፡ ከዚህ ከተማ መለያየት አልፈልግም» አለ፡፡
ከዚያም ከመስጂደ ነበዊ እያወጡት ሳለ፤ ወደ አረንጓዴው ጉልላት (ቁብተል ኸደራ) እየተመለከተ ልብ በሚሰብር ንግግር ተናገረ፦
«#ያ ረሱለላህ ﷺ! በመካከላችን የነበረው ቃል እንዲህ ነበረን?!
ንገሩኝ፤ ቤተሰቦቼን ወላጆቼን ትቼ ጎረቤት ሆነኝ ለመኖር መጣሁ… አሁን ግን እንደፊቴ አልፈቀዱልኝም!» 😭💔
ይህን እንደተናገረ መሬት ላይ ወደቀ። መጀመሪያ ፖሊሶቹ ለማምለጥ የተጠቀመው ዘዴ መስሏቸው ነበር፤ ነገር ግን ውሃ ፊቱ ላይ ቢያፈሱበትም ቢያንቀሳቅሱት ምንም መልስ አልሰጠም።
አምቡላንስ ተጠርቶ ወደ ሆስፒታል ተወሰደ። ሕክምናው ከተመረመረ በኋላ፦
ከአንድ ሰዓት ተኩል ገደማ በፊት ሕይወቱ እንዳለፈ ነገሯቸው
ፖሊሶቹም አይናቸው በእንባ ተሞልቶ፦
«በአላህ እንምላለን ገደባችንን እየተወጣን ሳለ በርግጥ የዚህህ ሰው ለነቢዩ ﷺ የነበረውን ጥልቅ ፍቅር አላወቅንም ነበር» አሉ።
ከዚያም ታጠበ፤ የጀናዛ ሶላት ተሰገደበት ወደ ሰማይ የተቀበሩበት በቀዕ መቃብር ተወሰደ ተቀበረ።
💗 ወደ አልጄሪያ ይመለሳል ተብሎ የተያዘው ወጣት፣ መጨረሻው ወደ በቀዕ ሆነ ። | 592 |
| 16 | 📖 የቁርኣን ብርሃን ወደ ቤትዎ! 📖
ቁርኣን መቅራትና፣ ማስተካከል ይፈልጋሉ? እንግዲያውስ ይህ ዕድል እንዳያመልጥዎ!
ልዩ የቁርኣን መቅሪያ የቴሌግራም ግሩፕ ተዘጋጅቶ ይጠብቅዎታል። ወደ ግሩፑ በመቀላቀል የቁርኣን ጉዞዎን ዛሬውኑ ይጀምሩ!
👉 አሁኑኑ ሊንኩን ተጭነው ይቀላቀሉ፡
https://t.me/Ahlul_Quran_2 | 635 |
| 17 | 🩶የታሪክ እዳ🩶
✍ፀሐፊ - አል -ዓረብ ኢብን ሙሀመድ
ክፍል 3⃣፡
ወራት አለፉ። የአቶ ከማል ቂም ሳይበረዝ፣ ለልጃቸው አስማእ ሌላ የጋብቻ ጥያቄ መጣ። እጩው ከሌላ ከተማ የመጣ፣ ሀብታምና በንግዱ አለም ታዋቂ የሆነው ሰኢድ ነበር። ሰኢድ በአካባቢው ሃብቱና ተፅዕኖው የሚታወቅ ቢሆንም፣ በዲን ጥንካሬውና በስነ-ምግባሩ ግን ከአንዋር ጋር የሚነጻጸር አልነበረም።
አቶ ከማል የሰኢድን ጥያቄ በፍጥነት ተቀበሉት። የድሮውን ቂም ለመበቀል እና የቤተሰባቸውን ስም ይበልጥ ከፍ ለማድረግ ይህንን ጋብቻ እንደ ትልቅ አጋጣሚ ቆጠሩት። ለአስማእ ውሳኔያቸውን ሲነግሯት፣ በቤቱ ውስጥ ያለው አየር በሙሉ ወደ ጭንቅ ተቀየረ።
"አባቴ... እባክህ ህይወቴን ከመወሰንህ በፊት ስሜቴን አዳምጠኝ" ስትል አስማእ በከፍተኛ ድንጋጤ ተማጸነች።
አባቷ ግን ፡ "አስማእ! እኔ ላንቺ የሚበጅሽን አውቃለሁ። ያ ያጋጠመሽን አላስፈላጊ ህልም እርሺው። ሰኢድ የቤተሰባችንን ክብር የሚያስጠብቅ አጋርሽ ነው፤ የጋብቻውም ስነ-ስርአት በሚቀጥለው ሳምንት ይፈጸማል" ሲሉ ውሳኔያቸውን ነገሯት።
አስማእ ወደ ሶላቷ ተመልሳ በሱጁድ ላይ ወደቀች። የዱንያ ፈተና እና የመለኮታዊ ውሳኔ (ቀደር) ምስጢር በልቧ ውስጥ ይበልጥ ተፋጠጡ።
በሌላ በኩል፣ የአስማእ እና የሰኢድ የጋብቻ ቀን መቆረጡን አንዋር ሲሰማ፣ ነፍሱ ከዚህ በፊት አውቃው የማታውቀውን የህመም ደረጃ አስተናገደች። ነገር ግን ከሃራም ጥሪ እና ከጥላቻ ይልቅ፣ እጁን ወደ ሰማይ ዘርግቶ ለአስማእ ሰላምና መልካም ህይወትን፣ ለራሱ ደግሞ ፅናትን ለመነ።
የኒካሁ ቀን ደረሰ። በአቶ ከማል ሰፊ ቤት ውስጥ የአካባቢው ታዋቂ ሰዎችና ወላጆች ተሰብስበዋል። አስማእ በክፍሏ ውስጥ ሆና በዱዓ ላይ ሳለች፣ ሳሎን ውስጥ የወረዳው ቃዲ (ኢማም) እና የሁለቱ ወገን ምስክሮች የኒካሁን ቃለ-መሃላ ሊያሰፍሩ ስነ-ስርአቱን ጀመሩ።
ቃዲው ሰነዱን አስቀርበው አቶ ከማልንና ሰኢድን ሊያስፈርሙ ሲሉ፣ ድገት ከቤቱ ደጃፍ አንድ ያልተጠበቀ እንግዳ ገብቶ የቃዲውን እጅ ያዘው...
በሳሎኑ ውስጥ ያለው ድባብ በአንድ አፍታ ወደ ጸጥታ ተቀየረ። የቃዲውን እጅ የያዘው እንግዳ ከጎረቤት ወረዳ የመጣ ታዋቂው የንግድ አበዳሪ እና የአካባቢው ታማኝ ሰው ነበሩ።
እሳቸው ድምጻቸውን ከፍ አድርገው፡ "ይህ ጋብቻ ከመፈጸሙ በፊት ሊጣራ የሚገባው ትልቅ አደራ አለ!" አሉ።
በቦታው የተቀመጡት አቶ ከማልም ሆኑ ሰኢድ በድንጋጤ ተዋጡ። ሰኢድ ፊቱ ላይ ያለው መረጋጋት ጠፍቶ በጭንቀት መበሳጨት ጀመረ። እሳቸው ይዘውት የመጡት ሰነድ ሰኢድ ከአካባቢው ምስኪኖች እና ከየቲሞች (ወላጅ አልባ ህፃናት) ንብረት ጋር በተያያዘ የፈጸመውን የፋይናንስ ማጭበርበር እና ያልተከፈለ ትልቅ እዳ የሚያሳይ ነበር። ሰኢድ ለአስማእ አባት የቀረበው የሃብትና የክብር ሽፋን ሙሉ በሙሉ በእዳ እና በሃራም ገንዘብ የተገነባ መሆኑ በጉባኤው ፊት ይፋ ሆነ።
አቶ ከማል በድንጋጤ እና በእፍረት አንገታቸውን ደፉ። የልጃቸውን እድል በሃብት ብዛት መዝነው ለእንዲህ አይነቱ ሰው አሳልፈው ሊሰጡ እንደነበር ሲረዱ፣ የህሊና ቁስል ወጋቸው። የጋብቻው ስነ-ስርአት ወዲያውኑ ተሰረዘ፤ ሰኢድም በቆሸሸ ስሙና በእፍረት የኒካሁን ቦታ ለቆ ወጣ።
ዜናው በክፍሏ ውስጥ ላለችው ለአስማእ ዘንድ ሲደርስ፣ በሱጁድ ላይ ወድቃ አላህን አመሰገነች። ይህ ክስተት ለአባቷ ትልቅ ትምህርት እንደሆነና አላህ በእውቀቱ ጥበቃ እንዳደረገላት ተረዳች።
ክፍል 4⃣ ይቀጥላል.... | 744 |
| 18 | 🩶የታሪክ እዳ🩶 ክፍል 3️⃣ ከምሽቱ 2:30 ...ይቀጥላል
አላችሁ ወይ???? | 594 |
| 19 | በፈገግታ አላህን ማመስገን ✨💫
በህይወታችን ያሉትን ቀላል የሚመስሉ ኒዕማዎች እናስተውላቸው.....
😊 ከቤተሰቦችህ ጋር ስትቀመጥ ፈገግ በል፤ ምክንያቱም ቤተሰብ እንዲኖራቸው የሚመኙ ሰዎች አሉ።
😊 ወደ ሥራህ ስትሄድ ፈገግ በል፤ ምክንያቱም ሥራ የሚፈልጉ ብዙ ሰዎች አሉ።
😊 ጤነኛ ስለሆንክ ፈገግ በል፤ ምክንያቱም በሕመም ላይ ያሉ ሰዎች ጤናቸውን በከፍተኛ ዋጋ እንኳን ለማግኘት ይመኛሉ።
😊 በሕይወት ስላለህ ፈገግ በል፤ ምክንያቱም የሞቱ ሰዎች በሕይወት ተመልሰው መልካም ሥራ ለመሥራት ይመኛሉና። | 570 |
| 20 | «ተመኘሁ... አገባሁ، ተመኘሁ... ወለድኩ، ነገር ግን ህይወት አልበቃ አለችኝ!»🥲
አንዲት ሴት እንዲህ አለች፦ ተመኘሁ... ማግባትን ተመኘሁ—እናም አገባሁ—ነገር ግን ቤቴ ባዶና በዝምታ የታፈነ ነበር። ስለዚህ ተመኘሁ... ልጆች መውለድን ተመኘሁ—እናም ወለድኩ። ሆኖም፣ ብዙም ሳይቆይ፣ የቤቱ ግድግዳዎች እንኳ አሰለቹኝ። ስለዚህ ተመኘሁ... ስራ ማግኘት ተመኘሁ—እናም አገኘሁ—ከዚያም የራሴ ቤት መኖር ዋናው ምኞቴ ሆነ። ከብዙ ትግል በኋላ፣ በመጨረሻ ያንን ቤት ባለቤት ሆንኩ፤ ነገር ግን ልጆቼ አድገው ነበር። ስለዚህ ተመኘሁ... ሲያገቡ ማየትን ተመኘሁ—እናም አገቡ። ነገር ግን ከስራ እና ከችግሮቹ ሰልችቶኝ ነበር፤ ስራው አድካሚ ሆኖብኝ ነበር። ስለዚህ ተመኘሁ... ጡረታ ወጥቼ እረፍት ማድረግን ተመኘሁ—እናም አደረግኩ—ነገር ግን ልክ ከትምህርት እንደተመረቅኩበት ጊዜ ሁሉ ብቻዬን ቀረሁ። ሆኖም፣ ከትምህርት ስመረቅ ህይወትን በጉጉት እጠብቅ ነበር፤ አሁን ግን ከእርሷ እየራቅኩ ነው። ግን አሁንም ምኞቶች አሉኝ... ስለዚህ ተመኘሁ...
ቁርአንን በቃሌ ለመያዝ ተመኘሁ፤ ነገር ግን የማስታወስ ችሎታዬ አላገዘኝም... ስለዚህ ተመኘሁ... ለአላህ ብዬ ለመጾም ተመኘሁ፤ ነገር ግን ጤንነቴ አልፈቀደልኝም... ስለዚህ ተመኘሁ... የለሊት ሶላትን ለመስገድ ተመኘሁ፤ ነገር ግን እግሮቼ ክብደቴን መሸከም አቃታቸው... ስለዚህ፤ ህመም ከመምጣቱ በፊት የጤንነትህን፣ እርጅና ከመምጣቱ በፊት የወጣትነትህን እድል ተጠቀምበት፤ እንዲሁም ስለ ዓለማዊ ሲሳይህ (ስለ ኑሮህ) የሚኖሩህ ሀሳቦች ከመጪው ዓለም (ከአኺራ) ጉዳይ እንዳያዘናጉህ ተጠንቀቅ
#የህይወት_ትምህርት# | 701 |
