cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal

The best fiction is far more true than any journalism 📢 ተዓማኒ የመረጃ ምንጭ ፤ ለሙያው ስነምግባር ተገዢ በሆኑ ጋዜጠኞች ብቻ 👉 በፌስቡክ ገፆቻችን https://www.facebook.com/simon.dereje.56 👉 https://www.facebook.com/mik0Man

Show more
Advertising posts
34 381Subscribers
+3324 hours
+2927 days
+1 90130 days
Posting time distributions

Data loading in progress...

Find out who reads your channel

This graph will show you who besides your subscribers reads your channel and learn about other sources of traffic.
Views Sources
Publication analysis
PostsViewsSharesViews dynamics
01
ቼልሲ በሌላ የለንደን ቡድን ከሶስት በላይ ጎሎች ተቆጥረውበት በፕሪሚየር ሊጉ ተሸንፎ አያውቅም ። መድፈኞቹ 5 ግቦችን ማስቆጠር ችለዋል 😯 #ዳጉ_ጆርናል
2 0683Loading...
02
ካይ ሀቨርትዝ የቀድሞ ቡድኑ ላይ በማስቆጠር ደስታውን አክብሯል 🥶 በ2021ዱ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ ማንችስተር ሲቲ ላይ ብቸኛውን ጎል አስቆጥሮ ቼልሲ ዋንጫ ማንሳቱ ይታወሳል 😬 #ዳጉ_ጆርናል
2 5581Loading...
03
የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ  ጨዋታ ተጠባቂ ጨዋታ       አርሰናል 5-0 ቼልሲ ⚽️ ትሮሳርድ ⚽️⚽️ ዋይት ⚽️⚽️ ሀቨርትዝ ጎሎቹን ለመመልከት 👉 @mikoethio #ዳጉ_ጆርናል
2 5152Loading...
04
የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ተጠባቂ ጨዋታ            አርሰናል 3-0 ቼልሲ ⚽️ ትሮሳርድ ⚽️ኋይት ⚽️ ሀቨርት ጎሎችን ለመመልከት 👉 @mikoethio #ዳጉ_ጆርናል
5741Loading...
05
የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ተጠባቂ ጨዋታ         አርሰናል 1-0 ቼልሲ ⚽️ ትሮሳርድ ጎሎችን ለመመልከት 👉 @mikoethio #ዳጉ_ጆርናል
3 1542Loading...
06
Media files
3 4145Loading...
07
የእስራኤል ባለስልጣናት አስታራቂዎችን እያጠቁ ነዉ ስትል ኳታር ወቀሰች የኳታር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማጅድ አል-አንሷሪ አንዳንድ የእስራኤል ሚኒስትሮች ኳታርን በጋዛ ጦርነት ድርድር ላይ ስውር ዓላማ እንዳላት አድርገዉ መናገራቸዉ ስህተት ነዉ ሲሉ ወቅሰዋል፡፡"በእኛ የሽምግልና ጥረታችን እና በጋዛ የሰብአዊነት ስራን በደንብ ከሚያውቁት የእስራኤል ባለስልጣናት እንዲህ ያሉ መግለጫዎች መዉጣታቸዉ በጣም አበሳጭቶናል ብለዋል፡፡ አስታራቂውን አካል ማጥቃት ቁርጠኝነትን አያሳይም። ከእስራኤላውያን ወገኖቻችን እያገኘን ያለነው ግን ይህንን ነው ፤ድብቅ ዓላማ እንዳለን ተከስሰናል። ግን ይህ ከእውነት የራቀ ነው። ይህንን ግጭት ለማስቆም ብቸኛው መንገድ ሽምግልና ነው ሲሉ አክለዋል፡፡ በጋዛ ያለውን እልቂት ለማስቆም እና የእስራኤል ምርኮኞችን ለመመለስ ሂደቱ ላይ እምነት ከሌለ የሽምግልናዉን የተሳካ ውጤት ለማየት በጣም አስቸጋሪ እንደሚሆን ይሰማኛል ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ አል-አንሷሪ አክለውም “የኳታር የሽምግልና ጥረቶች እስከቀጠሉ ድረስ፣ የሐማስ የፖለቲካ ቢሮ በዶሃ መገኘቱን የሚያረጋግጥ ምንም ምክንያት የለም። ይህ ቢሮ የተከፈተው ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር በመቀናጀት - በሁለቱም ወገኖች መካከል ለሽምግልና ዓላማ ነው ብለዋል። እስካሁን ድረስ በዚህ ረገድ የተለወጠ ነገር የለም” በማለት ተናግረዋል፡፡የኳታር ጠቅላይ ሚንስትር ሼክ መሀመድ ቢን አብዱራህማን ቢን ጃሲም አል ታኒ ቀጠናዊ ውጥረቶችን በማርገብ እና የእስራኤል በጋዛ ላይ ያደረሰችውን አውዳሚ ጦርነት ለማቆም መስራታቸውን ቀጥለዋል ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማጅድ አል አንሳሪ ተናግረዋል። በሌላ በኩል በካን ዮኒስ በሚገኘው ናስር ሆስፒታል በጅምላ መቃብር ውስጥ ቢያንስ 35 ተጨማሪ አስከሬኖች መገኘታቸውን የሲቪል መከላከያ ሰራተኞች ገልፀዋል፡፡ በአጠቃላይ በሆስፒታሉ የተገኙ አስከሬኖች ቁጥር ቢያንስ 310 ደርሷል።በካን ዮኒስ የተገደሉት ፍልስጤማውያን ዘመዶቻቸዉን ለማግኘት በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ የእስራኤል ወታደሮች ከተማዋን ለቀው ከወጡበት ጊዜ አንስቶ የአስከሬን ፍለጋ ናስር ሆስፒታል ዉስጥ በትጋት እየፈለጉ ይገኛል። በስምኦን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
4 3290Loading...
08
አርቲስት አማኑኤል ሀብታሙ በፀጥታ ሀይሎች ተያዘ አርቲስት አማኑኤል ሀብታሙ በዛሬው እለት አመሻሹን ሚያዚያ 15ቀን 2016ዓ.ም ወደ እስራኤል ሊያቀና በነበረበት ወቅት ላይ በፀጥታ ሀይሎች መያዙን የአርቲስቱ የቅርብ ምንጮች ገልፀዋል። ጉዳዩን አስመልክቶ የአርቲስቱ የቅርብ ወዳጅ በማህበራዊ ትስስር ገፁ "ያያ ዘልደታ" ጉዳዩን አስመልክቶ ተከታዩን አስፍሯል። " ዛሬ ከመሽ ዕብደት በሕብረት የተሰኘውን አዲሱን ትያትር ለማሳየት ወደ ሃገረ እስራኤል ለመሄድ ዝግጅቱን ጨርሶ እነሆ አሁን ከመሸ ከኤርፖርት ተይዞ ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ተወስዷል::" ሲል አስታውቋል። እስከ አሁን ባለው ሂደት ከመንግስት አካላት ስለ ጉዳዩ የተሰጠ ምላሽም ሆነ ማብራሪያ የለም። #ዳጉ_ጆርናል
3621Loading...
09
በአሜሪካ ዩኒቨርሲቲዎች ዉስጥ የፍልስጥኤም ድጋፍ እየተስፋፋ መምጣቱ ተነገረ የአሜሪካ ዩኒቨርሲቲዎች እየበረታ የመጣውን የተማሪዎች ተቃውሞ ለማብረድ ጥረት በማድረግ ላይ ናቸው።እስራኤል በጋዛ የምታካሂደውን ጦርነት የተቃወሙ ከ100 በላይ የኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውም ተቃውሞውን ወደሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች እያሰፋው ነው ተብሏል። ፖሊስ ትናንት ምሽት በኒውዮርክ ዩኒቨርሲቲ የነበረውን ተቃውሞ ለማስቆም በመግባት በርካታ ተማሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉ ተገልጿል።በየል፣ በርክሌይ፣ ማሳቹሴትስ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (ኤምአይቲ) እና ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ተማሪዎች ማደሪያቸውን በዳስ አድርገው ተቃውሟቸውን እያሰሙ ሲሆን፥ ሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ ከውጭ እንግዶች እንዳይገቡ በሩን ዝግ አድርጓል። 108 ተማሪዎች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ያደረገው ኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲም የገጽ ለገጽ ትምህርት አቁሟል።ተማሪዎቹ እስራኤል በጋዛ ላይ የምትፈጽመውን ድብደባ ዩኒቨርሲቲዎቻቸው እንዲያወግዙ እንዲሁም ለእስራኤል የጦር መሳሪያ ከሚያቀርቡ ኩባንያዎች ጋር ያላቸውን ግንኙነት እንዲያቋርጡ ጠይቀዋል።የፍልስጤም ደጋፊዎች በእስራኤል ላይ ተቃውሟቸውን ሲገልጹ ያስተላለፏቸው “ጸረ ሴማዊ መልዕክቶች” ግን እስራኤላውያን ተማሪዎችን ስጋት ውስጥ መጣሉን ነው አሶሼትድ ፕርስ የዘገበው። አይሁዳውያን ተማሪዎች የፍልስጤሙ ሃማስ አሁንም ድረስ እስራኤላውያንን አግቶ መያዙንና ከ1 ሺህ 100 በላይ እስራኤላውያንን ህይወት መቅጠፉን ያነሳሉ።ቁጥራቸው አነስ ይበል እንጂ እስራኤላውያን ተማሪዎችም በኮሎምቢያ እና ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ድምጻቸውን አሰምተዋል ተብሏል።ዩኒቨርሲቲዎቹ የተማሪዎቹን ጥያቄ ለመመለስ ከመሞከር ከመሆን ይልቅ ተማሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋል ላይ መጠመዳቸው ተቃውሞውን እያስፋፋው መሆኑ ተገልጿል። በአሜሪካ ዩኒቨርሲቲዎች እየተስፋፋ ስለመጣው የተማሪዎች ተቃውሞ የተጠየቁት ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን፥ ጸረ ሴማዊ ይዘት ያላቸው መልዕክቶች መተላለፋቸውን ተቃውመዋል።ፕሬዝዳንቱ “በፍልስጤም ምን እየተካሄደ እንደሆነ የማያውቁ” ያሏቸውን ወገኖችም ተቃውመዋል።የእስራኤል ዋነኛ አጋር በሆነችው አሜሪካ የጋዛው ጦርነት ከተቀሰቀሰ ጀምሮ በርካታ የአደባባይ ተቃውሞዎች ቢደረጉም ዋሽንግተን በቴል አቪቭ ዙሪያ የማይነቃነቅ አቋም እንዳላት የ26 ቢሊየን ዶላር ድጋፍ በማጽደቅ አሳይታለች። በስምኦን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
4 7131Loading...
10
Media files
4 2980Loading...
11
ሀሰተኛ የህክምና ማስረጃ በመጠቀም ወንድማችን ታሟል በማለት ሲያጭበረብሩ የነበሩ አምስት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ በደቡብ ኢትዮጵያ ወላይታ ሶዶ እና በ በተለያዩ ወረዳዎች በመዘዋወር ታማሚ በማስመሰል የማጨበርበር ተግባር ሲፈጽሙ የነበሩ  ግለሰቦች በህብረተሰቡ ጥቆማ መያዛቸውን ፖሊስ አስታዉቋል። በማጨበርበር ድርጊቱ የተሰማሩት ተጠርጣሪዎች አብዛኛዎቹ ወጣቶች ሲሆኑ  ከተለያዩ አከባቢዎች በመምጣት ሀሰተኛ የህክምና ማስረጃ በማዘጋጀት  ወንድማችን በህመም እየተሰቃየብን ነው በማለት መኪና በመከራየት ሲያጭበረብሩ መገኘታቸዉ ተገልጿል። ተጠርጣሪዎቹ  ከአስራ ዘጠኝ ሺህ ብር በላይ ከህብረተሰቡ በማጨበርበር መሰብሰባቸውን የደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን ህዝብ ግንኙነት እና ገጽታ ግንባታ ዳይሬክተር ኢንስፔክተር አሸናፊ ሀይሌ ለብስራት ሬዲዮ ቴሌቪዥን ተናግረዋል። በሳምራዊት ስዩም #ዳጉ_ጆርናል
4 8952Loading...
12
በትግራይ ክልል የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ተጀመረ የፖሊዮ በሽታ መከላከያ ክትባት ዘመቻ በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ በዛሬው ዕለት መጀመሩን የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቋል፡፡ በዚህ የክትባት ዘመቻ ከሁለት ሚሊዮን በላይ ዕድሜያቸው ከ 10 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናት ይከተባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የኢንስቲትዩት በክትባት መከላከል የሚቻሉ በሽታዎች ቅኝትና ምላሽ ቡድን መሪ አቶ ሚኪያስ አላዩ ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዢን ተናረዋል፡፡ በኢትዮጵያ በክትባት እጥረት ምክንያት የሚመጣ የፖሊዮ በሽታ ከ2019 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በተለያዩ የሃገሪቱ አካባቢዎች በመከሰቱ ፖሊዮን ጨርሶ የማጥፋት ጉዞን አስቸጋሪ አድርጎታል፡፡ እንደ ሀገር እ.ኤ.አ 2021 እና 2022 አዲሱን የፖሊዮ ክትባት በመጠቀም የተካሄዱ ሁለት ዙር ሃገር አቀፍ የክትባት ዘመቻዎች በጥሩ ተሞክሮነት የሚጠቀሱ መሆናቸውን ያነሱት አቶ ሚኪያስ በአንዳንድ የሃገሪቱ አካባቢዎች በጸጥታ ችግር ዘመቻዉ ሳይካሄዱ መቅረቱን አንስተዋል፡፡ በትግስት ላቀዉ #ዳጉ_ጆርናል
8760Loading...
13
በመላዉ አለም በየእለቱ በተደጋጋሚ የሚጠራዉ ቃል ምንድነዉ? ስንል ባሳለፍነዉ ቅዳሜ ወደእናንተ ላደረስነዉ ጥያቄ መላሾቻችን እና የ 100 ብር የሞባይል ካርድ አሸናፊዎች ታዉቀዋል። በዚህም መሰረት ጫላ መኮንን - ከሰበታ እና የኃላሸት ሸፈራው -ከችሎት መድሃኒያለም የጥያቄዉ መላሾቻችን ናቸዉ። ስለተሳትፎአችሁ እና ዳጉ ጆርናልን የመረጃ ምርጫችሁ እያመሰገንን ቀጣይ ተሸላሚ የሚያደርጉ ጥያቄዎችንም ወደእናንተ የምናደርስ ይሆናል። #ዳጉ_ጆርናል
4 6633Loading...
14
ጀርመን ለቻይና ሲሰልል ነበር ያለችዉን ግለሰብ በቁጥጥር ስር አዋለች የጀርመን ፖሊስ ለቻይና በመሰለል የጠረጠረዉን የቀኝ አክራሪ የአውሮፓ ፓርላማ አባል ረዳትን በቁጥጥር ስር አውሏል።አቃብያነ ህጎች በዛሬዉ እለት እንዳስታወቁት ጂያን ጂ በአውሮፓ ፓርላማ አሠራር ላይ መረጃን ለቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በተደጋጋሚ አሳልፎ ሰጥቷል ተብሎ ይታመናል:: እስሩ በሰኔ ወር ከአውሮፓ ኅብረት ምርጫ በፊት የዲሞክራሲ ስጋት ፈጥሯል የሚል ማስጠንቀቂያ የተነሳበት ሲሆን ቤጂንግ በበኩሏ ጸብ ጫሪ ብላዋለች፡፡ የጀርመን ባለስልጣናት በቁጥጥር ስር የዋለውን ሰው የቀጠረው የትኛው ፖለቲከኛ እንደሆነ አልገለፁም። ይሁን እንጂ ጀርመናዊው የማክሲሚሊያን ክራህ ረዳት እንደነበር ሚዲያዎች ዘግበዋል።ለመጪው የአውሮፓ ፓርላማ ምርጫ የቀኝ አክራሪው አማራጭ ለጀርመን (አፍዲ) ፓርቲ መሪ እጩ ናቸዉ። ክራህ በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ በቼክ የስለላ ድርጅት በተከፈተው ክስ የሩሲያን ደጋፊ የሆኑ ትርክቶችን ወደፊት ለማምጣት ጉቦ በመውሰድ የተጠረጠሩ በመላው አውሮፓ ካሉ ፖለቲከኞች ዝርዝር ውስጥ ይገኛል። ጂያን ጂ ሰኞ መገባደጃ ላይ በድሬዝደን ተይዞ በአፓርታማው ላይ ፍተሻ እንደተደረገበት አቃቤ ህግ አስታዉቋል። በጥር ወር የአውሮፓ ፓርላማ ድርድር እና ውሳኔዎች ላይ ሪፖርት ከማድረግ በተጨማሪ በጀርመን የሚገኙ የቻይና ተቃዋሚዎችን ይሰልል ነበር ተብሏል።የበርሊኑ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ናንሲ ፋዘር የስለላ ውንጀላ "እጅግ አሳሳቢ" ነው ብለዋል። በአውሮፓ ፓርላማ ውስጥ ለቻይና የስለላ ድርጅት ሰላይ ስለመሆኑ ከተረጋገጠ በአውሮፓ ዲሞክራሲ ላይ የሚደረግ ጥቃት ነው ስትል የበርሊኑ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ናንሲ ፋዘር አክላለች፡፡የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቤጂንግን ለማሳነስ እና የሁለትዮሽ ግንኙነትን ለማፍረስ በሚያደርገዉ ጥረት ስማቸው ያልተጠቀሰ ሀይሎችን መወንጀል ተቀባይነት የለዉም ብሏል፡፡ በስምኦን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
4 6640Loading...
15
Media files
4 3790Loading...
16
#Breaking ህወሓት ብልፅግናን ሊቀላቀቀል ነዉ መባሉን ተከትሎ ከብልፅግና ጋር የጀመርኩት ንግግር የለም ሲል አስተባበለ የህወሓት እና የብልፅግና ድርድር ከፕሪቶሪያ ስምምነት በኋላ የተፈጠረውን አንፃራዊ ሰላም ለማስፋት እና ለማጠናከር ያለመ ነው ያለው ህወሓት ፤ ህወሓት እና ብልፅግና መሰረታዊ የዓላማ እና የአስተሳሰብ ልዩነት ያላቸው ፓርቲዎች መሆናቸውን ገልጿል። አክሎም ልዩነቱ እንዳለ ሆኖ ሁለቱ ፓርቲዎች ሊወያዩባቸው የሚገቡ ብዙ አጀንዳዎች አሉና በነዛ ዙርያ ውይይት እያደረግን ነው ማለቱን ዳጉ ጆርናል ከፓርሪዉ መግለጫ ተመልክቷል። ከዚህ ውጭ ግን እንደሚወራው ህወሓት ብልፅግናን ለመቀላቀል ንግግር ጀምሯል የተባለው ጉዳይ ሐሰት ነው ሲልም በይፋዊ የፌስቡክ ገፁ ፓርቲዉ አጋርቷል። በዛሬዉ እለት ህወሓት ብልጽግና ፓርቲን ሊቀላቀል መሆኑን ዳጉ ጆርናል የዋዜማ ሚዲያ ዘገባን ዋቢ በማድረግ መረጃ ማድረሱ ይታወሳል። ይህንኑ ተከትሎም ህወሓት ይፋዊ መግለጫ አዉጥቷል። በሚሊዮን ሙሴ #ዳጉ_ጆርናል
4 9945Loading...
17
ለሰብዓዊ ተግባር በሚል ገንዘብ ሰብስቦ ለግል ጥቅም ማዋል እስከ አስር ዓመት በእስራት ያስቀጣል ተባለ የኢትዮጵያ የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ደንጋጌ ላይ እንደተቀመጠው ማንም ሰው ለሰብዓዊነት በሚል የተሰበሰበን ገንዘብ ሆነ ቁስ ለግል ጥቅሙ ማዋል የሚያስቀጣ የወንጀል ድርጊት ሆኖ መቀመጡን ብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን ያነጋገራቸው የሕግ ባለሙያ ተናግረዋል፡፡ ከጣቢያችን ጋር ቆይታ ያደረጉት በማንኛውም ፍርድ ቤት ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ የሆኑት ጠበቃ ካሳሁን አውራሪስ እንደተናገሩት በኢትዮጵያ የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ድንጋጌ መሰረት አግባብ ካለው ተቋም ፍቃድ ኖሮት ሆነ ሳይኖረው ማንኛውም ሰው ኃይማታዊ ፣ ፖለቲካዊ ፣ ሰብዓዊ ዝ ባህላዊ ወይም ማንኛውንም ጉዳይ ምክንያት አድርጎ  ከግለሰብ ወይም ከህዝብ ላይ ገንዘብ እና ቁስ ሰብስቦ በሙሉም ሆነ በከፊል ገንዘቡን ሆነ ቁስ ለተሰበሰበለት አላማ ሳይውል ለግል ጥቅሙ ያዋለ እንደሆነ በወንጀለኛ መቅጫ ህግ አንቀጽ 701 ንኡስ ቁጥር 4 ስር በተቀመጠው መስረት ይቀጣል፡፡ ስለቅጣቱ በተለይም ግለሰቡ እርዳታ የሚያስፈልው ሰው ሆኖ እርሱን በማሳየት በስሙ ሰብስበው ገንዘቡን ለግል ጥቅም ካዋለ ቅጣቱ እስምን ድረስ ነው ሲል ብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዢን ለህግ ባለሙያው ላነሳው ጥያቁ የህግ ባለሙያው ሲያብራሩ ፍቃድ አውጥቶ ገንዘቡን ሰብስቦ ለግል ጥቅሙ ካዋላ  በወንጀለኛ መቅጫ ህግ አንቀጽ 701 ንኡስ ቁጥር 4 ስር በተቀመጠው መስረት ከአስር አመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት እና ከ30 ሺ ብር የማይበልጥ መቀጮ ገንዘብ እንደሚቀጣ ህጉ አስቀምጧል፡፡ ለሰብዓዊ እርዳታ ይሁን ለሌላ አላማ ገንዘብ ሲሰበሰብ ከሚመለከተው አግባብ ካለው ባለስልጣን ፍቃድ ሳይኖረው ሲሰበስብ የተገኙ ከሆነ ፍቃድ ሳያገኝ በመስብሰቡ ብቻ በተጨማሪ በወንጀለኛ መቅጫ ህግ አንቀጽ 862 ላይ በተቀመጠው ህግ መሰረት ተጨማሪ ቅጣት ይጣልበታል፡፡ በአንቀጽ 701 አንደተደነገገ አንድ ሰው ጉዳት ሳይደርስበት ቸግር አለብኝ በማለት የሰበሰበ እዲሁም ሌላ ግለሰብም ሰብአዊ እርዳታ የሚያስፈለግው ሰውን በአደባባይ ይዞ የታመመ በማሰመሰል ሀሰተኛ መግለጫ በመስጠት በማጭበርበር በተለያዩ መንገድ ገንዘብ ከሰበሰቡ እስከ አምስት አመት እንደሚያስቀጣም ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ የሆኑት ጠበቃ ካሳውን ጨምረው ለጣቢያችን ተናግረዋል፡፡ እንደህግ ባለሙያ ማብራሪያም ይህ ቅጣት ተግባራዊ የሚሆነው የሰብዓዊ እርዳታ የተሰበሰበለት ግለሰብ ወይም ድጋፉን ባደረጉ ሰዎች ክስ ሲመሰረት  እና ማስረጃ ሲቀርብ መሆኑን ህግ ይደነግጋል፡፡ በትግስት ላቀው #ዳጉ_ጆርናል
4 8645Loading...
18
Media files
4 5230Loading...
19
ሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የተከሰተው እሳት በቁጥጥር ስር መዋሉን የሰሜን ጎንደር አስተዳደር አስታወቀ በአማራ ክልል ሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የተከሰተው እሳት በቁጥጥር ስር መዋሉን የሰሜን ጎንደር አስተዳደር አስታወቀ። ሚያዝያ 10 ቀን 2016 ዓ ም ከምሽቱ ሦስት ሰዓት መንስኤው እስካሁን ባልታወቀ ምክንያት በፓርኩ የተለያዩ አካባቢዎች የእሳት ቃጠሎ መነሳቱ ነው የተገለጸው። እሳቱ በአካባቢው ሕዝብ ርብርብ በቁጥጥር ስር መዋሉን ዛሬ ለዶይቼ ቬሌ የተናገሩት የሰሜን ጎንደር ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ቢምረው ካሣ በድርጊቱ የተጠረጠሩ ሦስት ሰዎች መያዛቸውን አመልክተዋል። በተጠርጣሪዎቹ ላይ በሕግ አግባብ ምርመራ ተደርጎ ጉዳዩ የሚጣራ መሆኑን፤ ቃጠሎው ያደረሰው የጉዳት መጠንም ተጣርቶ ይፋ እንደሚደረግም ዳጉ ጆርናል ከዘገባው ተመልክቷል። የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የሚገኝበት አካባቢ ሦስት ዓይነት የአየር ጠባይ እንዳለና በየዓመቱም ተመሳሳይ የእሳት አደጋ በሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ እንደሚከሰት ነው ባለሥልጣኑ የገለጹት። ከቀናት በፊት የተነሳው እሳት በፓርኩ የተለያዩ ክፍሎች ላይ እንደነበር በማመልከትም ፓርኩ ጓሳ እንደመሆኑ የተዳፈነ እሳት ንፋስ አቀጣጥሎት እንዳይነሳ ክትትል የማድረግ ጥረት መኖሩንም ተናግረዋል። የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ በጎርጎሪዮስ የዘመን ቀመር በ1978 በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና ባህል ድርጅት ዩኔስኮ በዓለም ቅርስነት ተመዝግቧል። #ዳጉ_ጆርናል
5 1125Loading...
20
በአርጀንቲና ቅድመ ክፍያ የፈፀምኩለት ተሽከርካሪ አልተሰጠኝም ያለው ግለሰብ በመኪና መሸጫ መደብር ውስጥ ለ15 ቀናት አልወጣም ማለቱ ተሰማ በደቡብ አሜሪካ አንድ አርጀንቲናዊ በመኪና መሸጫ መደብር ውስጥ ሌሊቱን ማደሩ የተሰማ ሲሆን ቅድመ ክፍያ የፈፀመበትን የጭነት ተሽከርካሪ ካልተሰጠው ስፍራውን ለቆ ለመውጣት ፍቃደኛ እንደማይሆን አስታውቋል። አልቤራዶ ኡሳንዲቫራስ የተባለው አርጀንቲናዊ ግለሰብ ከሁለት ሳምንታት በላይ ዓለም አቀፍ የዜና አርዕስተ ሆኖ ቆይቷል።በመኪና አቅራቢ ድርጅቶች በኩል የሚሰራውን ህገ ወጥ ድርጊት በመታገል ረገድም በተወሰነ ደረጃዋ ምልክት ተወስዷል። በሳልታ ነዋሪ የሆነው በአርባዎቹ አጋማሽ የእድሜ ክልል ውስጥ የሚገኘው ይህው ሰው ከ15 ቀናት በፊት ከቤተሰቦቹ ጋር በመሆን ወደ አርጀንቲና ዋና ከተማ ቦነስ አይረስ መጥታል። በጣም የሚፈልገውን የጭነት ተሽከርካሪ በወቅቱ ሊደርስለት ባለመቻሉ በቀጥታ አከፋፋዩን አግኝቶ ለማውራት ቢሞክርም ሳይሳካለት ይቀራል። ኡሳንዲቫራስ የሚፈልገውን መልስ ባለማግኘቱ እና ከባለቤቱ ጋር መገናኘት ባለመቻሉ ቃል የተገባለት ተሽከርካት ወይም ቢያንስ የከፈለውን ክፍያ ካልተመለሰለት ከመኪና መሸጫ መደብር ውስጥ እንደማይወጣ ይናገራል። ይህው የእርሱ ጉዳይ በፍጥነት ተሰራጭት የአቤላርዶ  ኡሳንዲቫራስ የመብት ትግል በሁሉም የላቲን አሜሪካ ሀገራት ውስጥ ትልቅ ርዕስ ሆኗል። ኡሳንዲቫራስ ባለፈው አመት አዲስ የጭነት መኪና ለመግዛት በመወሰን በቦነስ አይረስ ካለው አከፋፋይ ጋር ከተገናኘ በኋላ አሮጌውን የጭነት መኪናውን ለመሸጥ እና ለአዲሱ መኪና ሙሉ ክፍያ ለመፈጸም ይወስናል። እስከዚያ ድረስ ሁሉም ነገር ያለችግር ሄዷል። ነገር ግን የቅድሚያ ክፍያ ከፈፀመ በኋላ፣ ከአከፋፋዩ ሰምቶ የማያውቀውን ተሽከርካሪውን ለማስረከብ 120 ቀናት እንዲጠብቅ ቀነ-ገደብ ሲሰጥው እና ወደ ሌላ የአስተዳደር ክፍል ሲያመላልሱት ብስጭት ውስጥ ይገባል። ከታህሳስ ወር ጀምሮ ከአንድ ስልክ ወደ ሌላ ስልክ ደውል እያሉ ሲያንከራትቱኝ እና የኩባንያውን ተወካይ ስም እንኳን ሊነግሩኝ ፍቃደኛ አልነበሩም ሲል አቤላርዶ ኡሳንዲቫራስ ለጋዜጠኞች ተናግሯል። "እውነታው ግን የሌላቸውን የጭነት ተሽከርካሪ እንዳላቸው አድርገው ማስታወቂያ ሰርተዋል። ከዛም አገንዘብህን ተጠቅመው ሌላ ስምምነት ለማድረግ የሚጥሩበት የፋይናንስ ሥርዓት ነው ሲል አክሏል። አርጀንቲናዊው ግለሰን በከፈለው ገንዘብ ቅናሽ ሌላ መኪና እንደቀረበለት ተናግሮ አዲስ የጭነት መኪና ከፈለገ ተጨማሪ ክፍያ እንደሚፈጽም ቀድሞ ባልነበራቸው ውል መሰረት ተነግሮታል። ሴት ልጁን እና ትንሹን ወንድ ልጁን ጨምሮ መላውን ቤተሰቡን ወደ ቦነስ አይረስ እና እንዲሁም ለጭነት መኪናው የሚከፈለውን የቀረውን ክፍያ ካመጣ በኋላ አዲሱ መኪና ካልተሰጠው ከማከፋፈያ መደብሩ ውስጥ እንደማይወጣ አሳውቋል። በአካባቢው የሚገኙ ፖሊሶት ለሰዓታት ድርድር እና ሽምግልና ቢያደርጉም የአቤላርዶ ያልተለመደ የተቃውሞ አይነት መላው ሀገሪቱን አዳርሷል።ሌላው ቀርቶ አከፋፋዩን ‘መኪናውን አምጡልኝና እዚህ በጥሬ ገንዘብ ልክፈል ብላቸውም ሊሰሙኝ አልቻሉም፤ ምንም እንዳልገባኝ አድርገው ከገጠራማ አካባቢ የመጣ ሰው ነው ብለው ዝቅ ሊያደርጉኝ ቢሞክሩም አልተሸነፍኩም ብሏል። የቦነስ አይረስ የተሽከርካሪ አከፋፋይ በበኩሉ ኩባንያውን ከንግድ ውጪ ለማድረግ የተነደፈ የሚዲያ ዘመቻ ሰለባ ሆኛለው ብሏል። በኩባንያው ድረ-ገጽ ላይ የተለጠፈው መግለጫ እንደሚያሳየው የተካሄደብኝ "ቆሻሻ ስም የማጥላላት ጦርነት" አውግዟል በማለት ለደንበኞቼ ምርጡን አገልግሎት ለማቅረብ የተቻለኝን ሁሉ አደርጋለሁ ሲል አስታውቋል። በስምኦን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
5 0167Loading...
21
Media files
4 8140Loading...
22
ከየመን ወደ ጂቡቲ ስትጓዝ የነበረች ጀልባ ተገልብጣ የ16 ኢትዮጵያውያን ህይወት አለፈ ትናንት ምሽት ከየመን የባሕር ዳርቻ ልዩ ስሙ ‘አራ’ ከተባለ ቦታ 77 ኢትዮጵያውያን ሕገ-ወጥ ፍልሰተኞችን አሳፍራ ወደ ጂቡቲ ስትጓዝ የነበረች ጀልባ ጎዶሪያ አካባቢ ተገልብጣ የ16 ወገኖች ሕይወት አለፈ፡፡ እንዲሁም አብረው በጀልባዋ ተሳፍረው የነበሩ 28 ኢትዮጵያውያን እስካሁን አለመገኘታቸውን በጂቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ አመላክቷል፡፡በሌላ በኩል 33 ፍልሰተኞች በሕይወት ተርፈው ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑ ተገልጿል፡፡ ኤምባሲው የተሰማውን ሐዘን ገልጾ÷ ከጂቡቲ ወደ መካከለኛው ምሥራቅ ሀገራት የሚደረጉ ሕገ-ወጥ ጉዞዎች እጅግ አደገኛ ከመሆናቸውም በላይ በየጊዜው የዜጎችን ሕይወት እያሳጡ መሆኑን አስታውቋል፡፡ በመሆኑም ዜጎቻችን በሕገ-ወጥ ደላሎች የሐሰት ስብከት በመታለል ሕይወታቸውን አደጋ ላይ ጥለው በዚህ አደገኛ የጉዞ መስመር ከመንቀሳቀስ እንዲቆጠቡ ሲል አሳስቧል፡፡ #ዳጉ_ጆርናል
5 4005Loading...
23
ማላዊ 11 ኢትዮጵያዊያንን በእስራት እና በከባድ የጉልበት ስራ ቀጣች ማላዊ በህገወጥ መንገድ ሀገሬ ገብተዋል ያለቻቸዉን 11 ኢትዮጵያዊያንን በእስር መቅጣቷን ዳጉ ጆርናል ሰመቷል። የመዙዙ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኢትዮጵያዊያኑ በህገወጥ መንገድ ወደ ማላዊ ገብተዋል ያለ ሲሆን የኢሚግሬሽን ህግ አንቀጽ 21/1 በመጣስ ወደ ማላዊ ገብተዋል ሲል ወንጅሏል። ከ 11 ስደተኞች ዉስጥ ሰባት ያህሉ በካሮንጋ ወረዳ ሃንጋላዌ የባህር ዳርቻ ፓስፖርት ሳይዙ ባሳለፍነዉ ሳምንት በቁጥጥር ስር የዋሉ መሆኑ ተነግሯል። ሰባቱ ኢትዮጵያን ከከባድ የጉልበት ስራ ጋር የሁለት ወር እስራት እንደተፈረደባቸዉ ዳጉ ጆርናል ከዘገባዎች ተመልክቷል። የተቀሩት አራት ኢትዮጵያዊያን ደግሞ በአንድ ወር ጊዜ ዉስጥ ሀገሪቱን ለቅቀዉ እንዲወጡ የሚደረግ ሲሆን በአሁኑ ወቅትም በመዙዙ እስርቤት እንደሚገኙ ተነግሯል። በቅርቡም ሌሎች 52 ኢትዮጵያዊያን ስደተኞችን በተመሳሳይ ማላዊ በህገወጥ መንገድ ድንበሬን ጥሰዉ ገብተዋል ስትል ዉሳኔ ሰጥታባቸዋለች። የጉልበት ስራ ተብሎ በኢትዮጵያዊያኑ ላይ የተላለፈዉ ዉሳኔ እስረኞች በማረሚያ ቤት ቆይታቸዉ መጸዳጃ ቤቶችን ማጽዳት ፣ የጉልበት እና ሌሎች ስራዎችን እንዲሰሩ የሚደረጉበት ነዉ። በበረከት ሞገስ #ዳጉ_ጆርናል
5 5076Loading...
24
ኔታንያሁ በእስራኤል ወታደራዊ ክፍል ላይ የሚጣለዉን ማዕቀብ እንታገላለን ሲሉ በድጋሚ ቃል ገቡ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ በእስራኤል ጦር ውስጥ "በአንድ ክፍል ላይ ማዕቀብ ሊጥሉ ይችላሉ" ብለው የሚያምኑ ሰዎች እንደገና ሊያስቡበት ይገባል ሲሉ ተደምጠዋል፡፡የአይሁድ ፋሲካ ሴደር በዓልን ለማክበር በማህበራዊ ድረ-ገጾች ላይ በተጋራዉ ንግግራቸዉ ኔታንያሁ የእስራኤል ሃይሎችን በሰብአዊ መብት ረገጣ ለመቅጣት የሚደረገውን ማንኛውንም ሙከራ “በሙሉ ኃይሌ” እዋጋዋለሁ ሲሉ ተናግረዋል። "ወታደሮቻችን በጦር ሜዳ እኛን ለመከላከል አንድ ሲሆኑ በዲፕሎማሲው መስክም እነሱን ለመከላከል አንድ ነን" ብለዋል፡፡ኔታንያሁ አስተያየታቸውን የሰጡት ዩናይትድ ስቴትስ በዌስት ባንክ ፍልስጤማውያን ላይ በደረሰው የሰብአዊ መብት ረገጣ በአንድ የእስራኤል ጦር ክፍል ላይ ማዕቀብ ልትጥል መሆኑን ዘገባዎች እየወጡ መሆናቸዉን ተከትሎ ነዉ፡፡ የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ሰኞ እለት እንደተናገሩት በእስራኤል ወታደሮች የተፈጸሙ የመብት ጥሰቶችን ለማጣራት "ሂደቶች" እየተካሄዱ ነው፡፡በዌስት ባንክ ውስጥ የሚገኘው ኒታዝ ጁኡዳ ወይም "ዩሁዳ ለዘላለም" የተባለው የአይሁድ ወታደሮች ክፍል የማዕቀብ ኢላማ ሊሆን እንደሚችል ዘገባዎች ያመለክታሉ። በሌላ በኩል የእስራኤል ጦር የጦር አውሮፕላኖቹ በደቡባዊ ሊባኖስ ላይ በአንድ ሌሊት ጥቃት መፈጸማቸው ተሰምቷል፡፡ ከሰሜን እስራኤል ጋር በሚያዋስነው የያሩ መንደር አካባቢ ሂዝቦላህ "የሽብር መሰረተ ልማት" ናቸው ያላቸውን አምስት ቦታዎችን ደብድቧል፡፡የእስራኤል የምድር ጦር ሃይሎች በቅርቡ በያሮው አካባቢ ስጋትን ለማስወገድ ጥቃት ሰንዝረዋል ሲል ወታደሮቹ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ባወጡት ጽሁፍ ላይ በሊባኖስ ላይ በደረሰ የአየር ጥቃት ህንጻዎች ሲፈርሱ የሚያሳይ ምስል አካተዉ ይፋ አድርገዋል፡፡ በምህረት ታደሰ #ዳጉ_ጆርናል
5 6491Loading...
25
Media files
5 3580Loading...
26
የካናዳ ኤምባሲ በሰሜን ፣ መካከለኛ እና በኢትዮጵያ ድንበር አካባቢ ዜጎቹ እንዳይቀሰቅሱ መከረ 👉🏼 ኤምባሲዉ በአዲስአበባ ጭምር ዜጎቹ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል የካናዳ መንግስት ዜጎቹ ወደ ኢትዮጵያ በጥቅሉ አስፈላጊ እና አስገዳጅ ካልሆነ በስተቀር እንዳይጓዙ ሲል ማስጠንቀቂያ መስጠቱን ዳጉ ጆርና ታዝቧል። በሕዝባዊ አመፅ ፣ ብጥብጥ ፣ በትጥቅ ግጭት እና የወንጀል ድርጊት ይበዛባቸዋል  ምክንያት ወደ ኢትዮጵያ አላስፈላጊ ጉዞን ያስወግዱ ሲልም አሳስቧል። በዋነኛነት በሰሜን ኢትዮጵያ አማራ ፣ ትግራይ ከመቐለ ከተማ ዉጪ ወደ አዲግራት ፣ አቢ አዲ ፣ አድዋ ፣  ሽሬ እና ማይጨዉ አካባቢዎች እንዲሁም ወደ ቤኒሻንጉል ክልል ዜጎቹ አይጓዙ ሲል አስጠንቅቋል። በተጨማሪም መካከለኛዉ ኢትዮጵያ ክፍል ጋምቤላ እና ሲዳማ ክልሎች እንዲሁም ሰሜን እና ምዕራብ ሸዋ እና ወደ አራቱ የወለጋ ዞኖች ዜጎቹ እንዳይጓዙ ጠይቋል። እንዲሁም ኢትዮጵያን ከኬንያ ፣ ደቡብ ሱዳን ፣ ሱዳን ፣ ሶማሊያ እና ኤርትራ ጋር በሚያዋስኑ የድንበር አካባቢዎችም ዜጎቹ እንዲጠበቁ መክሯል። ኤምባሲዉ የካናዳ ዜጎች በአዲስአበባ ጭምር ራሱ ዜጎቹ በሚንቀሳቀሱበት ወቅት ከፍተኛ የተባለ ጥንቃቄ እንዲያደርጉም ማሳሰቡን ዳጉ ጆርናል ሰምቷል። በቅርቡ ካናዳን ጨምሮ ፈረንሳይ ፣ ጀርመን ፣ ጣሊያን ፣ ጃፓን ፣ ብሪታንያ እና አሜሪካ በሰሜን ኢትዮጵያ ያለዉ የጸጥታ አለመረጋጋት አሳስቦናል ሲሉ በጋራ ባወጡት መግለጫ ማስታወቃቸዉ ይታወሳል። በበረከት ሞገስ #ዳጉ_ጆርናል
5 61510Loading...
27
ማሌዥያ ውስጥ የባህር ሃይል ሄሊኮፕተሮች በአየር ላይ ተጋጭተው የ10 ሰዎች ህይወት አለፈ የንጉሣዊው የማሌዢያ ባህር ኃይል ወታደራዊ ልምምድ ላይ በነበረበት ወቅት ሁለት የባህር ሃይል ሄሊኮፕተሮች በአየር ላይ ተጋጭተው የ10 ሰዎች ህይወት አልፏል።በአገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ላይ የታተመው ቀረጻ እንዳመላከቱ ሁለቱ ሄሊኮፕተሮች መሬት ከመጋጨታቸው በፊት አንደኛው የሌላውን ሮተር ቆርጧል። ድርጊቱ ያጋጠመዉ በማሌዥያ ሉሙት ከተማ ሲሆን ይህም የባህር ሃይል ሰፈር ነው፡፡ በአደጋዉ በሕይወት የተረፉ ሰዎች ስለመኖራቸዉ ማረጋገጥ አልተቻለም፡፡የሮያል የማሌዢያ ባህር ሃይል ሁሉም ተጎጂዎች በስፍራዉ መሞታቸው የተረጋገጠ ሲሆን አስከሬን ለመለየት ወደ ሉሙት ወታደራዊ ሆስፒታል ተልኳል።የአደጋውን መንስኤ የሚያጣራ ኮሚቴ ተቋቁሞ እንደሚሰራም አክሏል። ከሄሊኮፕተሮቹ አንዱ የሆነው ኤም 503-3 ሰባት ሰዎችን አሳፍሮ በመንደርደሪያ መንገድ ላይ ወድቋል ተብሏል።ሌላው ፌንኔክ ኤም 502-6 ሌሎች ሶስት ተጎጂዎችን አሳፍሮ በአቅራቢያው በሚገኝ መዋኛ ገንዳ ውስጥ ወድቋል።የግዛቱ የእሳት እና የነፍስ አድን ክፍል አደጋዉ ከባድ እንደነበር ገልጿል፡፡ በመጋቢት ወር የማሌዢያ የባህር ጠረፍ ጠባቂ ሄሊኮፕተር በማሌዢያ አንጋሳ ደሴት በስልጠና  ላይ እያለ በባህር ላይ መዉደቁ ይታወሳል፡፡ፓይለቱ፣ ረዳት አብራሪው እና ሁለት ተሳፋሪዎች በአሳ አጥማጆች በመገኘታቸዉ ከሞት ተርፈዋል፡፡ በስምኦን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
5 36313Loading...
28
ከ1.5 ሄክታር በላይ ደን ያቃጠለው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ በባሌ ዞን ጎሮ ወረዳ ልዩ ስሙ ባሌ ጋዱላ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ የሚገኘዉን ሰፊ ደን በማቃጠል ጉዳት ያደረሰው ግለሰብ በእስራት ተቀጥቷል፡፡ ተከሳሽ አብርሀም ጌታሁን የተባለው ግለሰብ በባሌ ዞን ባሌ ጋዱላ አካባቢ በሚገኘው የባሌ ተራራ ጥቅጥቅ ደን ውስጥ በመግባት ከ 1.5 ሄክታር በላይ ደኖችን በማቃጠል እንዲወድሙ በማድረጉ በፖሊስ በቁጥጥር ስር መዋሉን የጎሮ ወረዳ ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ክፍል ኃላፊ የሆኑት ረዳት ኢንስፔክተር ፈቲ ሱፊያን ገልፀዋል። ፖሊስ ተከሳሹን በቁጥጥር ስር ካዋለው በኃላ በበቂ ምርመራ በማጣራት የምርመራ መዝገቡን  ለአቃቤ ህግ የላከ ሲሆን አቃቤ ህግም የዱር እንሰሳት እንክብካቤና የአካባቢ ጥበቃ አዋጅ በመተላለፉ ክስ መስርቶበታል። የተመሰረተውን ክስ ሲመለከት የቆየው የጎሮ ወረዳ ፍርድ ቤት ተከሳሽ አብርሀም ጌታሁንን በአስር አመት እስራት እንዲቀጣ የወሰነበት መሆኑን የጎሮ ወረዳ ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ክፍል ኃላፊ የሆኑት ረዳት ኢንስፔክተር ፈቲ ሱፊያን ለብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል። በመዓዛ ኃይሌ #ዳጉ_ጆርናል
5 4509Loading...
29
Media files
5 3801Loading...
30
የቻይና መንግስት ድጋፍ ያለዉ ፓርቲ በማልዲቭስ ምርጫ ከፍተኛ ድል በማግኘት አሸነፈ የማልዲቪያ ፕሬዝደንት መሀመድ ሙኢዙ ፓርቲ እሁዱ እለት በተካሄደዉ ምርጫ በከፍተኛ ድምፅ ማሸነፋቸዉን የቅድመ ምርጫ ውጤቶች አመላክተዋል፡፡ የህዝብ ብሄራዊ ኮንግረስ (ፒኤንሲ) ፓርላማውን ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር ከሚያስችለዉ ከ93 መቀመጫዎች ዉስጥ ሰባዉን አሸንፏል ሲሉ የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። ውጤቱ ማልዲቪስ ከቀድሞ አጋሯ ህንድ ፊቷን ወደ ቻይና ልታዞር እንደምትችል አመላክቷል፡፡ በቀድሞው ፕሬዝዳንት ኢብራሂም መሀመድ ሶሊህ የሚመራውና በህንድ መንግስት ከፍተኛ ድጋፍ የሚደረግለት የማልዲቪያ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኤምዲፒ) በቀድም ፓርላማ 65 መቀመጫዎች የነበሩት ሲሆን አሁና ላይ በመቃወም 15 መቀመጫዎችን ብቻ ማግኘቱን የሀገር ውስጥ የዜና ምንጭ ሚሃሩ ዘግቧል።ከተወዳዳሪዎቹ 41 ሴቶች መካከል ሶስት እጩዎች ብቻ መመረጣቸውን ሚሃሩ ዘግቧል። ውጤቱን ለማፅደቅ አንድ ሳምንት የሚቆይ ሲሆን አዲሱ ምክር ቤት ከግንቦት ወር መጀመሪያ አንስቶ ስራ ይጀምራል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ፒኤንሲ እና አጋሮቹ በስልጣን ላይ ባለው ፓርላማ ውስጥ ስምንት መቀመጫዎች ብቻ የነበራቸው ሲሆን ይህም ሙኢዙ በፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ካሸነፉ በኋላ በራሱ ፖሊሲ እንዳይራመድ አስቸጋሪ አድርጎታል።1,192 ትናንሽ ደሴቶች ያሏት ማልዲቭስ፣ በምድር ወገብ ላይ 800 ኪ.ሜአካባቢ ተበታትነው የሚገኙት በአየር ንብረት ቀውስ ምክንያት ለባህር ጠለል ከፍታ ተጋላጭ ከሆኑ ሀገራት አንዷ ናት። የሀገሪቱ መሪ የ45 አመቱ የቀድሞ የኮንስትራክሽን ሚኒስትር ሙኢዙ፣ መሬትን መልሶ ማልማት እና ደሴቶችን መገንባት ችግሩን ለመፍታት እንደሚያስችል ቃል ገብተዋል፣ ነገር ግን የአካባቢ ጥበቃ ባለሙያዎች እንዲህ ያለው እርምጃ የጎርፍ አደጋን እንደሚያባብስ ይከራከራሉ። በኤደን ሽመልስ #ዳጉ_ጆርናል
5 6011Loading...
31
በናሚቢያ የባህር ዳርቻ 10 ቢሊዮን በርሜል ነዳጅ ዘይት ተገኘ በናሚቢያ 10 ቢሊየን በርሜል የሚገመት ነዳጅ ዘይት መገኘቱን የፖርቱጋል የነዳጅ ዘይት ኩባንያ ጋልፕ ኢነርጂ አስታዉቋል።ኩባንያው በናሚቢያ የባህር ዳርቻ በሞፔን መስክ ያደረገውን የነዳጅ ፍለጋ የመጀመሪያ ምዕራፍ ካጠናቀቀ በኋላ የነዳጅ ሀብቱን ማግኘቱን ገልጿል። በሞፔን ብቻ፣ ተጨማሪ ፍለጋ ጉድጓዶች ከመቆፈራቸዉ ፊት፣ የሃይድሮካርቦን ምርት እና ቦታው ላይ 10 ቢሊዮን በርሜል ነዳጅ ወይም ከዚያ በላይ ይገኛለ ሲል ኩባንያዉ አስታዉቋል፡፡ሞፔን በሚገኝበት በናሚቢያ ኦሬንጅ ተፋሰስ ውስጥ በቅርብ ዓመታት ውስጥ ሰፊ የነዳጅ እና የጋዝ ክምችት ተገኝቷል። ግኝቶቹ በደቡባዊ አፍሪካዊቷ ሀገር ናሚቢያ በአለም አቀፍ የነዳጅ ኢንዱስትሪ ውስጥ ትልቅ ቦታ እንድትይዝ አድርጓታል።ሀገሪቱ በ2030 የነዳጅ ምርቷን በመጨመር ወደ ኦፔክ ወደ ዘይት አምራቾች ድርጅት ለመግባት እየጣረች ትገኛለች፡፡ በአበረ ስሜነህ #ዳጉ_ጆርናል
5 6015Loading...
32
ሕወሓት ብልፅግናን ለመቀላቀል በድርድር ላይ ነው ተባለ ሕወሓት ከአራት ዓመት በፊት “ሕገ – ወጥ ነው” ያለውን ገዥውን ፓርቲ ብልፅግና ለመቀላቀል ተከታታይ ድርድሮች እያደረገ መሆኑን ዳጉ ጆርናል ፤ ዋዜማ ከተለያዩ ምንጮች አሰባስቤ ሰራሁት ያለችዉ ዘገባ ያመለክታል። ከሁለት ዓመት ደም አፋሳሽ ጦርነት በኋላ የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት የፈረመው ሕወሓት ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ በሊቀመንበርነት የሚመሩትን ብልፅግናን በመቀላቀል በሀገራዊ ጉዳዮች አብሮ ለመስራት መስማማቱን ቢገልፅም ፓርቲውን ለመቀላቀል ቅድመ ሁኔታ አስቀምጧል። ከብልፅግና በፊት የነበረው ኢሕአዴግ እኩል የስራ አስፈፃሚና ማዕከላዊ ኮሚቴ ውክልና ያላቸው አራት ንዑስ ፓርቲዎች ጥምረት ሲሆን ብልፅግና ግን አንድ ወጥ ፓርቲ ነው። የብልፅግና የፓርቲ ውክልና በህዝብ ብዛት የሚወሰን እንጂ እንደ ኢሕአዴግ አባል ድርጅቶች እኩል ውክልና አይኖራቸውም። አሁንስ እየተደረገባቸው ባለው ድርድር ሕወሓት የብልፅግና ፓርቲ ሕገ-ደንብ ተሻሽሎ በፓርቲ ውስጥ አባል ድርጅቶች እኩል የማዕከላዊ ኮሚቴና የስራ አስፈፃሚ ውክልና እንዲኖራቸው ይፈልጋል። ብልፅግና ግን ሕወሓት የተናጠል ህልውናውን አክስሞ ብልፅግናን እንዲቀላቀልና ውክልናውም በትግራይ ህዝብ ቁጥር ልክ የሚወሰን መሆኑን ይገልፃል። የሕወሓት ሊቀ መንበር ደብረፅዮን ገብረሚካዔል በአዲስ አበባ ተገኝተው ይህን ድርድር የጀመሩት ሲሆን ከሁለት ሳምንት በኋላ የብልፅግና ምክትል ሊቀመንበር አደም ፋራህ ወደ መቀሌ ተጉዘው በጉዳዩ ላይ በስፋት ተነጋግረዋል። በሕወኋት በኩል ብልፅግናን መቀላቀል “ስህተት ነው …አስፈላጊም አይደለም” ብለው የሚያምኑ አመራሮች ቢኖሩም ፣ ውህደቱ ለትግራይ ችግሮች መፍትሄ ለማምጣት ጠቀሜታ አለው፣ በተለይም የትግራይን ፀጥታና ደህንነት ለመስጠበቅ ከብልፅግና ጋር አብሮ መቆም አስፈላጊ ነው ብለው የሚያምኑም አሉ። Via ዋዜማ #ዳጉ_ጆርናል
5 69128Loading...
33
Media files
5 3405Loading...
34
በአቡዳቢና ዱባይ የሚገኙ ኢትዮጲያዉያን ከጉዞ ሰነድና ቪዛ ጋር ተያይዞ ያሉ የአገልገሎት አሰጣጥ ችግሮች እንዲፈቱ ተጠየቀ በአቡዳቢና ዱባይ አካባቢ እየተሰጠ ባለው የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎቶች ከዚህ ቀደም የሚነሱ ቅሬታዎች እየተፈቱ መሆኑን የኮሚኒቲ አባላት፣ ተወካዮችና አመራሮች ተናግረዋል።በኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት የተመራ ልዑክ በአቡዳቢና ዱባይ ሚሲዮኖች የሚሰጡ የዜግነት አገልግሎቶችን ያሉበትን ሁኔታ ተመልክቶ ከሚሲዮን መሪዎችና ኮሙኒቲ ተወካዮች ጋር ተወያይቷል። በውይይቱ በሚሲዮኖቹ ከፓስፖርት እድሳትና ተያያዥ አገልግሎቶች ጋር በተያያዘ ዜጎች ላቀረቡት ጥያቄ የተሰጠው ምላሽ የሚደነቅ ቢሆንም፤ ከጉዞ ሰነድና ቪዛ ጋር ተያይዞ ያሉ የአገልገሎት አሰጣጥ ችግሮች እንዲፈቱ ተጠይቋል፡፡በተጨማሪም የመረጃ ልውውጥ ክፍተት፣ ሐሰተኛ ማስረጃ፣ የጉዞ ሰነድ (ሊሴ ፓሴ)፣ የበይነ-መረብ አጭበርባሪዎች መበራከት እንዲሁም ከዜግነት አገልግሎት ጋር ያሉ ክፍተቶች መኖራቸው ተጠቁሟል፡፡ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት÷ ተቋሙ 11 የሪፎርም አጀንዳዎችን ቀርጾ ወደ ስራ በመግባቱ ከዜጎች አገልግሎት ጋር በተያያዘ እየታዩ ያሉ ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴዎች መታየታቸውን ተናግረዋል።የሪፎርሙ ስራ ሙሉ ለሙሉ ሲጠናቀቅ በዘርፉ የተስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ እንደሚያስችልም ገልጸዋል። ከሰነድ አልባና ከዜግነት አገልግሎት ጋር ያሉ ስራዎች ከሀገር ደህንነት ጋር በጥብቅ የተቆራኘ በመሆኑ በጥንቃቄና በህግ አግባብ ብቻ መሰራት እንዳለበት አስገንዝበዋል።ልዑኩ ባደረገው ጉብኝት የዱባይ ሚሲዮን ቴክኖሎጂን በመጠቀም ረገድ የሚከተለው አሰራር እንደተሞክሮ ሊወሰድ የሚገባ መሆኑን እንደተመለከተ ዋና ዳይሬክተሯ ተናግረዋል። #ዳጉ_ጆርናል
5 6644Loading...
35
ስፓይሲ ገርልስ በቪክቶሪያ ቤካም 50ኛ ዓመት የልደት በዓል ላይ ዳግም ተገናኙ አምስቱም የስፓይሲ ገርልስ አባላት እንደገና ተገናኝተዋል፣ ቅዳሜ ምሽት ቪክቶሪያ ቤክሃም፣ ሜላኒ ብራውን፣ ኤማ ቡንተን፣ ጌሪ ሆርነር እና ሜላኒ ቺሾልም በመባል የሚታወቁት የእንግሊዝ የድምፃዊያን ቡድን የቪክቶሪያን 50ኛ ዓመት የልደት በአል በለንደን ለማክበር ተገናኝተዋል። የባንዱ አባላት ልክ እንደ 1997 በማመሰል ታዋቂ የሆነውን ስቶፕ የተሰኘውን ስራቸውን አቅርበዋል። ዴቪድ ቤካም ስነስርዓቱን በኢንስታግራም ገፁ ላይ አጋርቷል፣ እንዲሁም አብሮ ሲዘፍን ታይቷል። የቪክቶሪያ ባል እና የ48 አመቱ የቀድሞ የእንግሊዝ ካፒቴን ቤካም ደስተኛ ሆኖ እንደነበር ማስተዋል ተችሏል። በሜይፌር በሚገኘው የኦስዋልድ የግል  ክለብ ውስጥ በተካሄደው የልደት ድግስ ላይ እንደ ቶም ክሩዝ፣ ሳልማ ሃይክ፣ ሮዚ ሀንቲንግተን-ዊትሊ እና ጎርደን ራምሴ የመሳሰሉ ታዋቂ ሰዎች ተገኝተውበታል። በሰምሃል አለባቸዉ #ዳጉ_ጆርናል
1190Loading...
ቼልሲ በሌላ የለንደን ቡድን ከሶስት በላይ ጎሎች ተቆጥረውበት በፕሪሚየር ሊጉ ተሸንፎ አያውቅም ። መድፈኞቹ 5 ግቦችን ማስቆጠር ችለዋል 😯 #ዳጉ_ጆርናል
Show all...
🔥 26👎 6🥰 4👍 3😁 1
ካይ ሀቨርትዝ የቀድሞ ቡድኑ ላይ በማስቆጠር ደስታውን አክብሯል 🥶 በ2021ዱ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ ማንችስተር ሲቲ ላይ ብቸኛውን ጎል አስቆጥሮ ቼልሲ ዋንጫ ማንሳቱ ይታወሳል 😬 #ዳጉ_ጆርናል
Show all...
😁 21👏 5👍 3 1
የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ  ጨዋታ ተጠባቂ ጨዋታ       አርሰናል 5-0 ቼልሲ ⚽️ ትሮሳርድ ⚽️⚽️ ዋይት ⚽️⚽️ ሀቨርትዝ ጎሎቹን ለመመልከት 👉 @mikoethio #ዳጉ_ጆርናል
Show all...
😁 8👍 3🔥 3
የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ተጠባቂ ጨዋታ            አርሰናል 3-0 ቼልሲ ⚽️ ትሮሳርድ ⚽️ኋይት ⚽️ ሀቨርት ጎሎችን ለመመልከት 👉 @mikoethio #ዳጉ_ጆርናል
Show all...
8👏 3😁 2
የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ተጠባቂ ጨዋታ         አርሰናል 1-0 ቼልሲ ⚽️ ትሮሳርድ ጎሎችን ለመመልከት 👉 @mikoethio #ዳጉ_ጆርናል
Show all...
👍 18 2
ተጠባቂ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ አርሰናል ከ ቼልሲ ማን ያሸንፋልAnonymous voting
  • አርሰናል (መድፈኞቹ)
  • ቼልሲ (ሰማያዊዎቹ)
0 votes
👍 16👎 8
የእስራኤል ባለስልጣናት አስታራቂዎችን እያጠቁ ነዉ ስትል ኳታር ወቀሰች የኳታር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማጅድ አል-አንሷሪ አንዳንድ የእስራኤል ሚኒስትሮች ኳታርን በጋዛ ጦርነት ድርድር ላይ ስውር ዓላማ እንዳላት አድርገዉ መናገራቸዉ ስህተት ነዉ ሲሉ ወቅሰዋል፡፡"በእኛ የሽምግልና ጥረታችን እና በጋዛ የሰብአዊነት ስራን በደንብ ከሚያውቁት የእስራኤል ባለስልጣናት እንዲህ ያሉ መግለጫዎች መዉጣታቸዉ በጣም አበሳጭቶናል ብለዋል፡፡ አስታራቂውን አካል ማጥቃት ቁርጠኝነትን አያሳይም። ከእስራኤላውያን ወገኖቻችን እያገኘን ያለነው ግን ይህንን ነው ፤ድብቅ ዓላማ እንዳለን ተከስሰናል። ግን ይህ ከእውነት የራቀ ነው። ይህንን ግጭት ለማስቆም ብቸኛው መንገድ ሽምግልና ነው ሲሉ አክለዋል፡፡ በጋዛ ያለውን እልቂት ለማስቆም እና የእስራኤል ምርኮኞችን ለመመለስ ሂደቱ ላይ እምነት ከሌለ የሽምግልናዉን የተሳካ ውጤት ለማየት በጣም አስቸጋሪ እንደሚሆን ይሰማኛል ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ አል-አንሷሪ አክለውም “የኳታር የሽምግልና ጥረቶች እስከቀጠሉ ድረስ፣ የሐማስ የፖለቲካ ቢሮ በዶሃ መገኘቱን የሚያረጋግጥ ምንም ምክንያት የለም። ይህ ቢሮ የተከፈተው ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር በመቀናጀት - በሁለቱም ወገኖች መካከል ለሽምግልና ዓላማ ነው ብለዋል። እስካሁን ድረስ በዚህ ረገድ የተለወጠ ነገር የለም” በማለት ተናግረዋል፡፡የኳታር ጠቅላይ ሚንስትር ሼክ መሀመድ ቢን አብዱራህማን ቢን ጃሲም አል ታኒ ቀጠናዊ ውጥረቶችን በማርገብ እና የእስራኤል በጋዛ ላይ ያደረሰችውን አውዳሚ ጦርነት ለማቆም መስራታቸውን ቀጥለዋል ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማጅድ አል አንሳሪ ተናግረዋል። በሌላ በኩል በካን ዮኒስ በሚገኘው ናስር ሆስፒታል በጅምላ መቃብር ውስጥ ቢያንስ 35 ተጨማሪ አስከሬኖች መገኘታቸውን የሲቪል መከላከያ ሰራተኞች ገልፀዋል፡፡ በአጠቃላይ በሆስፒታሉ የተገኙ አስከሬኖች ቁጥር ቢያንስ 310 ደርሷል።በካን ዮኒስ የተገደሉት ፍልስጤማውያን ዘመዶቻቸዉን ለማግኘት በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ የእስራኤል ወታደሮች ከተማዋን ለቀው ከወጡበት ጊዜ አንስቶ የአስከሬን ፍለጋ ናስር ሆስፒታል ዉስጥ በትጋት እየፈለጉ ይገኛል። በስምኦን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
Show all...
👍 20👎 1
አርቲስት አማኑኤል ሀብታሙ በፀጥታ ሀይሎች ተያዘ አርቲስት አማኑኤል ሀብታሙ በዛሬው እለት አመሻሹን ሚያዚያ 15ቀን 2016ዓ.ም ወደ እስራኤል ሊያቀና በነበረበት ወቅት ላይ በፀጥታ ሀይሎች መያዙን የአርቲስቱ የቅርብ ምንጮች ገልፀዋል። ጉዳዩን አስመልክቶ የአርቲስቱ የቅርብ ወዳጅ በማህበራዊ ትስስር ገፁ "ያያ ዘልደታ" ጉዳዩን አስመልክቶ ተከታዩን አስፍሯል። " ዛሬ ከመሽ ዕብደት በሕብረት የተሰኘውን አዲሱን ትያትር ለማሳየት ወደ ሃገረ እስራኤል ለመሄድ ዝግጅቱን ጨርሶ እነሆ አሁን ከመሸ ከኤርፖርት ተይዞ ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ተወስዷል::" ሲል አስታውቋል። እስከ አሁን ባለው ሂደት ከመንግስት አካላት ስለ ጉዳዩ የተሰጠ ምላሽም ሆነ ማብራሪያ የለም። #ዳጉ_ጆርናል
Show all...
🤔 6
በአሜሪካ ዩኒቨርሲቲዎች ዉስጥ የፍልስጥኤም ድጋፍ እየተስፋፋ መምጣቱ ተነገረ የአሜሪካ ዩኒቨርሲቲዎች እየበረታ የመጣውን የተማሪዎች ተቃውሞ ለማብረድ ጥረት በማድረግ ላይ ናቸው።እስራኤል በጋዛ የምታካሂደውን ጦርነት የተቃወሙ ከ100 በላይ የኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውም ተቃውሞውን ወደሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች እያሰፋው ነው ተብሏል። ፖሊስ ትናንት ምሽት በኒውዮርክ ዩኒቨርሲቲ የነበረውን ተቃውሞ ለማስቆም በመግባት በርካታ ተማሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉ ተገልጿል።በየል፣ በርክሌይ፣ ማሳቹሴትስ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (ኤምአይቲ) እና ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ተማሪዎች ማደሪያቸውን በዳስ አድርገው ተቃውሟቸውን እያሰሙ ሲሆን፥ ሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ ከውጭ እንግዶች እንዳይገቡ በሩን ዝግ አድርጓል። 108 ተማሪዎች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ያደረገው ኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲም የገጽ ለገጽ ትምህርት አቁሟል።ተማሪዎቹ እስራኤል በጋዛ ላይ የምትፈጽመውን ድብደባ ዩኒቨርሲቲዎቻቸው እንዲያወግዙ እንዲሁም ለእስራኤል የጦር መሳሪያ ከሚያቀርቡ ኩባንያዎች ጋር ያላቸውን ግንኙነት እንዲያቋርጡ ጠይቀዋል።የፍልስጤም ደጋፊዎች በእስራኤል ላይ ተቃውሟቸውን ሲገልጹ ያስተላለፏቸው “ጸረ ሴማዊ መልዕክቶች” ግን እስራኤላውያን ተማሪዎችን ስጋት ውስጥ መጣሉን ነው አሶሼትድ ፕርስ የዘገበው። አይሁዳውያን ተማሪዎች የፍልስጤሙ ሃማስ አሁንም ድረስ እስራኤላውያንን አግቶ መያዙንና ከ1 ሺህ 100 በላይ እስራኤላውያንን ህይወት መቅጠፉን ያነሳሉ።ቁጥራቸው አነስ ይበል እንጂ እስራኤላውያን ተማሪዎችም በኮሎምቢያ እና ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ድምጻቸውን አሰምተዋል ተብሏል።ዩኒቨርሲቲዎቹ የተማሪዎቹን ጥያቄ ለመመለስ ከመሞከር ከመሆን ይልቅ ተማሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋል ላይ መጠመዳቸው ተቃውሞውን እያስፋፋው መሆኑ ተገልጿል። በአሜሪካ ዩኒቨርሲቲዎች እየተስፋፋ ስለመጣው የተማሪዎች ተቃውሞ የተጠየቁት ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን፥ ጸረ ሴማዊ ይዘት ያላቸው መልዕክቶች መተላለፋቸውን ተቃውመዋል።ፕሬዝዳንቱ “በፍልስጤም ምን እየተካሄደ እንደሆነ የማያውቁ” ያሏቸውን ወገኖችም ተቃውመዋል።የእስራኤል ዋነኛ አጋር በሆነችው አሜሪካ የጋዛው ጦርነት ከተቀሰቀሰ ጀምሮ በርካታ የአደባባይ ተቃውሞዎች ቢደረጉም ዋሽንግተን በቴል አቪቭ ዙሪያ የማይነቃነቅ አቋም እንዳላት የ26 ቢሊየን ዶላር ድጋፍ በማጽደቅ አሳይታለች። በስምኦን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
Show all...
👍 38🕊 10 2👎 1👏 1