✨KB Orthodox✝️
Open in Telegram
ኦርቶዶክሳዊ ጥቅሶችና መዝሙሮችን ያገኛሉ✝️ ሌላኛውን ቻናላችንን ይቀላቀሉ 👉 @KB_Creatives
Show more1 808
Subscribers
-524 hours
-117 days
-4230 days
Posts Archive
1 807
ጠቃሚ ምክር!
ገንዘብ ወዳጅ አትሁን ከባለፀጋም ሽሽ ትሑት ሰው ፈልግ እንጂ በእግዚአብሔር ዘንድ ክቡር ትሆን ዘንድ የባሕርይ ፍላጎትህንና ምኞትህን ሁሉ ተው የዚህን ዓለም ትርፍ ሁሉ ንቀህ አቃልለህ ተወው እጅህን ለመቀበል ያላይደለ ለመስጠት ዘርጋ!
(መፅሐፈ ወግሪስ በአባ ገብረኪዳን)
1 807
መልካም አድርግና እርሳው!
ስላደርግኸው ስለዚህ ነገር ማንኛውንም ዓይነት ውዳሴም ሆነ ሙገሳ አትሻ። መልካም ያደረግህለት ሰው አንተ እንዳደረግህለት ለአንተ መልካም የሆነውን አጸፋ እንዲመልስልህ ወይም አንተ አንደተንከባከብከው እርሱም እንዲንከባከብህ አትጠብቅ።
መልካም ስታደርግ በምላሹ መልካም ዋጋ አገኛለሁ ብለህ በመጠበቅ ላለመሆኑ እርግጠኛ ሁን! መልካም የምታደርገው መልካም ማድርግን ስለምትወድ ወይም መልካም ከማድረግ መከልከል ስለማትችል ለመሆኑ እርግጠኛ ሁን። መልካም መሆን በውስጥህ ያለ ጠባይ ይሁን። መልካም ጠባይ እንደ መተንፈስ ምንም ዓይነት ጥረት የማይጠይቅ ግብታዊ ነገር ይሁን።
እንዲህ ያለውን ነገር የምትረሳው ከሆነ እግዚአብሔር በዚህ ምድርም ሆነ በሚመጣው ዓለም ያስታውስሃል። መልካም ማድረግህን የምታስታውሰውና በውስጥህ ይዘኸው የምትቆይ ከሆነ ግን ታጣዋለህ።
✍🏻ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
1 807
መናገር ባለብህ ሰአት ብቻ ተናገር ... "አስተውል ከአይሁድ ጫጫታ ይልቅ የክርስቶስ ዝምታ ነው ጲላጦስን ያስጨነቀው"
አስተዋይ ግን ዝም ይላል(ምሳሌ 11:12)
1 807
✨እግዚአብሔርን ፈርታችሁ.....
ሥራ ስትሠሩ እግዚአብሔርን ፈርታችሁ ሥሩ : ስትናገሩም እግዚአብሔርን ፈርታችሁ ተናገሩ :ስታገቡም እግዚአብሔርን ፈርታችሁ አግቡ : ስትነግዱ እግዚአብሔርን ፈርታችሁ ነግዱ : መንገድ ስትሔዱም እግዚአብሔርን ፈርታችሁ ሂዱ : ስታስተዳድሩም እግዚአብሔርን ፈርታችሁ አስተዳድሩ ።
🗣አባ ገብረ ኪዳን
1 807
‛‛እግዚአብሔር ድካምህን እንደሚያውቅና
እስካሁን ድረስ እንደሚወድህ እርግጠኛ ሁን!
በኃጢአት ውስጥ ብትሆንም
እግዚአብሔር ሊያድንህ፣
ወደ እርሱ ሊያቀርብህና ወደ ቀደመ ደረጃህ
ሊመልስህ እንደሚሠራ እመን።’’
✍️አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ
1 807
በወዳጅነት ብዙ አመታትን
የዘለቁ ወዳጆችን ካየህ
ስንት ጊዜ ይቅር ተባብለው ይሆን
እዚህ የደረሱት ማለትን አትዘንጋ።
✍️ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ
1 807
"ሰው ቢጠላችሁ፣ ሰው ቢሸሻችሁ፣ ስታጡ ጓደኛም ቢከዳችሁ፣ ምንም ብትሆኑ ፤ ማለዳም ተነስታችሁ ገንዘብ ብታጡ፣ ስራም ብታጡ ቢቸግራችሁ ፣ ዳኛም ባይፈርድላችሁ፤ ዝም ብላችሁ አንድ ቃል በሉ ... 'እግዚአብሔር ከእኔ ጋር ነው' ።
1 807
"ምላስህን መግራት የጀመርክ ቀን፣ የነፍስህን ደጅ መቆለፍ ጀምረሃል። ከመናገርህ በፊት ቃላትህን በፍቅርና በእውነት ሚዛን ላይ መዝን። በቁጣ የተነገረ ቃል የጥፋት ዘር ነው፤ በትዕግሥት የተነገረ ቃል ግን የፈውስ ሥር ነው።"
ምንጭ፦ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣
"የመጀመሪያውና ሁለተኛው የቆሮንቶስ መልእክት ትርጓሜ"
1 807
"ዓይኖችህን በማዕበሉ ላይ ሳይሆን ነፋስን በሚያዝዘው አምላክ ላይ አኑራቸው። እምነት ማለት ፍርሃት አለመኖር አይደለም፤ በፍርሃትህ መካከል የእግዚአብሔር መገኘት፣ ነው እንጂ።"
"Do not let your eyes be fixed on the storm, but on the One who commands the wind. Faith is not the absence of fear, but the presence of God in the midst of your fear."
ምንጭ፦ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ፣ "ስለ፣ ፈተናዎች" የተሰጠ ትምህርት (በቅዱስ ማርቆስ ካቴድራል የተሰጠ ስብከት፣ ካይሮ)
1 807
Repost from የልብ ጥበብ
ብልጥ ከሆንክ የዋህ ሁን።
በቅንነት ሂሳባዊ ግንኙነት የለም!
ቅንነት ገንዘብ የማይገዛው ሀብት ነው።
ሁከት የማይነጥቀው ሰላም፤
መጠላት የማያሸሸው ፍቅር፤
መነጠቅ የማይቀማው ደስታ፤
መረገጥ የማይገታው የልብ ትህትና።
ጥበብም እውቀትም ፣እውነትም ፣ገንዘብም ሊኖርህ ይችላል ቅን ካልሆንክ ግን አሁንም ድሀ ነህ።
ጥበብ ቢኖርህ ቅን ካልሆንክ ሀዘንተኛ ነህ።
እውቀት ቢኖርህ ቅን ካልሆንክ ግብዝ ነህ።
እውነት ቢኖርህ ቅን ካልሆንክ ሰነፍ ነህ።
ገንዘብ ቢኖርህ ቅን ካልሆንክ ብቸኛ ነህ።
በቅንነት እና በትህትና ታጥቦ የሚሰጥ ስጦታ ፍቅር ይባላል እሱ ደግሞ ሀያላኑን ሁሉ ያንበረከከ ጥልቅ ማንነት ነው።
ዓለምን መግዛት ካሻህ ቅንና ትሁት ሁን🤝
#ቅንነት #የልብ_ጥበብ
© የልብ ጥበብ - t.me/Ye3773ab
1 807
✝ እንኳን ከዘመነ ጸደይ ወደ ዘመነ ክረምት መሸጋገሪያ ለሆነችው ዕለት በሰላም አደረሳችሁ !
ቅድስት ቤተ ክርስቲያ] ሁሉ ነገሯ በሥርዓት ነውና ዓመቱን በአራት ዘመናት ከፍላ ትጠቀማለች ። እሊሕም ዘመናት መጸው [ጽጌ] ፣ ዘመነ ሐጋይ [በጋ] ፣ ዘመነ ጸደይ [በልግ] እና ዘመነ ክረምት ናቸው ። ዘመናቱ ወቅቶችን ከመለየትና ከማሳወቅ ባሻገር የእኛ ሕይወትም ምሳሌዎች ናቸውና ልብ ልንላቸው ይገባል ።
በተለይ ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ "ሽሽታችሁ [ስደታችሁ] በክረምትና በሰንበት እንዳይሆን ጸልዩ" ብሎናልና [ማቴ.፳፬፥፳] (24:20) አብዝተን ልንጸልይ ይገባናል ። በዘመነ ክረምት ቅጠል እንጂ ፍሬ የለበትምና ፍሬ ምግባር ሣናፈራ ሞት እንዳይመጣ ፤ አንድም ክረምት የዝናብና የጭቃ ጊዜ በመሆኑ እንኩዋንስ ለስደት ለኑሮም አይመችም ። አበው ስለ ዝናም ሲያስተምሩ ዝናም ወደ መሬት ሲወርድ አንድ ጊዜ ዠቅ ብሎ በሙላ አለመውረዱ መከራ በመጠን በአቅም ለመሰጠቱ ምሳሌ ነው ይሉናል ። ወርኃ ክረምት በልዩነት የመከራ ወቅት ምሳሌ ነውና እንደ ሊቃውንት እንዲህ ብለን እንጸልይ :-
"በዝንቱ ፡ ክረምት ፡ በመዋዕሊነ ፡ እንበለ ፡ ፍሬ ፡ እንዘ ፡ በቆጽል ፡ ኀሎነ ፡ ናስተበቁዐከ ፡ እግዚኦ ፡ ኢይኩን ፡ ጉያነ ።"... #ትርጉም [ ክረምት ፡ በተባለ ፡ በእኛ እድሜ ፡ ፍሬ ፡ ሳናፈራ ፡ በቅጠል ፡ /ያለ ፡ መልካም ፡ ሥራ/ ፡ ሳለን : አቤቱ ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ ስደትን ፡ አታምጣብን ፡፡ ]
ስለ ዝናም ጸልዩ !
1 807
Repost from N/a
ስጦታና ስጦታ አሰጣጥ የፍቅር መለኪያዎች ናቸው።
ስጦታ ፦
- ጊዜን
- ማንነትን
- ሰላምን
ካካተተ የፍቅር ልክ ፅኑ ወደ መሆን ይደርሳል።
ምክንያቱም እነዚህ ስጦታዎች ልዩነትን አንድ አካል የማድረግ ሀይል ስላላቸው።
ስጦታ አሰጣጥ፦
- በትህትና
- ምላሽ በሌለው ጊዜ
- ምላሹ በከፋም ጊዜ
ሲሆን የፍቅርን እውነተኛነት ያመዝናል።
ፍቅርህን መለካት ከፈለክ፦
ምን እንደምትሰጥ ብቻ ሳይሆን
እንዴት እንደምትሰጥም ተመልከት።
በትህትና ስጥ።
ምንም ሳትጠብቅ ስጥ።
መልሱ መጥፎ ቢሆንም ስጥ።
ያኔ ነው ፍቅርህ እውነተኛ የሚሆነው።
#ስጦታ #ስጦታ_አሰጣጥ #ፍቅር #ትህትና #የልብ_ጥበብ
© የልብ ጥበብ - t.me/GO3773
