en
Feedback
የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን

የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን

Open in Telegram
5 357
Subscribers
No data24 hours
-97 days
+730 days
Posts Archive
ባለስልጣን መ/ቤቱ በ2018 በጀት ዓመት ሊያሳካቸው ካቀዳቸው ተግባራት አንጻር ተቋሙ ብቻውን ሊያሳካ የማይችላቸውን ተግባራት በአግባቡ በመለየት ለተቋሙ እገዛ ሊያደርጉለት ከሚችሉ 6 ሴከተሮች እና 4 ሲቪክ ማህበራት ጋር የጋራ በማድረግ እንዲሁም የስምምነት ሰነድ ፊርማ በማከናወን ወደ ተግባር መግባቱን አቶ አምላኩ ገልጸዋል ፡፡ በሪፖርታቸውም ከተቋማቱ ጋር በመሆኑ የተከናወኑ ተግባራት የተገኙ ውጤቶች እና የነበሩ ክፍተቶች በዝርዝር የቀረቡ ሲሆን በመልካም አስተዳደር እና አገልግሎት አሰጣጥ ረገድም በተቋሙ የተለዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮች የተወሰዱ የመፍትሔ እርምጃዎች እና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ለመድረኩ ተሳታፊዎች ተናግረዋል፡፡ በመጨረሻም በጋራ የአገልግሎት አሰጣጡን ለማሻሻል፣ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት ተቋማት የተሰጣቸውን በቅንጅት የመስራት ኃላፊነት በአግባቡ መወጣት እንደሚገባቸው የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ኢዘዲን ሙስባህ አስገንዝበዋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

ባለስልጣኑ የ2018 በጀት ዓመት የቅንጅታዊ ትስስር፣የመልካም አስተዳደርና የአገልግሎት አሰጣጥ የ1ኛ ሩብ ዓመት የእቅድ አፈጻጸም ከባለድርሻ አካላት ጋር ገመገመ፡፡ (ጥቅምት 6 ቀን 2018 ዓ.ም)የ
+9
ባለስልጣኑ የ2018 በጀት ዓመት የቅንጅታዊ ትስስር፣የመልካም አስተዳደርና የአገልግሎት አሰጣጥ የ1ኛ ሩብ ዓመት የእቅድ አፈጻጸም ከባለድርሻ አካላት ጋር ገመገመ፡፡ (ጥቅምት 6 ቀን 2018 ዓ.ም)የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ዛሬ ባካሄደው መድረክ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ኢዘዲን ሙስባህ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት የትምህርት ስልጠና ጥራትና አግባብነትን ለማረጋገጥ ባለስልጣኑ የሚያከናውናቸው በርካታ ተግባራት ቢኖሩትም የሚታቀዱ ስራዎች ጥራታቸውን ለማስጠበቅ፣ ውጤታማ እና የተሳካ እንዲሆን ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት መስራት ይገባል ብለዋል፡፡ በመሆኑም በጋራ እቅዶችን በማቀድ በ1ኛ ሩብ ዓመት የተከናወኑ ተግባራትን ምን እንደሚመስሉ እና የነበሩትን ክፍተቶች ለማረም የጋራ መድረኩ ማስፈለጉን ገልጸዋል፡፡ ወ/ሮ ታጋይቱ አባቡ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅና የጥራት ዘርፍ ሃላፊ እንደገለጹት ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋ ለማፍራት ሁሉም ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅባቸውን ሃላፊነት መወጣትና በጋራ አንድ ላይ በመሆን ውጤታማ ስራን ማከናወን ይገባል የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ በመድረኩ ላይ የባለስልጣኑ የአሠራር ጥራት ቁጥጥር ቡድን መሪ የሆኑት አቶ አምላኩ ተበጀ በ2018 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ቅንጅታዊ ትስስር ስራዎች፣ የመልካም አስተዳደር እና አገልግሎት አሰጣጥ የአንደኛ ሩብ አመት አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል፡፡

አቶ ሽመልስ አያሌው የባለስልጣኑ ሪፎርምና አገልግሎት አሠጣጥ ክትትልና ግምገማ ዳይሬከቶሬት ባለሙያ የመልካም አስተዳደር እና አገልግሎት አሰጣጥ የ2018 ዓ.ም የ1ኛ ሩብ አመት ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን፤በዚህም ከመልካም አስተዳደርና አገልግሎት አሰጣጥ አንጻር ባለስልጣኑ ያከናወናቸውን ተግባራት በሪፖርቱ ዘርዝረዋል፡፡ አቶ ኢዘዲን ሙስባህ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አሰኪያጅ በመርሀ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ማንኛውም ሰራተኛ በቅንነት በታማኝነት በሀላፊነት እንዲሁም ስራውን አለቃው በማድረግና ለተሰጠን ሀላፊነት ትኩረት በመስጠት ምርታማነትን፣ የስራ ተነሳሽነትንና ፍላጎትን በመጨመር የተሰጠውን ሀላፊነት ሰርቶ በማሳየት አደረጃጀቶችን በማስተካከል ለተሻለ ውጤት መዘጋጀት አለበት በማለት መልዕክት ያስተላለፉ የስራ አቅጣጫንም አስቀምጠዋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

ባለስልጣኑ የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት እቅድ ክንውኑን ከጠቅላላ ሰራተኛው ጋር ገመገመ፡፡ (ጥቅምት 6 ቀን 2018ዓ.ም)የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥ
+7
ባለስልጣኑ የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት እቅድ ክንውኑን ከጠቅላላ ሰራተኛው ጋር ገመገመ፡፡ (ጥቅምት 6 ቀን 2018ዓ.ም)የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት እቅድ ክንውኑን ጠቅላላ ሰራተኞችና አመራሮች ገመገሙ፡፡ አቶ ሽመልስ ቦጋለ የባለስልጣኑ የእቅድ በጀት ዝግጅት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ባለሙያ የሩብ ዓመት እቅድ ክንውኑን ያቀረቡ ሲሆኑ በሪፖርቱ የዝግጅት ተግባራት አፈጻጸም፣የቁልፍ ተግባራት አፈጻጸም፣ የአበይት ተግባራት አፈጻጸም፣ያጋጠሙ ችግሮችና የተፈቱበት አግባብ፣የነበሩ ጥንካሬዎችና የተገኙ ውጤቶች እንዲሁም ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ዝርዝር ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን የግልጽነትና ተጠያቂነት ስርዓትን ማሳደግ፣የበጎ አድራጎት ስራዎች፣አገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል የተሰሩ ስራዎችን በሪፖርቱ በማካተት በዝርዝር አቅርበዋል፡፡

ባለስልጣኑ ከቋሚ ኮሚቴው ጋር በጋራ ለመስራት የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ፡፡ (ጥቅምት 5 ቀን 2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ከአዲስ አበ
+3
ባለስልጣኑ ከቋሚ ኮሚቴው ጋር በጋራ ለመስራት የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ፡፡ (ጥቅምት 5 ቀን 2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት የሴቶች ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ጋር ቅንጅታዊ ስራዎችን በጋራ ለመስራት የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ፡፡ የስምምነት ሰነድ ፊርማው አላማ ባለስልጣኑ ከቋሚ ኮሚቴው ጋር በጋራ በመተባበርና በመተጋገዝ ስራዎችን በቅንጅት ለመስራት የህዝቡን ጥያቄ ለመመለስ ችግሮችን በጋራ ለመፍታት ስራዎችን በየጊዜው እየገመገሙ የተሻለ አገልግሎትን ለማህበረሰቡ ለማድረስ እንደሆነ ታውቋል፡፡ የስምምነት ሰነዱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት የሴቶች ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክብርት ሶፍያ አለሙ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ኢዘዲን ሙስባህ ተፈራርመዋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

ሪፖርቱን መሰረት በማድረግ የቋሚ ኮሚቴው አባላቱ ጥቄዎችን ያነሱ ሲሆን ከባለሰልጣኑ አመራሮች ምላሽና ማብራሪያ ተሠጥቶባቸዋል፡፡ የቋሚ ኮሚቴው አባላትም ባለስልጣኑ ሪፎርም ላይ ያለ ተቋም ቢሆንም ለትምህርትና ስልጠና ጥራት መጠበቅ እያከናወነ ያለው ተግባር ጠንካራ መሆኑን ገልጸው የቋሚ ኮሚቴው ድጋፍና ክትትል ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡ የባለስልጣኑ አመራሮችም ሱፐርቪዥኑ ከማህበረሰቡ የሚነሱ ሃሳቦችንና የባለስልጣኑ አሰራር ላይ ችግሮችን ለመፍታት ግልጸኝነትን ለመፍጠር በዘርፉ ላይም የጋራ ግንዛቤን ለማሳደግ የሚያግዝ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

ቋሚ ኮሚቴው የባለስልጣኑን የ2018 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት እቅድ አፈጻጸም ላይ ሱፐርቪዥን አካሄደ፡፡ (ጥቅምት 5 ቀን 2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥ
+4
ቋሚ ኮሚቴው የባለስልጣኑን የ2018 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት እቅድ አፈጻጸም ላይ ሱፐርቪዥን አካሄደ፡፡ (ጥቅምት 5 ቀን 2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት የሴቶች ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በመጡ አካላት የ2018 ዓ.ም የመጀመሪያ ሩብ ዓመት እቅድ አፈጻጸም ላይ ሱፐርቪዥን ተደረገለት፡፡ ክብርት ሶፍያ አለሙ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት የሴቶች ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እንደገለጹት ከተማችን በአለም አቀፍ ደረጃ ካሉ ከተሞች ተወዳዳሪ እየሆነች እንደ መምጣቷ ከተማችንን የሚመጥኑ የዘመኑ የትምህርት ተቋማትን መፍጠር አላማ አድርጎ መስራት እንደሚገባ ገልጸው በዚህ ረገድ ባለስልጣኑ ብቁና ተወዳዳሪ እንዲሁም ውጤታማ ዜጋ መፍጠር አላማው እንደመሆኑ ትኩረት አድርጎ መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ አዘዲን ሙስባህ የ2018 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት እቅድ ክንውን ለቋሚ ኮሚቴው ያቀረቡ ሲሆን የዝግጅት ምዕራፍ ተግባራት፣የቁልፍ ተግባራትና የአበይት ተግባራት አፈጻጸምን እንዲሁም ያጋጠሙ ችግሮችና የተፈቱበት አግባብ የነበሩ ጥንካሬዎችን ድክመቶች እንዲሁም መፍትሄዎቻቸውን በሪፖርቱ ተካተዋል፡፡ከዚህም ሌላ የሚሰጡ አገልግሎቶች በስታንዳርድ መሰረት ጥራት በጠበቀ መልኩ እየተሰጠ እንደሆነና ስራዎችን በቴክኖሎጂ በመታገዝ ለተገልጋይ አገልግሎትን ለመስጠት እየተሰራ እንደሆነ፤እንዲሁም ሌብነትና በልሹ አሰራርን በመከላከልና የተጠያቂነት ስርዓትን በማስፈን እየተሰራ እንደሆነ አብራርተዋል፡፡

በሰነዱ ላይም በቅርጫፍ ፅ/ቤቱ አገልግሎት ፈላጊ ተገልጋዮች እና ባለድርሻ አካላት የሚፈልጉትን አገልግሎት በፍትሀዊነት ለመስጠት እና ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅባቸውን ሚና በውጤታማነት እንዲወጡ የሚያግዝ የአሰራር ስርዓት በመዘርጋት ተግባራዊ ለማድረግ መሆኑ ተጠቅሷል፡፡ በዕለቱ የቅርጫፍ ፅ/ቤቱ የ2018 በጀት ዓመት መሪ እቅድ እና ቅንጅታዊ አሰራር ስምምነት ማስፈጸሚያ እቅድ ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን ሙስና እና ብልሹ አሠራርን በተመለከተ በጋራ እንዴት መታገል እንደሚገባ የሚያስገነዝብ መልዕክት በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በአቶ አማረ መኮንን ቀርቧል፡፡ በመጨረሻም ከውጭ ባለድርሻ አካላት ጋር የትስስር ሰነድ ፊርማ የተደረገ ሲሆን የመማክርት ጉባኤ የሚወከሉ ስራ አስፈፃሚ አካላት ምርጫም ተካሂዷል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

የትምህርትና ስልጠና ጥራትና ተገቢነትን ለማረጋገጥ የባለድርሻ አካላት ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተጠቆመ፡፡ (ጥቅምት 5 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር
+5
የትምህርትና ስልጠና ጥራትና ተገቢነትን ለማረጋገጥ የባለድርሻ አካላት ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተጠቆመ፡፡ (ጥቅምት 5 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የአራዳና ቂርቆስ ቅ/ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት ተግባራትን በጋራ ለማከናወን ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አደረጉ፡፡ አቶ ያሬድ ካሳ የአራዳና ቂርቆስ ቅ/ጽ/ቤት ስራ አስኪያጅ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት የመድረኩ ዋና አላማ የቅ/ጽ/ቤቱ አገልግሎት አሠጣጡን በቀጣይ ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ እና ሕዝቡ ተገቢውን አገልግሎት እንዲያገኝ ለማስቻል መሆኑን ጠቅሰው፤ በዚህም ባለስልጣኑ በከተማ አስተዳደሩ በአዋጅ 84/2016 የተሠጠውን ተግባር እና ኃላፊነት ለማስፈጸም በተለይ የትምህርት ስልጠና ጥራትና ተገቢነትን ለማረጋገጥ በአንድ ተቋም ብቻ የሚሳካ ባለመሆኑ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም ቅ/ጽ/ቤቱ የአሠራር ስርአት ዘርግቶ አግባብነት ባለው ሁኔታ ስራዎችን እየገመገመ እና ክፍተቶችን እየለየ በጋራ በመደጋገፍ በመስራት ውጤታማ መሆን ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡ በመድረኩ ላይ የአራዳና ቂርቆስ የትምህርት ስልጠና ጥራት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በአቶ ተስፋዬ አሠፋ የአገልግሎት አሰጣጥ መማክርት ጉባኤ (ተገልጋይ ካውንስል) ማቋቋሚያ ማንዋል አቅርበዋል፡፡

የባለስልጣኑ ጠቅላላ ካውንስል የ2017 የአጠቃላይ ትምህርት ቤቶች የእውቅና ፍቃድ እድሳት ትንተና ግኝት ውጤት ላይ ግምገማ አካሄደ፡፡ (ጥቅምት 5 ቀን 2018 ዓ.ም)የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
+5
የባለስልጣኑ ጠቅላላ ካውንስል የ2017 የአጠቃላይ ትምህርት ቤቶች የእውቅና ፍቃድ እድሳት ትንተና ግኝት ውጤት ላይ ግምገማ አካሄደ፡፡ (ጥቅምት 5 ቀን 2018 ዓ.ም)የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የ2017 ዓ.ም የአጠቃላይ ትምህርት ቤቶች የእውቅና ፍቃድና እድሳት ትንተና ሰነድ ቀርቦ ጠቅላላ ካውንስሉ የጋራ ውይይት እና ግምገማ አካሂዷል፡፡ ወ/ሮ ታጋይቱ አባቡ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ እና የጥራት ዘርፍ ሀላፊ በመርሃግብሩ ባስተላለፉት መልዕክት በትምህርት ቤቶች ላይ የሚታዩ ክፍተቶች ያሉ መሆኑን ገልጸው የሚታዩትን ችግሮች እና ዝንፈቶች በቀጣይ ለመፍታት የሚያስችሉ መመሪያዎችን በማሻሻልና ለትምህርት ጥራቱ የጀርባ አጥንት የሆኑ መመሪያዎችን ቅድመ ሁኔታ ላይ በማስቀመጥ ወደተግባር በመግባት እና ብቁ የሆኑት ተቋማትን በማስቀጠል በጥብቅ መሰራት ያለበት ተግባር መሆኑን አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡ በዕለቱ የባለስልጣኑ የእውቅና ፍቃድና እድሳት ዳይሬክቶሬት የውጤት ትንተና ሰነድ በማቅረብ በጠቅላላ ካውንስሉ ውይይትና ግምገማ የተካሂደ ሲሆን የተነሱት ሃሳቦች ተካተው በቀጣይ ለባለድርሻ አካላት የሚቀርብ ይሆናል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

የባለስልጣኑ ጠቅላላ ካውንስል የ2017 የአጠቃላይ ትምህርት ቤቶች የእውቅና ፍቃድ እድሳት እና የኢንስፔክሽን ትንተና ግኝት ውጤት ላይ ውይይት አካሄዱ፡፡ (ጥቅምት 4 ቀን 2018 ዓ.ም)የአዲስ አበባ
+4
የባለስልጣኑ ጠቅላላ ካውንስል የ2017 የአጠቃላይ ትምህርት ቤቶች የእውቅና ፍቃድ እድሳት እና የኢንስፔክሽን ትንተና ግኝት ውጤት ላይ ውይይት አካሄዱ፡፡ (ጥቅምት 4 ቀን 2018 ዓ.ም)የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የ2017 የአጠቃላይ ትምህርት ቤቶች የእውቅና ፍቃድ እድሳት እና የኢንስፔክሽን ትንተና ሰነድ ቀርቦ ጠቅላላ ካውንስሉ የጋራ ውይይት አካሂደዋል፡፡ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ኢዘዲን ሙስባህ እንደገለጹት ስርዓተ ትምህርቱን ተከትለው ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎችን ለመፍጠር የሚሰሩ ት/ቤቶችን እያበረታታን ከደረጃ በታች እና ደረጃቸውን ያላሻሻሉ ት/ቤቶች በተሰጠው የእርምት እርምጃ ማስተካከያ በማደረግ በተሰጣቸው ፈቃድ መሰረት የመማር ማስተማር ስራውን ማካሄድ አለባቸው ብለዋል፤እንዲሁም በቀረቡ ግብረ-መልሶችና ምክረ-ሃሳቦች ላይም ባለድርሻ አካላት ትኩረት አድርገው መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል፡፡ በቀጣይም በውይይቱ የተነሱ ሃሳቦች ተካተው ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት የሚካሄድበት መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

3ተኛዉ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባዔ ላይ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ብልፅግና ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ
3ተኛዉ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባዔ ላይ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ብልፅግና ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ ለምክር ቤቱ አባላት በሰጡት ማብራሪያ እና ምላሽ እንደገለፁት ምክር ቤቱ በመደበኛነት እያደረገ ያለዉ ቁጥጥር እና ድጋፍ በበከተማችን ለተመዘገቡ ተጨባጭ ዉጤቶች ማሳያ ነዉ ብለዋል፡፡ የምክር ቤቱ የህዝብ ተወካዮች አባላት ከወከላቸዉ ህዝብ ጋር በሚያደርጉት ተከታታይ ዉይይቶች የሚመጡ አስተያየቶችና ጥያቄዎችን አስፈፃሚዉ አካላት በግብዓትነት ወስዶ በፍጥነት እንዲያርም በመቻሉ በህዝቡና በመንግስት መካከል ጠንካራ ግንኙነት እንዲፈጠር ተችሏል ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ሃገራዊና ከተማ አቀፍ የተለያዩ ሃይማኖታዊና ህዝባዊ በዓላት ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ የድሉ ባለቤት መሆኑን እና በሰላም ወጥቶ በሰላም በግባት መቻሉ የለዉጣችን ማሳያ የሆነ ሌለኛዉ የከተማዋን ገፅታ የቀየረ እና የፖለቲካ ስብራትን መጠገን የቻለ ድል መሆኑንም ገልፀዋል፡፤ ለዚህም ሶስት አካላት በዋናነት መመስገን የሚገባቸዉና የማይተካ ሚና አላቸዉ ያሉት አቶ ሞገስ ባልቻ የከተማዋ ነዋሪ ፤የፀጥታ መዋቅሩ እና የፖለቲካ አመራሩ ናቸዉ ብለዋል፡፡ የእነዚህን ድምር ዉጤት ስናይ የከተማችንን ገፅታ በመቀየር የከተማችን ተፈላጊነት እንዲጨምር በማድረግ እና ከተማችን ዓለም አቀፋዊ እዉቅና በማግኘት የትኩረት ማእከል እንድትሆን ማስቻሉ ነዉ ብለዋል፡፡ በመጨረሻም ሁለተናዊ የድል ሚስጥሩ የገባነዉን ቃል ወደ ተግባር በመቀየር መስራት የመቻላችን ዉጤት ስለሆነ ይህን አጠናክሮ ማስቀጠልና ትልቁ ህልማችን ላይ መድረስ ይገባል በማለት ለምክር ቤት አባላትና ለከተማዋ ነዋሪ ልባዊ ምስጋናቸዉን አቅርበዋል፡፡

ባለፉት 3 ወራት ከ96 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶችና ሴቶች የስራ ዕድል ተፈጥሯል፡፡ አቶ ጥራቱ በየነ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥራቱ በየነ
+2
ባለፉት 3 ወራት ከ96 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶችና ሴቶች የስራ ዕድል ተፈጥሯል፡፡ አቶ ጥራቱ በየነ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥራቱ በየነ ለአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ተመራጭ አባላት በኩል ከመራጩ ህዝብ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ ባለፉት 3 ወራት ከ96 ሺህ 200 በላይ ለሚሆኑ ወጣቶችና ሴቶች የስራ ዕድል ተፈጥሮላቸዋል ብለዋል፡፡ የስራ እድል ከተፈጠረላቸው ወጣቶች መካከል 10 በመቶ ለአዳዲስ ምሩቃን እንዲሁም 56 በመቶ ለሴቶች ስራ እድል እንደተፈጠረላቸው አቶ ጥራቱ በየነ ተናግረዋል፡፡ ለኢንተርፕራይዞች በመንግስት የልማት ስራዎችና ለኢንዱስትሪዎች የጥሬ እቃ እንዲያቀርቡ በማድረግ የ2 ቢሊዮን የገቢያ ትስስር እንደተፈጠረላቸውም ገልጸዋል፡፡ በተመሳሳይ 996 የመስሪያ ሸዶችን ለአዳዲስ ስራ ፈላጊዎች ማስተላለፍ መቻሉን እና ሌሎችን በፍጥነት ለማስተላፍ እየተሰራ እንደሆነና እና በአመቱ መጨረሻም ለ350 ሺህ ወጣቶች የስራ እድል ለመፍጠር በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም አቶ ጥራቱ በየነ አስረድተዋል፡፡

3ተኛዉ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛመደበኛ ጉባዔ ላይ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡ በምክትል ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ጀማሉ ጀምበር በሰጡት ማብራሪያ እና ምላሽ እንደገለፁት የአገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን የተገልጋዩን እርካታ ለማረጋገጥ ከከተማ አስተዳደሩ ጋር ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡ በከተማችን በቅርቡ ተመርቀዉ ወደስራ የገቡት አዲስ የመሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት ለዚህ ማሳያ ነዉ ሲሉ ተናግረዋል፡፡ በዚህ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሰፊ አገልግሎት እና ሰፊ ተገልጋይ እንዲሁም ቅሬታ የሚበዛባቸዉ ተቋማት በመለየት አደረጃጀትን እና አሰራርን በመዘርጋት እንዲሁም ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር ወደ ትግበራ መግባት መቻሉን ጠቁመዋል፡፡ በዋና መስሪያ ቤት በአራዳ ክፍለ ከተማ 13 የሚሆኑ የከተማ አስተዳደሩ ተቋማት 107 አገልግሎቶችን በመያዝ የተለዩ የፌደራል ተቋማትን በማካተት እየተሰራ አንደሚገኝም ተናግረዋል፡፡ በተመሳሳይም በቦሌ ክፍለ ከተማ በአዲስ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት 12 የከተማ አስተዳደሩ ተቋማት 96 አገልግሎቶችን እንዲሁም የተለዩ የፌደራል ተቋማትን በማካተት በጥቅሉ 114 አገልግሎቶች እንዲገቡ ተደርጓል፤ በአመለካከት ፣በእዉቀት እና በክህሎት የበቁ ነባርና አዳዲስ ተመረቂ ባለሙያዎችን በማሰልጠንና በመመደብ ፤የቅሬታ አፈታት ስርዓትን በማዘመን ፤ከተቋማት ጋር በቅንጅት በመስራት ይፈጠራሉ ተብለዉ የሚገመቱ ችግሮችን ከወዲሁ ለማረም የተቻለበት ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል፡፡ በዚህም ከየትኛዉም በኩል የሚመጡ የዜጎች ምልልስ በማስቀረት፤ወጪና ጊዜን በመቆጠብ የተገልጋይን እርካታ ከፍ ማድረግ የተቻለበት ሁኔታ መፈጠሩን ዶ/ር ጀማሉ ጀምበር ተናግረዋል፡፡ ይህም ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በሌሎች ክፍለ ከተሞች ለማስፋፋት እቅድ ተይዞ በልዩ ትኩረት በቅንጅት እንደሚሰራ ገልፀዋል፡፡ በሌላ በኩልም አዲሱ የደመወዝ ጭማሪ በተመለከተ ለተነሳላቸዉ ጥያቁ ቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸዉና ክፍያዉ በቅርቡ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ እንደሚሆን አመላክተዋል ::

በከተማዋ የተከናወኑ ሁነቶች እና አበይት የአደባባይ በዓላት ስኬት ከህዝቡ ጋር በጋራ በመሰራቱ የተገኘ ውጤት መሆኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለፁ 3ኛው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ይገኛል ፡፡ በጉባኤው የተለያዩ የምክር ቤት አባላት ምላሽና ማብራሪያ ያስፈልጋቸዋል ያሉትን ጥያቄና አስተያየት አቅርበዋል ፡፡ የምክር ቤት አባላት ያቀረቧቸውን ጥያቄ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ምላሽ እየሰጡ ይገኛሉ ፡፡ አዲስ አበባ ላይ በተሰሩና እየተሰሩ ባሉ የኮሪደር ልማት ከተማዋ ዓለም ዓቀፍ ጉባኤዎችን የማዘጋጀት ዓቅሟ እያደገ መጥቷል፤ በእነዚህ ጉባኤዎችና በመስከረም ወር የተከናወኑ ዓበይት የአደባባይ በዓላት በከተማዋ የተከናወኑበት ወር ሲሆን እነዚህ ሁነቶች በድምቀት ተከብረው አልፈዋል ለዚህ ሰኬት የተሰሩ ስራዎች ምንድናቸው ለሚለው የምክር ቤት አባላት ጥያቄ ከንቲባዋ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ ለበዓላቱና ለሁነቶቹ ስኬት ከህዝቡና ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት በማድረግ ግልፅነት በመፍጠር ወደ ስራ መገባቱን ነው ከንቲባ አዳነች አቤቤ የገለፁት፡፡ በተለይ በተከናወኑ ጉባኤዎች፣ ሆቴሎች የአገልግሎት ጥራትን በማሳደግ እና ክፍያን ተመጣጣኝ በማድረግ ላደረጉት ትብብር ምስጋና ይገባል ሲሉ ከንቲባዋ ገልፀዋል፡፡ ህዝቡ አጠቃላይ እንግዶቹን በኢትዮጵያዊ አንግዳ ተቀባይነት ያደረገው ተሳትፎ የሚደነቅ ነው ያሉት ከንቲባዋ፤ በከተማዋ የተከናወኑ ሁነትና የአደባባይ በዓላት አብሮነትን እና አንድነትን በተግባር ያሳዩ ናቸው ሲሉ ገልፀዋል፡፡ ህዝቡ መሰረተ ልማቶች የኔ ናቸው ብሎ በመንቀሳቀሱ በከተዋማ በተከበሩ በርካታ ዓበይት በዓላት እና ሁነቶች አንድም የተበላሸ የኮሪደር ልማት አለመኖሩን የገለፁት ከንቲባዋ ይህም በሌሎቹ ስራዎች ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

በመዲናዋ የሚሰሩ አዳዲስ የመንገድ መሠረተ ልማት ስራዎች በዘላቂነት በኮሪደር ልማት ደረጃ እንደሚሰሩ፡- ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ፡፡ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በሁሉም አካባቢዎች የኮሪደር ልማት ስራ
+5
በመዲናዋ የሚሰሩ አዳዲስ የመንገድ መሠረተ ልማት ስራዎች በዘላቂነት በኮሪደር ልማት ደረጃ እንደሚሰሩ፡- ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ፡፡ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በሁሉም አካባቢዎች የኮሪደር ልማት ስራን ለማዳረስ ምን እንደታቀደ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ማብራሪያ የመኖሪያ ቤትን ጨምሮ በቂ ዝግጅትን የሚጠይቅ ነው ብለዋል፡፡ በመሆኑም በዚህ ዓመት አዲስ የኮሪደር ልማት ስራዎች እንደማይኖር የገለጹት ከንቲባ አዳነች አቤቤ ነገር ግን በመዲናዋ የሚሰሩ አዳዲስ የመንገድ መሠረተ ልማት ስራዎች በኮሪደር ልማት እስታንዳርድ ዘላቂነት እንዲኖራቸው ተደርጎ ይሰራሉ ብለዋል፡፡

በአዲስ አበባ ምክር ቤት አባላት የተነሱ ጥያቄዎች የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ይገኛል፡፡ በጉባኤው የምክር ቤት አባላቱ ከመረጣቸው ህዝብ ጋር ባደረጉት የመራጭ ተመራጭ የገፅ ለገፅ ውይይት ምላሽ ያስፈልጋቸዋል ተብለው የተነሱ የህዝብ ጥያቄዎችን ለከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አቅርበዋል፡፡ የተነሱት ጥያቄዎች ፡- 👉 በበዓል ሰሞን እና ምሽትን ተገን በማድረግ የትራንስፖርት ታሪፍ ጭማሪ ነዋሪዎችን ያማረሩ በመሆናቸው ለዚህም በቀጣይ ምን ታስቧል? 👉 ‎ንፁህ የመጠጥ ውሃ ለነዋሪዎች ለማቅረብ ከተማ አስተዳደሩ የያዛቸው እቅዶች ምንድን ናቸው? 👉 በአንድ አንድ የእሁድ ገበያ መደብሮች ከተቀመጠው ዋጋ በላይ ማስከፈል፣ ጥራታቸው ዝቅ ላሉ ምርቶች እኩል ዋጋ መጠየቅ እንደሚስተዋል እና ይህን ችግር ለመቅረፍ በቀጣይ ምን ታስቧል? 👉 በመዲናዋ የኮሪደር ልማት ያልደረሰባቸው አካባቢዎች የኮሪደር ልማትን ለማዳረስ ከተማ አስተዳደሩ ምን አቅዷል? 👉 የጤና ጣብያ እጥረት ያለባቸው አካባቢዎችን ችግር ለመቅረፍ ምን እንደታቀደ ቢገለፅ? 👉 መሰረቱ የማይናወጥ አካታች የወል ትርክት ለመገንባት ብሎም ተራማጅ አስተሳሰብ ማስረጽ፤ የእንችላለን ስነ-ልቦና ብሎም ልመናና ኋላ ቀር አስተሳሰብን በመስበር በኪነ- ጥበብ እያዋዙ ጠንካራ ኢንዱስትሪ ለመገንባትና ዘርፉን ለመደገፍ ከተማ አስተዳደሩ ምን አስቧል? 👉 ‎የኑሮ ሁኔታን በተመለከተ እየተሰራ ያለው ስራ ጎን ለጎን የኑሮ ጫናን ለመቀነስ፣ የነዋሪዎችን እርካታ ለማረጋገጥ የት፣ ምን ተሰርቷል? 👉 በመስከረም ወር የተካሄዱት ታላላቅ በዓላት በስኬት የመጠናቀቃቸውን ያህል በቀጣይም መሰል በዓላት በስኬት እንዲጠናቀቁ ምን ታስቧል? ይሄንንስ ድል እንዴት አገኘነው? 👉 የኮሪደር ልማቱን ህብረተሰቡ በእኔነት እንዲጠብቀው፤ ከተማውን ከተሜ ሆኖ እዲጠብቃት የግንዛቤ ማስጨበጫ ተሰጥቷል ወይ? 👉 ህብረተሰብ ከተማዋን ከተሜ ሆኖ እዲጠብቃት የሕግ ማዕቀፍ አለ? ማዕቀፍ አያስፈልግም ወይ? 👉 ወጣቶች ኮደርስ ስልጠና ወስደው ወደ ስራ አልገቡም፤ ምን ታስቧል? 👉 የፌዴራል መንግስት የሰራተኞች ደሞዝ እንዲስተካከል ወስኗል ከተማ አስተዳደሩ ይህንን ተፈፃሚ ለማድረግ ምን ዝግጅት አድርጓል? የሚሉ ጥያቄዎች በምክር ቤቱ አባላት የተነሱ ሲሆን ለጥያቆዎቹም በከንቲባ አዳነች አቤቤ ምላሽ ይሰጥባቸዋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡