en
Feedback
የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን

የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን

Open in Telegram
5 357
Subscribers
No data24 hours
-97 days
+730 days
Posts Archive
ባለስልጣኑ በአገልግሎት አሠጣጥ ፣በመልካም አስተዳደር፣ በሌብነት እና ብልሹ አሠራር ማክሰሚያ ዙሪያ ከአጠቃላይ ሰራተኞች ጋር ውይይት አደረገ፡፡ (ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም)የአዲስ አበባ ከተማ
+6
ባለስልጣኑ በአገልግሎት አሠጣጥ ፣በመልካም አስተዳደር፣ በሌብነት እና ብልሹ አሠራር ማክሰሚያ ዙሪያ ከአጠቃላይ ሰራተኞች ጋር ውይይት አደረገ፡፡ (ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም)የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በአገልግሎት አሠጣጥ ፣በመልካም አስተዳደር፣ በሌብነት እና ብልሹ አሠራር ማክሰሚያ ዙሪያ ከአጠቃላይ ሰራተኞች ጋር ውይይት ተከናወነ፡፡ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ምክትል ስራ አስኪያጅ እና የጥራት ዘርፍ ሃላፊ አቶ አለልኝ ወንዴ በውይይት መድረኩ ላይ እንደገለጹት ከተግባር ወደ ተግባር በሚል ሕብረተሰቡ ተጠቃሚ የሚሆኑበት በርካታ የልማት ስራዎች በመጀመሪያው ሩብ ዓመት መከናወናቸውን ጠቅሰው በተለይ በከተማችን ተስፋ ሰጪ ስራዎች የተሠሩበት አግባብ ያለ ሲሆን እንደባለስልጣንም በዘጠና ቀን እቅድ እጅግ አመርቂ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም በአገልግሎት አሠጣጥ፣ በመልካም አስተዳደር፣ በሌብነት እና ብልሹ አሰራር ማክሰሚያ ተግባራት ላይ መሻሻል የታየ ሲሆን እነዚህ ለውጦች እንዳሉ ሆነው የሚታዩ ችግሮችን በጋራ መቀረፍ ተገቢ እንደሆነ ጠቅሰው እንደተቋም የኛ ሚና ምን መሆን አለበት የሚለውን በማስቀደም ሃላፊነታችንን እንወጣ ብለዋል፡፡ አቶ ሰለሞን አለማየሁ የባለስልጣኑ አማካሪ በበኩላቸው እንደገለጹት በአገልግሎት አሠጣጥ ፣መልካም አስተዳደር፣ ሌብነት እና ብልሹ አሠራር ማክሰሚያን አስመልክቶ እንደተቋም በተጠናከረ መልኩ የሚሰራ መሆኑን ጠቅሰው የእኛ ነባራዊ ሁኔታ ምን ይመስላል የሚለውን በመፈተሽ ተግባራትን አጠናክረን መሄድ ተቋማችንን ውጤታማ ማድረግ ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡ በዕለቱ በቀረበው የመወያያ ሃሳብ ላይ ሠራተኞች ጥያቄ ያነሱና አስተያየት የሰጡበት ሲሆን ውይይትም ተደርጎበታል፡፡

ከዚህም ሌላ የፕሮግራሙ ይዘት የተቋሙን ዓላማ ማሳካቱን ለማረጋገጥ፣ተሳታፊዎች የግንዛቤና ልምድ የቀሰሙ መሆኑን ለማረጋገጥ የሰራተኛው አጠቃላይ እርካታ እና በቀጣይ በምን አግባብ መመራት እንዳለበት ለማወቅ አላማ አድርጎ መከናወኑን የገለጹ ሲሆን የመረጃ አሰባሰብ ሂደቱም በቃል ߹ በመጠይቅ እንዲሁም በቡድን ውይይትም ጭምር መረጃ እንደተሰበሰበ ገልጸው በተሰበሰበው መረጃም ፕሮግራሙ አዎንታዊ ምላሽ ያለው መሆኑን ገልጸዋል ፡፡ አቶ ኢዘዲን ሙስባህ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ለውጥ የሚጀምረው ከራስ እንዲሁም ከውስጣችን ነው ስለዚህ የተሻለ ለውጥ እንድናመጣ ከራሳችን እንዲሁም ከውስጣችን መጀመር ያስፈልጋል፡፡የምናገለግለው ሀገራችንን እንደመሆኑ ተቋማዊ ለውጥ የሚያመጡ ስራዎችን በመስራት መስተካከል የሚገባቸውን ጉዳዮች በጋራ በማስተካከል ወርቃማ ሰኞን ወርቃማ እንደሆነ ማስቀጠል ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ ወ/ሮ ታጋይቱ አባቡ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅና የጥራት ዘርፍ ሀላፊ ፕሮግራሙ አላማውን ያሳካ እንዲሁም ተቋማዊ ለውጥ የሚያመጣ ለውጤታማነት በመስራት እና ጥሩ መስተጋብር በመፍጠር የሰራተኛውን አጠቃላይ እርካታ በማሻሻል እና ያሉትን ክፍተቶች በማስተካከል አላማውን ያሳካ ወርቃማ ሰኞ መፍጠር ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ አቶ አለልኝ ወንዴ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅና የምዘና ዘርፍ ሀላፊ እንደገለጹት ሀገርም ተቋምም የጋራችን እንደመሆኑ የምናደርጋቸውን ነገሮች በሀላፊነት በመተግበር ያሉትን ክፍተቶች እንዴት ማስተካከል እንዳለብን በማሰብና ተቋማዊ ውጤት በማምጣት ወርቃማ የሆነ ሰኞን በውጤታማነት ልናስቀጥል ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ በመርሃ-ግብሩ በቀረበው ዳሰሳዊ ጥናት ላይ ሀሳቦች ተነስተው ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡

የወርቃማ ሰኞ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር ፕሮግራም አተገባበርን ለማሻሻል ዳሰሳዊ ጥናት ቀረበ፡፡ (ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም)የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር
+7
የወርቃማ ሰኞ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር ፕሮግራም አተገባበርን ለማሻሻል ዳሰሳዊ ጥናት ቀረበ፡፡ (ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም)የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ዘወትር ሰኞ ማለዳ የሚቀርበው የወርቃማ ሰኞ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር ፕሮግራም አተገባበርን ለማሻሻል ዳሰሳዊ ጥናት ተደረጎ ለአጠቃላይ ሰራተኞችና አመራሮች ቀረበ ፡፡ አቶ አምላኩ ተበጀ የባለስልጣኑ የአሰራር ጥራት ቁጥጥር ቡድን መሪ ዳስሳዊ ጥናቱን ያቀረቡ ሲሆን በወርቃማ ሰኞ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር አተገባበር የፕሮግራም አፈጻጸም ውጤታማነቱን ለማረጋገጥና ያጋጠሙ ችግሮችን በመፈተሽ በቀጣይ ማስተካከያ ስራዎችን ለመተግበር ታስቦ እንደተሰራ ገልጸዋል፡፡

ዛሬም የረዳን ፈጣሪ የተመሰገነ ይሁን ! ከሳርቤት - ጀርመን አደባባይ- ጋርመነት ፉሪ የሚዘልቀውን የኮሪደር ልማት ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እና የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ አባላት በተገኙበት መርቀን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል ። ሕዝባችንን በታማኝነት፣ በቅንነት ለማገልገል የገባነውን ቃል ቆጥረን እየተገበርን እንገኛለን። የተሰሩት መሰረተ ልማቶች ከተማችንን ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርጋት፣ ለዜጎቻችን ሰፊ የስራ ዕድል የፈጠረ እንዲሁም ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ መሰረታዊ የሆነ ለዉጥ ማምጣት በሚያስችል መልኩ የተሰራ ነው። በልማቱ ከመሬት በላይ ከሚታየው እኩል ከመሬት በታች ጭምር የተሰሩ በርካታ ስራዎች የከተማችንን አገልግሎት የሚያሳልጥ፣ በዘላቂነት ስማርት ሲቲ ለማድረግ የሰነቅነዉን ራዕይ ለማሳካት የሚያስችል መሰረታዊ ስራ የተሰራበት፣ ሰፊ የስራ ዕድል የተፈጠረበት ሲሆን፤ ለቱሪዝም ዘርፉ ተጨማሪ እሴት፤ የስበት ማዕከል የሆኑ ፅዳት፣ ውበት፣ አገልግሎትን ያጣመሩ ስራዎችም በስፋት ተሰርተውበታል ። ይህ የኮሪደር ልማት በሁለተኛ ዙር ከጀመርነው 6ኛዉና ከካዛንቺስ ኮሪደር ቀጥሎ በከተማችን ሁለተኛው ረጅሙ እና ሰፋ ያለ አካባቢ የሚሸፍነው ሲሆን ከ589 ሄክታር በላይ ቦታ የለማበት ነው። • እስከ 60 ሜትር የሚሰፋ 16.5 ኪ.ሜ አስፓልት መንገድ ( በተጨማሪ 3 .5 ኪ. ሜ የውስጥ ለውስጥ መንገድ) አለው ፣ • 33 ኪ.ሜ የእግረኛ መንገድ ፣ • 13.3 ኪ.ሜ የሳይክል መንገድ ፣ • 21 የተለያዩ ፕላዛዎች ፣ • ክረምት ከበጋ ፣ በቀን እና በምሽት አገልግሎት የሚሰጡ 20 የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች፣ • 20 የልጆች መጫወቻ ቦታዎች ፣ • 5.2 ኪ.ሜ ርዝመት ያለው የወንዝ ዳርቻ ልማት ፣ • 20 የመኪና ማቆሚያ ቦታና ተርሚናሎች ፣ 1 የመኪና ቻርጂንግ ስቴሽን ፣ • በግለሰቦች እና በመንግስት የተገነቡ 1,107 የንግድ ቤቶች ፣ • 50.5 ሄክታር ስፋት ያላቸዉ አረንጓዴ ቦታዎች ፣ • 40 የህዝብ መፀዳጃ ቤቶች ፣ • 38 የታክሲና አውቶቡስ ቤይ ፣ • 13 ካፌዎች እና 1 ሬስቶራንት እንዲሁም ከ 1 ሄክታር በላይ የነርሰሪ ቦታን በዉስጡ አካትቶ ይዟል ። ይህንን ለከተማችን ተጨማሪ ድምቀት ፣ ለዜጎቻችን መጠነ ሰፊ የስራ እድል እና የእውቀት ሽግግር የፈጠረን ፣ ለነዋሪዎቿ ደግም ምቾትን ያጎናፀፈውን ግዙፍ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት በታለመለት ጊዜ በጥራት እና በፍጥነት እንዲጠናቀቅ ላደረጋችሁ ፣ ከመደበኛ ስራችሁ ጎን ለጎን ሌት ተቀን ለለፋችሁ በየደረጃዉ ያላችሁ የከተማችን አመራሮች፣ ባለሞያዎች፣ እንዲሁም በልማት ስራው ሁልጊዜም የዘወትር ድጋፍ እና ትብብሩ ላልተለየን የአካባቢው ነዋሪ ማህበረሰብ ልባዊ ምስጋናዬን አቀርባለሁ። ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ ከንቲባ አዳነች አቤቤ

እውቅና ማግኘት ለተሻለ ስራ መነሳሳትን እንደሚፈጥርና ለበለጠ ውጤት እንደሚያተጋ ተገለጸ፡፡ (ጥቅምት 13 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስል
+8
እውቅና ማግኘት ለተሻለ ስራ መነሳሳትን እንደሚፈጥርና ለበለጠ ውጤት እንደሚያተጋ ተገለጸ፡፡ (ጥቅምት 13 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የ2017 በጀት ዓመት የአጠቃላይ ትምህርት የስታንዳርድ ኢንስፔክሽን ትንተና እና የተቋማት እውቅና ፍቃድና እድሳት ትንተና ቀርቦ የተሻለ አፈጻጻም ያላቸው ተቋማት እውቅና ተሰጥቷል፡፡ ባለስልጣኑ በ2017 በጀት ዓመት ከቅድመ አንደኛ ደረጃ እስከ ሁለተኛ ደረጃ በየእርከኑ ባሉ እድሳት ከተሰራላቸው ተቋማት መካከል የተሻለ አፈጻጸም ያላቸውን ተቋማት እንዲሁም በስታንዳርድ ኢንስፔክሽን ምዘና የተሻለ አፈጻጸም ላላቸው ተቋማት እንዲሁም በአፋን ኦሮሞ ስርዓተ ትምህርት ከሚሰጥባቸው የትምህርት ተቋማት ከቅድመ አንደኛ ደረጃ እና አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤቶች፣እንዲሁም በ2017 የውጤትና የደረጃ መሻሻል ያደረጉ የትምህርት ተቋማት በየእርከኑ የምስክር ወረቀትና ዋንጫ የተሰጠ ሲሆን ለባለስልጣኑ አላማ መሳካት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላበረከቱ ተቋማትም የምስጋና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷቸዋል፡፡ ሽልማትና እውቅና የተሰጣቸው ት/ት ስልጠና ተቋማት ከእውቅና ፈቃድ እድሳት በየእርከኑ 12 ተቋማት፣ ከኢንስፔክሽ ደረጃ ማሻሻል እና የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ በየእርከኑ19 ትምህርት ቤቶች ከክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤተ በላቀ ተሳትፎ 3 እና 8 ለባለስልጣኑ አላማ መሳካት ድጋፍ ያደረጉ ባላድርሻ አካላት እውቅና ተሰጥቷቸዋል፡፡ እውቅና የተሰጣቸው ተቋማት እንደገለጹት ባለስልጣኑ የሰጣቸው እውቅና እንዳስደሰታቸው ገልጽው የምንሰራው ትውልድ ላይ በመሆኑ ለነገ ስንቅ ሆኖን የተሻለ ስራን ማከናወን ያስችለናል ለውጤትም እንድንተጋ ያነሳሳናል ብለዋል፡፡

ከዚህም ሌላ ተቋማት በእውቅና ፍቃድ እድሳትም ሆነ በኢንስፔክሽን ምዘና የተሻለ አደረጃጀት በመያዝ የመማር ማስተማር ሂደቱ በተገቢው እንዲካሄድ ጥረት ማድረግ ይገባቸዋል ብለዋል፡፡ የትምህርት ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ምክትል ስራ አስኪያጅና የጥራት ዘርፍ ሃላፊ ወ/ሮ ታጋይቱ አባቡ በበኩላቸው እንደገለጹት የትምህርት ተቋማት ስርዓተ ትምህርቱን ጠብቀው አገራችን የምትፈልገውን ትውልድ ለመቅረጽ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ ተቋማት በመማር ማስተማር ሂደቱ ላይ የሚገጥሟቸውን ችግሮች በጋራ ለመፍታት ባለስልጣኑ ከጎናቸው መሆኑን ጠቅሰው ትውልድ የሚቀረጽበትን ትምህርት ተቋም በተገቢው የሚጠበቅባቸውን መስፈርት እያሟሉ መሄድ እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል፡፡ በመርሃ-ግብሩ ላይ አቶ ላመስግን አዳሙ የአጠቃላይ ትምህርት እውቅና ፍቃድ እድሳት ቡድን መሪ የአጠቃላይ ትምህርት ተቋማት የ2017 ዓ.ም የእውቅና ፈቃድ እድሳት ምዘና ውጤት ትንተና ያቀረቡ ሲሆን የ2017 ዓ.ም የትምህርት ቤቶች የኢንስፔክሽን ትግበራ ውጤት ትንተና ሰነድ በትምህርት ስልጠና ጥራት ምርምር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በአቶ አንዋር ሙላት ቀርቧል፡፡ በቀረቡት ሰነድ ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን ጥሩ አፈጻጸም ላገኙ ተቋማትም የእውቅና መርሐግብር ተካሂዷል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

በ2017 በጀት ዓመት የአጠቃላይ ትምህርት መደበኛ ኢንስፔክሽን ትንተና እና የተቋማት እውቅና ፍቃድና እድሳት ትንተና ሰነድ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዉይይት ተካሄደ፡፡ (ጥቅምት 13 ቀን 2018
+8
በ2017 በጀት ዓመት የአጠቃላይ ትምህርት መደበኛ ኢንስፔክሽን ትንተና እና የተቋማት እውቅና ፍቃድና እድሳት ትንተና ሰነድ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዉይይት ተካሄደ፡፡ (ጥቅምት 13 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በ2017 በጀት ዓመት የአጠቃላይ ትምህርት መደበኛ ኢንስፔክሽን ትንተና እና የተቋማት እውቅና ፍቃድና እድሳት ትንተና ሰነድ ከባለድርሻ አካላት ጋር የዉይይት መድረክ አካሂዷል፡፡ በመርሃግብሩ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ሴቶችና ህጻናት ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክብርት ሶፊያ አለሙ ባስተላለፉት መልዕክት መንግስት ከተማዋን የሚመጥን የልማት ስራ እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰው በትምህርት ዘርፍም ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት በርካታ ስራዎች እየተተገበሩ መሆኑን የገለጹ ሲሆን የትምህርት ተቋማት ተፈላጊውን ውጤት እንዲያስመዘግቡ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅተው መስራት ይገባቸዋል ብለዋል፡፡ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ኢዘዲን ሙስባህ እንደገለጹት ለሀገራችን ኢኮኖሚ እድገት እንዲሁም መልካም አስተዳደር መስፈን የትምህርት ጥራትና ተገቢነት አስፈላጊ እንደሆነ ጠቅሰው የትምህርት ስልጠና ተገቢነቱ ከኢኮኖሚው እና ከማህበራዊ እድገቱ ጋር ተሳስሮ መሄዱን ለማረጋገጥ በሂደቱ ላይ ያሉትን ጠንካራና ደካማ ጎኖችን ለመለየትና ለማስተካከል እና በጋራ ለመመካከር መድረኩ ማስፈለጉን ተናግረዋል፡፡

(ጥቅምት 13 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የ2017 በጀት ዓመት የአጠቃላይ ትምህርት የስታንዳርድ ኢንስፔክሽን ትንተና ሰነድ እና
+7
(ጥቅምት 13 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የ2017 በጀት ዓመት የአጠቃላይ ትምህርት የስታንዳርድ ኢንስፔክሽን ትንተና ሰነድ እና የተቋማት እውቅና ፍቃድና እድሳት ትንተና ሰነድ ከባለድርሻ አካላት ጋር የጋራ ለማድረግ ውይይት እየተከናወነ ይገኛል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

የትምህርትና ስልጠና ተቋማት የማስተማር /የማሰልጠን ፈቃድ ከማግኘታቸው በፊት በባለሙያ ተገምግመው በሚፈለገው የትምህርትና ስልጠና ስታንዳርድ መሰረት ብቁ ሆነው እንዲገኙ በማስቻል የትምህርትና ስልጠና ጥራት ማስጠበቅ ስራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውን ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም የቴክኒክና ሙያ የስልጠና ተቋማት በ2017 ዓ.ም የእውቅና ፈቃድ እደሳት ሪፖርት የቴክኒክና ሙያ የስልጠና ተቋማት እውቅና ፍቃድ እድሳት ቡድን መሪ በሆኑት በአቶ ብዙነህ ቱምሳ የቀረበ ሲሆን በዕለቱ በቀረቡት ሰነዶች ላይ ውይይት ተደርጎ ጥሩ አፈፃፀም ላገኙ ተቋማት እና በበጎ ፍቃድ አገልግሎት ለተሳተፉ ተቋማት የሰርተፍኬት እና የዋንጫ ሽልማት ተበርክቷል፡፡በመድረኩ ላይ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት እና የትምህርት ቤት ባለቤቶች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

የአራዳና ቂርቆስ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በእውቅና ፈቃድና እድሳት እና በስታንዳርድ ኤንስፔክሽን ግኝቶች ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አደረገ፡፡ (ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ም)በትምህርትና ስልጠ
+4
የአራዳና ቂርቆስ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በእውቅና ፈቃድና እድሳት እና በስታንዳርድ ኤንስፔክሽን ግኝቶች ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አደረገ፡፡ (ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ም)በትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የአራዳና ቂርቆስ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ያሬድ ካሳ በመድረኩ መክፈቻ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት በተቋማት ላይ የተካሄዱ የእውቅና ፍቃድ ስራዎች እንዲሁም በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የሙያ ደረጃ ጠብቆ ብቁ ዜጋ ለማፍራት የተሠጠውን የእውቅና ፍቃድ የተቋማቱን የጥራት ደረጃ አማላካች በመሆኑ ተቋማቱ ያሉበትን ደረጃና ክፍተቶችን በመለየት በቀጣይ መታረም ያለባቸውን በማረም ጥራት ያለው ትምህርት ስልጠና ለመስጠት መድረኩ ማስፈለጉን ተናግረዋል፡፡ በዕለቱ የትምህርት ስልጠና ጥራት ኤንስፔክሽን ባለሙያ የሆኑት አቶ አዲስ አላጋው የ2017 ዓ.ም የትምህርት ቤቶች ኢንስፔክሽን ትግበራ ውጤት ትንተና ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን በሪፖርታቸውም ቅ/ጽ/ቤቱ በስሩ ያሉ ትምህርት ቤቶችን ያሉበትን ሁኔታ የተለያዩ ስታንዳርዶችና አመልካቾን መሠረት በማድረግ ከግብአት ከሂደት እና ከውጤት አንጻር መታየቱን ተናግረዋል በዚህም ለተቋማቱ የደረጃ ፍረጃ መደረጉን አሳውቀዋል፡፡ በሌላም በኩል በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በ2017 በጀት ዓመት የእውቅና ፍቃድ ምዘና ያደረጉ የግልና መንግስታዊ ያልሆኑ ት/ቤቶች ጥቅል ውጤት ሪፖርት የአራዳና ቂርቆስ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት እውቅና ፈቃድ እድሳት ዳይሬክቶሬት ቡድን መሪ በሆኑት በወ/ሮ ጽዩን ጌታቸው ቀርቧል ፡፡

የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ኢዘዲን ሙስባህ የጥናት ቡድኑ ባቀረበው ጥናታዊ ስራ ላይ በተደረገው ውይይት የተነሱ ሃሳቦችን እና አስተያየቶችን የጥናቱ አካል በማድረግና በማዳበር በቀጣይ ለሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት እንደሚቀርብ ገልጸዋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

በአንደኛ ደረጃ የግል ት/ቤቶች የስርዓተ ትምህርት ጥሰት መንስኤዎች በሚል ርዕስ በቀረበ ጥናት ላይ የባለስልጣኑ አመራሮች እና የዘርፉ ባለሙያዎች ግምገማዊ ውይይት አካሄዱ፡፡ (ጥቅምት 10 ቀን 201
+3
በአንደኛ ደረጃ የግል ት/ቤቶች የስርዓተ ትምህርት ጥሰት መንስኤዎች በሚል ርዕስ በቀረበ ጥናት ላይ የባለስልጣኑ አመራሮች እና የዘርፉ ባለሙያዎች ግምገማዊ ውይይት አካሄዱ፡፡ (ጥቅምት 10 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የትምህርት ምዘናና ምርምር ጥናት ቡድን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባሉ የግል አንደኛ ደረጃ ት/ቤቶች ስለሚካሄደው የስርዓተ ትምህርት ጥሰት መንስኤዎች ላይ ያተኮረ ጥናት ቀርቦ የባለስልጣኑ አመራሮች እና የዘርፉ ባለሙያዎች ግምገማዊ ውይይት አካሂደዋል፡፡ የጥናት ግኝቱን ያቀረቡት አቶ ተስፋዬ አበበ የባለስልጣኑ የትምህርት ምዘናና ምርምር ጥናት ባለሙያ እንደገለጹት የስርዓተ ትምህርት ጥሰት በግል የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤቶች ላይ ጎልቶ እንደሚታይ የኢንስፔክሽን ግኝት ሪፖርት እንደሚያመላክት ተናግረው ይህን መሰረት በማድረግ የስርዓተ ትምህርት ጥሰት እንዲያካሂዱ የሚያደርጋቸው መንስኤዎች ፈልጎ ማግኘት የጥናቱ ዋና አላማ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም ጥናቱ የተጠናው በ8 ክፍለ ከተሞች ውስጥ በናሙና ከተመረጡ 89 የመጀመሪያ ደረጃ የግል ትምህርት ቤቶች ላይ ሲሆን በጥናቱ ውስጥም ርእሳነ መምህራን፣መምህራን፣ተማሪዎች፣ የተማሪ ወላጆች፣የግል ትምህርት ቤት ባለቤቶች እንዲሁም በዘርፉ የሚሰሩ ባለሙያዎች እና ሱፐርቫይዘሮች ተሳታፊ እንደሆኑም ተናግረዋል፡፡

አቶ ኢዘዲን ሙስባህ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አሰኪያጅ በመርሀ-ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት በራስ መተማመን ሲኖር በተሰማራንበት ስራ ላይ የበለጠ ስኬታማ እንደምንሆን የገለጹ ሲሆን አንድ ሰው ከማንም እንደማይበልጥ ከማንም እንደማያንስ በማሰብና ራስን በመግለጽ እንዲሁም ራስን ማወቅና ማንነታችንን ማሰጠበቅ አስፈላጊ እንደሆነ፣ እንደ ህዝብ እንደ ግለሰብ እንዲሁም ለስራ ውጤታማነት በራስ መተማመን አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

የባለስልጣኑ የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር ተካሄደ፡፡ (ጥቅምት 10 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን
+5
የባለስልጣኑ የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር ተካሄደ፡፡ (ጥቅምት 10 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የወርቃማ ሰኞ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር "በራስ መተማመን" በሚል ርዕስ ተካሂዷል፡፡ አቶ ግዛት መኮንን የባለስልጣኑ የእውቅና ፍቃድና እድሳት ባለሙያ “በራስ መተማመን ”በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ዝርዝር የመማማሪያ ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን በራስ መተማመን ምን ማለት ነው? ስንት አይነት በራስ መተማመን አለ?በራስ መተማመናችንን እንዴት መገንባት እንችላለን? ምን አይነት በራስ መተማመን አለን ?አንድ ሰው የትኛው የራስ መተማማን ቢኖረው መልካም ነው? እያንዳንዳችን የትኛው በራስ መተማመን ላይ እንገኛለን? የሚሉትን ሀሳቦች በሰነዳቸው ያነሱ ሲሆን ማንም ሰው ሲወለድ አይነቱ ካለተለያየ በስተቀር በራስ መተማመን አለው ያሉ ሲሆን የትኛውም ሰው በራስ መተማመኑን ማዳበር እንዳለበት አስገንዝበዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 በጀት ዓመት 1ኛ ሩብ ዓመት የፓርቲ እና የመንግስት የልማት ስራዎች ግምገማ መድረክ የቡድን ውይይት ተካሂዷል! የግምገማው መድረክ በበጀት ዓመቱ የሩብ ዓመት
+8
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 በጀት ዓመት 1ኛ ሩብ ዓመት የፓርቲ እና የመንግስት የልማት ስራዎች ግምገማ መድረክ የቡድን ውይይት ተካሂዷል! የግምገማው መድረክ በበጀት ዓመቱ የሩብ ዓመት ስራዎች አፈፃፀም፣ የዜጎችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥና ማሳለጥ፣ የከተማውን ሰላም ማጠናከር፣ የአገልግሎት አሰጣጥን ይበልጥ ማሳለጥ፣ የፕሮጀክቶች አፈፃፀም ፣ በባለፉት ሶስት ወራት በአዲስ አበባ ከተማ የተካሄዱ ዓለም አቀፍ፣ አህጉር አቀፍ;ሀገር አቀፍና ከተማ አቀፍ ኩነቶች አፈፃፀም፣ ወንድማማችነት እና የእህትማማችነት ዕሴትን በማጎልበት ፣ በጋራ ተግባቦት የነበሩ ስኬቶችን በሚያስቀጥል እና ጉለቶችን በማረም ለሁለንተናዊ ብልፅግና ስኬቱ አስተዋፅዖ ማድረግ በሚያስችል ደረጃ ውይይት የተደረገ ሲሆን ፤ የአመራሩን አቅም የሚያጎለብት የግንባታ መድረክ እንደሆነም ተመላክቷል።