en
Feedback
የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን

የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን

Open in Telegram
5 357
Subscribers
No data24 hours
-97 days
+730 days
Posts Archive
ባለስልጣኑ ከቅ/ጽ/ቤቶች ጋር በተከናወኑ ቁልፍ እና አበይት ተግባራት ላይ ግምገማ አካሂደ፡፡ (ህዳር 2 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣ
+2
ባለስልጣኑ ከቅ/ጽ/ቤቶች ጋር በተከናወኑ ቁልፍ እና አበይት ተግባራት ላይ ግምገማ አካሂደ፡፡ (ህዳር 2 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ከ9ኙ ቅ/ጽ/ቤት ስራ አስኪያጆች ጋር የተከናወኑ ቁልፍ እና አበይት ተግባራትን በጋራ ገምግመዋል፡፡ በመርሃግብሩ ላይ የሙያ ብቃት ምዘና ስራዎችን፣በመምህራን ሙያ ብቃት ምዘና እና በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ በተከናወኑ ተግባራት ላይ በቅ/ጽ/ቤት ስራ አስኪያጆች ዝርዝር ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል፡፡ አቶ ኢዘዲን ሙስባህ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ እንደገለጹት የተጀመሩ ስራዎችን በተቀመጠላቸው እቅድ መሰረት አጠናክሮ በመቀጠል የታዩ ክፍተቶች በማረም ጠንካራ ጎኖችን እና መልካም ተሞክሮችን በማስቀጠል የተሻለ ስራ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡በቀጣይም በሚከናወኑ ተግባራት ላይ አቅጣጫ በማስቀመጥ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡

የባለስልጣኑ የአራዳና ቂርቆስ ቅ/ጽ/ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ያሬድ ካሳ እንደገለጹት የትምህርትና ስልጠና ጥራትና ተገቢነትን ማረጋገጥ የባለስልጣኑ አላማ መሆኑን ገልጸው ለዚህም ጥራትን ለማረጋገጥ የመንግስት ድርሻ ብቻ ሳይሆን የማህበረሰቡም ድጋፍ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም አሁን ያለንበት ዘመን ተግባር ተኮር የሆነ የማስተማሪያ ስነ-ዘዴን የሚያበረታታ እንደመሆኑ ለትምህርት ጥራት መሻሻል ግብአት ወሳኝ መሆኑንም ጨምረው ገልጸው ጤናማ ግንኙነትን በመፈጠር የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል በጋራ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ የጥበብ እድገት የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ርዕሰ መምህርት ወ/ሮ ሀመረ ታደሰ ቅ/ጽ/ቤቱ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማትን በማስተባበር ለትምህርት ቤቱ ላደረገው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበው በትምህርት ለትውልድ ስራ የቤተ-መጽሐፍት መደርደሪያ (ሼልፍ) ሙሉ ለሙሉ እንደተሟላላቸው ገልጸው ለመማር ማስተማሩ ውጤት ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለውም ገልጸዋል፡፡ በግብዓት ርክክቡ ወቅት በባለስልጣኑ የአራዳና ቂርቆስ ቅ/ጽ/ቤት ስራ አስኪያጅ፣ዳይሬክተሮች፣ የአራዳ ክ/ከተማ ት/ጽ/ቤት ሀላፊ፣የአራዳ ክ/ከተማ ወረዳ 4 ምክትል ስራ አስፈጻሚ እና የትምህርት ቤቱ አመራሮችና መምህራን ተገኝተዋል፡፡

የአራዳና ቂርቆስ ቅ/ጽ/ቤት ለጥበብ ዕድገት የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ድጋፍ አደረገ፡፡ (ህዳር1 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የአራ
+7
የአራዳና ቂርቆስ ቅ/ጽ/ቤት ለጥበብ ዕድገት የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ድጋፍ አደረገ፡፡ (ህዳር1 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የአራዳና ቂርቆስ ቅ/ጽ/ቤት ከ90 ቀን እቅድ አንዱ የሆነውን ትምህርት ለትውልድ ተግባር የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማትን በማስተባበር 33 የመጽሐፍት መደርደሪያ (ሼልፍ) ለጥበብ ዕድገት የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ድጋፍ አድርጓል፡፡

አቶ ዳባ ጉተታ የባለስልጣኑ የትምህርት ምዘናና ምርምር ጥናት ከፍተኛ ባለሙያ የተግባራት ክንውን ማዘግየት በሚል ርእስ ላይ የመማማሪያ ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን ተግባራትን የማዘግየት ምንነት፣አይነቶች፣መንስኤዎች፣መፍትሄዎች በሚሉ ሃሳቦች ላይ በዝርዝር አስረድተዋል፡፡ተግባራትን ማዘግየት በውጤታማነት እና በጥሩ ስሜት ላይ አሉታው ተጽእኖ ይፈጥራል ብለዋል፡፡ አቶ ብርሃኑ ተሾመ የባለስልጣኑ አማካሪ እንደገለጹት ተግባራትን በጊዜና በስዓቱ አለማጠናቀቅ ለውድቀት መንስኤ እንደሚሆን እና ብዙ ዋጋ እንደሚያስከፈል ገልጸው፡፡ አሁን ላይ ነገሮችን በጊዜ የመጀመር እና የመጨረስ ልምምድ እየዳበረ መምጣቱ ገልጸው ለዚህም ከተማችን ላይ ያሉ ልማቶች ማሳያ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ እንዲሁም ሁሉም መፍጠን እና መፍጠር በሚል ህግ ከአለም ጋር እኩል መራመድ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያ እና የዕውቀት ሽግግር መርሃ ግብር ተካሄደ፡፡ (ህዳር1 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የወርቃማ ሰኞ
+7
የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያ እና የዕውቀት ሽግግር መርሃ ግብር ተካሄደ፡፡ (ህዳር1 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያ እና የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር በዛሬው እለት የተካሄደ ሲሆን በመድረኩም የባለስልጣኑ አመራሮች እና ሰራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

አቶ ሰለሞን አለማየሁ የባለስልጠኑ አማካሪ እንደገለጹት ባለስልጣኑ የሚሰጠውን አገልግሎት የተሻለና ውጤታማ ለማድረግ ሁሉም የየበኩሉን አስተዋጽኦ ማድረግ የሚጠበቅበት መሆኑን ጠቅሰው የተገልጋዩ እርካታ እንዲጨምር በየጊዜው ስራዎችን መገምገም ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ አቶ ሀሰን ሺፋ የስራ አስፈፃሚው ሰብሳቢ በበኩላቸው የታቀደው እቅድ የሚያሰራ መሆኑን ጠቅሰው ለውጤታማነቱ በሃላፊነት ስሜትና በጋራ እንስራ ብለዋል፡፡ በዕለቱ በአቶ አምላኩ ተበጀ የባለስልጣኑ የአሰራር ጥራት ቁጥጥር ቡድን መሪ እቅዱ የቀረበ ሲሆን ውይይትና አስተያየት ተሠጥቶበት በጠቅላላ ጉባኤው ጸድቋል፡፡

ባለስልጣኑ ለተገልጋይ መማክርት ጉባዔ የ2018 በጀት ዓመት የተገልጋይ ካውንስል ማስፈፀሚያ ዕቅድ ቀርቦ በጋራ ጸደቀ፡፡ (ጥቅምት 28 ቀን 2018 ዓ.ም)የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና
+7
ባለስልጣኑ ለተገልጋይ መማክርት ጉባዔ የ2018 በጀት ዓመት የተገልጋይ ካውንስል ማስፈፀሚያ ዕቅድ ቀርቦ በጋራ ጸደቀ፡፡ (ጥቅምት 28 ቀን 2018 ዓ.ም)የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የተገልጋይ መማክርት ጉባኤ የ2018 በጀት ዓመት የተገልጋይ ካውንስል ማስፈፀሚያ ዕቅድ ቀርቦ በጋራ ጸደቀ፡፡ አቶ አለልኝ ወንዴ የባለስልጣኑ ምከትል ስራ አስኪያጅና የምዘና ዘርፍ ሃላፊ በመርሃግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት ባለስልጣኑ በየዘርፉ ተለያዩ አገልግሎቶችን የሚሠጥ እንደመሆኑ በአገልግሎት አሰጣጡ የሚታዩ ውስንነቶችን ለማስተካከል እና በጋራ ለመቅረፍ ይህ ጉባኤ ትልቅ ጉልበት እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡

ባለስልጣኑ የገንዘብ ድጋፍ ላደረጉ የትምህርትና ስልጠና ተቋማት የእውቅናና የምስጋና ፕሮግራም አከናወነ፡፡ (ጥቅምት 27 ቀን 2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በ2018 በጀት ዓመት የአቅመ ደካማ ቤቶች ግንባታ ስራ ላይ የገንዘብ ድጋፍ ላደረጉ የትምህርትና ስልጠና ተቋማት የእውቅናና የምስጋና ፕሮግራም አካሄደ፡፡ ባለስልጣኑ በ2018 በጀት ዓመት የትምህርትና ስልጠና ተቋማትን በማስተባበር አስራ አምስት የአቅመ ደካማ ቤቶችን በመገንባት ማስረከቡ ይታወቃል፡፡በመሆኑም በዚህ በጎ አድራጎት ስራ ላይ ለተሳተፉ የትምህርትና ስልጠና ተቋማት የእውቅናና ምስጋና ፕሮግራም በዛሬው እለት አካሂዷል፡፡ ወ/ሮ ታጋይቱ አባቡ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅና የጥራት ዘርፍ ሀላፊ በመክፈቻ ንግግራቸው እንደገለጹት መስጠት ስላለን ብቻ ሳይሆን ቅን ልብ ስለተሰጠን ነው የሰውን ደስታ እንደማየት የሚያስደስት ተግባር የለም የማይተካ ደስታና በረከት ያለው ተግባር ነው የዚህ ልብ ባለቤት ሆናችሁ ስለሰጣችሁና ማህበራዊ ሀላፊነታችሁን እየተወጣችሁ ስላላችሁ እጅግ ልናመሰግናችሁ እንወዳለን ብለዋል፡፡

ባለስልጣኑ የገንዘብ ድጋፍ ላደረጉ የትምህርትና ስልጠና ተቋማት የእውቅናና የምስጋና ፕሮግራም አከናወነ፡፡ (ጥቅምት 27 ቀን 2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በ2018 በጀት ዓመት የአቅመ ደካማ ቤቶች ግንባታ ስራ ላይ የገንዘብ ድጋፍ ላደረጉ የትምህርትና ስልጠና ተቋማት የእውቅናና የምስጋና ፕሮግራም አካሄደ፡፡

የባለስልጣኑ የመማክርት ጉባኤ ስራ አስፈጻሚ የማስፈጸሚያ እቅድ ላይ ውይይት አደረገ:: (ጥቅምት 27 ቀን 2018 ዓ.ም)የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን
+4
የባለስልጣኑ የመማክርት ጉባኤ ስራ አስፈጻሚ የማስፈጸሚያ እቅድ ላይ ውይይት አደረገ:: (ጥቅምት 27 ቀን 2018 ዓ.ም)የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የመማክርት ጉባኤ ስራ አስፈጻሚ የማስፈጸሚያ እቅድ ላይ ውይይት አደረገ:: ወ/ሮ ታጋይቱ አባቡ የባለስልጣኑ ምከትል ስራ አስኪያጅና የጥራት ዘርፍ ሃላፊ በእቅድ ውይይቱ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት ጥራት ያለው አገልግሎት ለተገልጋዩ ለማድረስ እና የሚታዩ ውስንነቶችን በማረም ውጤታማ አገልግሎት ለመስጠት የመማክርት ጉባኤው ለተቋሙ ትልቅ አቅም እንደሚሆን ተናግረዋል፡፡ በተቋማት የሚሠሩ ተግባራት ተገልጋዩ ጋር ደርሰው እርካታን እንዲጨምሩ ለማስቻል ስራዎች የሚገመገሙበት አሠራር በመፍጠር ድጋፍና ክትትሉ በአግባቡ መከናወን አለበት ብለዋል፡፡ አቶ ሀሰን ሺፋ የስራ አስፈፃሚው ሰብሳቢ በበኩላቸው የታቀደው እቅድ ጥሩ መሆኑን ጠቅሰው የተሰጡትን አስተያየቶች እንደ ግብዓት በማካተት ወደ ስራ መገባት ያለበት መሆኑን ጠቅሰው በተለይ ድጋፍና ክትትሉ ወደ ታች በመውረድ አገልግሎት አሠጣጡን ምልከታ በማድረግ የበለጠ የማጠናከር ስራ መሰራት አለበት ብለዋል፡፡ በዕለቱ በአቶ አምላኩ ተበጀ የባለስልጣኑ የአሰራር ጥራት ቁጥጥር ቡድን መሪ እቅዱ የቀረበ ሲሆን የመማክርት ስራ አስፈፃሚዎች በቀረበው ዝርዝር እቅድ ላይ ሃሳብ አስተያየት የተሰጠበት ሲሆን በቀጣይም ለመማክርት ጠቅላላ ጉባኤ በማቅረብ እቅዱ እንደሚጸድቅ ታውቋል፡፡

የወርቃማ ሰኞ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር ተከናወነ፡፡ (ጥቅምት 24 ቀን 2018 ዓ.ም)የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ዘወትር ሰኞ ማለዳ
+6
የወርቃማ ሰኞ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር ተከናወነ፡፡ (ጥቅምት 24 ቀን 2018 ዓ.ም)የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ዘወትር ሰኞ ማለዳ የሚቀርበው የወርቃማ ሰኞ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር ፕሮግራም የሀገር በቀል እውቀትን ግንዛቤ መሰረት ያደረገ "የሀመር ብሄረሰብ የከብት ዝላይ" ባህል በሚል ርዕስ ለአጠቃላይ ሰራተኞችና አመራሮች ቀርቧል፡፡ አቶ ኤፍሬም ኢያሱ የት/ጥ/ማ/ባለሙያ የሀገር በቀል እውቀትን ግንዛቤ መሰረት ያደረገ የሀመር ብሄረሰብ የከብት ዝላይ ባህልን በቪዲዮ በተደገፈ መልኩ በዝርዝር አዝናኝ በሆነ መልኩ አቅርበዋል፡፡ በዚህም ከብት የመዝለል ባህል ለአንድ ወጣት ከአንደኛው የህይወት ምዕራፍ ወደሌላኛው ምዕራፍ የመሸጋገር እና የመቻል ምልክትን የሚያሳዩበት መሆኑን ገልጸው ለቀጣዩ የህይወት ምዕራፍ ዝግጁ መሆኑን የሚያመላክት ባህል መሆኑን አብራርተዋል፡፡ ወ/ሮ ታጋይቱ አባቡ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅና የጥራት ዘርፍ ሃላፊ በመርሃ-ግብሩ ላይ እንደገለጹት ሀገራችን ኢትዮጵያ እንደ ስፋቷ በርካታ ብሄር ብሄረሰቦች ያሏት ሀገር እንደመሆኗ እምቅና ጥልቅ የሆኑ ባህል ባለቤት በመሆኗ ይህንን እምቅና ጥልቅ ባህል የቱሪስት መስህብ በማድረግ ለሀገራችን የኢኮኖሚ አቅም መዳበር መጠቀም ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

የስራና ክህሎት ሚኒስቴር የድጋፍና ክትትል ቡድን ለባለስልጣኑ የምዘና ዘርፍ ድጋፍና ክትትል አደረገ፡፡ (ጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥ
+2
የስራና ክህሎት ሚኒስቴር የድጋፍና ክትትል ቡድን ለባለስልጣኑ የምዘና ዘርፍ ድጋፍና ክትትል አደረገ፡፡ (ጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የምዘና ዘርፍ ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር በመጡ የድጋፍና ክትትል ቡድን አባላት ድጋፍና ክትትል ተደረገለት፡፡ የድጋፍና ክትትል ቡድኑ በውጭ ሀገር ስራ ስምሪት የምዘና ሂደት አተገባበር ዙሪያ ላይ ትኩረት በማድረግ ድጋፍና ክትትሉን አከናውኗል፡፡፡ የድጋፍና ክትትል ቡድኑ አባላት የመጡበትን አላማውን እንደገለጹት የውጭ ሀገር ስራ ስምሪት በተጠናከረና በጥራት መምራት በሚያስችል ደረጃ ላይ ለማድረስ ያሉ ጥንካሬዎችንና እጥረቶችን በመለየት ስራዎችን ወደተሻለ ደረጃ ለማድረስ እንደሆነ የገለጹ ሲሆን በተዘጋጀ ቼክሊስት መሰረት ድጋፍና ክትትሉን አድርገዋል፡፡ የዘርፉ ዳይሬክተርና ቡድን መሪዎች አስፈላጊ መረጃዎችን በማሳየት፣ ግልጽነት የሚስፈልጋቸውን ሃሳቦች ለድጋፍና ክትትል ቡድኑ አብራርተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ ያነሷቸው ሃሳቦች-ክፍል ሁለት ሰላምና ጸጥታን በሚመለከት የኢትዮጵያን እድገት የማይሹ ሀገራት በጦርነት እንደማያሸንፉን ያውቁታል። ያላቸው ምርጫ ባንዳዎችን መላክ ነው። ኢትዮጵያን በቅጡ ያላወቁ የውስጥ ባንዳዎች ደግሞ ከጠላት ጋር በማበር ዓላማቸውን የሚያሳኩ ይመስላቸዋል። ይህ ፈጽሞ ሊሳካ አይችልም። ኢትዮጵያ ውስጥ የሚያስፈልገው ብቻው መንገድ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ነው። መንግስት ችግሮች አሉኝ የሚሉ አካላት ጋር ቁጭ ብሎ በመነጋገር ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት አሁንም በሩ ክፍት ነው። የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ላይ የተቀመጡ ዋነኞቹ ጉዳዮች ምንድን ናቸው - ህወሃት ያካሄደው ምርጫ ህጋዊ ምርጫ ባለመሆኑ መሰረዝ - በትግራይ ክልል ህጋዊ ባለሆነ ምርጫ የተቋቋመው የክልሉ አስተዳደርና ምክር ቤት እንዲፈርስ - ከሁሉም ወገን የተወጣጣ ጊዜያዊ አስተዳደር ማቋቋም - በህዝብ የተመረጠውን የፌደራል መንግስት ስርዓት ማክበር - በክልሉ ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ሃይሎች ትጥቅ መፍታትና በተሃድሶ ወደ መደበኛ ህይወታቸው መመለስ - የተቋረጡ አገልግሎቶችን ወደ ስራ ማስመለስ - ከቀያቸው የተፈናቀሉ ዜጎችን መመለስ - የትኛውም የውጭ ግንኙነት የማከናወን ስልጣን ያለው የፌደራል መንግስቱ ብቻ መሆኑን ማክበር የሚሉት ናቸው። በትግራይ ክልል ያለውን የሰላም ሁኔታ በሚመለከት በትግራይ ክልል ተጨማሪ ወጊያ እንዲካሄድ አንፈልግም። ከዚያ ይልቅ ተባበረን ሀገር ማልማት ነው የምንፈልገው። ከዚያ ውጭ መንግስትን በሃይል ለመጣል ፍላጎት ካለ እሱ ፈጽሞ ሊሳካ አይችልም። የፌደራል መንግስት ለትግራይ ክልል የሚመድበው በጀት ለልማት ሳይሆን ለታጣቂ እየዋለ ነው። ይህ ትክክል አይደለም። ትግራይ ልማት ያስፈልጋታል። በመሆኑም በሰላማዊ መንገድ በትብበር ለልማት መስራት ይገባል። 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ በተመለከተ ምርጫውን ለማከናወን መንግስት በቂ አቅምና ዝግጁነት አለው። 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ እስካሁን በኢትዮጵያ ከተካሄዱ ምርጫዎች የተሻለ እንደሚሆን ጥርጥር የለውም። ምርጫው ዴሞክራሲያዊና ብዘሃ ድምጾች ያሉት እንዲሆን በሃላፊነት እንሰራለን። እኛ እንደ ፓርቲም፤ እንደ መንግስትም ዝግጁ ነን። ተፎካካሪ ፓርቲዎችም ከወዲሁ መዘጋጀት አለባቸው። ተቋማዊ ሪፎርም በሚመለከት በአገልግሎት አሰጣጥ ያለውን እንግልት ለመቀነስ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በሀገር አቀፍ ደረጃ እይሰፋ ነው። አሁን ላይ 18 ማዕከላት አገልግሎት እየሰጡ ነው። ሶስት ማዕከላት ደግሞ በቅርቡ ስራ ይጀምራሉ ተብሎ ይጠበቃል። በተያዘው በጀት ዓመትም ይህን ቁጥር ወደ 100 ለማድረስ እየተሰራ ነው። ይህም በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ከፍተኛ ለውጥ እንደሚያመጣ ይጠበቃል። ዲጂታላይዜሽንን በሚመለከት ኢትዮጵያ ውስጥ 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ወጣቶች በነጻ የኮዲንግ ስልጠና ወስደዋል። ይህ ትልቅ ቁጥር ነው። 93 ሚሊዮን ደንበኞች ደግሞ የቴሌኮም አገልግሎት ተጠቃሚ ሲሆኑ 55 ሚሊዮን ዜጎች ደግሞ የሞባይል ባንኪንግ ተጠቃሚ መሆን ችለዋል። ይህ ኢትዮጵያን ዲጂታላይዝ ለማድረግ የጀመረነው ስራ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጨባጭ ለውጥ እያመጣ መሆኑን አመላካች ነው። የዓባይ ውሃ ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን በሚመለከት ኢትዮጵያ በብሔራዊ ጥቅሟ ላይ ኢ-ፍትሃዊና ኢ-ርታዊ ውሳኔ የተወሰነባት ሀገር ናት። ዓባይን መጠቀም ተፈጥሯዊና ህጋዊ መብቷ ነው። ሃብቱም በጋራ ለመጠቀም በቂ ነው። ኢትዮጵያ አሁንም ያላት አቋም ግልጽ ነው። ግብጻዊያንም ሱዳናዊያንም ወንድሞቻችን ናቸው። ስለዚህ የሚያዋጣው በመነጋገርና በመተባበር በጋራ ማደግ ነው። እኛ ማንንም በሚጎዳ መልኩ አናቅድም አንሰራም። ቀይ ባህርን በተመለከተ የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልከዓ ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ ነው ብለን እናምናለን። ይህንን በተረጋጋ መንገድ ማየት ያስፈልጋል። ኢትዮጵያን የቀይ ባህር የማጣት ውሳኔ ማን ወሰነ ብለን ስንፈልግ ተቋማት አልገቡበትም። ይህን የሚያህል የህልውና ጉዳይ ማን እንደወሰነ መጠየቅ ተገቢ ነው። ኢትዮጵያ ተዘግቶባት መኖር አትችልም። ለጎረቤቶቻችን መናገር የምንፈልገው ኢትዮጵያ ስታደግ ለቀጣናውም ልማት ምንጭ ትሆናለች። የምንፈልገው በትብብር ማደግ ነው። #የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላት ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለ
+1
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላት ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ፡፡ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ዛሬ ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ይካሄዳል፡፡ በመደበኛ ስብሰባው ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም ለሕዝብ ተወካዮች እና የፌዴሬሽን ም/ቤቶች የጋራ ስብሰባ ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ ከም/ቤቱ አባላት በሚቀርቡ ጥያቄዎች ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ፡፡ ይህን ተከትሎም ምክር ቤቱ የመንግስትን አቋም በማዳመጥ የድጋፍ ሞሽኑን ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡