የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን
Open in Telegram
5 357
Subscribers
No data24 hours
-97 days
+730 days
Posts Archive
+4
ወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያ እና የዕውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር ተካሄደ፡፡
(ህዳር 22 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያ እና የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር "Exponential Thinking "በሚል ርዕስ የባለስልጣኑ አመራሮች እና ሰራተኞች በተገኙበት ተካሂዷል፡፡
አቶ በቃሉ ያየህ የባለስልጣኑ የትምህርት ምዘናና ምርምር ጥናት ቡድን መሪ "Exponential Thinking"በሚል ርዕስ ሰነድ ያቀረቡ ነገሮችን በተለየና በጥልቀት ማሰብን በተሻለ የልህቀት ደረጃ የማሰላሰል ለሚገጥሙን ችግሮች ሁሉ ዋነኛ መውጫ መንገድ መሆኑን በገለጻቸው ያቀረቡ ሲሆን የሰው ልጅ የየራሱን አቅም መለካት እንዲት ይችላል የሚለውን በገለጻችው አብራርተዋል፡፡
በእለቱ የባለስልጣኑ አመራሮችና ሰራተኞች በቀረበው ሰነድ ላይ ውይይት አካሂደዋል፡፡
አቶ አጥላው ዘውዴ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጥ ባለሙያ የትንተና ሰነዱን ያቀረቡ ሲሆን የድንገተኛ ኢንስፔክሽን እቅድ አፈፃፀም፣በት/ት ተቋማት የስርዓተ ትምህርት ይዘትና ትግበራ፣አጠቃላይ በጥንካሬ የታዩና መሻሻል ያለባቸው ጉዳዮች በሚሉ ይዘቶች ላይ በዝርዝር ያቀረቡ ሲሆን ቅድመ አንደኛ 73 ፣ አንደኛና መካከለኛ 46 በድምሩ 119 ተቋማት የድንገተኛ ኢንስፔክሽን የተሰራላቸው መሆኑን ገልጸው እቅዱን ሙሉ በሙሉ ያሳኩ መሆኑንም ገልጸዋል::
ወ/ት ትእግስት ጌታነህ የቅ/ጽ/ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ በመልእክታቸው እየሰራን ያለነው ትውልድን በመገንባት ላይ መልካሙን መንገድ የማሳየት ስራ ላይ ነው በመሆኑም ያለንበትን ሀላፊነትና ተግባር በአግባቡ ተረድተን የሀገራችንን አደራ በመወጣት እና መልካም ትውልድን በመገንባት ላይ ትኩረት ሊኖረን ያስፈልጋል ያሉ ሲሆን በጋራና ስንሰራ ለውጥ እናመጣለን የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
አቶ ደረጀ ሙሉጌታ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በሃላፊነት ከተሰራ የትኛውም ችግር ሊፈታ የሚችል መሆኑን ገልጸው የተቋማቶቻችንን ችግር ለመፍታት በሀላፊነት እንዲሁም ወቅታዊነቱን የጠበቀ ስራ አስፈላጊ ነው ያሉ ሲሆን ይህን ለማድረግ ደግሞ የእቅድ አካል አድርጎ መስራት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
+7
ማንኛውንም ስራ ስንሰራ የሀገራችንን አደራ በመወጣት እና መልካም ትውልድን በመገንባት ላይ ትኩረት ሊኖረን እንደሚገባ ተገለጸ፡፡
(ህዳር 19 ቀን 2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የየካ ቅ/ጽ/ቤት የትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጥ ዳይሬክቶሬት የአጠቃላይ ትምህርት የ2018 ዓ.ም የቅድመ አንደኛ፣አንደኛእና መካከለኛ ደረጃ የግል ትምህርት ቤቶች የድንገተኛ ኢንስፔክሽን ግኝት ትንተና ለባለድርሻ አካላት አቀረበ::
ወ/ሪት ትእግስት ጌታነህ የቅ/ጽ/ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ በመልእክታቸው ተቋማት ወደ ስታንዳርድ መምጣት ግዴታ መሆኑን ገልጸው የችግሩ መፍትሄዎች የተቋማት ባለቤቶች እንደመሆናችሁ ከቀረበው ሪፖርት ክፍተታችሁን በመለየትና የእቅዳችሁ አካል በማድረግ ተቋማችሁን ማሻሻል የግድ ነው ብለዋል::
አቶ ደረጀ ሙሉጌታ የቅ/ጽ/ቤቱ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ከዉይይት መድረኩና ከቀረበው ትንተና በመነሳት ክፍተታችሁን በመለየትና ተቋማችሁ ላይ መስራት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸው ተቋማት መቀጠል የሚችሉት ህጋዊነታቸው ማረጋገጥ ሲችሉ ነው ብለዋል::
ወ/ሮ ሮዛ ሁሴን የቅ/ጽ/ቤቱ የስነ-ምግባርና ጸረ ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ሙስና የጋራ ጠላታችን እንደመሆኑ በጋር በመስራትና መረጃዎችን በመስጠት ሙስናን ልንከላከል ይገባል የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል::
+5
ቅ/ጽ/ቤቱ በ2018 ዓ.ም የአጫጫር ስልጠና የሚሰጡ ተቋማት የድንገተኛ ኢንስፔክሽን ግኝት ትንተና ሪፖርት ለባለድርሻ አካላት አቀረበ::
(ህዳር 19 ቀን 2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የየካ ቅ/ጽ/ቤት የትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጥ ዳይሬክቶሬት የ2018 ዓ.ም የቴ/ሙያ አጫጭር ስልጠና የሚሰጡ ተቋማት የድንገተኛ ኢንስፔክሽን ግኝት ትንተና ለባለድርሻ አካላት አቀረበ::
አቶ ወንድወሰን አየለ የቅ/ጽ/ቤቱ የቴ/ሙያ ተቋማት ጥራት ማረጋገጥ ቡድን መሪ የትንተና ሰነዱን ያቀረቡ ሲሆን በቦሌ፣በየካ እንዲሁም በሚኩራ ክ/ከተማ በድምሩ ለ93 ተቋማት ድንገተኛ ኢንስፔክሽን የተሰራ መሆኑን ገልጸው የድንገተኛ ኢንስፔክሽን ዋና ዋና ግኝቶች፣ከቼክሊስት መለኪያ አንጻር የታዩ ነጥቦች፣በጥንካሬ የታዩ ተቋማትና በስትራቴጅክ ጥሰት ተጠይያቂ የሆኑ ተቋማት ያጋጠሙ ችግሮችና የተፈቱበት አግባብ በዝርዝር አቅርበዋል::
ወ/ሮ ካሳ መኩሪያ የቅ/ጽ/ቤቱ የእውቅና ፍቃድና እድሳት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን የተከናወኑ ተግባራት፣ከስታንዳርድ አንጻር የተቋማት እዉቅና ፍቃድ እድሳት ትንተና ዋናዋና ግኝቶች ፣ደረጃ ማሳደግ እና አዲስ እዉቅና ፍቃድ ተግባራት ክንውን እንዲሁም ያጋጠሙ ችግሮች እና የተወሰደ መፍትሄ በሚሉ ይዘቶች ላይ በዝርዝር አቅርበዋል፡፡
በተጨማሪም ይህንን መሰረት ያደረገ የ2018 በጀት ዓመት መሪ እቅድ ፣ BSC እቅድ፣የመልካም አስተዳደር እቅድ፣የኪራይ ሰብሳቢነት ማክሰሚያ እቅድ እና ሌሎች የተለዩ ማስፈፀሚያ እቅዶች ታቅደው ወደ ስራ በመግባት በመተግበር ላይ ይገኛል ያሉ ሲሆን በ2018 ዓ.ም አዲስ እዉቅና ለተሰጣቸዉ ተቋማት በሙሉ ተገቢውን ስታንደርድ አሟልተው ስለመሰጠቱ /Accreditation Approval team/ በማቋቋም፣ቡድኑ በተሰጠው ተግባርና ኃላፊነት መሰረት አዲስ እውቅና የጠየቁ ተቋማትን ሙሉ በሙሉ እዲሁም እድሳት የተሰራላቸውን ተቋማት በናሙና በመለየት ተቋማት ድረስ በመሄድ ምልከታ በማድረግ ተገቢው ምዘና መደረጉን በመገምገም ተገቢነቱን የማረጋገጥ እና እርምት የመስጠት ስራ ተሰርቷል፡፡ ከደረጃ በታች የሆኑ ተቋማትን ማለትም በጣም ዝቅተኛ የማለፊያ ነጥብ ያመጣ ተቋም የ2018 ዓ.ም ምዝገባ ከመጀመሩ በፊት ተገቢዉን ውሳኔ በማስተላለፍ ተቋማቱ መዘጋታቸውን የማሳወቅ ስራ መስራት እና ተማሪ እንዳይመዘግቡ ማስጠንቀቂያ መስጠት መረጃውን ለሚመለከተው አካላት ተደራሽ ማድረግ ተችሏል ብለዋል፡፡
አቶ ሀፍቱ ገ/ሚካኤል የቅ/ጽ/ቤቱ የኢንስፔክሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የ 2018 በጀት ዓመት 1ኛ ሩብ ዓመት አቅድ አፈፃጸም ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን በሩብ ዓመቱ የተሰሩትን የቅድመ ዝግጅት ስራዎች፣እቅድ እና ሪፖርት ዝግጅት፣ ዋና ዋና ተግባራት፣አበይት ሰራዎች አፈጻጸም እንዲሁም የነበሩ ደካማ እና ጠንካራ ጎኖች ያጋጠሙ ችግሮችና የተፈቱበተት አግባብ በዝርዝር አቅርበዋል፡፡
አቶ አንዋር አብዲ የቅ/ጽ/ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ባስተላለፉት መልዕክት የትምህርት ተደራሽነትን የትምህርት ጥራትን እንዲሁም ተወዳዳሪነትን ለማስጠበቅ ዘግጁ መሆን ተቋማቶችን ወደ ስታንዳርድ እንዲመጡ ማድርግ ቁርጠኛ መሆን በጋራ መስራት የሚያጋጥሙ ችግሮችን በጋራ በሀላፊነት እንዲሁም በወቅቱ መፍታት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸው ተወዳዳሪ ትውልድ የምንፈጥረው ይህንን መፈጸምና ማሰፈጸም ስንችል ነው ያሉ ሲሆን የህግ የበላይነት እና ለህግ ተገዥ መሆን ደግሞ የግድ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
በመጨረሻም በክረምት በጎ ፍቃድ ስራዎች ላይ አስተዋጽኦ ላደረጉ የትምህርት ተቋማት እውቅና ተሰቷቸዋል፡፡
+8
ቅ/ጽ/ቤቱ የ2017 ዓ.ም የእውቅና ፍቃድና እድሳት እና የ2018 በጀት ዓመት 1ኛ ሩብ ዓመት አቅድ አፈፃጸም ሪፖርት ለባለድርሻ አካላት አቀረበ፡፡
(ህዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የኮልፌ ቀራንዮ ቅ/ጽ/ቤት የ2017 ዓ.ም የእውቅና ፍቃድና እድሳት እና የ 2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት አቅድ አፈፃጸም ሪፖርት ለባለድርሻ አካላት አቀረበ፡፡
+6
”የህጻናት ጥበቃና የመጫወት መብት ለሁሉም ህጻናት” 36ኛው አለም አቀፍ የህጻናት ቀን በድምቀት ተከበረ፡፡
(ህዳር 16 ቀን 2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን 36ኛውን አለም አቀፍ የህጻናት ቀን”የህጻናት ጥበቃና የመጫወት መብት ለሁሉም ህጻናት” በሚል መሪ ቃል የባለስልጣኑ ሰራተኞች አክብረዋል፡፡
ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሴቶች፣ህጻናት እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ወ/ሮ ራሄል ሙሉጌታ የህጻናት መብት ደህንነት ማስጠበቅ ባለሙያ ጨዋታ ለህጻናት እንደ ምግብ ሁሉ አስፈላጊና መሰረታዊ የሕጻናት መብት መሆኑን ገልጸው ለአካላዊ እድገት ፣ለአእምሮ ፣ለስሜት ፣ማህራዊ እና ለጤናማ እድገት ወሳኝ መሆኑን ባቀረቡት የግንዛቤ ማሳደጊያ ሰነድ አብራርተዋል፡፡በተጨማሪም ህጻናት ደስተኛና ጤናማ ሆነው እንዲያድጉ ወላጆች ፣መምህራን፣የአካባቢው ማህበረሰብ እና መንግስታዊ አካላት ወሳኝ ሚና እንዳላቸው ገልጸው ህጻናትን ከጥቃትና ከጉልበት ብዝበዛ ጥበቃ በማድረግ ደህንነታቸውን በማረጋገጥ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል ሀላፊነቱን እንዲወጣ አሳስበዋል፡፡
የባለስልጣኑ የአሰራር ጥራት ቁጥጥር ብድን መሪ አቶ አምላኩ ተበጀ ህጻናትን በጨዋታ በማስተማር እና ምቹ አካባቢን በመፈጠር ደህንነታቸውን ማስጠበቅ የሁሉም ሀላፊነት መሆኑን ተናግረዋል፡፡
+3
የአራዳና ቂርቆስ ቅ/ፅ/ቤት አመራሮችና ሰራተኞች 20ኛውን የኢትዮጵያ የብሔር-ብሔረሰቦችና ህዝቦችን ቀን በዓል በፓናል ውይይት ማክበራቸው ተገለጸ፡፡
(ህዳር 16 ቀን 2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የአራዳና ቂርቆስ ቅ/ፅ/ቤት አመራሮች፣ሰራተኞችና ባለድርሻ አካላት የ20ኛውን የኢትዮጵያ የብሔር-ብሔረሰቦችና ህዝቦችን ቀን "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ-ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ቃል በፓናል ውይይት ማክበራቸው ተገለፀ፡፡
በበዓሉ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቅ/ፅ/ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ያሬድ ካሳ በመልዕክታቸው የኢትዮጵያ የብሔር-ብሄረሰቦችና ህዝቦችን በዓል "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ-ብሄራዊ አንድነት"በሚል መሪ ቃል በዓሉን ስናከብር የህዝቦች መብት መከበር ዋስትና ያረጋገጠው ህገ-መንግስት የፀደቀበትን ቀን ህዳር 29 በየዓመቱ በተለያዩ ሁነቶች ላለፉት 19 ዓመታት ሲከበር መቆየቱን አስረድተው ዘንድሮም ለ20ኛ ጊዜ ሲከበር በአገራችን ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ማዕቀፍ የተገነባ ህብረ-ብሄራዊ አንድነት ስር እንዲሰድና እንዲዳብር ሰፊ ስራ መሰራቱን ዋና ስራ አስኪያጁ ገልጸዋል፡፡
በመጨረሻም የ20ኛውን የኢትዮጵያ የብሔር-ብሔረሰቦችና ህዝቦችን በዓል የውይይት ሰነድ ያቀረቡት የቅ/ፅ/ቤቱ የኢንስፔክሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ አሰፋ በዴሞክራሲ፣በፌዴራሊዝም ስርዓትና በፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ምንነት እና በዴሞክራሲያዊ ባህሪያት መካከል ያለውን ግንኙነት እና በሌሎችም ርዕሰ-ጉዳዮችን በማቅረብ ውይይትና ግንዛቤ ተፈጠሯል፤አስተያየቶችና ምላሾችም ተሰጥቶባቸዋል፡፡
ባለስልጣኑ አለም አቀፍ የጸረ ሙሰና ቀን"ትውልድን በስነ-ምግባር ተቋምን በአሰራር" በሚል መሪ ቃል አከበረ፡፡
(ህዳር 15 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በአለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ በአገር አቀፍ ደረጃ ለ21ኛ ጊዜ የሚከበረውን የጸረ ሙሰና ቀን"ትውልድን በስነ-ምግባር ተቋምን በአሰራር" በሚል መሪ ቃል አከበረ፡፡
የባለስልጣኑ የስነ-ምግባርና ጸረ- ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አበበ ወንድሙ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን ስነ-ምግባርና ሙስና፣የጸረ ሙስና ትግል ሁኔታ፣የባለድርሻ አካላት ሚና፣የጸረ-ሙስና ትግሉ ቀጣይ አቅጣጫዎች በሚሉ ይዘቶች በሰነዳቸው አካተዋል፡፡ ሁላችንም ስነ-ምግባር ራሱን መገንባት ላይ ግልጽነትና ተጠያቂነት ላይ ሙስና እና ብልሹ አሰራር መለየትና ማጋለጥ ላይ የስነ-ምግባር እሴት ግንባታ ማጠናከር ላይ በትኩረት መስራት አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡
ቀኑን ምክንያት በማድረግ በ9ኙም የባለስልጣኑ ቅ/ጽ/ቤቶች በተለያዩ ሁነቶች በድምቀት ተከብሮ ውሏል፡፡
ባለስልጣኑ አለም አቀፍ የጸረ ሙሰና ቀን"ትውልድን በስነ-ምግባር ተቋምን በአሰራር" በሚል መሪ ቃል አከበረ፡፡
(ህዳር 15 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በአለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ በአገር አቀፍ ደረጃ ለ21ኛ ጊዜ የሚከበረውን የጸረ ሙሰና ቀን"ትውልድን በስነ-ምግባር ተቋምን በአሰራር" በሚል መሪ ቃል አከበረ፡፡
+5
የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያ እና የዕውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር ተካሄደ፡፡
(ህዳር 15 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያ እና የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር "የተግዳሮት ምላሽ አሰጣጥ "በሚል ርዕስ የባለስልጣኑ አመራሮች እና ሰራተኞች በተገኙበት ተካሂዷል፡፡
አቶ አምላኩ ተበጀ የባለስልጣኑ የአሰራር ጥራት ቁጥጥር ቡድን መሪ በርዕሱ ላይ ዝርዝር ሰነድ እና ተሞክሯቸውን ያጋሩ ሲሆን ህይወት በተለያዩ ውጣ ወረዶች ያሏት ብትሆንም የተለያዩ ችግሮች የህይወት ውጣ ውረዶች ቢገጥሙንም ወደ አስደናቂ ነገር እና ወደ ታላቅ ጥበብ መለወጥ እንዲሁም አይበገሬነትን ተቋቁሞ ማለፍን ማዳበር አለብን ያሉ ሲሆን በህይወታቸው የገጠሟቸውን ተግዳሮቶችና ያለፉበትን መንገድ አጋርተዋል፡፡
አቶ አበበ ወንድሙ የባለስልጣኑ የስነ-ምግባርና ጸረ- ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ችግር ሊያጋጥም ይችላል ያንን ችግር የምንወጣበትን ጥንካሬ እና ጥበብ መላበስ አስፈላጊ እና የግድ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አቶ አበበ ወንድሙ የባለስልጣኑ የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የመወያያ ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን የዴሞክራሲያዊ ሥርዐት ጽንሰ ሃሳብ እና ባህሪያት፣ የዴሞክራሲ ትርጉም፣በዴሞክራሲና በፌዴራሊዝም መካከል ያለዉ አንድነትና ልዩነት ምንድነዉ?፣በፌዴራልዝምና በፌዴሬሽን መካከል ያለዉ አንድነትና ልዩነት ምንድ ነዉ?፣ አንድ አገር ፌዴራል ሥርዓት አለ የሚለዉ መቼ ነዉ፣ የሚሉ ሃሳቦችን ባቀረቡት ሰነድ በዝርዝር አብራርተዋል፡፡
አቶ አምላኩ ተበጀ የባለስልጣኑ የአሰራር ጥራት ቁጥጥር ቡድን መሪ በውይይቱ ማጠቃለያ ላይ እንደገለጹት ኢትዮጵያ የጋራ ሀገራችን ስለሆነች በሀገራዊ ሁኔታ ላይ የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ ህብረ ብሔራዊ አንድነታችንን ማጠናከር ተገቢ ነው ብለዋል፡፡
በዕለቱ በቀረበው የመወያያ ሰነድ ላይ የባለስልጣኑ ሰራተኞች ሰፊ ውይይት አድርገውበታል፡፡
+8
“ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሔራዊ አንድነት”
(ህዳር 10 ቀን 2018 ዓ.ም)የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን “ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል ለ20ኛ ጊዜ የሚከበርውን የብሄር ብሔረሰቦች ቀን አስመልክቶ ውይይት አከናወነ፡፡
አቶ ኢዘዲን ሙስባህ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ በመርሀ-ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ሀገራችን የብዙ ብሄሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ባለቤት መሆኗን ገልጸው ይህን ብዝሃነትና ህብረ ብሔራዊነት በእኩልነት፣አንዳችን ለሌላችን መተሳሰብን መከባበርን እንዲሁም ወንድማማችነትን በመፍጠርና በመተግበር ህብረ- ብሔራዊ አንድነትን ከፍ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
+6
የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያ እና የዕውቀት ሽግግር መርሃ ግብር ተካሄደ፡፡
(ህዳር 8 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያ እና የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር በዛሬው እለት የተካሄደ ሲሆን በመድረኩም የባለስልጣኑ አመራሮች እና ሰራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
አቶ ግዛት መኮንን የአጠቃላይ ትምህርት እውቅናና ፍቃድ እድሳት ባለሙያ ደስታ ምንድነው? ደስታን እንዴት እናገኛለን? ደስታን የሚያሳጡን ነገሮች ምንድናቸው? በሚል ርእስ ላይ የመማማሪያ ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን ደስታ ለሰው ልጆች የተሰጠ ጸጋ በሰው ልጆች አእምሮ ውስጥ ያለና የሚኖር የአዕምሮ ውቅር ነው ብለዋል፡፡አክለውም የሰው ልጅ ፍላጎት ገደብ የለሽ እንደመሆኑ ደስታችንን እንዳያሳጣን መጠንቀቅ አለብን ብለዋል፡፡
ዶክተር ደሳለኝ ጴጥሮስ የባለስልጣኑ አማካሪ በመርሀ-ግብሩ ላይ እንደገለጹት ደስታ ከራስ ይጀምራል ያሉ ሲሆን ደስታን በሰው ልጆች ህይወት ውሰጥ በየትኛውም አጋጣሚ በመፍጠር ደስተኛ መሆን ይገባል፤ በመሆኑም ባለን ነገር ደስተኛ እንሁን ብለዋል፡፡
