en
Feedback
Ethio monitor

Ethio monitor

Open in Telegram
1 482
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ከአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር የተላለፈ ትዕዛዝ ፦ በቀን 19/11/2015 ዓ.ም ጎርጎራ እና ጮሃይት አካባቢ ባሉ ገዳማት በፆሙ የገዥው ስርዓት በሬ ማረዱን ተከትሎ የህዝብን ቁጣ መቀስቀሱ ቀደም ብለን ገልፀን ነበረ። ሆኖም ግን ህዝባችን በግዥው ሃይሎች በከባድ መሳሪያ እየተደበደበ በመሆኑ የተነሳ በአርበኛ ግዛቸው እና በአርበኛ ደረጄ የሚመራው ፋኖ አሁን ውጊያ ላይ ነው!! ከዚህ አንፃር ፦ ► የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር የቢትወደድ አዳነ ብርጌድ በሰሜኑ አቅጣጫ ► የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር የጎቤ ብርጌድ በአርማጭሆ አቅጣጫ ► የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር የጎንደር ብርጌድ(ጎንደር ከተማ) ► የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር የቋረኛው ብርጌድ በደንቢያ አቅጣጫ ► የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር የበጌምድር ብርጌድ(ደቡብ ጎንደር) ► የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር የሚኒልክ ብርጌድ ► የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር የብርሌው ብርጌድ በመተማ አቅጣጫ አጠቃላይ ህዝባችን ጮሃይት የተፈጠረው ጉዳይ የሁላችንም ጉዳይ ስለሆነ እራሳቹህን በፍጥነት እንድታዘጋጁ!! በስልክ በሚሰጣቹህ መመሪያ መሰረት ለትግበራ በተጠንቀቅ ላይ ሁኑ!! ከአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር

ከ30 ሺ በላይ የአማራ ተወላጅ የሆኑ የመከላከያ ሰራዊት አባላት መታሰራቸው ታወቀ። በአማራ ሕዝብ ላይ የተከፈተውን መጠነ ሰፊ መንግሥታዊ ወረራ የተቃወሙና ሊቃወሙ ይችላሉ የተባሉ ከ30 ሺ በላይ የአማራ ተወላጅ የሆኑ የመከላከያ ሰራዊት አባላት መታሰራቸውን ከደህንነትና ከወታደራዊ ምንጮች ለማረጋገጥ ችያለሁ። በየዕዝ መምሪያ ቦታዎች ጉዳያቸው በህግ ሳይታይ በእነ ብርሀኑ ጁላ ቀጥተኛ ትዕዛዝ እንደታሰሩ ከመረጃ ምንጮቼ አረጋግጫለሁ። ከዚህ በተጨማሪ የመከላከያ ሰራዊት በአማራ ሕዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን ግፍ በመቃወም የአማራ ሕዝባዊ ኃይልን እየተቀላቀሉ ያሉ የአማራ ተወላጅ የሆኑ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከቀን ቀን ቁጥራቸው እያሻቀበ መሆኑን ምንጮቼ አክለው ገልጸዋል። አንዳንድ ለጊዜው ስማቸውን የማልጠቅሳቸው ጀነራሎች ከስራ ውጭ ተደርገው ክትትል እየተደረገባቸው እንደሆነም ታውቋል። በተሾመ ቶጋ የሚመራው የተሃድሶ ኮሚሽን ከ3 መቶ 70ሺህ በላይ የቀድሞ ጦር በዲ-ሞቢላይዜሽን ስም ለመበተን እየሠራ መሆኑ በመንግሥት ሚዲያዎች መነገሩ ይታወሳል። በወያኔ የአገዛዝ ዘመን ከ40 ሺ በላይ የአማራ ተወላጅ የሆኑ የመከላከያ ሰራዊት አባላት መባረራቸው ይታወሳል። ድል ለአማራ ሕዝብ!

የብልፅግና የኮማንዶ ሠራዊት አባላት ለፋኖ እጃቸውን ሰጥተዋል። እንደምርኮኛ ጫማቸው ቢወልቅም ምትክ ተሠጥቷቸዋል። ይሔ የኮማንዶ አባላቱ ተግባር ሊበረታታ የሚገባው ተግባር ነው። ሌላው የሠራዋቱ አባል
+1
የብልፅግና የኮማንዶ ሠራዊት አባላት ለፋኖ እጃቸውን ሰጥተዋል። እንደምርኮኛ ጫማቸው ቢወልቅም ምትክ ተሠጥቷቸዋል። ይሔ የኮማንዶ አባላቱ ተግባር ሊበረታታ የሚገባው ተግባር ነው። ሌላው የሠራዋቱ አባልም ሊከተለው የሚገባ ነው።

የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ም/ሃላፊው ከሃላፊነት ተነሱ!
የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ም/ሃላፊው ከሃላፊነት ተነሱ!

የድል ትውልድ አካል ነን ‼ ድል ለአማራ !! #AmharaStruggle #Justice4Amhara #AmharaGenocide
የድል ትውልድ አካል ነን ‼ ድል ለአማራ !! #AmharaStruggle #Justice4Amhara #AmharaGenocide

የብልጽግና መንግስት ያሉበትን ማነቆዎች ለይቶ ገመድ ማጥበቅ ሌላው ያልሰራንበት የትግል ስልት ነው። አብይ አህመድ እንደወረቀት እያተመ የሚበትነውን የኢትዮጵያ ገንዘብ ማሳተም እስከማይችልበት ደረጃ ድረስ በውጭ ምንዛሬ እጥረት ተወጥሯል።ከሰሞኑ አንድ የስዊዝ ገንዘብ አታሚ ድርጅት ክፍያ አልተለቀቀልኝም በሚል ያተመውን በርካታ ቢሊዮን የኢትዮጵያ ገንዘብ አለቅም ብሏል። በተመሳሳይ የዳንጎቴ ሲሚንቶን ትርፍ 180 ሚሊዮን ዶላር ለባለሀብቱ ማቅረብ ያቃተው ብሔራዊ ባንካችን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከናይጀሪያ ትኬት ቢሮ የሰበሰበውን 120 ሚሊዮን ዶላር ጭማድ አስይዞታል። አየር መንገዱ በምትኩ ከብሔራዊ ባንክ በኢትዮጵያ ብር እንዲቀበል ተገዷል። የወደብ ኪራይ መሸፈን ያልቻለው ብልፅግና አንድለናቱ የሆነውን አየር መንገድ ለኤርትራ መደራደሪያ አቅርቧል። ኤርትራ 30% ከአየር መንገዱ ድርሻ ይሰጠኝ በማለቷ እነሳውዲ አረቢያ ለሽምግልና ተጋብዘዋል።  ዲያስፖራው የሬሚታንስ እቀባ በማድረግ፤ እንዲሁም አሁን ላይ ትልቁ የውጭ ምንዛሬ ምንጭ የሆነውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጉዞ አማራጭ ባለማድረግ ስርዓቱን የበለጠ ማዳከም ይቻላል። ምስጋናው ዘ-ግዮን

"በወራሪዎች የተያዙ ግዛቶቻችንን ከወራሪዎቹ አፅድቶ እንዲያስረክበን የመከላከያ ሰራዊት ሃላፊነት ተሰጥቶታል።ህዝባችን የተሟላ ሰላም አገኘ የሚባለው በእነዚህ ኋላቀር ወራሪዎች የተያዙት ሁሉም ግዛቶቻችን ሲመለሱ ነው።በዚህ ዙሪያ ከመንግስት ጋር ስለተሰማማን በአፈፃፀሙ ዙሪያ የመንግስት መከላከያ ሰራዊት መሬት ላይ የጀማመራቸው አንዳንድ ተግባራዊ እንቅስቃሴዎች አሉ። ያም ሆነ ይህ መንግስት ወራሪዎቹን ካካባቢው አፅድቶ ግዛቶቻችንን መልሶ ያስረክበናል ማለት ነው። ይፈጥናል ? ወይስ ይዘገያል ?መቼ ያስረክበናል የሚለው ግን በፌደራል መንግስቱና በመከላከያ ሰራዊቱ አፈፃፀም የሚወሰን ይሆናል።" (ጌታቸው ረዳ ለትግሬ ዲያስፖራ ከተናገረው የተወሰደ ነው! ትርጉም Asfaw Abreha ) ድል ለአማራ! #AmharaStruggle #Justice4Amhara #AmharaGenocide #WarOnAmhara

"የሰንበት ውሎ" Natnael Ye ዛሬ እኔ፣ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ ጄነራል ተፈራ ማሞ እና ባለቤቱ መነን ኃይሌ ከጠዋቱ 3 ሰዓት በዝነኛው ማጎሪያ ቃሊቲ ወህኒ ደርሰናል። የጉዞ ዓላማችን በዐማራ
"የሰንበት ውሎ" Natnael Ye ዛሬ እኔ፣ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ ጄነራል ተፈራ ማሞ እና ባለቤቱ መነን ኃይሌ ከጠዋቱ 3 ሰዓት በዝነኛው ማጎሪያ ቃሊቲ ወህኒ ደርሰናል። የጉዞ ዓላማችን በዐማራነታቸው በግፍ የታሰሩትን መስከረም አበራ፣ ዳዊት በጋሻው፣ ጎበዜ ሲሳይ፣ ዶ/ር ወንደሰን እና ሌሎች ስድስት ወንድም እህቶቻችን መዘየር ነው። በዚህም ሁሉም ታሳሪዎች በጠንካራ መንፈስና በጥሩ መነቃቃት ላይ በመሆናቸው ተደስተን ተመልሰናል። ማስታወሻ:- እኔ ይህን ፎቶና ጽሑፍ ፖስት ያደረኩት እስረኛ መጠየቃችንን ለማወጀ አይደለም። እናንተም ተመሳሳዩን ታደርጉ ዘንድ ለማስታወስ እንጂ። ትግል፣ በምትችለው ዐቅም መሳተፍ ማለት ነውና። እንዴትስ በሚሊዮኖች አማራ በሚኖርባት አዲስ አበባ፣ በዐማራነታቸው የታሰሩ ወገኖች ጉዳይ ስለምን የቅርብ ቤተሰብና የወዳጆቻቸው ብቻ ይሆናል? እንዲህ ዓይነቱ ግዴለሽነትም ነው ጠላትን የልብ ልብ ሰጥቶ የሚያጠናክረው። በተረፈ፣ ሁላችንም ከእስረኞች ጎን ቆመን በፍርድ ቤትም ሆነ ወህኒ መገኘት ስንችል:- አንድነታችን እየጠነከረ፣ ጉልበታችን እየፈረጠመ፣ ፍርሃት እየተሸነፈ፣ የለውጡ ቀናት እየቀረበ ይሄዳል። አዳዲስ ጀግኖችም እንዲወለዱ በር ይከፍታል። ከግፉአን ጎን መቆም፣ ግፈኛ ሥርዓትን መታገል ነው!

በነቀምቴ እስር ቤት፣ ከባኮ ጀምሮ እስከ ሻምቡና ደንጎሮ፣ ከጊምቢ ጀምሮ እስከ ደንቢደሎ ያሉ እና በሌሎችም የኦሮሚያ አካባቢዎች የህሊና እስረኞች የሚገኙበትን የእስር አያያዝና መከራ ጠቅለል አድርጎ የሚያሳይ ከእስር ቤት የወጣ መረጃ! እነ ሙሉቀን አንተነህ እና ሌሎች በማንነታቸው በበነቀምት በግፍ እስር ላይ የሚገኙ አማራዎች:_ 1ኛ-  በመጀመሪያ ደረጃ የተከሰሱበት ክስ በኦሮሚያ የተጻፈ በመሆኑና እኛም በነበረው የትምህርት ስርዓት በአማራ የተማርን በመሆኑ የቋንቋ እጥረት ስለሚኖር በማለት ክሱን ቋንቋ በሚችሉ ሰዎች በማስተርጎም የክሱን ሁኔታ መረዳት፤ 2ኛ- የተከሰሱበት በሐሰት መስካሪዎች የተሞላ በመሆኑና በሶስት አይነት የክስ መዝገብ በመሆኑ በህግ ባለሙያዎች ማለትም ጠበቃ በመያዝ በከፍተኛ የፌዴራል ፍርድ ቤት ክሱን በዝርዝር በማቅረብ በገለልተኛ አካል እንዲጣራ ማድረግ ሲሆን ክሱ በከፍተኛ ወንጀል፣ በመካከለኛና አነስተኛ በሚል የተዘረዘረውን ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ ለጠበቃዎቹ በቅርበት መረጃዎቹን መግለጽና በጹሑፍ ማስረጃነት ማቅረብ፤ 3ኛ- በእዚህ ሁሉ እስረኞች ላይ የተፈጸመውንና እየተፈጸመ ያለውን የሰብዓዊ ጥሰት አያያዝ ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ልክ እንደዚህ ቀደሙ በማስረዳት በቦታው ተገኝተው ለፍርድ ቤቱ ግብዓት የሚሆን በተቋሙ[ኢሰመጉ] የተረጋገጠ ለጠበቃዎቹ በቋሚነት ፊት ለፊት በመቅረብ ለተያዙት ጠበቃዎች ማስረጃዎችን ማቅረብ፤ 4ኛ- ለእስረኞቹ ጠበቃ ለተባሉት በአንዳንዳችን ለአንድ ጠበቃ 50ሺህ ብር ተብሎ የቀረበብንም ፍትሐዊ አለመሆኑንና የነቀምቴ ከፍተኛ ፍርድ ቤት እስረኞች ጠበቃ ይዘው መከላከያ ማቅረብ እንዳንችል መደረጋችንንም አንዱ ጫና መሆንና ፍርድ ቤቱ ያለምንም ይግባኝ ፅኑ ፍርድ ለመስጠት መሆኑን፤ 5ኛ- ክሱ በዘር ማጥፋት በሚል በመሆኑ ለዚህ ደግሞ እንዲያመቻቸው የትግራይ ተወላጆችንና የኦሮሞ ተወላጆችን ብቻ በመጥቀስ የአማራ ተወላጆች ሞትን ደግሞ እንደገዳይ በማስቆጠር መስራታቸውን ማስገንዘብ፤ 6ኛ-  ክሱን አስመልክቶ በእለቱ ያልነበሩ የፈጠራቸውን የማይፈሩ ግለሰቦችን አቅርበው ለማስመስከር ስለሚችሉ፣ እነዚህን የሐሰት ምስክሮች መስቀለኛ ጥያቄ ለመጠየቅ ሰፊ ጊዜና ነፃነት ሊሰጡን ስለማይችሉ፥ "ፍርደ ገምድል" ስለሚሆን በተቻለ መጠን በህግ አግባብ እንዲቻል በየትኛውም መንገድ ከሚመለከታቸው ጋር በመነጋገር መሞከር፤ 7ኛ- ማህበራዊ ሚድያን በሰፊው ስለመጠቀምና ማሳወቅ፣ ክሱ መርጠህ ወይም ፈልገህ ምታ እንጂ እውነተኛና የተጣራ ባለመሆኑ፣ በእለቱ በማን ችግር እንደተፈጸመ፣ ማን እንደፈጸመው፣ የጠፋው የሰውና የንብረት ውዲመት በማን እንደተፈጸመ በገለልተኛ አካል ሳይጣራ ክሱ መመስረት እንደሌለበት ማስረዳት፤ 8ኛ- የሞቱት ከሁሉም ብሔር ቢሆንም በክሱ የቀረበው ግን ሆን ተብሎ የክልሉ ሰዎችና ትናንት እንደውሻ ሲናጠቁ የነበሩትን የህወሐት ሰዎችን ዛሬ ተቆርቋሪ በመምሰል ማካተቱ በቀጣይ ሊሰሩት ያሰቡትን ቁማር በግልጽ ያሳያል። 9ኛ- ከክሱ ጀርባ ያሉ ምስክሮች ስም ዝርዝር በተመለከተ አንድ የከተማ አስተዳደር (የፀጥታ)  መዋቅር "የዘር ማጥፋት" ወንጀል ትርጉም ምን እንደሆነ ሳይገነዘብ ፅፎ የላከው ደብዳቤን በተመለከተ በርካታ ብሔርን ከሚያስተዳድር አካል የሚጠበቅ እንዳልሆነና ዘር ማጥፋት ወንጀል ምንነቱን የማያውቅ መሆኑን እንደማስረጃ ተጽፎ ከቀረበው ማስገንዘብና በቀጣይ እንዴትስ ህዝቡን ሊመራ እንደሚችል፤ ዘር ማጥፋት ማለት በአንድ ቤተሰብ በአንድ ቦታ ላይ ባሉበት አንድም ሰው እንዳይተርፍ አድርጎ ለሚወሰድ እርምጃ ሲሆን በአንድ ሁኔታ ለተፈጠረ ግጭት ሊፃፍ ስለማይገባ፥ ዋና አላማው ይህ ደብዳቤ የሚያሳየው አስተዳደሩ የሚሰራው ለተለየ ወገን ብቻ መሆኑን ነው። 10ኛ- በባኮ ተወላጆችና በ10 ተወላጆች ላይ የተፈጸመው በተመሳሳይ በኛ ላይ ሊፈጽሙት እንደሆነ እየተገነዘብን ነው። ስለዚህ ይህ መልዕክት እንደደረሳችሁ ምንም ሳትሰላለቹ በሚድያና ለህግ አካል ጋር ጠበቃ በመያዝ በገለልተኛ አካል እንዲጣራ ተጽዕኖ መፍጠር ይኖርባችኋል።       "መቼም ይሁን መቼም እናሸንፋለን!"        "መታሰር ሽንፈት አይደለም!" መልዕክቶች እና ሌሎች ተያያዥ ማስረጃዎችን በተከታታይ እናቀርባለን። ምንጭ_የአንገር ጉትን ልዩ ዞን ጥያቄ (አጉልዞ) ጥያቄ

የፋኖ ልዕልና !! ከብልፅግና ተልዕኮ የወሰደ አንድ ሠርጎገብ ባንዳ፡ የአባይ ሸለቆ ብርጌድ መሪ ሙሉቀን አደራውን ለመግደል F1 ቦምብ በመወርወር ሁለት የአባይ ሸለቆ ዘብ አባላቶች ላይ መጠነኛ ጉዳት
የፋኖ ልዕልና !! ከብልፅግና ተልዕኮ የወሰደ አንድ ሠርጎገብ ባንዳ፡ የአባይ ሸለቆ ብርጌድ መሪ ሙሉቀን አደራውን ለመግደል F1 ቦምብ በመወርወር ሁለት የአባይ ሸለቆ ዘብ አባላቶች ላይ መጠነኛ ጉዳት አድርሷል። ይሄ ባንዳ በክትትል ከተያዘ በኋላ ግን እርምጃ አልተወሰደበትም። ይልቁንም አማራዊ እሴቶችንና ትግሉን አስረድተው በጥፋቱ ተፀፅቶ መግደል የፋኖ ተግባር አይደለም የሚል ትምሕርት ቀስሞ በምህረት ተለቋል። ድል ለአማራ !! - * ፎቶ፥ በምክር የተላከው ባንዳ በባዶ እግሩ ህዝብ እየተጓዘ የሚገኘው ነው።

Inbox " የአማራ ህዝብ እያደረገ ባለው የህልውና ተጋድሎ የኪነጥበብ ባለሞያዎች ህዝብን በማንቃት በማስተባበር ትልቅ አስተዋፅኦ ማድረግ ሲገባቸው አንቀላፍተዋል ከወያኔ የኪነት ሰወች አልተማሩም በሰላሙ ጊዜ ማጫፈር ገንዘብ መሰብሰብ ብቻ ህዝብ መከራ ላይ ሲወድቅ ሲጨፈጨፍ ቁጭ ብሎ ማየት!  "

photo content
+4

ምን ብዬ ልንገራት? #የመንግስታዊ_ክህደቱ_ማሳያ ... ከነሀሴ 24 /2014 ዓ.ም ጀምሮ ለ28 ተከታታይ ቀናት በሰማይና በምድር ጦር ተሞክሯል። 8 ጊዜ ፊት ለፊት ውጊያ ተካሂዶበታል ፣ 1 ጊዜ በጤፍ ውሃ በስተግራ በኩል በሜካናይዝድ ክፍለ ጦር ፥ በመድፍና ቢኤም ፥ በሞርተርና በታንክ ፣ ....ወዘተ እሳት ዘንቦበታል ፤ ልዩ የኮማንዶ ጦር ገብቶ የሞት ሽረት ትንቅንቅ አድርጎበታል። ይሁን እንጂ የበላጎ ስትራቴጂክ ተራራዎችን ይዞ ለወራት እንደፍልፈል ምሽግ ሲቆፍር ፣ በኮንክሬት ሳይቀር ሲገነባ የነበረው የትግራይ ወራሪ ሀይል ከምሽጉ ንቅንቅ ሊል አልቻለም። ...ሠራዊቱ ደከመ ፣ ተስፋ አስቆራጭ ሆነበት ፣ በምን አይነት ስትራቴጂ የላጎን ምሽግ መስበር እንዳለበት የሀሳብ ድሪቶ ማባዘቱን ቀጥሏል። ወደፊት ሲገሰግሱ ''ተመለሱ!' የሚባለው የተለመደ የጦርነቱ ትራጄዲም እንደቀጠለ ነው። በዚህ መሀል እግር ተክለውና መሬት ሳይለቁ የሚዋጉት የምስራቅ አማራ ፋኖዎችም ህልቆ መሳፍርት መስዋዕትነት እየከፈሉ ከመንግስት ጦር ቀድመው መዋደቃቸውን እንደቀጠሉ ናቸው። ነገርግን ፋኖዎቹ የበላጎ ምሽግ አይደፈሬነትና የመንግስት ጦር በዚህ ስትራቴጂካዊ ቦታ ተስፋ እየቆረጠ መምጣት ብሎም የተቀዛቀዘው የማጥቃት ሁኔታ እንደእግር እሳት ፈጅቷቸዋል። ይህን ምሽግ መስበር የሞት ሽረት ጉዳይ መሆኑን አምነዋል። የሚከፈለውን መስዋዕትነት ለመክፈልም በሙሉ ልብ ቆርጠው ተነስተዋል። መስከረም 15/16/2015 ዓ.ም የምስራቅ አማራ ፋኖ በላጎን ለመያዝ በበስተቀኝ በኩል በጥጃውሃ አቦ ቆርጦ የመግባት ድፍረት የተሞላበት የጦር ስትራትራጂ በመንደፍ ቅልጥ ያለው ውጊያ ተጀመረ። በተደጋጋሚ ሙከራ ተስፋው የተሟጠጠው የመንግስት ሰራዊት ከበላጎ ይልቅ በሌሎች አቅጣጫዎች ላይ በማተኮሩ ለበላጎ የተሰጠው ትኩረት እምብዛም ነበር። ነበልባሎቹ ፣ ምሽግ ደርማሾቹ ፣ ወፍ አርጋፊዎቹ የምስራቅ አማራ ፋኖዎች 24 ሰአት የፈጀ የሞት ሽረት ትንቅንቅ አደረጉ። የጠላት ምሽግ ላይ ዘለው ገቡበት ፣ ለወራት የመሸገውን የጠላት ጦር ሙትና ቁስለኛ አድርገው ረመረሙት ፤ እልህ አስጨራሹ የበላጎ ምሽግ ከረዥም ወራት በኃላ በምስራቅ አማራ ፋኖዎች ቁጥጥር ስር ወደቀ። ለወራት ያልተደፈረው አደገኛ ምሽግ ተደረማመሰ ...! ይሁን እንጂ ተስፋ የቆረጠው የጠላት ጦር የተማረኩ የመከላከያ ሰራዊቶችን የደምብ ልብስ ለብሶ ከጀርባ በመምጣት አንጀቱን ባሳረሩት ፣ ለወራት የጨመደደውን ባስለቀቁት ፋኖዎች ላይ ጥቃት ሰነዘረ። በዚህ ጥቃትና በነበረው እልህ አስጨራሽ በጀብድ የተሞላ ትግል፣ የምስራቅ አማራ ፋኖ በጦርነት ታሪኩ ከባድ የሚባለውን መስዋትነት ከፈለ ፤ ጀግናው አሸናፊ አለሙን ጨምሮ በርካታ የምስራቅ አማራ ጀግኖች በበላጎ ምሽግ ላይ ወደቁ ...! ዋ! በላጎ...! ታዲያ በዚህ ውጊያ ከተሰውት ጀግኖች መካከል አሁን በስም የማልጠቅሰው ጀግና የፍም እሳት ወንድማችን ፣ መስከረም 15 እናቱን ደውሎ ካናገራት በኃላ ያቺ ድምፁ የመጨረሻው ሆነች። እናት ''ልጄ ሞቶም እንደሆነ ፣ በህይወትም ካለ እባካችሁ ቁርጤን ልወቅ !'' የጧት ማታ ለቅሶና እዬዬዋ ሆነ። ከማውቃቸው ሰዎች ጋር እየሄደች በተደጋጋሚ ስታፈላልግና ስትጠይቅ በቅርበት አውቃለሁ..... እውነታውን ግን ልቤ ያውቃል ...! የምስራቅ አማራ ፋኖ ያንን ሁሉ ተነግሮ የማያልቅ ጀብድ ፈፅሞ ''ጦርነቱ የስልጣን ግብግብነት መሆኑን በሚያሳብቅ መልኩ በፖለቲከኞቹ መተቃቀፍ '' ማብቃቱ ከተበሰረ በኃላ ፣ የሰማዕት ጀግኖቹን መርዶ ለቤተሰብ የማርዳት ፣ የቆሰሉትን የማሳከም ብሎም የጠፉትን የማፈላለግ ስራ ጀምሮ እየተንቀሳቀሰ ባለበት ሁኔታ ፣ ከጎኑ መስዋዕትነት የከፈለለት ኃይል ''በምስጋናና በሽልማት'' ፋንታ ዙሮ ሊያጠቃው ጠብመንጃ አዙሮ ከበሩ ድረስ መጣ። መርዶ የማርዳቱ ተግባር ፣ ከዚች በር በር እያየች ቁርጧን ከምትጠብቅ እናት ጋር ሳይደርስ ፣ የምስራቅ አማራ ፋኖ ዳግም በነፍሱ ከደረሰለት ሀይል ጋር ፣ የክህደት ጦርነትና ሰዶ ማሳደድ ውስጥ ገባ....! ይቺ የጀግና እናትም መርዶዋን ሳትሰማ ዛሬም እንባዋ ከጉንጯ ሳይደርቅ ፣ ''በር በር ....!'' እያየች ልጇን በመጠበቅ ላይ ትገኛለች። ልጇ ጀግናና የሚያኮራ ታሪክ የፃፈ ሰማእት ቢሆንም ፣ በተለይ ለወላድ አንጀት ከባድ መሆኑ ግልፅ ነው። ግና ምን ልቤ በሀዘን ቢደማ ፣ ምን ብዬ ልንገራት ? ምንም! ነገ ታሪክ ተቀይሮ ከጀግኖቹ ጋር በጀግና ስነ-ስርአት እርሟን እንደምታወጣ ተስፋ አደርጋለሁ! በፋኖ ላይ ለሆነው ሁሉ ይህ አንዱ ልብን የሚያደማ ጉልህ ማሳያ ነው! አዎ! የክህደት ጥግ .....! አብሯቸው ድንጋይ የተንተራሰው ፣ የደማው የቆሰለው ፣ የተራበው የተጠማውን የምስራቅ አማራ ፋኖ ዙረው እንደጠላት በክህደት ሊወጉት በሩ ድረስ ሲመጡ ፣ የሰማእቶቹን መርዶ እንኳ በቅጡ አርድቶ ሳይጨርስ ነበር ...! ክህደት‼️ ክህደት‼️ ክህደት‼️ ከ #ዘሪሁን_ገሠሠ ገፅ የተወሰደ

ከድርጅት አባልነት እንድንሰናበት ስለመጠየቅ! ከላይ በርዕሱ ለመግለፅ እንደተሞከረው እኛ የፍኖተ ሰላም ከ/አስ/ከ/መ/ልጽ/ቤት በተለያየ የሙያ ዘርፍ ህዝብን እያገለገልነ የምንገኝ ከዚህ በፊት በአንድ
ከድርጅት አባልነት እንድንሰናበት ስለመጠየቅ! ከላይ በርዕሱ ለመግለፅ እንደተሞከረው እኛ የፍኖተ ሰላም ከ/አስ/ከ/መ/ልጽ/ቤት በተለያየ የሙያ ዘርፍ ህዝብን እያገለገልነ የምንገኝ ከዚህ በፊት በአንድም ይሁን በሌላ መንገድ የብልጽግና ፓርቲ አባል ሆነን የቆየን መሆነ ይታወቃል፡፡ ይሁን እንጅ እየተባባሰ የመጣውን የኑሮ ውድነት ከሚከፈለን ደመዎዝ አንፃር መቋቋም ስላልቻልነ ከድርጅት አባልነት በራሳችን ፍላጎት የለቀቅነ መሆኑን እያሳወቅነ ለአባልነት ክፍያ ከደሞዛችን የሚቆረጠው ብር ከሐምሌ 1/2015 ዓ/ም ጀምሮ እንዳይቆረጥብን እያልነ ይህ ሳይሆን ቢቀር በህግ አግባብ በፍ/ቤት የምንክስ መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን፡፡

ዘመን የማይለውጠው ጠላትነት!! ትናንት ለወያኔ አድሮ የአማራ ልጆች ከሠራዊቱ ሲገፉና ሲሳደዱ እሱ በከፍተኛ ታማኝነት የማዕረግ እድገት እና ጥቅም ፊት ተሰላፊ ነበር። ዛሬም ለኦነጋዊው ፋሽስት በማደር
ዘመን የማይለውጠው ጠላትነት!! ትናንት ለወያኔ አድሮ የአማራ ልጆች ከሠራዊቱ ሲገፉና ሲሳደዱ እሱ በከፍተኛ ታማኝነት የማዕረግ እድገት እና ጥቅም ፊት ተሰላፊ ነበር። ዛሬም ለኦነጋዊው ፋሽስት በማደር የአማራ ልጆችን የመጨፍጨፍ ፊት መሪ ሆኖ አማራ ላይ ጦር እየመራ ነው። ትናንት ያስደርግ እንደነበረው ዛሬም ጦርነቱን የሚቃወሙ የአማራ ጀነራሎችን እና ወታደራዊ መኮንኖችን በቁም እሥር እና ክትትል እንዲሸማቀቁ እየሠራ ይገኛል። ነገ ደግሞ እንደወትሮው  በፍረጃ ከሠራዊቱ የሚባረሩና የሚቀነሱ የአማራ መኮንንኖችን ገምጋሚና አባራሪ ሆኖ ይቀመጣል። በነገራችን ላይ በርካታ አማራዎች ጀነራል አበባውን ስም አጥፈታችኋል ተብለው ፍርድቤትና እሥርቤት የሚሠቃዩ አሉ። ሆኖም ፥ ትናንት አንተን ጨምሮ ነፃ አውጥቶህ በስሪትህ ወደባርነት ብትመለስም የአማራ ልጆች የሚከፍሉትን ከፍለው ለድል ሲበቁ ደግመህ ነፃ መውጣትህ አይቀርም። ምክንያቱም የአማራ ድል አይቀሬ ነው። የትናንት ጌቶችህ የሉም። የዛሬ ጌቶችህም አይኖሩም። ድል ለአማራ !! #AmharaStruggle #Justice4Amhara #AmharaGenocide

ለወራት በእስር ሲንገላታ የነበረው ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ አስፋው ከአቅም በላይ በሆነ ችግር አገር ጥሎ መሰደዱ ተነገረ! ለወራት ከቆየበት እስር በዋስ የተለቀቀው ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ አስፋው ከአቅም በላይ በ
ለወራት በእስር ሲንገላታ የነበረው ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ አስፋው ከአቅም በላይ በሆነ ችግር አገር ጥሎ መሰደዱ ተነገረ!     ለወራት ከቆየበት እስር በዋስ የተለቀቀው ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ አስፋው ከአቅም በላይ በሆነ ችግር ከአገር መውጣቱ ተሰምቷል። ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ በአገር ውስጥ በጋዜጠኝነት ሙያው ለመስራት ከአቅም በላይ ስለሆነበት ከአገር መውጣቱን ነው ቤተሰቦቹ የገለጹት፡፡ በተጨማሪም በድህንነቶች ክትትል ይደረግበት እንደነበር ተገልጿል። በያዝነው አመት በወራት ውስጥ ሁለት ጊዜ ለእስር የተዳረገው ቴዎድሮስ ኢትዮ ሰላም የሚል የዩቲዩብ ሚዲያ በመክፈት ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና አጠቃላይ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ትንታኔ በመስጠት ይታወቃል፡፡ ©ሮሃ ቲቪ

የአማራ ወኪሎችን የማሸማቀቅ መንግስታዊ ድራማ!! የጥላቻ ንግግርና ስም ማጥፋት ዘመቻ በመንግስታዊ መዋቅር በአዲስ አበባ ምክር ቤት አባል በዶ/ር ካሳ ተሻገር ላይ ነው። ዶክተር ካሳ ተሻገር በማንነት
+1
የአማራ ወኪሎችን የማሸማቀቅ መንግስታዊ ድራማ!! የጥላቻ ንግግርና ስም ማጥፋት ዘመቻ በመንግስታዊ መዋቅር በአዲስ አበባ ምክር ቤት አባል በዶ/ር ካሳ ተሻገር ላይ ነው። ዶክተር ካሳ ተሻገር በማንነት አማራ በመሆናቸው በአዲስ አበባና ኦሮሚያ እሰር ቤቶች ስለሚሰቃዩ ንፁሃን አማሮች ጥያቄ ማንሳታቸውን ተከትሎ የተደረገ የጥላቻ ዘመቻ ነው። ኢትዮጵያ ላይ የጥላቻ ትርክት ማሽን ራሱ ፓርቲው እና የብልጽግና ካድሬዎች ናቸው። ከዚህ በታች በምስል የቀረበው የጥላቻ ፕሮፖጋንዳ ዘመቻ ከከተማ እስከ ቀበሌ እንዲደረግ ትዕዛዝ የሰጡት የአዲስ አበባ ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ሜኤሶ ናቸው። ብልፅግና ማለት ከዲሞክራሲ የተጣላ፡ በዚህ ደረጃ የራሱን ወኪል ሀሳብ ለማፈን የሚሠራ የአምባገነን ዘረኞች መነሓሪያ ነው።

“ እኔ ምንም መወሰን አልችልም:: እነሱ ( ኦህዴድ) የፈቀዱልኝን ብቻ ነው የምሰራው ምንም ነገር ማድረግ አልችልም:: እንደውም ክትትል ይደረግብኛል:: እነሱ አድርጊ ያሉኝን ካላደረኩ ችግር ውስጥ ነ
“ እኔ ምንም መወሰን  አልችልም:: እነሱ ( ኦህዴድ) የፈቀዱልኝን ብቻ ነው የምሰራው ምንም ነገር ማድረግ  አልችልም:: እንደውም ክትትል ይደረግብኛል::  እነሱ አድርጊ ያሉኝን ካላደረኩ ችግር ውስጥ ነው ያልሁት:: ከዚህ term በኃላ መስራት አልፈልግም:: ወደ  አሜሪካ ልጆቼ ጋር ሄጀ እኖራለሁ:: ከ UN የሚከፈለኝ በቂ ጡረታ አለኝ አንድ ስድስት ሽህ ዶላር በወር ይከፈለኛል እሱ ይበቃኛል ጭንቅ ውስጥ ነው ያለሁት..." ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ (ይሄን ጨዋታ ያጋሩት የቅርብ ሰው ለ ኢትዮ 360 ያጋራው መረጃ ነው:: ) #MinilikSalsawi

ትናንት ከወያኔ ጋር ተዋግቶ ደሙን አፍሶ የወያኔ ወረራን የቀለበሰው እና የአምባገነኑን አገዛዝ እድሜ ያረዘመው የአማራ ሚሊሻና ፖሊስ፣ ዛሬም የፋሽስቱን አገዛዝ እድሜ ለማራዘም ከራሱ ወንድሞች ጋር ይዋጋል ብሎ መጠበቅ እብደት ነው። (አንዳንዶች በማወቅም ይሁን ባለማወቅ እየተሳተፉ መሆኑ ቢታወቅም) አገዛዙ በስህተት እያዋጋቸው መሆኑን የተረዱ ቀን ያስታጠቃቸው መሳሪያ እና ጥይት ወደ እሱ ማዞራቸው አይቀርም። ከዚህ ውጭ ያለውን የጥፋት መንገድ እከተላለሁ የሚል ሚሊሻና ፖሊስ ስልጠና ሳይሆን አማኑኤል መላክ የነበረበት ነው። አገዛዙን ተማምኜ እገጥማለሁ የሚል ካለ የፋኖን በትር ይቀምሳል። አሁን ባለው በብዙው የአማራ አካባቢ ግን ሚኒሻው እና ፖሊሱ ይሄንን አልቀበልም ብሏል። ድል ለአማራ ሕዝብ!! #AmharaStruggle #Justice4Amhara #AmharaGenocide

አዲስአበባ ኡራኤል አካባቢ ነው ። ከዚህ ቀደም በለሚኩራ ተመሳሳይ ለፍቶ አዳሪ አማራዎችን በማሳደድ አስወጥተዋቸዋል። ከከተማው አማራን ለማስወጣት የሚደረገው መልከብዙ የዘር ማፅዳት አካል ነው። የሰፊ
አዲስአበባ ኡራኤል አካባቢ ነው ። ከዚህ ቀደም በለሚኩራ ተመሳሳይ ለፍቶ አዳሪ አማራዎችን በማሳደድ አስወጥተዋቸዋል። ከከተማው አማራን ለማስወጣት የሚደረገው መልከብዙ የዘር ማፅዳት አካል ነው። የሰፊው የኢኮኖሚ ጄኖሳይድ ሴራ አካል ነው። ሆኖም በጋሪ የሚሸጡትን ሙዝና ቲምቲም በሚደፉ ደንብ አስከባሪዎች ላይ ነጋዴዎቹ እርምጃ መውሰድ ጀምረዋል ። አንዱ የሥርዓቱ አገልጋይ መሬት ይዟል። ድል ለአማራ !! #AmharaStruggle #Justice4Amhara #AmharaGenocide