en
Feedback
Ethio monitor

Ethio monitor

Open in Telegram
1 482
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ከ42 ቀናት እስር በኋላ በ10,000 ብር ዋስትና ተፈትቷል። እንኳን ለቤት አበቃህ ጓድ !!
ከ42 ቀናት እስር በኋላ በ10,000 ብር ዋስትና ተፈትቷል። እንኳን ለቤት አበቃህ ጓድ !!

በሸዋሮቢትና በአካባቢው የሚገኘውን የፋኖ ሀይል ለመደምሰስ አመሻሹን ፋሽስታዊው አገዛዝ ሰራዊት ጥቃት ከፍቷል። በአማራ ፋኖ የሸዋ ብርጌድ እየተመከተና አስፈላጊው እርምጃ እየተወሰደበት ይገኛል። በሸዋ
+1
በሸዋሮቢትና በአካባቢው የሚገኘውን የፋኖ ሀይል ለመደምሰስ አመሻሹን ፋሽስታዊው አገዛዝ ሰራዊት ጥቃት ከፍቷል። በአማራ ፋኖ የሸዋ ብርጌድ እየተመከተና አስፈላጊው እርምጃ እየተወሰደበት ይገኛል።  በሸዋ ሮቢትና አካባቢው የሚገኙ አማራዎች ሁሉ ፋሽስታዊውን ሀይል በሚችሉት ሁሉ እንዲያጠቁና ስምሪቱን እንዲያስተጓጉሉ ጥሪ ቀርቧል። እስካሁን 3  የፋሽስቱ ሀይል ተሽከርካሪዎች ጋይተዋል። ድል ለአማራ !! #AmharaStruggle #Justice4Amhara #AmharaGenocide

ትናንት ከወያኔ ጋር  ተዋግቶ ደሙን አፍሶ  የአምባገነኑን አገዛዝ እድሜ ያረዘመው የአማራ ሚሊሻና ፖሊስ፣ ዛሬም የፋሽስቱን አገዛዝ እድሜ ለማራዘም ከራሱ ወንድሞች ጋር ይዋጋል ብሎ መጠበቅ እብደት ነው። እንደዚህ የሚያስብ ሚሊሻና ፖሊስ ስልጠና ሳይሆን አማኑኤል መላክ አለበት። ድል ለአማራ !! #AmharaStruggle #Justice4Amhara #AmharaGenocide

ደራሲና ፀሃፊ አሳዬ ደርቤ በ10ሺ ብር ዋስ ከእስር ተፈቷል። ከመኖሪያ ቤቱ በፀጥታ ሃይሎች ተይዞ የታሰረው ደራሲና ፀሃፊ አሳዬ ደርቤ በዋስትና ጉዳይ ክርክር ለማድረግ ትናንት ሐምሌ 10 ቀን 2015
ደራሲና ፀሃፊ አሳዬ ደርቤ በ10ሺ ብር ዋስ ከእስር ተፈቷል። ከመኖሪያ ቤቱ በፀጥታ ሃይሎች ተይዞ የታሰረው ደራሲና ፀሃፊ አሳዬ ደርቤ  በዋስትና ጉዳይ ክርክር ለማድረግ ትናንት ሐምሌ 10 ቀን 2015 ዓ/ም የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርቦ ነበር። ፍርድ ቤቱም አቃቢ ህግ በአሳዬ ላይ ያቀረበውን  ክስ ከመረመረ በኋላ  የተከሳሽ ጠበቆች ያቀረቡትን የዋስትና  ጥያቄ በማዳመጥ ተከሳሹ በ10,000 ብር ዋስትና እንዲለቀቅ ብይን ሰጥቷል። አሳየ የዋስትና መብቱ ተከብሮለት በአሁን ሰአት ከእስር ተፈቶ ወደ ቤቱ ገብቷል ሲል አሻራ ዘግቧል።

አመለ ሸጋው ስራ ወዳዱ አንድ ፋኖ ጎንደር ማክሰኝት በዛሬው ዕለት ሐምሌ 11 ቀን 2015 ዓ.ም በአደባባይ በስርዓቱ ጦር ታፍኖ የነበረ ቢሆንም ጀግኖች ፋኖዎች ተናበው የአብይን ወታደር፣ አድማ ብተና
+2
አመለ ሸጋው ስራ ወዳዱ አንድ ፋኖ ጎንደር ማክሰኝት በዛሬው ዕለት ሐምሌ 11 ቀን 2015 ዓ.ም በአደባባይ በስርዓቱ ጦር ታፍኖ የነበረ ቢሆንም ጀግኖች ፋኖዎች ተናበው የአብይን ወታደር፣ አድማ ብተና እና ሚኒሻ ጥሰው በመግባት ከበባውን ሰብረው ሊያስወጡት ችለዋል። የኦህዴድን የበላይነት እና የብአዴንን ወንበር ለማፅናት እና በደምና በአጥንት የተመለሱትን ወልቃይትና ራያን ለወያኔ ለመስጠት በቆረጡ በህዝብ ጠላቶች አማካኝነት ለማንነታቸው፣ ለርስታቸው እና ለህልውናቸው ዋጋ የከፈሉ ጀግኖችን አፍኖ እንዲወስድ እንዲገድል አንፈቅድም። ሲያፍኑ አፈና ምን ያህል እንደሆነ አፋኝን የአፋኝን ቤተሰብ ማፈን፣ ሲገድሉ መግደል የወቅቱ የትግላችን መንገድ ነው። ማንም አፋኝ ማንም ታፋኝ፤ ማንም ገዳይ ማንም ተገዳይ መኖር የለበትም። የትግል ግባችን ለጊዜው የታፈኑትን ማስለቀቅ ብቻ ሳይሆን ዋና ግባችን ለመሠረታዊ ለውጥ ሲሆን በተደረገው ጥሪ ፈጥናችሁ ደርሳችሁ ከአፈና ያዳናችሁ እና በሚዲያ ሰፊ እርብርብ ያደረጋችሁ በሙሉ አንድነታችን ተጠናክሮ እንዲቀጥል በርትተን መሥራታችን እንቀጥል። ድል ለአማራ ፋኖ!! ድል ለአማራ ሕዝብ! /የፈራ ይመለስ/

ለእርስ በርስ ጦርነት 53 ሚሊዬን ብር? በአማራ ክልል ለሚሊሻና መደበኛ ፖሊስ ሊሰጥ የነበረው ስልጠና የተወሰኑ የሚሊሻ አባላት ስልጠናውን ለመውሰድ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው መራዘሙ ተጠቆመ በአማራ ክልል ለሚሊሻና ለፖሊስ ሠላም አስከባሪ ኃይል እንዲሁም ለመደበኛ ፖሊስ ኃይል ከትናንት ሐምሌ 10/2015 ጀምሮ ለሰባት ተከታታይ ቀናት ሊሰጥ የነበረው ስልጠና፤ የተወሰኑ የሚሊሻ አባላት ስልጠናውን ለመውሰድ ፈቅደኛ አለመሆናቸውን ተከትሎ ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙን አዲስ ማለዳ ሰምታለች፡፡ ስልጠናው በክልሉ 18 ዞኖች ለሚገኙ የሚሊሻና የፖሊስ ሰላም አስከባሪ አባላት እንዲሁም ለመደበኛ ፖሊስ ኃይል ለመስጠት ታቅዶ የነበረ ቢሆንም፤ "ስለስልጠናው በቂ መረጃ ሳይሰጠን አንሰለጥንም" ያሉ የሚሊሻ አባላት በመኖራቸው እንዲራዘም መደረጉን መረዳት ተችሏል። የክልሉ መንግሥት የስልጠናው ዋነኛ ዓላማ በክልሉ በየጊዜው የሚፈጠሩ የጸጥታ ችግሮችን ለመፍታት ነው መሆኑን ቢገልጽም፤ "ችግር የሚፈጥረው አካል ማነው ለሚለው ጥያቄ፤  ቅድሚያ ማብራሪያ ሊሰጠን ይገባል" በማለት ስልጠናውን ለመውሰድ ፈቃደኛ ያልሆኑ የሚሊሻ አባላት መኖራቸው ተጠቁሟል፡፡ የስልጠናው ዓላማ የመንግሥት የጸጥታ አካላቱ ከፋኖ አባላት ጋር እንዲዋጉ ታስቦ ከሆነ፤ ሃሳቡን የማይቀበሉ የሚሊሻ አባላት ሊኖሩ እንደሚችሉ ተመላክቷል። በዚህም በስልጠናው ወቅት ችግር ሊፈጠር እንደሚችል አመላካች ነገር በመገኘቱ ስልጠናው እንዲራዘም መደረጉን ነው አዲስ ማለዳ ከሚሊሻ አባላትና ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት መረዳት የቻለችው።  በሌላ በኩል ሥማቸውን እንዲጠቀስ ያልፈለጉ በክልሉ የሚገኙ አንድ የመንግሥት የሥራ ኃላፊ፤ ሥልጠናው የተራዘመው ለሥልጠናው የሚረዱ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በጊዜ ባለመጠናቀቃቸው መሆኑን ለአዲስ ማለዳ ጠቁመዋል። ስልጠናው የሚሰጠው ለ40 ሺሕ 486 ሰልጣኞች መሆኑን ጠቁመው፤ "ለሰልጣኞች ምግብ እና የማረፊያ ቦታ ባለመመቻቸቱ ነው እንዲራዘም የተደረገው።" ብለዋል፡፡ ለስልጠና የሚያስፈልጉ ቅድመ ዝግጅቶች እየተጠናቀቁ በመሆኑም አንድ ሳምንት በማይበልጥ ጊዜ ውስጥ ስልጠናው እንደሚሰጥ ጠቅሰዋል። ከትናንት ሰኞ ሐምሌ 10/2015 እስከ እሁድ ሐምሌ 17/2015 ለተከታታይ ሰባት ቀናት ሊሰጥ ታስቦ ለነበረው የጸጥታ አካላት ስልጠና፤ የክልሉ ሚሊሻ ጽህፈት ቤት ከ53 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት ጠይቋል። ስልጠናው የጸጥታ ኃይሉን በክልሉ በየጊዜው ለሚፈጠሩ የጸጥታ ችግሮች ምላሽ ለመስጠት በሚያስችል መንገድ ለማጠናከር ያስችል ዘንድ እንዲሁም በወታደራዊ ስነምግባር፣ እውቀትና ክህሎት ለማብቃትና በስነልቦና ለማዘጋጀት ታስቦ የተዘጋጀ ነው ተብሏል። /አዲስ ማለዳ/

አይረሳም‼ "ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ የአማራ ብሔር ተወላጆችን በየካምፑ ከሠራዊቱ በከዱ የትግራይ ተወላጆች አማካኝነት አሰቃቂ አገዳደል ገድለዋል"   ገፅ- 107 ⁽⁽የአማራ ተወላጅ የሠራዊት አባላት እየተመረጡ ዘግናኝ በሆነ ሁኔታ ተጨፍጭፈዋል"  ገፅ -108 "የገረመን የአማራ ተወላጆችን ከየካምፑ እየለቀሙ አርደው ገድለው፣ በድንጋይ ቀጥቅጠው ገድለው በአስከሬኑ ፎቶ ሲነሱ፣ አስከሬኑን ሽንት ቤት ሲከቱ፣ አስከሬኑን እጅና እግሩን አስረው እራቁቱን አስፓልት ላይ ጥለው፣ በመጥረቢያ ፈልጠው ገድለው አስከሬኑን በመኪና ጨፍልቀው፣ የሴት ጓዲቶችን ጡት በጭካኔ ቆርጠው ዛፍ ላይ አንጠልጥለው፣ መንገድ ላይ አውጥተው በሲኖትራክ ጨፍልቀው፣ የአማራን ልጆች እየጨፈጨፉና ደመ ከልብ እያደረጉ በምን ሞራላቸው ነው የአማራ ህዝብ ከትግራይ ህዝብ ጎን ይቁም የሚል ጥሪ የሚያስተላልፉ?? በምን ዓይነት ህሊናቸው ነው ልጁን እየገደሉ አባትዮውን ደግፈኝ እያሉ የሚጋብዙት? በሠራዊቱ ላይ ያደረሱት ከበደል የከፋ በደል አይሰማም መስሏቸው ነውን? ከግፍ የበዛ ግፋቸውን በሚስጢር ነው ያደረግነው ብለው አስበው ይሆን? " የተካደው ሰሜን ዕዝ ፡ 50 አለቃ ጋሻዬ ጤናው (2014)

ነው። ጎንደር የታገተ እስራኤላዊ የለም!! አንድ ቤተ እስራኤላዊ የኾኑ የእስራኤል ዜጋ ባለፈው ሳምንት አማራ ክልል ጎንደር አካባቢ በታጣቂዎች ስለመታገታቸው የተሠራጨው መረጃ ሐሰት መኾኑን የእስራኤል ጋዜጦች ዘግበዋል። የእስራኤል ባለሥልጣናት ከኢትዮጵያ ጸጥታ ኃይሎች ጋር በመተባበር ታግቻለኹ ያሉትን ፍራንሲስ አደባባይ የተባሉ እስራኤላዊ ለማፈላለግ የጀመሩትን ጥረት ማቋረጣቸውንም ዘገባዎቹ አመልክተዋል። የ79 ዓመቱ እስራኤላዊ የሐሰት እገታ መረጃውን ያሠራጩት፣ ለእገታ ማስለቀቂያ ሊከፈል የሚችለውን ገንዘብ ለግል ጥቅማቸው ለማዋል መኾኑን የእስራኤል ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር እንዳመነበት ዘገባዎቹ ጨምረው ጠቅሰዋል። "አጋቾች" ለታጋቹ ማስለቀቂያ 45 ሺህ ዶላር ገደማ ጠይቀዋል ተብሎ ተዘግቦ ነበር።

አማራ ላይ የሚካሔድ ጦርነት ለመከላከያ አባላት ምን ትርጉም ይሰጥ ይሆን⁉ 1) በ2 አመት ጦርነት ዋጋ የከፈለ ሕዝብ ነው። ያለውን ሳይሆን የሌለውንና የማይደግመውን የሰጠ ነው። ስንቅ ጭኖ ያቀረበ ፣ ደም እየለገሰ በራሱ የጤና ተቋማት ያከመ፣ በመደበኛ ኃይል አልቻንም ክተት ተብሎ የዘመተና የሞተ ሕዝብ፣ በጦርነቱ ሀብቱንና ነፍሱን ብቻ ሳይሆን ሕይወቱን ሰጥቶ ከመከላከያ ጎን የተሠለፈ ሕዝብ ነው። ፋኖውና ልዩ ኃይሉ የፈፀመው ጀብዱና ተሳትፎ መስካሪው መከላከያ ነው። ብርሃኑ ጁላ ሳይሆን አውደ-ውጊያ የነበሩ ያውቁታል። 2) ይሔንን ሁሉ ላደረገው ሕዝብና ዘማች፤      = በመንግስታዊ ፖለቲካ ውድቀት ለጥቃት የዳረጉትን በመካስ ፈንታ፥     =  የወደመበትን በመጠገን ፋንታ፥     = የሟችን ቤተሰብ በማፅናናት ፈንታ ፥     = በምርት ላይ የተፈጠረን ክፍተት በማካካስ ፈንታ፥     = ሥራና ትምህርት ያቋረጠውን ታጣቂ ወደሥራና ትምህርት በመመለስ ፈንታ፥     ፧     ፧ እንዴት ወረራ ይከፈትበታል!? እንዴት ታንክ ይነዳበታል!? ለምን ጥይት ይጮህበታል!? ለምን ተመልሰህ ከወንድሞችህ ተዋጋ ይባላል!? ከራሱ ነፍጎ መከላከያ ያጎረሰ ሕዝብ ፣ አብሮ ተሰልፎ ከጠላት ጋር የተዋደቀና የተዋጋ ፋኖና ልዩ ኃይል ለምን አዲስ ጦርነት ይታወጅበታል!? ድንቁርና ለወረረው የብዐዴን ደደብ አመራር ይቅርና ለሚሊሻው ለአርሶአደሩ ለፖሊስ አባላት ይሔ ምን ትርጉም ይሰጣችኋል⁉ ይሔ ለአገሪቱ መከላከያ ሠራዊት አባላት የሚሰጠው ስሜት ምንድን ነው ⁉ ፍትሕ ከአማራ ጋር ነችና ድል አይቀርም!! ድል ለአማራ !! #AmharaStruggle #Justice4Amhara #AmharaGenocide

የሻለቃ ምሬ ወዳጆ ጥሪ!! የሻለቃ ምሬ ወዳጆን ንግግር ሰምታችሁት ይሆን? ስሙት! እኔ ደጋግሜ ሰማሁት። በበኩሌ ከምንም በላይ ትግላችን በተግባር የተፈተኑ እንደ እነ ምሬ ያሉ መሪዎችን እየወለደ በመ
የሻለቃ ምሬ ወዳጆ ጥሪ!! የሻለቃ ምሬ ወዳጆን ንግግር ሰምታችሁት ይሆን? ስሙት! እኔ ደጋግሜ ሰማሁት። በበኩሌ ከምንም በላይ ትግላችን በተግባር የተፈተኑ እንደ እነ ምሬ ያሉ መሪዎችን እየወለደ በመሆኑ በጣም ደስተኛ ነኝ። ምሬ ለሁላችንም ጥሪ አቅርቧል። ታጥቆ ጫካ የገባውም ሆነ በየቤቱ አድፍጦ የተቀመጠው ሁሉ ትግሉን እንዲቀላቀል ጥሪ ቀርቦለታል። ቆቦ የሚተኮሰው መድፍ ሁላችንንም እንደአማራ ኢላማ ያደረገ ነው፤ ወረፋ መጠበቅ ይቁም! ምሬ አንዱ ጥሪ ያቀረበላቸው አካላት ሚሊሺያና ፖሊሶች ናቸው፤ ከኦሮሙማው የፋሽስት ቡድን ጎን ከሞቆም እንዲቆጠቡ እና ትግሉን እንዲቀላቀሉ ካልሆነ ግን ....... የሚል የወንድምነት ጥሪ አቅርቦላቸዋል። እኔም ዛሬ ሰንበትን እነዚህን አካላት ለማንቃት ብንጠቀምበት የሚል ሃሳብ መጣልኝ። * ሁላችንም ፖሊስና ሚሊሺያ ዘመድ ወይም ጎረቢቶቻችንን ዝርዝር እናውጣ * በስልካቸው እየደወልን ሁኔታውን እናስረዳቸው / በአካልም ከተቻለ * ስልክ የሌላቸው ካሉ በጎረቤት ወይም በቤተሰባቸው እንድረሳቸው * ይህ ጦርነት እነሱ ከገቡበት የእርስ በርስ ጦርነት እንደሚሆን እና እነሱን መልሶ እንደሚበላቸው፣ ልጆቻቸው ያለ አሳዳጊ እንደሚቀሩ፣ እንደ አማራ ነገ እነሱም እንደማይቀርላቸው ለማሳመን ጥረት እናድርግ ቻሌንጁን ተቀላቀሉ /ምስጋናው ዘ ግዮን/

የጀነራል አበባው ታደሰ የግል ሀብቶች‼ ▪ከ5500 ካሬ በላይ ጎርጎራ ላይ ለሎጅ በሚል ቦታ ወስዶ ክስ ተመስርቶበታል። ▪በጦርነቱ ሰሞን #ኮምቦልቻ ከተማ ባለ ኮከብ ሆቴል ለመገንባት ከ1000 ካሬ በ
+2
የጀነራል አበባው ታደሰ የግል ሀብቶች‼ ▪ከ5500 ካሬ በላይ ጎርጎራ ላይ ለሎጅ በሚል ቦታ ወስዶ ክስ ተመስርቶበታል።  ▪በጦርነቱ ሰሞን #ኮምቦልቻ ከተማ ባለ ኮከብ ሆቴል ለመገንባት ከ1000 ካሬ በላይ ቦታ ወስዷል። ▪ሰሞኑን ባህርዳር የሚገኘውን የሜድሮክ ኢትዮጵያ (አላሙህዲን) ሀብት በስሙ አዛውሯል። ▪ዱባዩ ላይ በወር 1.9 ሚሊዮን ብር ማስገባት የሚችል እኔነኝ ያለ ድርጅት አለው።  ▪ሰሜን ሸዋ ቱለፋ ከተማ ላይ 10 ካ.ሜ ቦታ ላይ ነዳጅ ማደያ አለው። ▪ባህርዳር ከተማ ላይ እጅግ ቅንጡ ሆቴል አለው። (አልዋቅ ሆቴሌ) ይኽን ጉድ እያየህ፤ አንተ ከአንድ ክላሽ መሳሪያ ውጭ ምንም የሌለህ እግረኛ ወጥቶአድር ሆይ! ለምን ብለህ ነው፤ ወገንህ ላይ ጥይት እየተኮስህ አጎል ሞት የምትሞተው? 🤔 By Devis Wondimu ድል ለአማራ !! #AmharaStruggle #Justice4Amhara #AmharaGenocide

ብዐዴን - የአማራ እርግማን !! 1) ቀደም ያለውን የሩብ ክፍለዘመን ሚናውን፣ ለውጡ ሲመጣ ያለውን፣ የሕዝቡን ትግል የት አደረሰው የሚለውን እርግማኑን እናቆየው፤ 2) ትናንት ለውጡን ለባለጊዜ ሸጦ፣ ለታሳቢ ጦርነት ሳይዘጋጅ ሕዝቡን ለአዋራጅ ወረራና ጦርነት ዳረገው፤ ለማምለጥና ለመውጣት ሲያደባ የነበረው እድፍ ሳይጠየቅ ፡ ሳይጠረግ፡ በተላላኪ ወራዳ ስብዕና ቀጠሉ!! 3) በጦርነት የደቀቀው ሕዝብ ካሳው ዝምታ ሲሆን ፣ ገንዘቡን ለጦርነት መድቦ ወገኑን የታደገው ባለሀብት በሥራ ድጋፍ ፋንታ በጠላት ውንጀላዎች ሲሳደድ፣ ትናንት ነፍሱን አሲይዞ የተዋደቀው ወጣት ጠላት ሲደረግ፣ ትናንት በነፍስ ወከፍ ጠበንጃ ይዞ የተዋደቀው አርሶአደር ማዳበሪያ ሲከለከል፣ .... ብዐዴናዊው የእርግማን ስብስብ ፊትለፊት ተቀምጦ ይላላካል!! 4) ያኔ በጦርነት ወቅት ያልደረሱለትን ሕዝብ ያለውን ይዞ ወጥቶ ፣ ራሱ ሰልጣኝ ፣ ራሱ ታጣቂ ፣ ራሱ ስንቅ፣ ራሱ  ተከላካይ ሆኖ ጦርነቱን የተወጣውን ሕዝብና ወጣት መልሶ፥ ሳያላምጥ በዋጠው የጠላት አጀንዳ ተወስዶ በጅምላ እያሳደደ ማሰር ውስጥ ገባ። ይባሱኑ ትናንት ሕዝቡንም እሱንም ከወረራ የታደጋቸውን ልዩ ኃይልና ፋኖ በቴሌቪዥን መስኮት ወንጅለው እናጠፋሃለን ብለው ዝተው በተኑት። በሀሰት ክስ ሲያብጠለጥሉት የነበሩት ጠላቶች ጦር አዝምተው ሲጨፈጭፉት የአማራው እርግማን ከፊት ተሰልፎ አስፈፃሚ ሆነ !! 4) ዛሬ ሕዝብ የሞተለትን ወጣት ማጥቃት በቃ ሲል ፤  በውዳቂ ስብዕናው ተለይቶ የተመለመለው የብዐዴን እርግማን ፥ ማዳበሪያ የጠየቀውን አርሶአደር  ሰልጥነህ ዘምተህ ወገንህን ውጋ ፣ ትናንት ከወረራ የታደገህን ወጣት ተዋጋ ብሎ ስልጠና አዘጋጅቷል። ይሔ ከውዳቂ የመላላክ ታሪክ ተሰባስቦ የቆመ "የፖለቲካ ጎሳ" እንዲወገድ ካልሆነ፡ የጠላት መሣሪያ፡ የአማራው እርግማን ሆኖ ይቀጥላል !! ሞት ለጠላት-ብዐዴን እና ጋላቢዎቹ ጠላቶቻችን !! ድል ለአማራ ሕዝብ!! #AmharaStruggle #Justice4Amhara #AmharaGenocide

«አልሞት ባይ ተጋዳይ፣ የሞት የሽረት ትግል ነው እያደረግን ያለነው አሁን።» -ፋኖ አበበ ፈንታው_የምስራቅ አማራ ፋኖ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ የኦህዴድ ብልጽግና አገዛዝ በሰሜን ወሎ ራያ ቆቦ ያሰማራው ጦር በምስራቅ አማራ ፋኖ እና በቆቦ እና አካባቢው ማህበረሰብ ላይ ሀምሌ 6/2015 ከጠዋት ጀምሮ ሙሉቀን ጦርነት ከፍቶ ውሏል። በዚህ ጥቃትም በቆቦ መሀል ከተማ ላይ በመግባት መሳሪያ ባልያዙ ንጹሃን አማራዎች ላይ በተለይም በወጣቶች ላይ ግድያ ፈጽሟል። አንደኛው የዐይን እማኝ እንደሚለው የአገዛዙ ጦር መሃል ቆቦ ከተማ ላይ በአምስት ወጣቶች ላይ ተኩሶ ባደረሰው ጉዳት ሁለቱ ወዲያውኑ ሲሞቱ ሶስቱነወደ ህክምና ተወስደዋል። ሌላኛው እንዳለው ካራንቡላ ሲያጫውት የነበረ አንድ ጠቋር የተባለ ወጣትን ተኩሰው ገድለውታል። ሴቶች እና ህጻናትም የጸረ አማራው ጥቃት ሰለባ ሆነዋል። የብልጽግናው አገዛዝ ጦር በምስራቅ አማራ ፋኖዎች እና በህዝቡ የሚደርስበትን ጥቃት ባለመቻሉ እግሬ አውጭኝ እያለ ሲሸሽ ቢስተዋልም ያለ የሌለ ኃይሉን ከወልድያ እና ከራያ አላማጣ መስመር እያስመጣ መሆኑ መስተዋሉን ምንጮች ገልጸዋል። አማራ ሚዲያ ማዕከል (አሚማ) በራያ ቆቦ፣አራዱም ፣አሳመምቻ ፣ቀመሌ ተክለሃይማኖት ፣ጠዘጠዛ ፣ሮቢት እና ጎብዬ ዙርያ ባሉ አካባቢዎች የምስራቅ አማራ ፋኖ አዛዥ እነ ዋርካው ምሬ ወዳጆ፣ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው አበበ ፈንታው እና ሌሎችም የጦሩ መሪዎች ከህዝብ ጋር በመሆን የተከፈተባቸውን ጦርነት ለመመከት እና ለመቀልበስ እያደረጉት ስላለው ተጋድሎ ከምስራቅ አማራ ፋኖ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ከሆነው ከፋኖ አበበ ፈንታው ጋር ቆይታ አድርጓል። ከፋኖ አበበ ፈንታው ንግግር ከተቀነጨቡ  መልዕክቶች መካከል የሚከተለው ይገኝበታል። ▪የኦሮሙማው ብልጽግና መንግስት በመከላከያ ሰራዊት ህግ ማስከበር በሚል ሽፋን በአማራ ህዝብ ላይ መደበኛ የሆነ ጦርነት ከከፈተ ሶስት ወር አልፎታል።*ህዝባችን በዚህ መዘናጋት የለበትም፤ ጦርነት፣ ኦፕሬሽን እንጀምራለን በማለት የሀገር ሽማግሌዎችን እያስፈራራ ከጀመረ ግን ሶስት ወር አልፎታል። በተሳካ መልኩ እየሄደላቸው ስላልሆነ ወደ ህዝብ እየተኮሰ ማንም ያሸነፈም ስለሌለ እስከ ዛሬ የተገፋ ህዝብ፣ ሀቅ የያዘ፣ እውነት የያዘ ህዝብ ነው፤ ይህንን የተከፈተበትን ጦርነት እየተጋፈጠ ያለበት ሁኔታ ነው ያለ። በሽምግልና ሲባል በሽምግልና እየገባ በደሉን እየቻለ ነገሮችን እያለፈ የነበረበት ሂደት አለ። ▪የምስራቅ አማራ ፋኖ ለመከላከያ ለተወሰነ ጊዜም ቢሆን “አንተ የሀገር ጠባቂ ነህ፤ እንደ ተቋም የሁሉም ኢትዮጵያዊያን ነህ። እኛም ራሳችን ከቤት ለቤታችን እናቶችም ከመቀነታቸው እየፈቱ ደመወዝ የሚከፍሉህ ሰራዊት ነህ። አትድረስብን፤ አንደርስብህም። ጠላታችን የብልጽግና መንግስት ነው። ይህ ስርዓት በህዝብ ተመርጫለሁ ቢልም ህዝብን በሰላም፣ በፍቅር፣ በአንድነት እንዲያስተዳድር ነውና ከዛ በዘለለ መንገድ ግን በአማራ ህዝብ ላይ በክልሉም ከክልሉ ውጭም ጦርነት ከፍቶ ያለበት ሁኔታ ስላለ አትድረስብን” ብለን ነበር ያው እንግዲህ አልሆነም። የሚያዙት የአማራ ጠላቶች ናቸው፤ የኦሮሞ ብልጽግና ነው እያዘዘው ያለው መከላከያውን። የእነሱን ትዕዛዝ ተቀብሎ ዛሬ ማለዳ ሰራዊቱ የተወለደበትን አካባቢ ለቆ በርሃ ለበርሃ ነው እየተንከራተተ ያለው። ባለንበት ድረስ መጥተው ነው ተኩስ የከፈቱት ገበሬዎቹ አይተዋቸው ጥቆማ ሰጥተውን ነው ሰራዊታችንን ማትረፍ የቻልነው። አልሞት ባይ ተጋዳይ፣ የሞት የሽረት ትግል ነው እያደረግን ያለነው አሁን። ከፋኖ ሰራዊት ጋር መዋጋት ሲያቅተው ወደ ከተማ እየገባ ንጹሃን ላይ እየተኮሰ ነው ያለው በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ፤ መሀል አስፓልት ላይ ግራ እና ቀኝ ሆቴለሎች ላይ ያለን ህዝብ እየጨፈጨፈ ያከበት ሁኔታ ነው ያለው። በተደጋጋሚ እንደተናገርነው አጠቃላይ ህዝቡ ላይ ነው። የታጠቀው ግንባር ቀደሙ ላይ ሳይሆን እንደ ህዝብ የአማራን ህዝብ መበተን፣ ብኩን ማድረግ ከተቻለም ማጥፋት የተነሱበት አላማ ስለሆነ ይህን እያደረገ ነው ያለው። ከዛም አልፎ አየር መቃወሚያ፣ ሞርታሮች፣ መድፎች መሀል ከተማ ላይ ደግሞ ብረት ለበስ ታንኮችን አስገብቶ ውጊያ እያደረገ ነው ያለበት ሁኔታ ነው፤ እጅግ በጣም የሚያሳፍር ነው። በጎን ግን ለእኛ ያኮራናል፤ ውጊያውን ማሸነፍ የምንችልበት ሙሉ አቅም እንዳለን እና እንደከበድናቸው የሚያሳይ ነው፤ እነዚህን የጦር መሳሪያዎች እየተጠቀሙ ያሉት። ሰራዊቱ በአንድም በሌላ ሁኔታ አመራሩ ነው እንጅ  ታችኛው የአማራ ተወላጅም አሉበት፤ ሌሎች ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያኖችም አሉበት። መዋጋትም አልፈለገም። ቢዋጋም ደግሞ እየደረሰበት ያለው ሁኔታ ትንሽ ከበድ ያለ ስለሆነ ያልኩህን ከባድ መሳሪያዎችን ተጠቅሞ ጦርነት ከፍቶብናል። ንጹሃንን በጣም ጨፍጭፏል፤ ተዋጊውን ላይ ምንም ዓይነት ጉዳት ማድረስ ስላልቻለ፣ አቅም ስላጠረው ወደ ከተማ እየገባ ንጹሃን ሴቶች፣ ህጻናት፣ ወጣቱ ላይ እየተኮሰ ነው ያለውና አማራ መንግስት የለሽ ነው፤ አገሪቱ መንግስት የላትም፤ አማራው ደግሞ የበለጠ መንግስት የለውም፤ ከሌሎች ክልሎች በተለዬ። ስለዚህ ያለው አማራጭ የሞት የሽረት ትግል  ማድረግ እንደ ህዝብ ወጥቶ አደባባይ አገሩን ለቆ እንዲወጣ የማድረግ ስራ መሰራት መቻል አለበት። ካልሆነ ግን እዚህ ላይ ሌላ ጦርነት ከፍቶ በሰሜኑ በኩል የፕሪቶሪያውን ስምምነት ማክበር ስላልቻለ የብልጽግና መንግስት በኃይል እንዲገቡ ሲመክራቸውም ስለከረመ እሱን እንዲያደርጉ በር እየከፈተላቸው ነው ያለው። ከዚህ አንጻር እንግዲህ ልብ ያለው ሸብ ይበል ነው፤  የአማራ ህዝብ እየተፈጠረ ያለውን ነገር በቅጡ ተረድቶ ለማይቀረው የሞት የሽረት የህልውና ትግል መነሳት ነው አለበት ብዬ ነው የማስበው ብሏል አበበ ፈንታው    

የኦሮሙማ አመራር ከአማራ ጋር ጦርነት በማድረግ እንዲለማመዱ የላካቸው የኢ-መደበኛ ሠራዊቱ አባላት ናቸው። የመከላከያን ልብስ አልብሶ ነው ወደውጊያ ያሰማራቸው። ሆኖም፤ የአማራን ክንድ ቀምሰዋል። የፋ
+1
የኦሮሙማ አመራር ከአማራ ጋር ጦርነት በማድረግ እንዲለማመዱ የላካቸው የኢ-መደበኛ ሠራዊቱ አባላት ናቸው። የመከላከያን ልብስ አልብሶ ነው ወደውጊያ ያሰማራቸው። ሆኖም፤ የአማራን ክንድ ቀምሰዋል። የፋኖን ክንድ እያጣጣሙ ይገኛሉ። መከላከያውን አዋረዱት። የደንብ ልቡሱን አረከሱት። በስሙ ማንም እየነገደ ነው። ለማንኛውም ሊለማመዱ ገብተው መለማመጃ ሆነዋል። ድል ለአማራ !! #AmharaStruggle #Justice4Amhara #AmharaGenocide

አስገድዶ ስወራ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል!! ኢሰመኮ ዛሬ ይፋ ባደረገው ዓመታዊ የሰብዓዊ መብት ሪፖርት የሰዎች በሕይወት የመኖር መብት፣ ሰላምና ደኅንነት፣ በእንቅስቃሴ ላይ የሚጣሉ ገደቦችና የአስገድዶ መሠወር የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሳቸውን አስታውቋል። ሪፖርቱ፣ የጭካኔና አዋራጅ ኢሰብዓዊ አያያዝ፣ የኢመደበኛ ማቆያ ቦታዎች መበራከትና የዘፈቀደ እስሮችና የመብት ገደቦች በጣም አሳሳቢ እንደኾኑም ገልጧል። የጸጥታ ኃይሎችና ታጣቂዎች የኃይል ርምጃ በዜጎች በሕይወት የመኖር መብት ላይ አደጋ መደቀኑን የጠቀሰው ሪፖርቱ፣ ጸጥታ ኃይሎች በአማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤልያስ ገዳም፣ በሰሜን ሸዋ ዞን ሸዋሮቢት፣ በደቡብ ክልል ጉራጌ ዞን ወልቂጤና በአንዋር መስጊድ በወሰዷቸው የኃይል ርምጃዎች ሲቪሎች መገደላቸውን ዘርዝራል። ሪፖርቱ፣ በኦሮሚያ በሆሮጉድሩ ወለጋ፣ ምሥራቅ ወለጋ፣ ምዕራብ ወለጋ፣ ቄለም ወለጋ፣ ሰሜን ሸዋ፣ ኢሉ አባቦራ፣ ምሥራቅ ሸዋ፣ ምዕራብ ሸዋ፣ አርሲና ጉጂ ዞኖች ግጭት መቀጠሉንም ገልጧል!!

ባለፈው ዓመት ከተለያዬ የአለማችን ክፍል የተውጣጡ በማህበራዊና ፖለቲካዊ አክቲቪዝም ውስጥ ያሉ ሰዎች የተገኙበት ጉባኤ ላይ የመሳተፍ እድሉ ነበረኝ። ከላቲን አሜሪካ፣ ከሰሜን አፍሪካ፣ ከመካከለኛው ምስራቅና ከጎረቤት ሀገር ሱዳን የተውጣጡ አክቲቪስቶች ስኬታቸውን እና ፈታኝ አጋጣሚዎችን እያጋሩን ነበር። በዋናነት በአመፅ አልባ ትግል የተሻለ ስርዓት እንዲመጣ ያደረጉ፣ የሰብአዊ መብት አቅንቃኞች፣ የህዳጣን መብት አክቲቪስቶች፣ የማህበራዊ ለውጥ አቀንቃኞች ናቸው። ከእነዚህ መካከል አንዲት ኩርዲስታን ነበረች፤ እዚህ ማህበራዊ ሚዲያው ላይ የኩርድ ህዝብ የመበታተን እና የመጥፋት ምሳሌ ተደርጎ ስለሚወሰድ እኔም ይህ ነገር አነሳስቶኝ አንዳንድ ጥያቄዎችን አንስቼላት የነገረችኝ ታሪክ አሁን እኛ እየሄድንበት ካለው ጋር ፈፅሞ ተመሳሳይነት ይታይበታል። ልጂቷ የመጣችው ከደቡብ ምስራቅ ቱርክ ነው፣ ምስራቃዊ እና ደቡብ ምስራቃዊ የቱርክ ክፍል ኩርዶች የሚኖሩበት ሲሆን ኩርዶቹ በዚህ አካባቢ ራስ ገዝ ግዛት እንዲኖራቸው ይታገላሉ። በተቃራኒው የቱርክ መንግስት ለኩርዶች እውቅና አይሰጥም፤ ኩርድ የሚባል ህዝብ በግዛቱ እንደሌለ እንዲሁም ኩርድ ነን የሚሉትን ህልውናቸውን በመካድ Mountain Turks (ደገኛ ቱርኮች) ይላቸዋል። በቱርክ ምድር ኩርዲሽ ቋንቋ መናገር በህግ ተከልክሏል፤ ከ 2020 ጀምሮ በቱርክ ዩኒቨርሲቲዎች ስለኩርዶች ጥናት ማጥናት በይፋ ተከልክሏል፣ የኩርድ መንደሮች ስያሜ ተቀይሯል ....... እያለች ብዙ በደላቸውን ዘረዘረችልኝ። ለነፃነት የሚታገል አካል የላችሁምን? ቀጣዩ ጥያቄ ነበር። PKK የሚል ስም ጠራችልኝ። ፒኬኬ የትጥቅ ትግል ያካሂዳል። ምሁሮቻቸው ደግሞ በቋንቋቸው መማር ስለተከለከሉ የራሳቸውን የትምህርት ስርዓት አበልጽገዋል፣ ህፃናቱ በየሰፈሩ በግለሰቦች ቤት ይማራሉ፣ ከክፍል ክፍል ይዘዋወራሉ... ይመረቃሉ። የቱርክ መንግስት በበኩሉ ፒኬኬን በአሸባሪነት ይፈርጀዋል። የኛም ነገር ወደዚያ ደረጃ እያመራ ይመስላል። የስርዓቱ አፈ ቀላጤዎች አማራ የሚባል የለም የሚሉት መኖራችን ጠፍቷቸው አይደልም _ ከግባቸው መጀመራቸው መሆኑን እንረዳዋለን። በጎን ደግሞ የለም የሚሉትን ህዝብ መገለጫ የሆኑ ነገሮች ለማጥፋት የሚያደርጉትን ሩጫ እናያለን። በየቦታው ያለው ግድያና ማፈናቀል፤ የከተማና የጎዳና ስያሜዎች መቀየር፣ አዲስ አበባ ውስጥ ልጆቻችን ተገደው ከአፍ መፍቻ ቋንቋቸው እንዲነጠሉና ኦሮምኛ በግድ እንዲማሩ የሚደረገው፤ ዩኒቨርሲቲ ላይ በማንነት ተመርጦ መታገት፣ የፖለቲካ ጥያቄ የሚያነሱ ቡድኖችን በአሸባሪነት መፈረጅ፤ ጅምላ እስርና እንግልት፤ ጦርነት ..... ይሄን ሁሉ ግፍ ዛሬ በርትተን ካልቀለበስነው ነገ መቋቋም ወደማንችልበት ደረጃ እንደርሳለን። የዳር ተመልካች መሆን ነገ ለፀፀት ይዳርጋል፤ ዛሬን እንጠቀምበት። ኩርዲስታኗ የሚደርስባቸውን በደል From denial to war በማለት ትገልፀዋለች። እኛም ጋር የሆነው ተመሳሳይ ነው_ ህልውናን ከመካድ ጀምሮ በጦር እስከመደብደብ የደረሰ! በተረፈ አክቲቭዝማችን ከሌሎች አንፃር የሞተ ነው። ብዙ ሆነን ሳለ ሚናችን ከአንድ ያነሰ፤ ከሀሳብ ይልቅ የሁነት ዘገባ የሚያበዛ፣ ስርዓቱን በሚገባ ያልበየነ፣ በራስ ከመቆም ይልቅ ጁኒየር ለመሆን አለቃ ፍለጋ የሚዳክር ፤ ለመብረር የሚያኮበኩቡትን ክንፍ ለመምታት የሚሽቀዳደም የአክቲቪዝም ቅርጽ እታዘባለሁ። ድል ለህዝባችን! /ምስጋናው ዘ ግዮን/

ፌደራል ፖሊስ በአማራ ክልል የዞን እና የወረዳ ጤና መምሪያዎችን በማስገደድ ሀሰተኛ የሞት ሪፖርት መቀበሉ ተሰማ! (የአማራ ድምፅ/ሀምሌ 04/2015 ዓ/ም) ፌደራል ፖሊስ በእነ ዶ/ር ወንድወሰን አሰፋ መዝገብ ክስ የመሰረተባቸው ተጠርጣሪዎች በአማራ ክልል በቀሰቀሱት አመፅ በርካታ ሰዎች ህይወታቸው አልፏል በሚል በክልሉ የዞን እና የወረዳ ጤና መምሪያዎችን በማስገደድ ሀሰተኛ የሞት ሪፖርት መቀበሉን የአማራ ድምፅ ካሰባሰበው መረጃ ለማረጋገጥ ችሏል። በአማራ ክልል በሚገኙ ዞኖችና ወረዳዎች የተሰማራው የፌደራል ፖሊስ ቡድን "ምን ጠፋባችሁ? ምን ያህልስ ከሰራችሁ?" በሚል የተለያዩ መንግስታዊ ተቋማት ሀሰተኛ ሪፖርት እንዲፅፉለት ያስገደደ ሲሆን ይህንን ሀሰተኛ ሪፖርትም ተጠርጣሪዎቹ በቀሰቀሱት አመፅ የጠፋ የሰው ህይወትና ንብረት በሚል በክሱ እንዲካተት ተደርጓል። ከፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የተላከው ግበረ ኃይሉ በየዞኑ እና በየወረዳው የሚገኙ ጤና መምሪያዎችን በማስገደድ በህመም እና በተለያዩ ምክኒያቶች በየሆስፒታሉና በየጤና ጣቢያው ህይወታቸው ያለፈን ሰዎች ጭምር በማካተት ሀሰተኛ የሞት ሪፖርት እንዲፃፍለት ያስደረገ ሲሆን ተጠርጣሪዎቹ በቀሰቀሱት አመፅ የተገደሉ ሰዎች ዝርዝር በሚል የክሱ አንድ አካል መሆኑ ታውቋል። በርካታ የዞንና የወረዳ ጤና መምሪያዎች ተጠርጣሪዎቹ ቀሰቀሱት በተባለው አመፅ ህይወቱ ያለፈ ሰው እስከ አሁን በተቋማችን አላጋጠመንም የሚል ምላሽ የሰጡ ቢሆንም ነገር ግን ከአመፁ ጋር በተያያዘ በርካታ ሰዎች መሞታቸውን የሚገልፅ ደብዳቤ መፃፍ እንዳለባቸው ነው ማስጠንቀቂያና ማስፈራሪያ የተሰጣቸው ተብሏል። ስለሆነም የጤና መምሪያዎቹ በዚህ ሁለት ወራት በየተቋሞቻቸው በተለያየ ምክኒያት ህይወታቸው ያለፉ ሰዎችን ዝርዝር ከአመፁ ጋር በማያያዝ ለግብረ ኃይሉ ተገደው ሪፖርት ማድረጋቸውን ነው ለደህንነታቸው ሲባል  የእሳቸው እና የተቋማቸው ስም ያልተጠቀሰ የአይን እማኝ ለአማራ ድምፅ የገለፁት። አንዳንድ ጤና መምሪያዎች በወሊድ ምክኒያት ህይወታቸው ያለፈ እናቶችን እና በመኪና አደጋ ህይወታቸው ያለፈ ሰዎችን ስም ዝርዝር ከአመፁ ጋር አያይዘው ሪፖርት አድርገዋል ተብሏል። አንዳንዶች ደግሞ ኤች አይ ቪ ኤድስን ጨምሮ በተለያዩ በሽታወች ህይወታቸው ያለፈ ሰዎችን ስም ዝርዝር በተቀሰቀሰው አመፅ ህይወታቸው ያለፉ ናቸው በሚል በተሰጣቸው አስገዳጅ ትዕዛዝ መሠረት ለግብረ ኃይሉ ደብዳቤ ፅፈዋል ሲሉ የአይን እማኛችን ገልፀዋል። በባህርዳር ከተማ የሚገኝ አንድ ትልቅ ሆስፒታል ተቀሰቀሰ በምትሉት አመፅ ምክኒያት ህይወቱ ያለፈም ሆነ ጉዳት ደርሶበት ወደ ተቋማችን የመጣ ሰው የለም በሚል ለግብረ ኃይሉ ምላሽ በመስጠቱ በአስተዳደር አካላቱ ላይ ዛቻና ማስፈራሪያ ተፈፅሟል ሲሉ ሌላኛው የአማራ ድምፅ የመረጃ ምንጭ ተናግረዋል። ተጠርጣሪዎቹ በቀሰቀሱት አመፅ በርካታ ሰዎች ህይወታቸው አልፏል በሚል ከፍተኛ የሟች ቁጥር ለግብረ ኃይሉ ሪፖርት ካደረጉት መካከል በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ጤና መምሪያ አንዱ መሆኑንም ምንጮቻችን ጠቁመዋል። ፌደራል ፖሊስ በእነ ዶ/ር ወንድወሰን መዝገብ የተካተቱ 51 ተጠርጣሪዎች ቀስቅሰውታል ባለው አመፅ ህይወታቸው አልፏል በሚል ከተቀበለው የሟቾች ዝርዝር ሪፖርት በተጨማሪ በክልሉ በሚሊየኖች ብር የሚገመት ንብረት ወድሟል በሚል በየአከባቢው አስገዳጅ ሀሰተኛ ሪፖርት ማስፃፉም ነው የተገለፀው። በየወረዳው እና በየዞኑ የሚገኙ ተቋማት በአመፅ ምክኒያት የወደመብን፣ የከሰርነው ንብረት የለም ያሉ ቢሆንም ነገር ግን ከሁለት ወራት ወዲህ በተለያዩ አጋጣሚወች የጠፋ ንብረት ካላቸው ሪፖርት እንዲያደርጉ ግብረ ኃይሉ አስገዳጅ መመሪያ ሰቷል ሲሉ በሰሜን ወሎ ዞን በመንግስት መስሪያ ቤት የሚሰሩ አንድ ባለሞያ ለአማራ ድምፅ ገልፀዋል። ግብረ ኃይሉ ዞንና ወረዳዎች በተለያየ ምክኒያት የጠፋባቸውን ንብረት በዝርዝር እንዲገልፁለት በሰጠው አስገዳጅ ትዕዛዝ መሠረት አንድ ወረዳ ለቢሮ ፅዳት አገልግሎት የተቀመጠ  አራት ፈሳሽ ሳሙና ጠፍቶብኛል በሚል ሪፖርት ያደረገ ሲሆን፡ ይህም ተቀሰቀሰ በተባለው አመፅ የጠፋ ንብረት በሚል በክሱ ውስጥ ተካቷል ነው የተባለው። ሌላኛው በምስራቅ ጎጃም ዞን የሚገኝ አንድ ወረዳ ደግሞ ለስራ የምንጠቀምበት አንድ ተሽከርካሪ የኋላ ፍሬቻ ባልታወቀ ሁኔታ ተሰብሮብናል የሚል ሪፖርት ለግብረ ሀይሉ ያቀረበ ሲሆን ይህም በአመፁ የወደመ ንብረት በሚል በክሱ ላይ እንዲካተት መደረጉ ተገልጿል። የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የገቢዎች ሚኒስቴር በባህር ዳር ቅርንጫፍ ፅ/ቤት በባህርዳር ከተማ በተፈጠረው አመፅ የጠፋባችሁን ሀብትና ንብረት  እንዲሁም አመፁ ባይፈጠር ኖሮ ልታገኙት የምትችሉትን ገንዘብ አስልታችሁ አሳውቁኝ የሚል አስገዳጅ ትዕዛዝ ከግብረ ኃይሉ በተደጋጋሚ የተሰጠው ቢሆንም ነገር ግን መስሪያ ቤቱ ምንም አይነት ሀብትና ንብረት አልጠፋብኝም የሚል ምላሽ በመስጠቱ በአስተዳደር አካላቱ ላይ ዛቻና ማስፈራሪያ እንደተፈፀመባቸው ለአማራ ድምፅ የደረሰው መረጃ አመላክቷል። ወደ አማራ ክልል የተላከው የፌደራል ፖሊስ ግብረ ኃይል ያስፃፈውን በማስፈራሪያና በማባበያ የተደገፈ በሰው ህይወት እና በንብረት ላይ ደረሰ የተባለውን የጉዳት መጠን ሪፖርትን ጨምሮ መርማሪ ፖሊስ የሰው እና የሰነድ ማስረጃዎችን አሰባስቤ ጨርሻለው በማለት መዝገቡን ለዐቃቢ ህግ ያስተላለፈ ሲሆን ዐቃቢ ህግም በተጠርጣሪዎቹ ላይ ክስ መስርቷል። ዐቃቤ ህግ ብዛታቸው 51 የሚሆኑ ምሁራን፣ ጋዜጠኞች፣ የማህበረሰብ አንቂዎች፣ የአማራ ፋኖ አመራሮችና አባላት፣ የጉልበት ሰራተኞችን እንዲሁም  ሌሎችንም በአንድ መዝገብ በማካተት ነው 970 ገፅ ማስረጃ አለኝ ያለውን የ71 ገፅ ክስ የመሠረተው። ከእነዚህ መካከል 24ቱ ባሉበት፤ ቀሪዎቹ 27 የሚሆኑት ደግሞ በሌሉበት ክስ የተመሰረተባቸው መሆኑን ይታወቃል።

90 ቀናት! ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው በግፍ ዕስር ዛሬ 90 ቀናት አስቆጥሯል። በርካታ ንጹሃን በተመሳሳይ የግፍ ዕስር ውስጥ ይገኛል። ለፋሽስቱ የኦሮሙማ መንግስት እነዚህ ታሳሪዎች ዋነኛ ጥፋታቸው አማራ
90 ቀናት! ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው በግፍ ዕስር ዛሬ 90 ቀናት አስቆጥሯል። በርካታ ንጹሃን በተመሳሳይ የግፍ ዕስር ውስጥ ይገኛል። ለፋሽስቱ የኦሮሙማ መንግስት እነዚህ ታሳሪዎች ዋነኛ ጥፋታቸው አማራ መሆናቸው ብቻ ነው!!

ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው ዛሬ በችሎት ከተናገረው ታሪካዊ ንግግር‼ ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ.ም አሻራ ሚዲያ ፣ << ጠቅላይ ሚኒስርት ዐቢይ አህመድ 'የፍትህ ተቋማት ዳኞች ሌቦች ናቸው' ብለዉ ተናግረዋል። ነገር ግን ዐቃቢ ህግ  አልከሰሳቸውም። >> << ..እኛ 'የፖለቲካ እስረኞች ነን' ስንል በምክንያት ነው።  51ዱም ተከሳሾች በሙሉ አማራዎች ናቸው። የተከሰስነው ሰርቀን አይደለም ወይም ወለጋ ሰዉ ጨፍጭፈን አይደለም ፤ ሸገር ሲቲ ዜጎችን አፈናቅለን አይደለም። ነገም ደጋግመን እንለዋለን ክሳችን ወንጀላችን አማራ ሆነን ነው። ይሄ አይቀየርም ፤ ከፈለጋችሁ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ሄዳችሁ ብታዩ  በሙሉ አማራ ብቻ ናቸው። >> <<...እኔ በአንድ ወቅት የመንግስት መገናኛ ብዙኸን ውስጥ ጋዜጠኛ ነበርኩኝ ። እንዴት እንደሚሰራ አውቃለሁ። የፓርቲ ትእዛዝ እንደወረደ አይቀርብም። በእኔና በረ/ፕሮፌሰር  ሲሳይ አውግቸው 'የፀጥታ ደህንነት ግብረሃይል መግለጫ' በማለት ሽብርተኛ ብሎ በእኛ ላይ ሁለት ጊዜ ዘገባ ሰርቷል። >> << በዚህ ችሎት ባሉ ተከሳሾች ሁሉም ላይ በተደጋጋሚ የሽብርተኝነት ዘገባ ተሰርቷል። ይህ ሆን ተብሎ የተደረገ ነው። እኔ ጋዜጠኛ ነኝ ፤ ወረቀትና እስኪብርቶ እንጅ የጦር መሳሪያ ይዤ ፎቶ አልተነሳሁም። ከየት አምጥቶት ነው ግብረሃይሉ ፎቶሾፕ ያቀናበረው? ስለዚህ ፍ/ቤቱ  ፋና ዋልታ እና OBN የመንግስት መገናኛ ብዙሀን በሰሩት ዘገባ መጥተዉ እንዲያስረዱ ጥብቅ ትህዛዝ ይሰጥልን። በተሰራው ዘገባ የሞራል ድቀት አድርሰውብናል ፤ ቤተሰቦቻችን በእጅጉ ተጎድተዋል። በፍርድ ቤት ሂደት ያለን ሰዎች ነፃ ሆነን የመታየት ህገመንግስታዊ መብታችን ተጥሷል። >> << የአማራ ተወላጅ በመሆናችን የፖለቲካ እስረኛ ነን ፥ የምንለው በተጨባጭ ማሳያ ነው። የሚዲያዉ ኃላፊዎች መጥተው ለምን እንደዘገቡት ያስረዱ። ይህ ካልሆነ ጠንከር ያለ እርምጃ እኛም እንወስዳለን።>> << ጠቅላይ ሚኒስርት ዐቢይ አህመድ የፍትህ ተቋማት ዳኞች ሎቦች ናቸው ብለዉ ተናግረዋል። ነገር ግን ዐቃቢ ህግ አልከሰሳቸውም። >> //ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው ዛሬ ሀምሌ 3/2015 ዓ.ም በችሎት የተናገረውን -ስንታየሁ ቸኮል እንዳጋራው/

⁽⁽አማራ ዝም ብሎ እንድሮው፡ ኢትዮጵያ ፡ ኢትዮጵያ እያለ ፥ ካልተደራጀ፡ ካልተሰባሰበ፣ ጠንካራ ትግል ካላደረገ ፡ ከጥቃቱ ሊድን አይችልም፤ ከአዙሪቱ ሊወጣ አይችልም⁾⁾ ልደቱ አያሌው (በአንድ አማራ
⁽⁽አማራ ዝም ብሎ እንድሮው፡ ኢትዮጵያ ፡ ኢትዮጵያ እያለ ፥ ካልተደራጀ፡ ካልተሰባሰበ፣ ጠንካራ ትግል ካላደረገ ፡ ከጥቃቱ ሊድን አይችልም፤ ከአዙሪቱ ሊወጣ አይችልም⁾⁾ ልደቱ አያሌው (በአንድ አማራ ሚድያ ውይይት)