en
Feedback
Ethio monitor

Ethio monitor

Open in Telegram
1 482
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ሌላ ተጨማሪ የድሮን ጥቃት በበረኸት‼️ በምንጃር በረኸት ከተማ ከትላንቱ በተጨማሪ ዛሬም ተጨማሪ የድሮን ጥቃት ተፈፅሟል። የደረሰው ጉዳት መጠን ምን ያህል እንደሆነ እስካሁን ለማወቅ አልቻልንም። በምንጃር ሸንኮራ በረኸት ላይ 6ኛ ቀኑን የያዘ እጅግ ከፍተኛ ጦርነት እየተካሄደ ነው። በዚህ ጦርነት መከላከያ ያለ የሌለ ኃይሉን አሰልፎ በአየር፤ በድሮን እና በብረት ለበስ ተሽከርካሪዎች እየተዋጋ ይገኛል። ፋኖ ይሄን ሁሉ ተቋቁሞ በርካታ የአብይ አህመድ ሰራዊትን የደመሰሰ ሲሆን መንግስት በበኩሉ የበቀል እርምጃውን በንፁሃን ላይ እያሳረፈ ይገኛል። ከዚህ በተጨማሪ ከፍተኛ ሰራዊቱን ወደ በረኸት በተለምዶ #መተህብላ ወደሚባል አካባቢ እያስገባ ይገኛል። የአብይ አህመድ መንግስት ዛሬም በበረኸት የድሮን ጥቃት የፈፀመና በርካታ ንፁሃንን የገደለ ሲሆን ፋኖዎች በዚህ ብስጭት ብረት ለበስ ተሽከርካሪዎችን እና ተዋጊ ድሮኖችን ካሰለፈው ገዳይ ቡድን ጋር ፊት ለፊት ውጊያ እያደረጉ ይገኛሉ።በሌሎች አካባቢዎች የምትንቀሳቀሱ የፋኖ አባላት ወደ አካባቢው በመንቀሳቀስ አስፈላጊውን እገዛ እንድታደርጉ ጥሪ ቀርቧል

#-ለሁሉም ፋኖ አመራሮች በይፋ የሚነገር ብልብላ ዳንግላ ፍኖተ ሰላም ኩል መስክ ለሚ ደበረ ሊባኖስ ድረስ አገዛዙ መረጃ ስላሰባሰበ በዚያ አካባቢ የምትንቀሳቀሱ ፋኖዎች የከባድ መሳሪያ እና የድሮን ጥቃት ሊኖር ስለሚችል አስፈላጊውን ጥንቃቄ ሁሉ እንድታደርጉ እናሳስባለን። (ከውስጥ የተላከ)

"ከእንግዲህ በኋላ አማራ ኢትዮጵያን አይመራም፡፡ Not in a million years!" ... አብይ አህመድ፡፡ (ምንጭ አበበ ገላው፡፡) "አማራ ከሚሊዮን አመታት በኋላ እንኳ አራት ኪሎ አይገባም"... ጃዋር መሀመድ፡፡ ተናበው ነው የሚታገሉን! አማራ ግን ያሸንፋል!!

ረቡዕ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ተገኝቼ የወንድምና እኅቶቼን ችሎት የምታደም ይሆናል።
ረቡዕ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ተገኝቼ የወንድምና እኅቶቼን ችሎት የምታደም ይሆናል።

ለደፋሪ ብድር??? በቡድን የሚደፈሩ ወገኖቻችን፣ በአደባባይ የሚረሸነው ሲቪል ቁጥር በእጅጉ እየጨመረ ቢሆንም አድቮኬሲ ላይ መዘናጋት ይታያል። ማወቅ ያለብን ነገር ቢኖር የአብይ አህመድ ሰራዊት በፋኖዎች ብርቱ ምት ሲገጥመው አፈሙዙን ወደንፁሃን ያዞራል፤ ክብራቸውን አጉድፎ በሴቶቻችን ስቃይ ሊበቀለን ይታትራል። ፋኖዎቻችን ለእያንዳንዱ ጥቃት የሚወስዱት የአፃፋ እርምጃ የሚያስደንቅ ነው፤ "በእህቶቻችን ላይ ጥቃት ያደረሰ በህይወት መውጣት የለበትም" የሚል ቃል አላቸው። እኛ በመሳሪያ የማንዋጋውስ ለምን የራሳችንን የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ አናድርግም? አብይ አህመድ ከ IMF እና ከ European Union ብድር ለመቀበል ደፋ ቀና በሚልበት ሰዓት እኛ ዝምታን መርጠናል። ሴቶችን በቡድን የሚደፍር ወታደር ላሰማራ መንግስት ብድርና ድጋፍ ቢሰጠው ከሰጪዎች በላይ እኛ ተጠያቂዎች እንሆናለን። በተለይ ዲያስፖራው ወገናችን! በውጭ የሚመሰረቱ አዳዲስ ማህበራት የዲያስፖራውን አንድነት በማናጋታቸው አክቲቪዝሙ ተበድሏል። ይሄንን ክፍተት ለመሙላት ለየት ያለ የአድቮኬሲ ቲም ማዋቀር ያስፈልጋል!! @ምስጋናው ዘ ግዮን

ከባ/ዳር 40 ኪሜ ላይ በምትገኘው  አዴት ከተማ በመስከረም 29 እና 30 ሁለት ክፍለ ጦር የተደመሰሰበት ባንዳው አበባው ታደሰ ዛሬ ቤት ለቤት እየገባ ንጹሃንን እየጨፈጨፈ ነው። ወራሪው ካምፕ አድርጎት በነበረው የአዴት ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በርካታ መቃብሮች ተገኝተዋል።

Update from Amhara Region! በትላንትናው ዕለት በጥቅሉ በ17 ግንባሮች ውጊያ ነበር፤ በሁሉም ግንባሮች የወገን ሃይል ድል ተቀዳጅቷል።   የወገን ሃይል የተጓደለ ትጥቅ ያሟላበት፣ ጠላት የተመናመነበት ታሪካዊ ቀን ሆኗል - ጥቅምት 02 ቀን 2016 ዓ.ም! በሌላ በኩል አብይ አህመድ የሞቱ የጦር መኮነን ቤተሰቦችን ከ 6 ኪሎ የወታደራዊ መኮነኖች መኖሪያ ግቢ (ኮስትራ) አስወጥቷቸዋል። ወታደሩ የአብይን ስልጣን ለመጠበቅ ይሞታል፤ አብይ ደግሞ በ "ተጠቅሞ መጣል" መርሁ ቤተሰብ ይበትናል።   በተመሳሳይ አዲስአበባ ሳር ቤት ሩሲያ ካምፕ ከሚባለው ግቢ ውስጥ የአማራ ተወላጅ የኮማንዶ አባላት ታስረው እየተሰቃዩ ይገኛሉ። አብይ አህመድን ማገልገል ከስቃይ የሚያድን፣ በድሎት የሚያኖር የሚመስላቸው አማራ ባንዳዎች ከዚህ ትምህርት ውሰዱ።  ለኦህዴድ በመታዘዝ ኦሮሞ መሆን አይቻልም ወይም ከእነሱ እንደ አንዱ ልትሆኑ አትችሉም..... ምህረት አያደርጉላችሁም! Source: ምስጋናው ዘ ግዮን ድል ለአማራ ህዝብ!

ሰበር‼️ሰበር‼️ሰበር‼️ አማራ  ሲቢሊያን በሮኬት ተደበደቡ‼️ ተደጋጋሚ ሽንፈት የገጠመው ፋሽስታዊና ሽብርተኛው የአብይ ስርዐት ኢንተርኔትና ኔትወርክ ዘግቶ ወደ ህዝብ ሮኬት እየተኮሰ መሆኑ ታውቋል። ዛሬ ጠዋት ደጋ ዳሞትና ቢቡኝ ወረዳ መካከል የወይን ውኃ የምትባል የገጠር መንደርን በሮኬት ደብድቧል። ወደ ፍኖተ ሰላምም ሮኬት እንዳስወነጨፈ ታውቋል። ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉ ወገኖች እንደተጎዱም ተነግሯል።

የተመድ የዘር ማጥፋት ወንጀል መከላከል ልዩ አማካሪ አሊስ ዋይሙሩ በኢትዮጵያ አኹንም የዘር ማጥፋት ወንጀል እንዲፈጸም የሚያስችሉ ኹኔታዎች አሉ ሲሉ አዲስ ባወጡት መግለጫ አስጠንቅቀዋል። በአገሪቱ "የቤተሰብ አባላት በሙሉ የሚገደሉበት" ኹኔታ እንዳለ የገለጡት ሃላፊዋ፣ ትግራይና አማራ ክልሎችን ጨምሮ ከአገሪቱ የሚወጡ የጥሰት ሪፖርቶች "እጅግ የሚረብሹ ናቸው" ብለዋል። በአገሪቱ የዘር ማጥፋት ወንጀልና ሌሎች ጥሰቶች እንዳይከሰቱ ከአኹኑ መከላከል እንደሚያስፈልግም ሃላፊዋ አሳስበዋል። ሃላፊዋ፣ በአማራ ክልል ውስጥ ከግጭቱ ጋር በተያያዘ የሚፈጸሙ ጥሰቶች ባስቸኳይ እንዲቆሙም ጠይቀዋል።

~ ትናንት ወደ ጭስ አባይ ገብቶ የነበረው የብልፅግና ሰራዊት ተጠርጎ ወጥቷል፤ ዛሬም ከሰዓት በኋላ ጀምሮ በባህርዳር ከተማ መውጫ ዙሪያ ሃይለኛ ውጊያ እየተካሄደ ነው። ገንጅ ተዓምር ሰርቷል። በርካታ ባለስልጣናት አሁን ከመሸ ባህርዳር ኤርፖርት ታይተዋል። የሀገር ውስጥ ኩብለላ መሆኑ ነው😁

ፋኖ ንፁሃንን ሳይገድሉ ከነመሳሪያቸው እጃቸውን የሚሠጡ የስርዓቱ ወታደሮችን በሰላም ወደቤተሰቦቻቸው እየሸኘ መሆኑን አስታውቋል። በጎጃም ቀጠና ብቻ ከተያዙት ውስጥ 1640 ያህል ወታደሮች ደቡብ ኢትዮጵያ ከሚገኙ ቤተሰቦቻቸው ጋር በሰላም መቀላቀላቸውን፤ 300 ያህል ቆስለው በህክምና ላይ እንደሚገኙና ሌሎች 6000 ያህል ወታደሮች ደግሞ ህዝባዊ ሃይሉን ተቀላቅለው ስርዓቱን እየተዋጉ እንደሚገኙ ተገልጿል። ከዚህ ቀደም ተማርከው የተለቀቁና ለ2ኛ ጊዜ የተማረኩ፣ ንፁሃንን ሲገድሉ የተያዙ እና በመድፈር የተሳተፉ ወታደሮች ብቻ በእጃቸው እንደሚገኙ የቀጠናው ፋኖ ቃል- አቀባይ ገልፆልኛል። በሌሎች ግምባሮችም እየተጣራ ተመሳሳይ እርምጃ እየተወሰደ ይገኛል። መከላከያ ሰራዊት ውስጥ ልጆቻችሁን የላካችሁ ቤተሰቦች ልጆቻችሁን በዓይነ-ስጋ ማየት ከፈለጋችሁ እየደወላችሁ እጅ እንዲሰጡ አድርጉ። የአብይ አህመድ ዙፋን እግሩ ተሰብሯል፤ በድሀ ልጆች ደም ሊጠገን ከማይችልበት ደረጃ ደርሷል። ሞት ሳይቀድማችሁ ቅደሙት!

ዛሬ ወደ ደብረ ታቦር ለኦፕሬሽን ሲጓዙ የነበሩ በርከት ያሉ የክልል ባለስልጣናት አለም በር አካባቢ በደፈጣ ኦፕሬሽን "መሸኘታቸውን" ሰምተናል። ሦሥት ወታደራዊ ተሽከርካሪዎችን ጨምር የስርዓቱ መገልገያ ቁሶች ከጥቅም ውጭ ሆነዋል። ከሁለት ቀናት በፊት 9 ያህል የጃማ እና ደጎሎ የወረዳ ባለስልጣናት በፋኖ እጅ መውደቃቸው ይታወቃል። የብአዴን ካድሬዎች የአማራን ህዝብ እያስጨፈጨፉ በነፃነት ሊንቀሳቀሱ አይገባም። ከእነርሱ በላይ የህዝባችን ጠላት የለም። @ምስጋናው ዘ ግዮን

የብልፅግና ወታደር በዚህ ሰዓት ከዳንግላ አቅጣጫ በBM ሮኬት እያስወነጨፈ ነው። ወደ አቸፈር እና ሜጫ አቅጣጫዎች በዘፈቀደ ወደ መኖሪያ መንደሮች እየተተተኮሰ ይገኛል። የዚህ ተኩስ ዋነኛ ዓላማ ንፁሃንን መጨፍጨፍ ብቻ ነው። #WarOnAmhara

~ የአማራ ህዝብ ምርጫው ግልጽ ነው፤ ይህም ህልውናዬ ይከበር፣ ፍትህ ይስፈን የሚል ነው! ከዚህ ያነሰ ፍላጎት ሊኖር አይችልም። የመኖር መብትን ለማስከበር የሚከፈልን የህይወት መስዋዕትነት የሚያህል ብጽዕና ከየትም ሊገኝ አይችልም። አማራ ይህን ምርጫው እንዲያስከብርለት የሚጠይቀው መንግስት የለውም። ብቸኛው ህልውናን ማረጋገጫ መንገድ የአደጋው መንስኤ የሆነውን ፋሽዝም እና ፋሽስታዊ አገዛዝ ማስወገድ ነው። ይህም በተሳካ ሁኔታ እየተከወነ ነው። አገዛዙ በቁሙ የፈረሰ ሰራዊቱን ለጦርነት ልኮ እንዳይጠገን አድርጎ እያፈራረሰው ይገኛል። ከፍርስራሹ ውስጥም የአማራ ብሄራዊ ጦር ተወልዷል፣ እየተወለደም ነው። ይህ ብስራትም-ስብራትም የሆነ ክስተት መጨረሻው የአማራ ድህነት መሆኑ ዕርግጥ ነው። የአገዛዙ ዕብሪት ከጅምሩም መልካም አጋጣሚ እንደሚሆን ተናግረናል፣ የሆነውም እንደዚያ ነው። አሁንም ይኸው ዕብሪት ተጨማሪ አቅም እየፈጠረ ነው። የጦርነቱ መጨረሻ ከጅምሩ የተረጋገጠ ነው፤ የአማራ ህዝብ የተቃጣበትን የህልውና አደጋ ያሸንፋል፤ ፋሽዝም ይቀበራል። ይኸው ነው! ድል ለአማራ ❗️ #AmharaRevolution

ነገ ጀምሮ መከላከያ በሁሉም ቦታ እንዲያጠቃ አሁን ከመሸ ትዕዛዝ ተሰጥቶታል !! መረጃዉን  ለሕዝብ ልጆች ላከው !!

የተፈናቀልክ እና ልትፈናቀል የታጨህ አማራ ሆይ ....‼ በጠላቶች ክፋትና ዘር አጥፊ ዓላማ የተነሳ ከኑሮህና ከቤትህ እየተገፋህ ያለህ አማራ ከጠላት ደጅ ምሕረት አታገኝም። ገዳዮችህ፣ አፈናቃዮችህ በፖለቲካ ዓላማ የፈፀሙት ነውና። ተሳስተው፣ ሕግ ማስከበር ፈልገው፣ ወይም ከአቅማቸው በላይ የሆነ ታጣቂ ስላለ አይደለም። የሞቱት እና የተፈናቀሉት ሁሉ የዘረኛውን ልሒቅ የፖለቲካ ዓላማ ለማሳካት የሚሠሩ ናቸው። የምትድነው ይሔንን ጠላት ሊታገሉ ዱር ቤቴ ያሉ የአማራ ልጆችን ስትቀላቀል ብቻ ነው ‼ ወለጋ በታጣቂያቸው ያስገደሉህን እና ያፈናቀሉህን፤ አዲስአበባ ዙሪያ ላይ ቀጥለውታል።  ወለጋ ላይ ሕገወጥ ታጣቂ በሚል ያስፈፀሙትን፣ መንግስት ነን ብለውም  "ሕግ ማስከበር" በሚል ሽፋን  ማፈናቀልና ማራቆት ሥራዬ ብለው ይዘውታል። የፖለቲካ ዓላማ እና ዕቅድ ተይዞለት የሚፈፀም ነው ‼ ወለጋ ላይ ካስታጠቁት ቡድን ጋር ስምምነት ልናደርግ ነው ቢሉም የአማራ ጥቃት ይቀጥላል። "ሕገወጥ ቤት" የሚል ጥሩ ሽፋን አግኝተዋል። በወለጋው ጭፍጨፋ እና በኦሮሚያ ከተሞች በሚፈፀመው መካከል ልዩነት የለም።  ተፈናቃዩ እና ሟቹ አማራ ነው፥ ገዳዩና አፈናቃዩ ዘረኛው የኦሮሞ ልሒቅ ነው።  ልዩነቱ ሰበብ ብቻ ነው። ገዳይ ታጣቂ ያሰማሩት፣ ማፈናቀያና መግደያ ሰበብ ቸግሯቸው ስለነበር ነው። ወለጋ ላይ ቢስማማማም የአማራ ጥቃትና መፈናቀል ይቀጥላል‼️ አማራውን  በቀጣይነት  የማፈናቀልና ሜዳ የመጣል አላማቸውን በ600  ከተሞች በመንግስታዊ መዋቅር ሊፈፅሙት ተዘጋጅተዋል። "ከተሞቻችንን ነፍጠኛ ይዞብናል" ሲሉ የኖሩት ዝም ብለው አይልነበረም። አሁን የሚያደርጉት ሲተርኩት እንደኖሩት  "ከተሞቻቸውን ከነፍጠኛ የማፅዳት" እንጂ ሕግ የማስከበር አይደለም። ሕግንማ ሲጫወቱባት እየዋሉ ነው‼️ ንፁሕ ዜጋን በቀን ከሌት እያፈነ የሚሠውር መንግስት ሕግ እያስከበረ ከመሰለህ ትልቁ ሞኝ አንተ ነህ!! ሕግና ፋሽዝም አይተዋወቁም ‼ ዘር እያፀዳ ነው‼️ ከአማራ እና መሠሎች የፀዳች ኦሮሚያ እየተሠራች ነው ‼ የፋሽስቱ ሽመልስ አብዲሳ መንግስት በኦሮሚያ ከ127ሺህ በላይ ንግድ ፈቃዶች ሕገ ወጥ ናቸው እያለ ነው። "ኢኮኖሚውን ይዘውብናል" ሲል የኖረ በመሆኑ ከኢኮኖሚ ሥራ ሊያፈናቅልህ እየተዘጋጀ ነው። ነዋሪንም ፣ ነጋዴንም በማፅዳት ከአማራና መሠል ሠርቶ አዳሪ ማሕበረሰብ የፀዳች ኦሮሚያን እየፈጠረ ነው። የምትድነውም የምትበቀለውም  የወንድሞችን ትግል በመቀላቀል ነው‼️ ስለሆነም ተፈናቅለህና ሜዳ ወድቀህ የሰው እጅ የምታይበት ዘመንና ሁኔታ ሊያጥር የሚችለው  የአማራ ወታደራዊ አደረጃጀቶችን እየተቀላቀልክ ጠላትን መዋጋት ስትችል ብቻ ነው። በስቃይህ የሚስቅ እንጂ ስቃይህን የሚያስቀር መንግስት የለም። በውርደትህ የተዘጉ አንደበቶች እንጂ፣ ለምን የሚል ሕግና ሞራል በኢትዮጵያ ሰማይ ነጥፏል። የሚያድንህ ሜዳ ወድቀህ፣ በአገርህ ስደተኛ ጣቢያ ገብተህ የአፈናቃይህን ስንዴና እጅ መጠበቅ አይደለም፤ የሚያድንህ ክንድህ ብቻ ነው !! ድል ለአማራ !! #AmharaStruggle #Justice4Amhara #AmharaGenocide

ሰሞኑን ስልክ እየከፈቱ ናቸው፤ በሁሉም ቦታ ለሁለት ወይም ለሶስት ቀን ይከፍታሉ፡፡ አላማቸው በፋኖውች እና በህዝብ፣ በህዝብ እና በህዝብ መካከል የሚካሄደውን ልውውጥ መሰረት አድርጎ የመጨረሻ ላሉት ዘመቻ "ማፕ"ለመስራት ነው፡፡ ስለዚህ ስልክ ፋኖውች በተለይ ስልክ መጠቀም ማቆም፡፡ ህዝቡም ሴንሲቲቨ የሆነ፣ ትግልን እና ፋኖን የተመለከቱ ቃላትን በንግግሩ እንዳይጠቀም፡፡ ከተራ ንግግሮች ውጭ ምንም የረባ ነገር እንዳያወራ፡፡ ምን ያህል ታማኝ ነው የሚለው እንዳለ ሆኖ የሚከተለው መልእክት የተወሰነ ትርጉም አለው፡፡ ስለዚህ መጠንቀቁ ይበጃል፡፡ ጽሁፉ እንደወረደ ነው፡፡ ቢጣራም ባይጣራም መልእክቱ ጠቃሚነት ስላለው ነው ሼር ያደረግኩት፡፡ <<በዚህ ሳምንት ዉስጥ በመላዉ አማራ ዳታና ሙለ የስልክ አገልግሎት ለ 1 ቀን ወይም 2 ቀን በመላዉ አማራ ይለቀቃል  ምክንያቱም 1ኛ የፋኖ አባላት ያሉበትን ቦታ ጂፒs አክሰስ ለማድረግ ወዲያኑ ስልክ እንደተለቀቀ ስልክ ያላቸዉ የፋኖ አባላት በተለይም የፋኖ አመራሮች የመረጃ ልዉዉጥ ይጀምራሉ የትግል ስትራቴጂ ይለዋወጣሉ ቤተሰብ ደዉለዉ ይጠይቃሉ በዚህ ኮሚኒኬሽን ፋኖዎች የት ቦታ እንዳሉ የጂፒs አክሰሱ ሬጅስተር ይደረጋል ስለዚህ አማራ ክልል ላይ የት ቦታ ላይ ፋኖ እንደተቀመጠ ለማወቅ ስለተቸገረ ዳታዉ የግዴታ አስፈላጊ ስለሆነ ከተቻለ በ 1 ቀን ካልሆነ  ግንበ 2 ቀን ዳታዉን ሰብስቦ ለመጨረስ መሳሪያ ተገጥሞ ዳታ ሚሰበስቡ ሰዎች ሰልጥነዉ ላብራቶሪዉ ሴት አፕ(ተዘጋጅቶ)  እየተጠባበቁ ነዉ ለሙከራ ዛሬ ለ 30 ደቂቃ ሙሉ የስልክ አገልግሎት ተለቆ ነበር አማራ ክልል ላይ የተዘጋጀዉ ላብራቶሪ በትክክል እየሰራ መሆኑን ለማረጋገጥ 2ኛዉ የተቀረፁ ቪዲዮዎዎች በተለይ መከላከያ ጭካኔ የተሞላበት ግድያ ሲፈፅም የተቀረፁ ቪዲዮዎች በማህበራዊ ሚዲያ እንዲለቀቁ #ምክንያቱም ወዲያዉ ዳታ እንደመጣ ቪዲዮ የቀረፁ ሰዎች ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ሲለቁት የመከላከያ የበላይነት መምጣት ሚችለዉ ጭካኔዉ በህብረተሰቡ ዘንድ ሳይኮሎጂ ተፅኖ ሲፈጥር ነዉ ተብሎ ስለታሰበ የተቀረፁት ቪዲዮዎዎች ሚለቀቁበት ምክንያት እኛ ያንን ስናይ እዲሰቀጥጠን እና እንድንፈራ ሳይኮሎጂካሊ የተሸናፊነት ስሜት ኖሮን እንደዚህ በጭካኔ ከምንገደል እንደበቅ ይቅርብን ብለን ሳይኮሎጂካሊ የተሸናፊነት ስሜት እንዲኖረን ለማድረግ ነዉ 3ኛዉ ከዉጪ ያለዉ ዲያስፖራ እየደወለ ያለዉን የመልእክት ልዉዉጥ ለመጥለፍ ነዉ ዳታ ሲለቀቅ ቤተሰብ ጋርም ሆነ የፋኖ አባላት ጋ እየደወሉ ስለፋኖዎች ሚወራዉን መረጃ ለመጥለፍ ታቅዶ ነዉ>>

የጠለምት አማራ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ሰብሳቢ መምህር ፀጋዬ እሸቴ የጠለምት ጉዳይ ለሕዝበ ውሳኔ እንዲቀርብ ተስማማ የማትስማማ ከሆነ እርምጃ ይወስድብሃል መባሉን ከቅርብ ሰዎች ማረጋገጥ ተችሏል። ይ
የጠለምት አማራ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ሰብሳቢ መምህር ፀጋዬ እሸቴ የጠለምት ጉዳይ ለሕዝበ ውሳኔ እንዲቀርብ ተስማማ የማትስማማ ከሆነ እርምጃ ይወስድብሃል መባሉን ከቅርብ ሰዎች ማረጋገጥ ተችሏል። ይህ ማስጠንቀቂያ የተሰጠው በሰሜን ጎንደር አስተደደር ዲያቆን ሸጋው ውቤ አዛገ በኩል ነው። ፀጋዬ "የጠለምት ሕዝብ ማንነት ለሕዝበ ውሳኔ አይቀርብም" በማለት ባሕርዳር ስብሰባ ረግጦ መውጣቱ ይታወሳል። ፀጋዬ ብልጽግና የጠለምትን ሕዝብ አሳልፎ የሚሰጠው ከሆነ ሕዝብ የራሱን እርምጃ እንዲወስድ ጥሪ ማቅረቡን ተከትሎ አዳርቃይ በመከላከያ ካምፕ ታስሮ እየተሰቃዬ ይገኛል። ከሁለት ቀናት በፊት ወደ ደባርቅ አምጥተው ለፌደሬሽኑ በሕዝብ ውሳኔው ተስማምቻለሁ ብለህ ፈርም ተብሎ የቀረበለትን ጥያቄ አልቀበልም በማለቱ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶት በቀዝቃዛ ክፍል ታስሮ ይገኛል። ህዝብ ያሸንፋል! /ምስጋናው ዘ ግዮን/

በአዊ ዞን ባንጃ ወረዳ 6 ህፃናትን ጨምሮ 21 ንፁሃን በገዳዩ የብልፅግና ሰራዊት ተጨፍጭፈዋል። አገውና አማራ የማይነጣጠል እጣ ፈንታ አለው፤ ደስታችንም ሆነ መከራችን የጋራችን ነው። ይህንን ሃቅ በመሸሽ የአብይ አህመድ ወታደሮች ጎጃም ውስጥ አዊ ዞንን እንደምሽግ እንዲጠቀሙ ያመቻቹት እንዲሁም ሚሊሺያ መልምለው ያሠማሩ ከሃዲ ካድሬዎች የእጃቸውን ያገኛሉ። አማራ ያሸንፋል!!

Who would have thought in less than two years Abiy Ahmed Ali would have sent more people to their death than Mengistu, Meles and Emperor Haile Selassie combined: 1 million deaths and counting -Millions displaced - 25+ billion in destruction including the largest social infrastructure destructions in the #Amhara region. Š Dawit