en
Feedback
Ethio monitor

Ethio monitor

Open in Telegram
1 482
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
የጥቅምት 30 ነገር..... ኦህዴድ እስከ ጥቅምት 30 ፋኖን አጥፍቶ ክልሉን ለብአዴን ለማስረከብ ቃል ገብቶ የነበረ ቢሆንም እቅዱን ማሳካት አልቻለም። እንዲያውም ሽንፈቱን መቋቋም ተስኖት በድሮን ንፁሃንን በአውቶቡስ መናሃሪያ ላይ ሳይቀር ሲጨፈጭፍ ታይቷል። የብልጽግና ሰራዊት ከእቅዱ ማሳካት የቻለው 15% ብቻ መሆኑን እወቁልኝ ብሏል። ለመሆኑ 15% ስኬት የተባለው የትኛው ይሆን? ብርሃኑ ጁላ ስኬት ብሎ ያቀረባቸው:- 1. የፋኖ ስልጠና ማስተጓጎል 2. የፋኖ ስንቅ ማውደም ( የገበሬ ሰብል በማቃጠል መሆኑን ልብ ይሏል) 3. የፋኖ ግንኙነቶችን ማስተጓጎል በግምገማቸው ዘመቻው ያልተሳካባቸው ምክንያቶች ተብለው የቀረቡት:- 1. የጠላትን አከርካሪ አለማወቅ 2. በጠላት ወጥመድ መውደቅ 3. በከፊል መቆረጥ 4. አሳሳች መረጃዎች 5. አውራ መንገዶች በጠላት መያዝ 6. በሰራዊቱ ውስጥ እየሰፋ የመጣው የብሄር ክፍፍል 7.የአመራር መማረክ 8. የቁጥር ብልጫን በአግባቡ አለመጠቀም 9. የመንገድ መሪዎች መሠዋት እና መሠወር 10. ከባድ መሳሪያ መማረክ እና ውድመት 11. ከመልክዓ ምድሩ ጋር በቶሎ አለመላመድ ጥቅምት 30 በዚህ መንገድ ተቋጭቷል። መቼም ቢሆን በፋሽስቶች ፍላጎት እና እቅድ መሠረት የሚሳካ ዘመቻ አይኖርም። ማሠብ የተሳነው የብአዴን ግሪሳ ይሄንን መርዶ ሰምቶ በመግለጫ ሲንጫጫ የዋለው ለዚሁ ነው። የብአዴኖች ተገደልን፣ ተጠላን..... ወዘተ የሚል መግለጫቸው ለወደፊቱ እቅዳቸው መንደርደሪያ ሊሆን እንደሚችል ግምቱ አለ። በእርግጥ የወደፊቱ እቅዳቸው ደርሶን የወገን ሃይሎች እየመከሩበት ነው። በድሮን፣ በከባድ መሳሪያ፣ በሚዲያ ሽብር በመፍጠር ሊያሸንፉ የሚፈልጉ ገልቱ ፍጥረታት መቼም አይሳካላቸውም። ህዝብ ያሸንፋል!

#Inbox Indiscriminate killings taking place in Quarit, west Gojjam. በማይካድራ ከተጨፈጨፈው አማራ በላይ በድሮን፣ በመድፍ፣ በሮኬት ጎጃም እየተጨፈጨፈ ነው። ጎጃም ላይ አስቀቃቂ የጅምላ እልቂት እየተፈፀመ ነው። በቀን በቀን ቢያንስ ከ6 በላይ የድሮን ጭፍጨፋ እየተካሄደ ነው።

የተመረጡ 10 መረጃዎች 1. በአንኮበር 2 ቦታዎች ላይ በተጣለ ደፈጣ የብልጽግና ሰራዊት ከፍተኛ ጉዳት አስተናግዷል። ከ3 ቀናት በፊት በድሮን ጥቃት ለተገደሉ መምህራን እና ንፁሃን መታሰቢያ የተፈፀመ ኦፕሬሽን ሲሆን በበርካታ ተሽከርካሪዎች ሲጓዝ የነበረው ሰራዊት ሙትና ቁስለኛ ሆኗል። 2. ክምር ድንጋይ ላይ በብልፅግና ሰራዊት ካምፕ ውስጥ በተፈፀመ የቦንብ ጥቃት በርካታ የሰራዊቱ አባላት ተደምስሰዋል። 3. በደሴ ከተማ መግቢያ /መውጫ ሁለት ቦታዎች ላይ በተጣለ የደፈጣ ጥቃት በተሽከርካሪ ሲጓዙ የነበሩ የስርዓቱ ወታደሮች ሙትና ቁስለኛ ሆነዋል። ከሆስፒታል ምንጮች በተገኘው መረጃ መሠረት 32 ቁስለኞች ሲኖሩ የሟቾቹን ቁጥር ማረጋገጥ አልተቻለም። 4. አዘዞ ከተማ በተፈፀመ ጥቃት የከማው የፀጥታ አመራሮች እና የፖሊስ አባላት ተወግደዋል። 5. ጅጋ አቅራቢያ በተጣለ ደፈጣ በጉዞ ላይ የነበረ የስርዓቱ ኮንቮይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበታል። 6. ውጫሌ በድጋሚ በፋኖ እጅ ገብታለች። 7. ከጃማ ደጎሎ እስከ መሬ ባለው ቀጠና የስርዓቱ ወታደር እየተመታ የፋኖ ሃይሎች ይዞታቸውን እያጠናከሩ ይገኛሉ። 8. ኩታበር አቅራቢያ በተጠመዱ መድፎች የ አምባሰል ከፍተኛ ቦታዎች እየተደበደቡ ይገኛሉ። 9.. ዋበር የህዝብ መናሃሪያ ላይ በተፈፀመ የድሮን ጥቃት በርካታ ንፁሃን ተጨፍጭፈዋል። 10. ጎንደር ከተማ ዙሪያ በሁለት ግንባር ውጊያ ተቀስቅሷል።

10 የተመረጡ የዛሬ መረጃዎች  ከምስጋናው 📍 1. ታሪካዊቷ እና የድንቅ ቅርሶች መገኛ የሆነችው ላሊበላ ከተማ በፋኖ ቁጥጥር ውስጥ ገብታለች፤ እስር ቤቱ ተሰብሮ ያለጥፋታቸው ሲሰቃዩ የነበሩ የኮማንድ ፖስቱ ታጋቾች ተለቀዋል።  የአውሮፕላን በረራዎች ተቋርጠዋል። 2. በተመሳሳይ በሌላኛዋ ታሪካዊ ከተማ መርጡለማርያም አቅራቢያ በነበረ ውጊያ የብልፅግና ሰራዊት ክፉኛ ሲመታ ከተማዋን ለማቃጠል የነዳጅ ማደያዎችን በከባድ መሳሪያ ደብድቧል።  ሆኖም በፈጣሪ ጥበቃ ቃጠሎ ሳይነሳ ቀርቷል። 3. ከለላ ከተማ ውስጥ ፋኖን ለማጥቃት በአዳራሽ ውስጥ ምክክር ላይ በነበሩ የመንግስት ሃይሎች ላይ ነበልባሎቹ ከበባ ፈፅመው ደምስሰዋቸዋል። ከተማዋ አሁን በፋኖ እጅ ነች፣ በዚህ ሰዓት መኩ-city boy ከሩቅ ሆኖ ከባድ መሳሪያ እያስወነጨፈ ይገኛል። 4. ድጎ ፅዬን ከተማ ከሞጣ አካባቢ በሚተኮስ BM ሮኬት ቀኑን ሙሉ ስትደበደብ ውላለች። በዚሁ አካባቢ በተጣለ የደፈጣ ጥቃት የብልጽግና ሰራዊት ጉዳት አስተናግዷል። 5.ደጋ ዳሞት ለመግባት በሁለት አቅጣጫ እየተካሄደ ያለው ውጊያ 4ኛ ቀኑን ይዟል። በዚህ ግንባር የፋኖ ጦር በርካታ የሰራዊቱ አባላትን ለመማረክ ችሏል። 6. ሸዋሮቢት ከተማ በተጣለ ደፈጣ በፓትሮል የሚንቀሳቀሱ እና ኬላ ላይ የነበሩ የአገዛዙ ወታደሮች ተወግደዋል። 7. አይምባ እና ጫንድባ የፋኖ ሃይሎች ከተሞችን ይዘዋል። ጫንድባ በነበረ ውጊያ የአገዛዙ ሰራዊት ክፉኛ ተቀጥቅጧል። 8. መካነየሱስ ከተማ በነበረው የብልጽግና ሰራዊት ላይ የፋኖ ሃይሎች ጥቃት አድርሰዋል። 9. ቋሪት ለመግባት በሁለት ግንባር የተከፈተው ውጊያ በፋኖ ሃይሎች ተገትቷል። 10. የብልጽግና አመራሮችን አጅቦ በሚጓዝ የብልጽግና ሰራዊት ላይ ዳንግላ አካባቢ በተጣለ የደፈጣ ጥቃት ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል።

የአማራ ህዝብ ይህንን ስርዐት ማሸነፍ አለበት! ይህ ስርዓት ለተጨማሪ አንድና ሁለት ወራት በቆየ ቁጥር የአማራ ህዝብ ላይ መጠነሰፊ ጥፋት እንዲሆን ፈቀድን ማለት ነው። የሚያፈገፍግ አማራ ካለ አስቀድ
የአማራ ህዝብ ይህንን ስርዐት ማሸነፍ አለበት! ይህ ስርዓት ለተጨማሪ አንድና ሁለት ወራት በቆየ ቁጥር የአማራ ህዝብ ላይ መጠነሰፊ ጥፋት እንዲሆን ፈቀድን ማለት ነው። የሚያፈገፍግ አማራ ካለ አስቀድሞ ራሱንና አማራነቱን መካድ ይኖርበታል!

ደራ 😥 * 3 አብያተ ክርስቲያናት ተቃጥለዋል * ከ10 በላይ ካህናት ተገለዋል በሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሀገረ ስብከት በሚገኘው ደራ ወረዳ በታጠቁ ኃይሎች በደረሰ ጥቃት * 3 አብያተ ክርስቲያናት መቃጠላቸው እና * ከ10 በላይ አገልጋይ ካህናት መገደላቸው ተገልጿል። በምእመናን ላይ እየደረሰ ያለው ግድያ እንደቀጠለ ገልጸው በደራ ወረዳ ሕገ ወጥ ታጣቂዎቹ ባደረሱት ጥያት ከ400 በላይ የኦርቶዶክሳውያን ቤቶች መቃጠላቸውም ነው የተገለጸው። ታጣቂዎቹ ባደረሱት ጥቃት ከ8 ወረዳዎች በላይ የሚሆኑ የሚሆኑ በርካታ ዜጎች ከአካባቢያቸው ተሰደው ወደ አጎራባች ከተሞች እንደሚገኙ ፤ በከተማው የሚገኙ ኦርቶዶክሳውያንን ደግሞ አግተው ገንዘብ እየጠየቁ መሆኑም ተመላክቷል። ችግሩን ለመፍታት የሚመለከተው አካል ምንም አይነት ጥረት እያደረገ ባለመሆኑ የምእመናኑ የመኖር ህልውና በአደጋ ውስጥ እንደሚገኝ ለከባድ እንግልትም መዳረጋቸው ነው የተገለጸው። በሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሀገረ ስብከት በሚገኘው ደራ ወረዳ በታጠቁ ኃይሎች ኦርቶዶክሳውያን ላይ ተኮር በሆነ መልኩ በተፈጸመው ጥቃት በተለይም በገጠሩ ክፍል የሚገኙ አብዛኞቹ አብያተክርስቲያናት መዘጋጀታቸውን እና በደረሰው ጉዳት ቤተክርስቲያን አገልግሎት መስጠት መቆሙም ተገልጿል ሲል ማኅበረ ቅዱሳን ዘግቧል።

የሁለቱ ወንድሞቼ መልእክት ከዐቢይ አህመድ ማጎሪያ ደርሶኛል። "በድሮን ጥቃት የአንደ አመት ከሰባት ወር ልጅ መሞቷን ስሰማ ለአማራ ህዝብ አይደለም መታስር ብሞትለት ብዬ ተመኘው የአማራ አንገቱ አንድ
+1
የሁለቱ ወንድሞቼ መልእክት ከዐቢይ አህመድ ማጎሪያ ደርሶኛል። "በድሮን ጥቃት የአንደ አመት ከሰባት ወር ልጅ መሞቷን ስሰማ ለአማራ ህዝብ አይደለም መታስር ብሞትለት ብዬ ተመኘው የአማራ አንገቱ አንድ ነው!" ዳዊት በጋሻው * "ከዚህ በፊት ከኢሳት በአማራ ጉዳይ ተባርሬ እና ተከስሼ ነበር ፍርድ ቤት ነፃ ነህ ብሎኝ ከነካሳው አሸነፍኩ! በኬሚሴ ጉዳይም ታፍኜ ተጥያለሁ በኋላም ከጓዶቼ ጋር ለወራት ታስሬ ነፃ ተብያለሁ! አሁንም እውነትን እስከያዝን ድረስ ነፃ እንወጣለን በርግጥ እኛ የጮህንለት እና የታሰርንበትን ትግል ከእኛ አልፎ ህዝቡ ተቀብሎታል ትግሉ የህዝብ ስለሆነ እንኳን መታሰር መሞትንም በፀጋ እንቀበለዋለን ትግላችን ተፋፍሞ ከዜሮ ስለጀመረ እናሸንፋለን የአማራ አንድ መሆን እንደታሰርን እንዳይሰማን አድርጎናል" ጎበዜ ሲሳይ (ከቃሊቲ እስር ቤት)

Ethiopia: Statement by High Representative Josep Borrell on the situation in Amhara "The EU expresses serious concern regardi
Ethiopia: Statement by High Representative Josep Borrell on the situation in Amhara "The EU expresses serious concern regarding the on-going conflict, alleged violations and abuses of human rights, and reports of dozens of civilian casualties in the Amhara region of Ethiopia.  Large-scale detentions, notably since the proclamation of a State of Emergency are being reported. The EU joins the African Union, the Ethiopian Human Rights Commission and the Ethiopian National Dialogue Commission in calling for the protection of civilians, for a cessation of hostilities and for a dialogue between the parties. "

photo content

የማኀበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ጥሪ (ጥቅምት 20 እና 21) 1- "እኔም ዐማራ ነኝ!" 2- "ስለ ፍትሕ እንጮኸለን!" በእነዚህ ሁለት ቀናት:- ከአዲስ አበባ እስከ ፌደራል ፖሊስ፣ ከመከላከያ ካምፕ እስከ
የማኀበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ጥሪ (ጥቅምት 20 እና 21) 1- "እኔም ዐማራ ነኝ!" 2- "ስለ ፍትሕ እንጮኸለን!" በእነዚህ ሁለት ቀናት:- ከአዲስ አበባ እስከ ፌደራል ፖሊስ፣ ከመከላከያ ካምፕ እስከ ማይታወቁ ማጎሪያዎች፣ ከቂሊንጦ እስከ ቃሊቲ፣ ከአዋሽ አርባ እስከ አፋር በረሃ፣ ከዐማራ ክልል እስከ መላው ኢትዮጵያ ድረስ በሚዘረዘሩ ቦታዎች ዐማራ በመሆናቸው ብቻ ተቆልፎባቸው እየተሰቃዩ ያሉ ወገኖቻችን አንድም በአስቸኳይ እንዲፈቱ፤ ሁለትም ከጎናቸው እንዳለን ለማስታወስ ስንል የምናካሄደውን የማኀበራዊ ዘመቻ እንድትቀላቀሉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። ዘመቻው ሁሉንም የማኀበራዊ ድረ-ገፆችን ጨምሮ፣ የአገር ውስጥ እና የውጪ ሚዲያዎችን ያካትታል። በምስል፣ በድምጽ፣ በካርቶን ስእሎችና ቪዲዮዎች የተደገፈ ይሆናል። ማንም ሰው የዘመቻውን ዋና አላማ ከግብ የሚያደርስ የራሱን ፈጠራ ሊጠቀም ይችላል። አስታውሱ ዘመቻው የፊታችን ማክሰኞ እና እሮብ የሚካሄድ ሲሆን፤ የመጀመሪያው ቀን ማክሰኞ ጥቅምት 20 መሪ ቃሉ:- "እኔም ዐማራ ነኝ" የሚል ነው። የሁለተኛው ቀን ጥቅምት 21 መሪ ቃል ደግሞ "ስለ ፍትሕ እጮኸለው" የሚል ይሆናል።

በአዋሳ ኢንደሥትሪ ፓርክ ለወራት ሲመረት የነበረው 156,000 የመከላከያ ዮኒፎርም በሁለት ካርጎ አውሮፕላን ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ ውሏል፡፡ ከዚህ ውሥጥ 25ሺህ የአማራ ልዩ ኃይልና 25,000 የኤርትራ መከላከያ የደንብ ልብሥም ተመርቶ አብሮ መጫኑን አረጋግጠናል፡፡

~ ጥብቅ ማሳሰቢያ ! የተለያዩ ሚዲያዎች ባለቤቶችና ጋዜጠኞች ሆናችሁ በየቀኑ እና በየሠዓቱ ወደ ፋኖ አመራሮች በመደወል በሚዲያ የምትለቁ ወገኖች ከድርጊታችሁ እንድትቆጠቡ አሳስባለሁ። "ለትግሉ ቅርበት ያለንና የምንመራው እኛው ነን" ለማለት አስባችሁ ከሆነም ትግል በ commentator የሚመራ የእግር ኳስ ጨዋታ እንዳልሆነ ልብ ልትሉት ይገባል። የተገኘው መረጃ እና ድምፅ ሁሉ አይለቀቅም። ትላንት አንድ የፋኖ ከፍተኛ አመራር ላይ በኮሜንታተሮች ተደጋጋሚ ስልክ ምክንያት ለጥቂት ከአደጋ ተርፏል። የፋኖ አዛዦች በየቀኑ በሚዲያ የመቅረብ ግዴታ የለባቸውም። እባካችሁ የፕሮግራም ማሟያ አታድርጓቸው። የሠው ሀይል አሠላለፍን፣ ወትሮ ዝግጁነትንና እቅድን በየቀኑ በሚዲያ ይፋ እያደረጉና ለወዳጅም ለጠላትም እያሳወቁ ለድል የሚበቃ ትግል የለም። ለፋኖ አመራሮችም በቂ ግንዛቤ ማስጨበጫና ጠርናፊ መመሪያ የሚሠጥ ሲሆን በገንዘብም ሆነ በተለያዩ ጥቅማጥቅሞች በማታለልና ፊተኛ ታጋዮች  እንደሆናችሁ ለማሳየት ሌት ከቀን የፋኖ አመራሮችን በሚዲያ የምታቀርቡ ግለሠቦች ከድርጊታችሁ ታቀቡ። አይጠቅምም! የሚዲያ ሚናው ሌላ ነው! ፋኖ ድል ያደርጋል!!

የደመቀ መኮነን ደላላዎች ድጋሚ ስምሪት መውጣታቸው እየተነገረ ነው። ደመቀ አደገኛ የአማራ ትግል "spoiler" ነው፤ አብን የምትባለዋን ፓርቲ በምስር ወጥ ከገዟት በኋላ እረፍት ላይ የነበሩት ደላላዎች አሁንም ለሌላ ተልዕኮ ወጥተዋል። ለዚህም አንድ በፖለቲካ ድለላ የተካነ ሰው ለይስሙላ ከአንድ ወር በላይ አስረው አቆይተው ከሁለት ቀን በፊት ምሽት ከእስር በመውጣት በቀጥታ ወደ DC እንዲበር ሆኗል ( ከእስር ቤት በቀጥታ ወደቦሌ ኤርፓርት የተሸኘ)። ብአዴን ከመቸውም በላይ የአማራውን ትግል ለማኮላሸት እና የፋኖን እንቅስቃሴ ለማጥፋት ላለፉት 2 ዓመታት ከፍተኛ እንቅስቃሴ አድርጓል። ለገሚሡ እርሻ መሬት፣ ለውስኑ የከተማ ቦታ፣ ለአብዛኛው እስርና ግድያ እየሸለሙ ትግሉን ለማክሰም ብዙ ደክመዋል። ይህንን ተቋቁመው በጉርሻም በምልጃም የማይንበረከኩ እሩቅ አልመው የሚጓዙ ሺዎች ተፈጠሩና ብአዴኖችም ተሽመደመዱ! በዚህ ሂደት የፋኖ ትልቁ ስኬት ህዝቡን የትግሉ ባለቤት ማድረጉ ነው። የአማራ ህዝብ ሁሌ ትግሉን እየተዘረፈ የዳር ተመልካች የሆነባቸው አጋጣሚዎች ብዙ ናቸው። ከመሬት ለአራሹ ጀምሮ የነበሩ የፖለቲካ እንቅስቃሴዎችን መመልከት ይቻላል። የቅርቦቹን ብናይ እንኳ ግንቦት 7፤ ኦሮማራ (ኦህዴድ) ፣ አብን የአማራውን ትግል በመዝረፍ የቡድን እና የግል ስልጣን መወጣጫ አድርገውታል። ህዝቡ ጭቆናውን ታቅፎ ቀረ፣ ሌላው ይቅርና በትግሉ የሞቱ፣ የቆሰሉ አስታዋሽ አልነበራቸውም። ዛሬ ያ እንዲሆን እድል አንሰጣቸውም! በአንድ ሰው ትክሻ ሳይሆን በሁሉም አማራ ትክሻ ላይ ያረፈ ትግል በመሆኑ ከመሪዎቹ አንዱ ዝንፍ ቢል ሌላው እንዲያቃናው ሆኖ ዲዛይን የተደረገ የትግል ስልት ነው። ብአዴን መሬት ላይ ክፍተት ሲያጣ ወደ ሚዲያዎች ዞሯል። በተለይም የአማራውን ትግል የሚደግፉ የሚባሉትን ሚዲያዎች ኢላማ ያደረገ እንቅስቃሴ መኖሩን ሰምተናል። ስለሆነም Ethio 360 እና ተመሳሳይ የመረጃ ሰጭ ሚዲያዎች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አደራ እንላለን። በዚህ የትግል ሂደት የሚሠራ ስህተት በቀላሉ ላይጠገን ይችላል። የሚዲያ ሰዎችም ትግሉን በተመለከተ መሬት ላይ ካሉት መሪዎች አቅጣጫ በመቀበል በማስተዋል መጓዝና የግል ፍላጎትን ገታ በማድረግ መንቀሳቀስ አለባቸው። ብአዴን አይሳካለትም! ፋኖ ድሉን ያስቀጥላል!

ፋኖነትን ከአባቱ የወረሰው የጎቤ ዋዋ ልጅ ፋኖ እሱባለሁ ጎቤ ‼
ፋኖነትን ከአባቱ የወረሰው የጎቤ ዋዋ ልጅ ፋኖ እሱባለሁ ጎቤ  ‼

ሰላማዊ ዜጎችን እያገተ፤ ማስለቀቂያ ከ500 ሺህ እስከ 2 ሚሊዮን ብር በመጠየቅ የሚታወቀው የእነ ሽመልስ አብዲሳው ቅምጥል ኦነግ ሸኔ የሚባለው ቡድን ነበር። በተመሳሳይ የአገዛዙ ሰራዊት "እኔስ ለምን ይቅርብኝ" በሚል በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ስም ሰላማዊ ዜጎችን በጅምላ እያፈሰ በማሰር ማስለቀቂያ 200 ሺህ ብር ድረስ እየተቀበለ ይገኛል። በደብረ ማርቆስ ከተማ ይኽ ዐይን ያወጣ ዝርፊያ እየተፈጸመ ይገኛል። 100 ሺህ ብር ከፍሎ የተፈታ ሰላማዊ ዜጋ አለ፤ 200 ሺህ ብር ክፈል ተብሎ የሚከፍለው ብር አጥቶ ለብድር የተዳረገ ገበሬ አለ። 10 ሺህ ብር እና 8 ሺህ ብር ተጠይቀው፤ የተጠየቁትን ከፍለው ከእስር ያልተለቀቁ ሰላማዊ ዜጎችም አሉ። በተመሳሳይ ላሊበላ አካባቢ ለገበያ የመጡ ገበሬዎችን፣ የከተማዋ ነጋዴዎችን እና ወጣቶችን እያሠሩ ገንዘብ መቀበል የአብይ አህመድ ሰራዊት ተቀዳሚ ተግባር ሆኗል። እንግዲኽ እነ ጀነራል አበባው ታደሰ ይኽን ሠራዊት ነው "ዓላማው ሕዝብን ለመጠበቅ ነው" የሚሉት!? ለዚኽ ሰራዊት ነው "የድጋፍ ሰልፍ" ያስፈልገዋል የሚሉት!?

ምስራቅ አማራ ፋኖ ከድልብ እስከ ጎብዬ ውሎ! ዛሬ ማለትም ጥቅምት 13 ቀን 2016 በጎብዬ ዱር ለበስ በመንጀሎ የገጠመው ፋሽታዊ ቡድን ተመትቷል። እስረኞችን ይዛ የነበረች መኪና ከነ ሰራዊቷም ተማር
ምስራቅ አማራ ፋኖ ከድልብ እስከ ጎብዬ ውሎ! ዛሬ ማለትም ጥቅምት 13 ቀን 2016 በጎብዬ ዱር ለበስ በመንጀሎ የገጠመው ፋሽታዊ ቡድን ተመትቷል። እስረኞችን ይዛ የነበረች መኪና ከነ ሰራዊቷም ተማርካለች። #አሁንም ዶሮ ግብር ላይ ከፍተኛ ትግል እየተደረገ ሲሆን የዶሮ ግብር ከተማን ፋኖ ከቧታል። #ድልብን ሊሻገር የሞከረው ፋሽት በደፈጣ ከነሙሉ መኪናው ተረክበውታል። #ሰሜን ወሎ ሙሉ ደጋውን ክፍልም ምስራቅ አማራ ፋኖ ተቆጣጥሮታል። ምስራቅ አማራ ፋኖ ከወትሮው በተለዬ ትሥሥር ፈጥሮ ትግል እያደረገ ይገኛል። ምስራቅ አማራ ፋኖ!

"የት ሂጄ ልጄን ላሳድግ? መቃወም አልችልም…መደገፍም አልችልም… ዝም ማለትም አልችልም። ምን አይነት ሙዚቃ ልስራ? ስለምን ልዝፈን? ከዛሬ ነገ ምን ይፈጠር ይሆን እያልን አለን። ሁሉም ሰው ተፈራርቶ
"የት ሂጄ ልጄን ላሳድግ? መቃወም አልችልም…መደገፍም አልችልም… ዝም ማለትም አልችልም። ምን አይነት ሙዚቃ ልስራ? ስለምን ልዝፈን? ከዛሬ ነገ ምን ይፈጠር ይሆን እያልን አለን። ሁሉም ሰው ተፈራርቶ ነው ያለው። ሁሉም ሰው ኑሮ ከብዶታል። እባካችሁ ተውን!!" /አቀናባሪው ሚኪ ጃኖ በኢቢኤስ ቅዳሜ ከሰአት የሻይ ሰአት ላይ የተናገው/

አገር ጠባቂ ተብሎ ተጨፍጭፎ በእርስበርስ ጦርነት ያለቀው የሠራዊት አባል የትየለሌ ነው። ያ ሁሉ ሠራዊት እንዲያልቅ ያደረጉት አካላት በፌሽታና የፍቅር ዘፈን ተቃቅፈዋል። የድሃ ልጅ የሆነው ሠራዊት ግ
+2
አገር ጠባቂ ተብሎ ተጨፍጭፎ በእርስበርስ ጦርነት ያለቀው የሠራዊት አባል የትየለሌ ነው። ያ ሁሉ ሠራዊት እንዲያልቅ ያደረጉት አካላት በፌሽታና የፍቅር ዘፈን ተቃቅፈዋል። የድሃ ልጅ የሆነው ሠራዊት ግን በየጎራው ወድቆ ቀረ። በዚያ ክፉ ወቅት ከጎኑ የነበረው የአማራው ሕዝብ ለሠራዊቱ አለኝታ ነበር። ዛሬ ግን ያው ሠራዊት ያጎረሱ እጆችን እንዲነክስ የክፉ ገዢዎችን አላማ ይዞ ግፍ እየፈፀመ ነው። ፍትሐዊው አማራ ያሸንፋል ‼ ድል ለአማራ ‼ #AmharaRevolution

ብልፅግና ቆላ ወርዶ፣ ደጋ ወጥቶ ፋኖ ላይ ወንጀል ቢፈልግም አልተሳካለትም። አሁን ደግሞ ባንኮችን "እባካችሁ ተዘረፍን በሉ" አይነት ጥያቄ ጠይቋቸዋል። የ6 ባንኮን ምላሽ የማየት ዕድሉ ነበረኝ፤ "ም
ብልፅግና ቆላ ወርዶ፣ ደጋ ወጥቶ ፋኖ ላይ ወንጀል ቢፈልግም አልተሳካለትም። አሁን ደግሞ ባንኮችን "እባካችሁ ተዘረፍን በሉ" አይነት ጥያቄ ጠይቋቸዋል። የ6 ባንኮን ምላሽ የማየት ዕድሉ ነበረኝ፤ "ምንም ዓይነት ጉዳት አልደረሰብንም" የሚል ምላሽ ሰጥተዋል። የሌሎችም ከዚህ የተለየ ሊሆን አይችልም። ኦሮሚያ ላይ ሁሉም ባንኮች ዘረፋ ተፈፅሞባቸው እስካሁን ለማጣራት አልተሞከረም። ባንኮችም ምርመራ እንዲደረግላቸው ጠይቀው ምላሽ አልተሰጣቸውም። ተረኝነቱ ለጫላ የወንጀል ድርጊት አበበን እስከመጠየቀ የደረሰ ሆኗል። /ምስጋናው ዘ ግዮን/

የአብይ አህመድ ሰራዊት ጦርነቱን ሲጀምር ለማሸነፍ አይደለም፤ አለቆቹም የአማራን ህዝብ ማሸነፍ እንደማይችሉ ጠንቅቀው ያውቁታል። ዋነኛ አላማቸው በቻሉት መጠን ውድመት መፈፀም ነው። ከልክ በላይ ቁሳዊ እና ሰብዓዊ ውድመት በማድረስ ህዝቡን ወደ በሽታ እና ድህነት አዘቅት ማውረድ ተቀዳሚ ስራቸው አድርገዋል። ከሞት የተረፈው ህዝብ እና የተደፈሩ ወገኖቻችን ህክምና እንዳያገኙ ሆስፒታሎች እንዲዘጉ አድርገዋል፤ መድሃኒቶች በወታደሩ እየተዘረፉ እየተጫኑ ይገኛሉ። የሆስፒታል አንቡላንሶች የፋሽስቱ ወታደሮች መጓጓዣ ሆነዋል። በተመሳሳይ ህዝባችንን በረሃብ ለመጨረስ አስቀድመው በዘር ወቅት ማዳበሪያ ከለከሉት፣ አሁን ደግሞ የደረሰ ሰብሉን በከባድ መሳሪያ እያቃጠሉት ይገኛሉ። በጥቅሉ አማራ ክልል የገባው ሰራዊት አጥፍቶ ጠፊ የኦሮሙማ ርዕዮተ ዓለም ተሸካሚ ነው።