en
Feedback
Abu Meryem Neja Lobete Channel(የአቡ መርየም ነጃ ሎበቴ ቻናል)

Abu Meryem Neja Lobete Channel(የአቡ መርየም ነጃ ሎበቴ ቻናል)

Open in Telegram

ተውሒድና ሱና የአንድነት ምንጭ ሲሆኑ፣ ሺርክና ቢድዓ ደግሞ የልዩነት ምንጭ ናቸው። ስለዚህ ተውሒድና ሱና አጥብቀህ ያዝ። ሺርክና ቢድዓ ደግሞ በእጅጉ ራቅ። አላህ ቁርኣንና ሐዲስን በደጋግ ቀደምቶች መንገድ አረዳድ ተረድተው ከሚጓዙ ምርጥ ባሮቹ ያድርገን። ቻናሉን ለሌሎችም ሼር ያድርጉ። ለአስተያየትና ጥቆማ እንዲሁም እርምት 👉 @NejaLobete 👈

Show more
7 585
Subscribers
-224 hours
-347 days
-14230 days
Posts Archive
ነገ ሐሙስ ነው! የቻለ ይፁም! ያልቻለ ሌሎችን ያስታውስ!

እንቁጣጣሽ!! እውነትም እንቁ ነው ጣጣዋ!

አዲስ አመት፣ ዘመን መለወጫ፣ ኢሬቻ፣ ገና፣ መስቀል፣ጥምቀት፣እንቁጣጣሽ እና የመሳሰሉት በዓላት ከሌሎች እምነት ጋር የተያያዙ በዓላት ናቸው። ስለዚህ ሙስሊሞችን በጭራሽ አይመለከታቸውም። የሙስሊሞች በዓላት ሳምንታዊ የጁሙዓ ቀን፣ዒድ አል-ፊጥርና ዒድ አል-አድሗ ብቻና ብቻ ናቸው።ሙስሊሞች ሆይ! ከእነዚህና ከመሳሰሉት ኢስላም ከማያውቃቸው በዓላት መውሊድንም ጨምሮ ተጠንቀቁ!ራቁ     ✒️ወንድማችሁ:- አቡ መርየም የቴሌግራም ቻናል:- http://t.me/AbuMeryemNeja http://t.me/AbuMeryemNeja     

⚠️ አስተውሉ❗️ በቁርአን ውስጥ "ኸሊሉላህ" ተብሎ የተጠራው ነቢይ ማን ነው?

«ያ አላህ! በቻናሌ በማስተላልፈው መልዕክት ባልሰራበት እንኳን ወደ በጎ ወደ መልካም ነገር ያመላከተ ሰው የሚያገኘውን አጅር አታሳጣኝ።»

ብዙዎቻችን ፍፁም ምቹ ሁኔታን እየጠበቅን፣ የምንጀምራቸውን ነገሮች እናዘገያለን። እውነታው ግን፣ ምርጡ የመነሻ ጊዜ አሁን ነው። ትልልቅ ስራዎች የሚገነቡት በትንንሽ፣ ተከታታይ እርምጃዎች ነው። ዛሬውኑ አንድ እርምጃ እንውሰድ!

ኡስታዝ ዛሬ ለመግባት ስላልተመቸኝ ነገ ብሏል።

"በሰሞኑ የሰይዪድ ቁጥብ ጉዳይ ከተመቸኝ ዛሬ ከመግሪብ በኋላ በድምፅ ለመግባት አስቤያለሁ" ብዬ ነበር። አሁን ላይ ስላልቻልኩኝ ከቻልኩ ምሽት 3:00 ላይ በቴሌግራም ቻናሌ ( https://t.me/IbnuMunewor ) በቀጥታ (live) ለማቅረብ እሞክራለሁ ኢንሻ አላህ።

🎉🎉ልዩ የሰርግ ጥሪ!🎉🎉 ~ በአሏህ ፈቃድ በቅርቡ የሰርግ ስነስርዓቴ ላይ እንድትገኙልኝ ስጋብዛችሁ በደስታ ነው። 🗒ቀን: ባታውቁትም ግድ የለም። 🗓ሰዓት: አይመለከታችሁም። አድራሻ: አያገባችሁም። እቤት ቆዩ ባትመጡ ይሻላል¡ ✋ያልኩት እኔ አይደለሁም።ስጀመር እኔ ለእናንተ አልነግራችሁም።እንዴትስ እነግራችኋለሁ! ወሬውን ለእንትና ነግራችኋት ችግር ውስጥ ልታስገቡኝ ሆ!😁 ዐረብ እኮ! አይቀልድ! ለመሆኑ እንዲህ አይነት የሰርግ ጥሪ አጋጥሟችሁ ያውቃል!😁

"አንዳንድ ትግሎች፣ጦርነቶች የሚጀምሩበትና የሚያበቁበት ጊዜና ወቅት አላቸው።ከነፍሲያችን ተንኮልና ከሸይጧን ጉትጎታ ጋር ያለን ትግልና ጦርነት ማብቂያው ግን ይህቺን የዱኒያ ህይወት ተሰናብተን ቀብር ስንገባ ብቻ ነው።!" ✍ወንድማችሁ:-አቡ መርየም የቴሌግራም ቻናል:- http://t.me/AbuMeryemNeja http://t.me/AbuMeryemNeja

وَيْلٌ لِّلْمُطَفِّفِينَ የሚለው አያህ ስለ ምን ያወራል?

👌ማስጠንቀቂያ‼️ ከቅርብ አመታት ወዲህ እስከ ዛሬም ድረስ በአንዳንድ ሩቃ ቤቶች ውስጥ የሚፈፀሙ እጅግ አስደንጋጭና አሳዛኝ ለጆሮ የሚሰቀጥጡ ድርጊቶችን መስማት ከጀመርን ትንሽ ሰንብቷል!! በመጀመሪያ በሲሕር በዐይን-ናስና በተለያዩ በሽታዎች እየተሰቃዩ ያሉ ወንድምና እህቶቻችንን ሁሉ አሏህ ሙሉ ዓፊያ ጤና ይስጣቸው! ሲቀጥል በተለያዩ በበሽታ አይነቶች እንድንታመምም የሚያደርገን ከበሽታዎችም በኋላ ሙሉ ፈውስ ዓፊያ ሊሰጠን የሚችለው አንድ አሏህ ብቻና ብቻ መሆኑን እርግጠኞች በመሆን ሰብር ማድረግ ይኖርብናል።ስለዚህ ጉዳትም ሆነ ጥቅም ሊያመጣ የሚችለው አሏህ ነው።ይህንንም አውቀን ከቻልን ከቻልን እኛው ራሳችን የተለያዩ ሰበቦችን በመጠቀም ተወኩላችንን ተስፋችንን በአሏህ አድርገን ራሳችንን ለማከም መሞከር አለብን።ለምሳሌ:- በተለያዩ ዒባዳዎች ላይ በመንጠከርና በመዘውተር፣የአሏህን ትዕዛዛት በትክክል ለመፈፀም መጣርና በዚሁ እስከ መጨረሻው ቀጥ ለማለት መሞከር፣እንዲሁም የአሏህን ክልክላዎችን አለመዳፈር መራቅና መታቀብ፣የጧትና የማታ አዝካሮችንና ከሰላት በኋላ የሚደረጉ ዚክሮችን ሌሎችንም አዘውትሮ ማለት፣ቁርኣንን ጧትና ማታ አብዝቶ መቅራት፣ዱዓ በማድረግ ላይ በመጠንከርና በመብርታት ኢንሻ አሏህ በአሏህ ፈቃድ በሽታው ከመከሰቱም በፊት በሽታው እንዳይመጣ እንዳይከሰት ሰበብ ማድረስ መከላከልና ከተከሰተም በኋላ በዚህ መንገድ መፈወስ ዓፊያ መሆን ይቻላል። ይህ ካልተቻለና ካልሆነ ግን ታማሚው የግድ ሩቃ ቤት መሄድ ካለበት ወንድ በወንድ ሴት በሴት ሩቃ ወደ ሚደረግበት ሩቃ ቤት መሄድ።ይህም ካልተቻለ ካሉት ሩቃ ቤቶች የተሻሉ ናቸው ስርዓት አላቸው ወደሚባሉት ሩቃ ቤቶች ጠያይቆ ታማሚዋ ሴት ከሆነች ከባሏ ወይም ከወንድሟ ከሌሎችም ለሷ መሕረም ከሚሆን ሰው ጋር መሄድ አለባት።የፈለገ ቢሆን ታማሚዌ ሴት ከሆነች ለብቻዋ ሩቃ ቤት መሄድ የለባትም። ሌላው ከእነዚህ ሩቃ ቤቶች ከሚሰሙና ከሚስተዋሉ ስህተቶችና ጥፋቶች መካከል በጥቂቱ:-ታማሚ ሴቶችን ያለ መሕረም በአንድ ክፍል ውስጥ ለብቻ በመሆን (በኸልዋ)ሩቃ ማድረግ።ከዚህም አልፎ ሰውም ቢኖር ከመጋረጃ ጀርባም ቢሆን ታማሚ ሴቶችን ሰውነታቸውን እየደባበሱ እየነካኩና እየተሻሹ ሩቃ ማድረግ።ከዚህም አልፎ ደግሞ ያለ መጋረጃ ከታማሚ ሴቶች ጋር አንድ ላይ ፊት ለፊት ተቀምጦ አንዳንዴም ወደ ሌላ ወሬ እየገቡ ሩቃ ማድረግ።ከዚህም የባሰው አልፎ ከሩቃው ኬዝ ውጭ የማይገናኝ የሆነ ነገር መጠየቅና ስለ ሌሎች ስለ ግል ጉዳዮች መነጋገርና ወደ ሌላም ተግባር መግባት...ጭራሽ! ታማሚ ሴቶች ላይ መስተፋቅር በማሰራት ባለ ትዳር ከሆኑ ባላቸውን እንዲጠሉና ሩቃ አድራጊዎችን እጅግ እንዲወዱና ከባላቸው ተጣልተው ተለያይተው ትዳራቸውን በትነው ሁልጊዜ እነሱጋ እንዲመላለሱ ማድረግና ከበሽታቸው ፈውስ እናገኛለን ዓፊያ እንሆናለን ብለው የመጡ ታማሚ ሴቶችን የበለጠ ወደ ከፋው ችግር ውስጥ እንዲገቡ በማድረግ ማሰቃየትና ተስፋቸውን ማጨለም።ሌላው ለሩቃው ለህክምናው ከሚያስፈልገው መጠን በላይ የተጋነነ ገንዘብ በመጠየቅ እንደ ቢዝነስ የገቢ ምንጭ አድርጎ በመያዝ ህዝበ-ሙስሊሙን መበዝበዝና መዝረፍ።ከበሽታው የማይገናኝና ከህክምና ባለሞያዎች ዘንድ መድሃኒትነታቸው ያልተረጋገጡ የሆኑ መድሃኒቶችን በመስጠት ለከፋ ጉዳት እንዲጋለጡ ማድረግና ከዚህም አልፎ ለሞት መዳረግ።ይህም ብቻ አይደለም በዚህ መጥፎ ድርጊታቸውንና አካሄዳቸው ምክንያት ሙስሊሞች በህክምና ስም ወደ ሌሎች ሙስሊም ወዳልሆኑ ሰዎች ከበሽታ እንፈውሳለን ባዮች ዘንድ ሄደው ከኢስልምና እንዲወጡና እንዲከፍሩም ሰበብ የሚሆኑበት አጋጣሚ አለ።ብቻ ነገረ ስራቸው ለዚህ ሁሉ የሚዳርግ ድርጊት ነው የሚፈፅሙት። ስለዚህ በእንደዚህ አይነት ሩቃ ቤቶች እንዲህ አይነት በደልና ግፍ የተፈፀመባቸው ወንድሞች በተለይ እህቶቻችን በእነሱ የደረሰው በደል ግፍና ብዝበዛ በሌሎች ወንድምና እህቶች ላይ እንዳይደርስና እንዲጠነቀቁ እንዲህ አይነት ሩቃ ቤቶችን ለህዝበ-ሙስሊሙ ማጋለጥ ይኖርባቸዋል።መጅሊስም በእንዲህ አይነትና መሠል ሩቃ ቤቶች ላይ ተገቢና ለሌሎችም አስተማሪ የሆነ እርምጃ እንዲወሰድባቸው መስራት አለበት ባይ ነኝ። መልዕክቱ ወደ ሌሎችም እንዲደርስ ሼር በማድረግ አድርሱላቸው። ✒️ወንድማችሁ:- አቡ መርየም የቴሌግራም ቻናል:- http://t.me/AbuMeryemNeja http://t.me/AbuMeryemNeja

ኡመቱል-ቁርኣን ተብለን ሳለ አሁን ላይ ኡመቱል👉 internet መሆናችን እጅግ በጣም ያሳዝናል!!

አብሽሩ! ሁሉም ነገር ለኸይር ነው!! አንድ ቀን...

⚠️ አስተውሉ❗️ ከሚከተሉት ነቢያት (الأنبياء) ውስጥ ሱረቱል አንቢያ (سورة الأنبياء) ላይ ስማቸው ያልተጠቀሰው የትኛው ነው?

አሏህ ዱዓችንን ሰምቶ ቶሎ አልመለሰም ብለን ለምን እንጨነቃለን?! እሱ እኮ! በምንሰራው ወንጀል ላይ ቸኩሎ አልቀጣንም!!

ሐራም የሆኑ ግንኙነቶች «ጊዜያዊ ደስታ…. ዘለዓለማዊ ጸጸትና ቁጭት ናቸው።»

«እየተቀጣህ ነው፤ ነገር ግን የተቀጣህ አይመስልህም!»   ✅ ሌሊቱን ሙሉ ነቅተህ እያደርክ፣ የሌሊት ሶላትን (ቂያሙል ለይልን) ከመስገድ ተነፍገሃል፤   ✅ በቂ ትርፍ ጊዜ እያለህ፣ ቁርኣን ማንበብ ተከልክለሃል፤   ✅ አንደበትህ ገርና ተናጋሪ ሆኖ ሳለ፣ አላህን ማውሳት (ዚክር ማድረግ) ተስኖሃል፤   ✅ ዱዓእ ማድረግን ረስተሃል፤ ተነፍገሃል፤ ነፍስህም ወደ አላህ እጅዋን መዘርጋት ከብዷታል፤   ✅ በሶላትህ ውስጥ እርጋታን (ኹሹዕን) አጥተሃል፤   ✅ ብቻህን በሆንክ ጊዜ በሰራኸው ወንጀል ማልቀስና መጸጸት ተነፍገሃል። አንተ ሚስኪን! እጅግ ቀላል ከሆኑ ዒባዳዎች እንኳን ተነፍገህ ሳለ፣ አሁንም የተቀጣህ አይመስልህም⁉️ ታዲያ ልብህ ወደ ቀጥተኛው መንገድ የሚመለስበት ጊዜ አልደረሰምን? «በታዘዝከውም መሠረት ቀጥ በል!» ሱብሓነሏህ! የአብዛኞቻችን ሁኔታ! የቴሌግራም ቻናል:- http://t.me/AbuMeryemNeja http://t.me/AbuMeryemNeja

አንዳንድ ሰዎች እንዲሁ ከመሬት ተነስተው ያኮርፉንና ከዚያም ለምን እንዳኮረፉ ምክንያት መፈለግ ይጀምራሉ!

አንዳንዴ ዱዓእ አድርገህ ቶሎ ምላሽ ላያገኝ ይችላል ያኔ ለምን የሚል ጥያቄ ከተመላለሰብህ አሏህን በድብቅ ስታምፀውም ለምን ቶሎ አልቀጣኝም የሚልም ነገርም በዛው ቆም ብለህ አስብ❗️ ያኔ የአሏህ እዝነት ይገባሃል! ምናልባት ዱዓውም ያዘገየብህ ላንተ በይበልጥ ሚያስፈልገህ ሰአት እሱ ያውቀዋልና ለዛኔ ሊሰጥህ አዝኖልህ ይሆናል እና ወንድሜ አትቸኩል እህቴ አትቸኩይ ዱዓእ አድርግ ከዛ ምላሽ እንደምታገኝ እርግጠኛ ሁን ከዛ በትግስት ጠብቅ!!