ESSA YUSUF
4 414
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
የቁንድዶ ፈረሶች
ስንቶቻችሁ ስለነዚህ አስገራሚ ፈረሶች ታሪክ ታውቃላችሁ?
ቁንድዶ እጅግ በጣም በተፈጥሮ የተዋበ ተራራ ነው:: የሚገኘው በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሃረርጌ በጃርሶ እና ጉርሱም ወረዳ ነው:: ይህ ተራራ ጫፉ ላይ ውሃ አለ:: አረንጓዴ እና በተፈጥሮ ፀጋ የታደለ ነው:: ብዙ የውጭ እና የሃገር ውስጥ ተመራማሪዎች ስለዚህ ተራራ እና ፈረሶቹ ብዙ ምርምር አካሂደዋል::
በአለም ላይ ብቸኛ ባለቤት የሌላቸው የዱር ፈረሶች እዚሁ ላይ ይገኛሉ:: ፈረሶቹ አመጸኛ ናቸው፤ ሰዎችን ሲያዩ ማንፏረር፣ ጆሮ መቀሰር፣ ለጸብ መጋበዝ ይቀናቸዋል:: የኤጀርሳ ጎሮ ገበሬዎች ወደ ተራራው ይልኳቸው የነበሩ ማቲ እረኞች ሳይቀሩ በፈረሶቹ ይነከሱ፣ ይገደሉም እንደነበር ተዘግቧል:: በአሁን ሰአት የፈረሶቹ ቁጥር እየተመናመነ መጥቷል::
ታሪካቸው እስካሁን ድረስ ህዝቡን ለሁለት ከፍሏል:: ግማሹ የአህመድ ግራኝ ወታደሮች ፈረሶች ናቸው ሲሉ ገሚሶቹ ደግሞ የዐጼ ገላውዲዮስ ፈረሶች ናቸው በማለት ይከራከራሉ:: ብዙም ያልተነገረላቸው እና በሚገባው ልክ እንክብካቤ ስላልተደረገላቸው ባክኖ የቀረ የቱሪዝም ሃብት ሆኗል::
የኦሮሚያ ቱሪዝም ቢሮ አይኑን ገልጦ ልክ እንደ ወንጪ አይነት ፕሮጀክቶችን እዚህ አከባቢ ማድረግ አለበት:: አስገራሚ የቱሪዝም መዳረሻ ይወጣዋል:: ፈረሶቹና ተራራው ለአከባቢው ልዩ ግርማ ሞገስን ሰተውታል:: ባለሃብቶችም በአከባቢው የተለያዩ ደረጃቸውን የጠበቁ ሆቴሎችን ቢገነቡ ለቱሪስቶች ማረፊያነት ጠቃሚ ነው::
ትኩረት ለቁንዳዶ ተራራ ፈረሶች
👍 9🥰 1😢 1
በብዙ የፈጠራ ስራዎቹ የሚታወቀው ወጣት ሸሃብ ሱሌይማን Shehab Suleyman ሙሉ በሙሉ የራሱ ፈጠራ የሆነውን ሞተር ማምረቱን ገልፁጿል:: የሞተሩም ስም ኡርጂን " urjiin" በሚል ሰይሞታል:: ሙሉ በሙሉ በሃገር ውስጥ የተመረተው ኡርጂን ሞተር ምርቶቹን ለገበያ አቅርቧል:: በራሳችን ምርት እንኩራ::
የባሌ ምድር ያፈራችው ወጣት ሹሄብ ከዚህ ቀደም የተለያዩ የፈጠራ ስራዎችን በመፍጠር ለህዝብ ማቅረቡ ይታወቃል:: እኛም እንደነዚህ አይነት ወጣት የስራ ፈጠራ ባለሙያዎችን ማበረታታት አስፈላጊ ነው::
ይህ የቁቤ ትውልድ ይለያል ስልህ በምክንያት ነው
👍 19👏 1
Choose a Different Plan
Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.