Nessim Mahaba 📚 نسيم المحبة 🛖
Open in Telegram
╱◥██████◣ │∩│🪟▤│🪟│ ▓▆▇█▓🚪▓█▇ አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ የ ቻናላችን ተከታታዬች በዚህ ቻናል ➤ ኢስላማዊ ባህሎችን ➤ የሀገራችን ዓሊሞች ስራዎችን ➤ ልዩልዩ መጽሐፍ pdf ➤ ዳእዋ መንዙማ ታሪኮችንና የተለያዩ ስራዎች እናቀርባለን ╱◥██████◣ │∩│🪟▤│🇪🇹 @nessim_muhaba ዓላማችን ኢስላማዊ ባህላችንን ማስፋፋት ነው♥
Show more5 184
Subscribers
-224 hours
+157 days
+12130 days
Posts Archive
ከጥም በላይ የሆነ ፍቅር…
ሰይዲና ዐሊይ ኢብኑ አቢ ጧሊብ [ረዲየላሁ ዐንሁ] የረሱለላህ [ﷺ] በልባቸው የነበራቸውን ቦታ ሲገልጹ፦
««كان رسولُ الله ﷺ أحبَّ إلينا من أموالِنا وأولادِنا وآبائِنا وأمّهاتِنا، ومن الماءِ الباردِ على الظمأ»»
«የአላህ መልእክተኛ [ﷺ] ከገንዘባችን፣ ከልጆቻችን፣ ከአባቶቻችን እና ከእናቶቻችን በላይ እኛ ዘንድ የተወደዱ ነበሩ፤ በከባድ ጥም ጊዜ ከሚጠጣ ቀዝቃዛ ውሃም በላይ የተወደዱ ነበሩ።»
💧 አስቡት!…
ከፍተኛ ጥም ላይ ያለ ሰው ለቀዝቃዛ ውሃ ያለው ፍላጎት ምን ያህል ነው!?… በጥም ለነደደ አንጀት ጠብታ ውሃ ያለው ዋጋ ምን ያህል ነው?!… ከዚያ በላይ ነበር ለሶሓቦች የነቢዩ [ﷺ] ፍቅር!
ይህ ሰሐቦች ለነቢዩ [ﷺ] የነበራቸው ፍቅር አጭር መግለጫ ነው። በእርግጥም የአላህን ነቢይ [ﷺ] መውደድ በአንደበት ብቻ የሚገለጽ መፎክር አይደለም። ሱናቸውን መከተል፣ ስነ-ምግባራቸውን መላበስ፣ ለፍጥረት ሁሉ ርኅራኄና ምሕረት ማሳየትን የሚያካትት ሰፊ ጉዳይ ነው።
የአላህ መልክተኛ [ﷺ] በሌሊት ከእንቅልፋቸው ሲነሱ፦
❶ «ዐሥር ጊዜ «አላሁ አክበር»፤
❷ ዐሥር ጊዜ «አልሐምዱ ሊላህ»፤
❸ «ሱብሓነላሂ ወቢሐምዲሂ» ዐሥር ጊዜ፤
❹ «ሱብሓነል-መሊኪል-ቁዱስ» ዐሥር ጊዜ፤
❺ «አስተግፊሩላህ» ዐሥር ጊዜ፤
❻ «ላ ኢላሃ ኢለላህ» ዐሥር ጊዜ ይሉ ነበር።
ከዚያም፦
❼ ዐሥር ጊዜ «አላህ ሆይ! ከዱንያ ጭንቀትና ከቂያማ ቀን ጭንቀት በአንተ እጠበቃለሁ።» ይሉ ነበር።
ከዚያም የሌሊት ሶላት ይጀምሩ ነበር።»
📚 አሕመድና አቡ ዳውድ ዘግበውታል፤ ይህ ቃል አቡ ዳውድ ያስተላለፉት ሲሆን በሐሰን ሰነድ የተዘገበ ነው።
ከሞት በላይ የሆነ ፍቅር…
በአንድ ወቅት የነቢዩ ﷺ ሶሓቦች ወደ አንድ አካባቢ ለዳዕዋ ተልከው ነበር። ነገር ግን ከሃዲያን በመንገድ አጥምደው ያዙአቸው። በግፍ የገደሉትን ገድለው የተወሰኑትን ወደ መካ በእስር አመጧቸው።
ከእነርሱም መካከል ዘይድ ኢብኑ ደሲናህ [ረዲየላሁ ዐንሁ] ነበሩ። ወደ መካ ወስደው ለሶፍዋን ኢብኑ ኡመያህ ሸጧቸው። ሶፍዋንም ዘይድን የአባቱን ሞት ለመበቀል ሊገድላቸው አሰበ።…
የግድያው ቀን ደረሰ። ዘይድ [ረዲየላሁ ዐንሁ] ከሞት ጋር ፊት ለፊት ቆሙ።…
በዚያን ጊዜ አቡ ሱፍያን ወደ እርሳቸው ቀርቦ እንዲህ አላቸው፦
«ዘይድ ሆይ! ሙሐመድ [ﷺ] አሁን በአንተ ቦታ ቢሆንና አንተ በቤተሰቦችህ መካከል ብትሆን፣ ሙሐመድ [ﷺ] ላንተ ቤዛ እንዲገደሉ ትመኛለህ?»
ዘይድ [ረዲየላሁ ዐንሁ] ምንም ሳያመነቱ መለሱ፦
«በአላህ እምላለሁ! ሙሐመድ [ﷺ] አሁን ባሉበት ቦታ እሾህ እንኳን እንዲወጋቸው፣ እኔ ግን በቤተሰቦቼ መካከል በሰላም እንድሆን አልወድም!»
ሱብሐነላህ!
እኔ ድኜ ቤተሰቦቼ ጋር ለመመለስ እርሳቸው በዚያ ፈንታ አይደለም መገደል እሾህ እንዲወጋቸው እንኳን አልሻም አሉ!…
አቡ ሱፍያን በዚህ መልስ በጣም ተደንቀው እንዲህ አሉ: ‐
«የሙሐመድ [ﷺ] ሶሓቦች ለሙሐመድ [ﷺ] ያላቸውን ፍቅር ያህል አንድ ሰው ሌላን ሰው ሲወድ አላየሁም!»
:
ተመልከቱ!
የዘይድ ንግግር የአንድ ሰው የመጨረሻ ቃል ብቻ አልነበረም። ሶሐቦች ለነቢዩ [ﷺ] የነበራቸውን የማይነጥፍ ፍቅር የሚመሰክር ቃል ነበር።
ከዚያም ዘይድ [ረዲየላሁ ዐንሁ] ተገደሉ። ሰውነታቸው ወደ አፈር ተመለሰ፤ ነገር ግን ታሪካቸው በየዘመኑ የሚመነዘር የአፍቃሪዎች ፈለግ ሆነ።
ፍቅር ማለት የአንደበት ጨዋታ አይደለም። በመስዋዕትነትና በታማኝነት የሚረጋገጥ ተመን አልባ እንቁ ነው።
ዘይድ [ረዲየላሁ ዐንሁ] ለራሳቸው ሕይወት ሲሉ የነቢዩ [ﷺ] ሕይወት እንዲጎዳ ማሰብ እንኳን አልፈለጉም። እሾህ እንዲወጋቸው ማሰብ እንኳን ልባቸው አልፈቀዱም!
ረዲየላሁ ዐንሁ ወዐን አስሓቢ ነቢይ [ﷺ]
:
አላህ የሰይዳችንን ፍቅር በልባችን ያኑርልን! ሱናቸውን ይርዘቀን! ከባንዲራቸው ስር ይቀስቅሰን! በእጃቸው ሐውዷቸውን ያጠጣን!
አሚን!
በድሬ ሐሪማ ተወሱላት አውታድ መንዙማ LYRICS VIDEO MENZUMA TAWSULAT DUA'A شي لله سيد يا شهاب الداني || مكتوبه
https://youtube.com/watch?v=L7YjRTd-1E8&si=di2kIGSN5vfXV-tB
المنحة الغيبية في الرد على فرقة الوهابية للمحديث الكبير الشيخ محمد سراج المفتي بن الشيخ محمد سعيد الجبرتي الأني قدس الله سره ونفعنا بأسراره أمين
ታላቁ ሊቅ የሐዲስ ባለሙያ የጊዜያችን ብርሃን [ሙፍቲ ሙሀመድ ሲራጅ ሸኽ ሙሀመድ ሰኢድ አል-አንይ #ሙፍቲ_ራያ] ኪታብ በ pdf ሐፊዘሁሏሁ ተዓላ፣ ብርታቱንም ደራርቦ ይደርብላቸው። የምንጠቀምባቸው አላህ ያድርገን አሜን
كتاب شفاء القلوب في مناقب صاحب النبي المحبوب السيد علي بن الشيخ أمانيّ المرسي نسبا الإفاتي الخيرأنبي المتوفي سنة ١٣٨١ هـ
المنحة الربانية في شرح المنظومة البقونية،
تأليف المحديث الكبير الشيخ محمد سراج المفتي بن الشيخ محمد سعيد الجبرتي الأني حفظه الله وقواه ونفعنا بأسراره أمين
