ፈለገ ጥበባት +++
Open in Telegram
+++የቀደምት ኢትዮጵያውያን ስልጣኔን ማሳየት እንዲሁም ገዳማት እና አድባራትን ማሳወቅ፡፡+++ የተረሱ አድባራትና ገዳማትን ማስታወስ ፤የ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያንን ጥበብ እውቀትን በምንችለው ሁሉ መመርመር የአባቶቻችን ልጆች በመሆን ትላንት በዛሬ እና በነገ ውስጥ ማስቀጠል ማስቻል ነው።
Show more7 163
Subscribers
-524 hours
-267 days
-7330 days
Posts Archive
7 163
ሚካኤል ወርዶ ያነጋገራቸው ድንቅ ሰው!
በኮከብ የተመሩት ጻድቅ..በአናብረት የሚጠበቀው ገዳም.....ሚስጥራዊው ዋሻ!
ከደቂቃወች በኋላ በዩቲብ ቻናላችን ይቀርባል!
7 163
አለምን ያስጨነቀው 666 ማንድን ነው?
ዩሐንስ በ ራዕዩ 666 ብሎ የገለጸው ታላቅ ሚስጥር በሚስጥር አዋቂ ተመራማሪ ሊቃውነት እንዴት ይፈታል?
እውነት 666 መንፈስ ጊዌው አሁን ነው? የአለም ህዝብ እንዳያውቀው የተደረገው ከጀረባው ያለው ሴራ እና አደገኛው ደባ ምንድን ነው?
ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊያወቀው የሚገባ እጂግ አስደናቂ የሊቁ ትንታኔ ከዚህ ፕሮግራም በኋላ ብዙ ነገሮች ግልጽ ይሆናል ።
በዩቲብ ቻናላችን ይቀርባል..ይጠብቁን!
7 163
ተ ክለ ጻድቅ መኩርያ ግብጻዊው ጸሐፊ ማክሪዝ Historia Rerum Isi amiticarumin Abissinia በሚለው መጽሐፉ የገለጠውን መሠረት በማድረግ «የኢትዮጵያ ታሪክ ከይኩኖ አምላክ እስከ ልብነ ድንግል» በሚለው መጽሐፋቸው ላይ እንደሚተርኩት አስቀድሞ በሰይፈ አርእድ ዘመን በግብጹ ሡልጣን እና በኢትዮጵያዊው ንጉሥ መካከል የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት የልዑካን ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ነበር፡፡ የልዑካን ቡድኑ መሪ የኢየሩሳሌሙ ፓትርያርክ አባ ዮሐንስ ነበሩ፡፡
ልዑካኑ ወደ ኢትዮጵያ ሲደርሱ ያገኟቸው ዐፄ ዳዊትን ነበር፡፡ በሁለቱ ሀገሮች መካከል የነበረውን ችግር በውይይት እና በስምምነት ፈትተው አስማሟቸው፡፡ ዐፄ ዳዊትም ግማደ መስቀሉን እንዲልኩለት የኢየሩሳሌሙን ፓትርያርክ አቡነ ዮሐንስን አደራ አላቸው፡፡ እርሳቸውም ከግማደ መስቀሉ ጋር ሌሎች ንዋያትንም ጨምረው ላኩለት፡፡ በግብጹ ሡልጣን እና በንጉሥ ዳዊት መካከል የተፈጸመው ስምምነት ለኢትዮጵያውያን ተሳላሚዎች እና ነጋዴዎች ጥበቃ ማድረግን የሚያካትት ስለ ነበር ግማደ መስቀሉን የያዙት የዐፄ ዳዊት መልእክተኞች ያለ ችግር ኢትዮጵያ ገቡ፡፡
አንዳንድ የታሪክ መዛግብት ዐፄ ዳዊት ጥቅምት ዘጠኝ ቀን 1404 ዓም በድንገት ሲያርፉ ግማደ መስቀሉ በሱዳን ስናር ነበር ይላሉ፡፡ ከስናር ያነሡት ዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ መሆናቸውንም ይተርካሉ፡፡ ተክለ ጻደቅ መኩርያ ግን ዐፄ ዳዊት ወደ ኢትዮጵያ አስገብተውት በተጉለት ውስጥ ቤተ ክርስቲያን ሠርተውለት እንደ ነበር ይናገራሉ፡፡ ዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ የነገሡት በ1434 ዓም ነው፡፡ በእነዚህ ሠላሳ ዓመታትም አያሌ ነገሥታት ተፈራርቀዋል፡፡ እነዚህ ነገሥታት ግማደ መስቀሉን ለመውሰድ ያልቻሉበትን ምክንያት ማወቅ አይቻልም፡፡ ምናልባት ግን በነበረው የርስ በርስ ሽኩቻ ተጠምደው ይሆናል፡፡ ሌሎች መዛግብት እንጂ በኋላ ዘመን /ምናልባትም በዐፄ ልብነ ድንግል/ የተጻፈው የዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዜና መዋዕል የግማደ መስቀሉን ነገር አይነግረንም፡፡
ዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ግሼን አምባ ላይ ግማደ መስቀሉን ያስቀመጠበት ሁለት ምክንያቶች ይኖራሉ፡፡ የመጀመርያው የአምባው የመስቀለኛ ምልክት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ አምባው በዘመኑ በልዩ የንጉሠ ነገሥቱ ኃይል ይጠበቅ ስለ ነበር ነው፡፡ በግራኝ አሕመድ ወረራ ጊዜም ቢሆን ሌሎች ሀብቶች ከአምባው ላይ መዘረፋቸውን እንጂ የተቀበረውን ለማውጣት ሙከራ መደረጉን የግራኝን ታሪክ የጻፈው ዐረብ ፋቂህ አያነሣም፡፡///
ግማደ መስቀሉን የማውጣት ጥረት ተደረገ የሚባለው በ1851 ዓም ዐፄ ቴዎድሮስ በጣም የሚወዷቸው ባለቤታቸው እቴጌ ምንትዋብ ከሞቱ ከአንድ ዓመት በኋላ ነው፡፡ ንጉሥ ቴዎድሮስ እቴጌ ምንትዋብን እጅግ ይወዷቸው ስለነበር በመስቀሉ አማካኝነት ከሞት ለማስነሣት አስበው ነበር፡፡ ይህንንም በወታደሮች ኃይል በማስቆፈር አስጀምረውት ነበር፡፡ በመካከል ግን ከጉድጓዱ ኃይለኛ ሽታ እና ጢስ ወጥቶ ከቆፋሪዎቹ የተወሰኑትን በመግደሉ ሃሳባቸውን ሠርዘው ባለቤታቸውን በግሼን አምባ ቀብረው ተመልሰዋል፡፡
የ መስቀሉን እውነተኛ መገኛ አሰሳየ ወደ ግሸን ደብረ ከርቤ አቀናሁ..በወሎ ክፍለ ሃገር፣ አምባሰል ወረዳ ውስጥ ግሸን ተራራ አናት ላይ የምትገኝ ቤ/ክርስቲያን አቀናሁ....። ለዚች ቤ/ክርስቲያን መግቢያ አንድ መንገድ ብቻ ነው.....የመንገድሽ ነገር አይወራ ተብሎ የሚነገርላትን የአንባሰል ተራሮች ወገብ እየታከኩ ከፍ ቢሉ በታላላቅ ቋጥኝ የታጠሩ በቁጥቋጦወች የተዋቡ ከ ሰማዩ ጋር አፋቸውን ገጥመው የሚያወጉ ፀሐይን ያዘሉ ደመናን የተሸከሙ የሚመስሉ ተራሮች ወደ ታች ቢመለከቱ ከመንገዱ በመቶ ሜትሮች ዝቅ ብለው ለመጓዝ የሚያስደነግጡ ስምጥ ሸለቆወችን መመልከት የተለመደ ነው።
አለም የዳነበትን መስቀል ምድራችን ካላት እጂግ አስደናቂ ታላቅ ሚስጥር የተገለጠበት የሚወዳደረው ያለለው ውድ እቃን በጉያዋ አቅፋ እጂግ በሚያስደንቅ የተፈጥሮ መልካአ ምድር ውስጥ በክብር የተቀመጠው መግነጢሳዊው አማናዊው ሃያሉ መስቀል....በግሸን ረቂቅ ተራራ ውስጥ በርከት ያሉ ቤተክርስቲያን አሉ ...ይህ ቅዱስ ክርስቶስ የተሰሸለበት ሃያሉ መስቀል ከየትኛው ይገኛል....ብየ በ ግሸን ውስጥ የሚኖሩ የቅድመ አባቶች ልጆች ዘር የሆኑ ሰወችን ከ 600 አመታት በላይ በዚሁ የኖሩ አባቶቻችሁ ስለ መስቀሉ ምን ይላሉ ብየ ማጠያየቆን ጀመርኩ መረጃወችን እያሰባሰብኩ መልሱሉ ከግሸን አንባ ውስጥ በየትኛው ስፋራ አርፋል ለሚለው ጥያቄየ መልሱን ወደ ማግኘት ተጠጋሁ። ....
የሚያስገርመው ብዙሃኑ እንደሚሉት ዛሬም ድረስ የ መስቀሉ ሃይል ከ ተቀመጠበት ቤተክርስትያን ጣራ ሃይለኛ ሙቀት ነገር ስለሚለቀቅ ቤተክርስትያኑን ሲሰሩ ለነበሩ አንጺወች ሃይሉን መቋቋም የማይችሉት ፈተና ሆኑ በርካታ አስደናቂ ስራወችን እንደሚሰራ በርካታ ኖሪወች ይናገራሉ....
ይህ ፈለገ ጥበባት ነው ያላችሁን ሃሳብ አስተያየት @Nabuti21 ላይ አድርሱኝ።
7 163
አንዳንድ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት የመስቀሉ ክፍልፋዮች ወደ ተለያዩ ሀገሮች መወሰድ የጀመሩት በዚህ ጊዜ ነው፡፡ በሞሪታንያ ቲክስተር በተባለ ቦታ የተገኘውና በ359 ዓም አካባቢ የተጻፈው መረጃ የመስቀሉ ክፍልፋዮች ቀደም ብለው ወደ ሌሎች ሀገሮች መግባት እንደ ጀመሩ ያሳያል፡፡ ቄርሎስ ዘኢየሩሳሌም መስቀሉ ከተገኘ ከሃያ አምስት ዓመታት በኋላ በ348 ዓም በጻፈው አንድ ጽሑፍ ላይ «ዓለሙ በሙሉ በጌታችን መስቀል ክፍልፋዮች ተሞልቷል» በማለት ገልጦ ነበር፡፡ ከዚህም ጋር «ዕጸ መስቀሉ እየመሰከረ ነው፡፡ እስከ ዘመናችንም ድረስ ይኼው እየታየ ነው፡፡ ከዚህ ተነሥቶም በመላው ዓለም እየተሠራጨ ነው፡፡ በእምነት ክፍልፋዮቹን እየያዙ በሚሄዱ ሰዎች አማካኝነት» ብሏል፡፡/On the Ten Points of Doctrine, Colossians II. 8./
ዮሐንስ አፈ ወርቅም የመስቀሉን ቅንጣቶች ሰዎች በወርቅ በተሠራ መስቀል ውስጥ በማድረግ ምእመናን በአንገታቸው ላይ ያሥሩት እንደ ነበር ጽፏል፡፡ በዛሬዋ አልጄርያ በቁፋሮ የተገኙ ሁለት ጽሑፎች የመስቀሉ ክፍልፋዮች በ4ኛው መክዘ የነበራቸውን ክብር ይናገራሉ፡፡ /Duval, Yvette, Loca sanctorum Africae, Rome 1982, p.331-337 and 351-353/፡፡ በ455 ዓም በኢየሩሳሌም የነበረው ፓትርያርክ ለሮሙ ፖፕ ለልዮን የመስቀሉን ቁራጭ እንደ ላከለት ተመዝግቦል። በአውሮፓ ምድር የተዳረሰው አብዛኛው የመስቀሉ ክፍልፋይ የተገኘው ከባዛንታይን ነው፡፡ በ1204 ዓም በአራተኛው የመስቀል ጦርነት ጊዜ የዘመቻው ተካፋዮች በዓረቦች ጦር ድል ሲመቱ ፊታቸውን ወደ ቁስጥንጥንያ አዙረው ከተማዋን፣ አድባራቱን እና ገዳማቱን ዘረፏቸው፡፡ በዚያ ጊዜ ተዘርፈው ከሄዱት ሀብቶች አንዱ ዕሌኒ ከኢየሩሳሌም ያመጣችው የመስቀሉ ግማድ ነበር፡፡ ይህንን ግማድ እንደ ገና በመከፋፈል አብዛኞቹ የአውሮፓ አብያተ ክርስቲያናት ሊዳረሱት ችለዋል፡፡ የወቅቱን ታሪክ ከመዘገቡት አንዱ ሮበርት ዲ ክላሪ «በቤተ መቅደሱ ውስጥ አያሌ ውድ ንዋያት ይገኙ ነበር፡፡ ከእነዚህም መካከል ከጌታ መስቀል የተቆረጡ ሁለት ግማዶች ነበሩ፡፡ ውፍረታቸው የሰው እግር ያህላል፤ ቁመታቸውም ስድስት ጫማ ይህል ነበር» ብሏል፡፡ /Robert of Clari’s account of the Fourth Crusade, chapter 82: OF THE MARVELS OF CONSTANTINOPLE/
የመስቀሉ ለሁለተኛ ጊዜ መጥፋት እስከ ስድስተኛው መክዘ ድረስ በኢየሩሳሌም ጎልጎታ የነበረው መስቀል በ614 ዓም በፋርሱ ንጉሥ ክሮስረስ 2ኛ /Chrosroes II/ ተወሰደ፡፡ የፋርሱ ንጉስ ኢየሩሳሌምን በወረረ መስቀሉን እና ፓትርያርክ ዘካርያስን ማርኮ ወደ ፋርስ ወሰዳቸው፡፡ እንደ ገና ወደ ኢየሩሳሌም የተመለሰው ሕርቃል በ627 ዓም ባደረገው ጦርነት ክሮስረስ ድል ሲሆን ነው፡፡ ሕርቃል በመጀመርያ ወደ ቁስጥንጥንያ ካመጣው በኋላ እንደ ገና ወደ ኢየሩሳሌም ወስዶ በቀድሞ ቦታው በጎልጎታ አስቀምጦት ነበር፡፡
እስከ አሥረኛው መክዘ ድረስ በኢየሩሳሌም በቀድሞ ክብሩ ቢቆይም ዐረቦች አካባቢውን እየተቆጣጠሩ ሲመጡ በኢየሩሳሌም የሚኖሩት ክርስቲያኖች መስቀሉን በ1009 ዓም አካባቢ ሠወሩት፡፡ ለ90 ዓመታት ያህል ያለበት ቦታ ተሠውሮ ከኖረ በኋላ በመጀመርያው የመስቀል ጦርነት ጊዜ በ1099 ዓም ከተሠወረበት ወጥቶ እንደ ቀድሞው መታየት ጀመረ፡፡
ለሦስተኛ ጊዜ መጥፋት በ1187 ዓም በሐቲን ዐውደ ውጊያ ሳላሕዲን የተባለው የዓረቦች የጦር መሪ የመስቀል ጦረኞችን ድል አድርጎ ኢየሩሳሌምን ሲቆጣጠር በዚያ የነበረውን መስቀል መውሰዱን አንዳንድ የታሪክ መዛግብት ይገልጣሉ፡፡ ከዚያ በኋላ ግን መስቀሉ የት እንዳለ እስካሁን ማረጋገጥ አልተቻለም፡፡ በወቅቱ የነበሩት የሮም ነገሥታት መስቀሉን ለማግኘት ከሳላሕዲን ጋር ብዙ ድርድር አድርገው ሳይሳካላቸው ቀርቷል፡፡
በአብዛኞቹ ጥንታውያን አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ የመስቀሉ ክፍልፋይ እንዳለ ሁሉም ይናገራሉ፡፡ አንዳንዶቹ አለ የሚባለው ክፍልፋይ ከመብዛቱ የተነሣ የሚያነሡት ትችት አለ፡፡ ጆን ካልቪን «ሁሉም ክፍልፋዮች ከመስቀሉ የወጡ ከሆነ፤ እነዚህን ሁሉ ብናሰባስባቸው አንድ መርከብ የግድ ያስፈልጋቸዋል፡፡ ወንጌል ግን ይህንን መስቀል አንድ ሰው እንደ ተሸከመው ይነግረናል» ብሎ ነበር፡፡
ይህንን የካልቪንን ሂስ በተመለከተ መልስ የሰጠው ራውል ዲ ፈሌውሪ /Rohault de Fleury,/ በ1870 ዓም በዓለም ላይ አሉ በሚባሉት የመስቀል ክፍልፋዮች ላይ ጥናት አድርጎ ነበር፡፡ ራውል መጀመርያ የት ምን ያህል መጠን እንዳለ ካታሎግ አዘጋጀ፤ ከዚያም መጠናቸውን አንድ ላይ ደመረ፡፡ በታሪክ እንደሚነገረው የመስቀሉ ክብደት 75 ኪሎ፣ ጠቅላላ መጠኑም 178 ኪዩቢክ ሜትር ነው፡፡ ራውል ያገኛቸውና አሉ የተባሉት ክፍልፋዮች አንድ ላይ ቢደመሩ .004 ኪዩቢክ ሜትር /3.‚942‚000 ኪዩቢክ ሚሊ ሜትር/ ነው፡፡ በዚህም መሠረት ቀሪው 174 ኪዩቢክ የሚያህለው ሜትር የመስቀሉ ክፍል ጠፍቷል ማለት ነው ብሏል፡፡ /Mémoire sur les instruments de la Passion, 1870/
ግማደ መስቀሉ በኢትዮጵያ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን መዛግብት እንደሚሉት ግማደ መስቀሉ ወደ ኢትዮጵያ የገባው በ14ኛው መክዘ በዐፄ ዳዊት ዘመነ መንግሥት ነው፡፡ በግሼን አምባ የተቀመጠው ደግሞ በዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመነ መንግሥት ነው፡፡
ኢትዮጵያውያን ወደ ኢየሩሳሌም ያደርጉ የነበረውን ጉዞ፣ የኢትዮጵያ ነገሥታት የነበራቸውን ታዋቂነት እና ወደ ሀገረ ናግራን ተጉዘው የሠሩትን ሥራ ስንመለከት ኢትዮጵያ እስከዚያ ዘመን ድረስ ግማደ መስቀሉን ለማግኘት ትዘገያለች ብሎ ለማሰብ ይከብዳል፡፡ በኢየሩሳሌም የሚገኘው የኢትዮጵያ ገዳም መስቀሉ ለወጣበት ቦታ እና ለጎልጎታ ያለውን ቅርበት፤ ዐፄ ካሌብም ከናግራን ዘመቻ በኋላ ዘውዳቸውን ለጎልጎታ ቤተ ክርስቲያን መላካቸውን ስናይ ይህንን የመሰለ ቅዱስ ንዋይ ኢትዮጵያውያን እስከ 13ኛው መክዘ ድረስ አንዱን ክፋይ ሳያገኙት ቆዩ ለማለት ያስቸግራል፡፡ ኤርትራ ውስጥ ግማደ መስቀሉ አለበት የሚባል አንድ ገዳም መኖሩን ሰምቻለሁ፡፡
ክርስትና ብሔራዊ ሃይማኖት ከሆነ በኋላ ነገሥታቱ በሳንቲሞቻቸው ላይ የመስቀል ምልክት ማድረጋቸው፣ እንደ ንጉሥ አርማሕ ያሉትም በበትረ መንግሥታቸው ላይ መስቀል ማድረጋቸው፤ ከቀደምት ክርስቲያን ነገሥታት አንዱ የሆነው ንጉሥ ዐፄ ገብረ መስቀል ተብሎ መሰየሙን ስናይ የመስቀሉ ነገር በኢትዮጵያ ውስጥ የነበረውን ቀደ ምት ታሪክ ያመለክተናል፡፡
በዛግዌ ሥርወ መንግሥትም ዐፄ ላሊበላ ስመ መንግሥቱ ገብረ መስቀል መባሉን፣ ሚስቱም ንግሥት መስቀል ክብራ መባሏን፣ ከሠራቸው አስደናቂ ውቅር አብያተ ክርስቲያ ናት አንዱ ቤተ ጊዮርጊስ በመስቀል ቅርጽ መሠራቱን ስናይ ኢትዮጵያውያን ከመስቀሉ ጋር ቀድመው መተዋወቃቸውን ያስገምተናል፡፡ በመሆኑም በዚህ ረገድ መዛግብትን የማገላበጥ እና የመመርመር ሥራ የሚቀረን ይመስላል፡፡
በዐፄ ዳዊት ዘመን መጥቶ በዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ አማካኝነት በግሼን አምባ የተቀመጠው ግማደ መስቀል በይፋ የታወቀውና በነገሥታቱ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት የመጣው ዋናው እንጂ የመጀመርያው ነው ለማለት ያስቸግራል፡፡
7 163
ግሸን ውስጥ የሚኖሩ የቅድመ አባቶች ልጆች ዘር የሆኑ ሰወችን ከ 600 አመታት በላይ በዚሁ የኖሩ አባቶቻችሁ ስለ መስቀሉ ምን ይላሉ ብየ ማጠያየቆን ጀመርኩ መረጃወችን እያሰባሰብኩ መልሱሉ ከግሸን አንባ ውስጥ በየትኛው ስፋራ አርፋል ለሚለው ጥያቄየ መልሱን ወደ ማግኘት ተጠጋሁ። ....
የሚያስገርመው ብዙሃኑ እንደሚሉት ዛሬም ድረስ የ መስቀሉ ሃይል ከ ተቀመጠበት ቤተክርስትያን ጣራ ሃይለኛ ሙቀት ነገር ስለሚለቀቅ ቤተክርስትያኑን ሲሰሩ ለነበሩ አንጺወች ሃይሉን መቋቋም የማይችሉት ፈተና ሆኑ በርካታ አስደናቂ ስራወችን እንደሚሰራ በርካታ ኖሪወች ይናገራሉ....
በእምነት ታሪክ ውስጥ የታሪክ፣ የአርኬዎሎጂ እና የቅርስ ጥናት ሰዎችን ያስጨነቁ ሁለት ጥያቄዎች አሉ፡፡ ታቦተ ጽዮን እና ጌታ የተሰቀለበት መስቀል የት ነው ያሉት? የሚሉት ጥያቄዎች፡፡ እነዚህን ጥያቄዎች ለመመለስ አሰሳዎች፣ ቁፋሮዎች፣ መዛግብትን የማመሳከር ሥራዎች፣ አሉ የተባሉ የይዞታ ጥያቄዎችን የመመርመር ፍተሻዎች በመካሄድ ላይ ናቸው፡፡ በጣም የሚገርመው ነገር ግን የዓለም ቅርሶች መናኸርያ የሆነችው ኢትዮጵያ ሁለቱንም በተመለከተ ለዓለም የምትገልጣቸው ነገሮች አሏት፡፡
ሰሞኑን በሀገራችን ኢትዮጵያ የመስቀል በዓል በመከበር ላይ በመሆኑ «ለመሆኑ ጌታ የተሰቀለበት መስቀል የት ነው ያለው?» የሚለውን ጥያቄ በተመለከተ ያሉ መረጃዎችን እንቃኝ፡፡ በአብያተ ክርስቲያናት ከሚነገረው ትውፊት በስተቀር ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተሰቅሎት የነበረው መስቀል እንዴት ሊጠፋ እንደቻለ የተመዘገበ ታሪክ እኔ አላገኘሁም፡፡ አብዛኞቹ ጥንታውያን አብያተ ክርስቲያናት ግን አይሁድ በመስቀሉ ላይ ይደረግ የነበረውን ተአምራት በመቃወም ከክርስቲያኖች ነጥቀው እንደ ቀበሩት ይተርካሉ፡፡ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ጸሐፊው አውሳብዮስ የቆስጠንጢኖስ የሕይወት ታሪክ /Life of Constantine/ በተሰኘው መጽሐፉ ላይ በክርስቲያኖች ዘንድ ታላቅ ሥፍራ የነበረው የጌታ መቃብር ተደፍኖ በላዩ ላይ የቬነስ ቤተ ጣዖት ተሠርቶ እንደ ነበር ይናገራል፡፡ አውሳብዮስ በዝርዝር አይግለጠው እንጂ ይህ የቬነስን ቤተ መቅደስ በጎልጎታ ላይ የመሥራቱ ጉዳይ የሮሙ ንጉሥ ሐድርያን በ135 ዓም ኢየሩሳሌምን Aelia Capitolina አድርጎ እንደ ገና ለመገንባት የነበረው ዕቅድ አካል ነው፡፡
አይሁድ በሮማውያን ላይ እስከ ዐመጹበት እና ኢየሩሳሌም ከክርስትና በኋላ ለመጀመርያ ጊዜ እስከ ጠፋችበት እስከ 70 ዓም ድረስ መስቀሉ በክርስቲያኖች እጅ እንደ ነበር ይታመናል፡፡ በኋላ ግን ክርስቲያኖቹ የሮማውያንን እና የአይሁድን ጦርነት በመሸሽ ከኢየሩሳሌም ወጥተው ወደ ሌሎች ሀገሮች ሲሰደዱ፤ በኋላም በባር ኮባ ዐመፅ ጊዜ /132-135 ዓም/ ኢየሩሳሌም ፈጽማ በሮማውያን ስትደመሰስ የመስቀሉ እና የሌሎችም ክርስቲያናዊ ንዋያት እና ቅርሶች ነገር በዚያው ተረስቶ ቀረ፡፡ ንጉሥ ሐድርያንም የኢየሩሳሌም ከተማን ነባር መልክ በሚለውጥ ሁኔታ እንደ ገና ሠራት፡፡ ያን ጊዜ ነው እንግዲህ የቬነስ ቤተ መቅደስ በጌታችን መቃብር ላይ የተገነባው፡፡ ቆስጠንጢኖስ ለኢየሩሳሌሙ ኤጲስ ቆጶስ ለአቡነ መቃርዮስ በጻፈው እና ሶቅራጥስ እና አውሳብዮስ መዘግበው ባቆዩን ደብዳቤ ላይ ይህ ታሪክ ተገልጧል፡፡
ቀጣዮቹ 300 ዓመታት ለክርስቲያኖች የመከራ ጊዜያት ነበሩ፡፡ የሮም ቄሳሮች ክርስትናን እና ክርስቲያኖችን የሚያሳድዱባቸው ዓመታት በመሆናቸው መስቀሉን የመፈለግ ጉዳይ በልቡና እንጂ በተግባር ሊታሰብ አይችልም፡፡ ዓመታት እያለፉ ሲሄዱም ኢየሩሳሌም እየተዘበራረቀች እና የጥንት መልኳ እየተቀየረ በመሄዱ በጌታ መቃብር ላይም የሮማ አማልክትን ለማክበር ቤተ መቅደስ በመሠራቱ ነገሩ ሁሉ አስቸጋሪ እየሆነ ሄደ፡፡
የመስቀሉ እንደገና መገኘት ጥንታውያን የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ጸሐፊዎች መስቀሉን እንደገና ያገኘችው ንግሥት ዕሌኒ መሆንዋን ይናገራሉ፡፡ በ380 ዓም አካባቢ የተወለደው ታሪክ ጸሐፊው ሶቅራጥስ Ecclesiastical History በተሰኘው መጽሐፉ ላይ በምእራፍ 17 መስቀሉ እንዴት እንደ ተገኘ ዝርዝር መረጃ ይሰጠናል፡፡ ንግሥት ዕሌኒ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዛ በጎልጎታ የጌታ መቃብር ላይ የተሠራውን የቬነስ ቤተ መቅደስ አፈረሰችው፤ ቦታውንም በሚገባ አስጠረገችው፡፡ በዚያን ጊዜም የጌታችን እና የሁለቱ ሽፍቶች መስቀሎች ተገኙ፡፡ ከመስቀ ሎቹም ጋር ጲላጦስ የጻፈው የራስጌው መግለጫ አብሮ ተገኘ፡፡
ሶቅራጥስ ከሦስቱ መስቀሎች አንዱ የክርስቶስ መሆኑን እንዴት ሊታወቅ እንደቻለ ሲገልጥ እንዲህ ይላል «አቡነ መቃርዮስ በማይድን በሽታ ተይዛ ልትሞት የደረሰችን አንዲት የተከበረች ሴት አመጡ፡፡ ሁለቱን መስቀሎችንም አስነኳት፤ ነገር ግን ልትድን አልቻለችም፤ በመጨረሻ ሦስተኛውን መስቀል ስትነካ ድና እና በርትታ ተነሣች፡፡ በዚህም የጌታ መስቀል የትኛው እንደሆነ ታወቀ» ይላል፡፡ ከዚያም ንግሥት ዕሌኒ በጌታ መቃብር ላይ ቤተ ክርስቲያን አሠራች፡፡ ከመስቀሉ የተወሰነውን ክፍል ከፍላ ከችንካሮቹ ጋር ወደ ቁስጥንጥንያ ስትወስደው ዋናውን ክፍል በጎልጎታ ቤተ ክርስቲያን ተወችው፡፡
ይህንን ታሪክ ሄርምያስ ሶዞሜን የተባለው እና በ450 ዓም አካባቢ ያረፈው ታሪክ ጸሐፊም Ecclesiastical History, በተሰኘው ጥንታዊ መጽሐፉ በክፍል ሁለት ምእራፍ አንድ ላይ ይተርከዋል፡፡ ዞሲማን እንደሚለው በ325 ዓም የተደረገው ጉባኤ ኒቂያ ሲጠናቀቅ የቆስጠንጢኖስ ትኩረት ወደ ኢየሩሳሌም ዞረ፡፡
ምንም እንኳን ሶዞሜን ባይቀበለውም መስቀሉ የተቀበረበትን ቦታ ያመለከተው ከከተማዋ በስተ ምሥራቅ ይኖር የነበረ አንድ አይሁዳዊ መሆኑን እና እርሱም ይህንን መረጃ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ ከነበረ መዝገብ ማግኘቱን እንደ ሰማ ጽፏል፡፡ ንግሥት ዕሌኒ ባደረገችው አስቸጋሪ ቁፋሮ መጀመርያ ጌታ የተቀበረበት ዋሻ፤ ቀጥሎም ከእርሱ እልፍ ብሎ ሦስቱ መስቀሎች መገኘታቸውን ሶዞሜን ይተርካል፡፡ ከመስቀሎቹም ጋር የጲላጦስ ጽሑፍ አብሮ መገኘቱን እና የጌታ መስቀል ከሌሎች የተለየበትን ሁኔታ ከሶቅራጥስ ጋር ተመሳሳይ በሆነ ሁኔታ ይተርከዋል፡፡
ንግሥት ዕሌኒ በጎልጎታ፣ በቤተልሔም፣ በደብረ ዘይት፣ አብያተ ክርስቲያናትን አሠርታ እንዳረፈች ሶዞሜን ይተርካል፡፡ ብዙ የታሪክ ጸሐፊዎች ዕረፍቷን በ328 ዓም አካባቢ መስቀሉ የተገኘ በትንም በ326 ዓም ያደርጉታል፡፡ በ457 ዓም አካባቢ ያረፈው ቴዎዶሮት የተባለው ታሪክ ጸሐፊም የመስቀሉን የመገኘት ታሪክ ተመሳሳይ በሆነ መንገድ ያቀርበዋል፡፡
ንግሥት ዕሌኒ ለበረከት ያህል የተወሰነ ክፍል ወደ ቁስጥንጥንያ ከመውሰዷ በቀር አብዛኛውን የመስቀሉን ክፍል በብር በተሠራ መሸፈኛ አድርጋ በጎልጎታ ቤተ ክርስቲያን እንዲቀመጥ ለአቡነ መቃርዮስ ሰጥታቸዋለች፡፡ ይህ መስቀል በየተወሰነ ጊዜ እየወጣ ለምእመናኑ ይታይ እንደ ነበር አንዳንድ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ በ380 ዓም ኤገርያ የተባለች ተሳላሚ መነኩሲት ቅዱስ መስቀሉ ወጥቶ በተከበረበት በዓል ላይ ተገኝታ ያየችውን ለመጣችበት ገዳም ጽፋ ነበር፡፡ /M.L. McClure and C. L. Feltoe, ed. and trans. The Pilgrimage of Etheria, Society for Promoting Christian Knowledge, London, (1919)/
7 163
እንኳን አደረሳችሁ!
ከደቂቃወች በኋላ የግሸኑ መሰቀል የሰራውን ታምር መገኛ እንዲሁም በርካታ ያልተነገሩ የ ነገረ መስቀሉ ጉዳይ ይዠላችሁ እቀርባለሁ......
7 163
እጂግ አስደናቂው እውንት!
በ አንባሰል ተራራ በግሸን አንባ ረቂቅ ተራራ ውስጥ በርከት ያሉ ቤተክርስቲያን አሉ...
በ ግሸን ውስጥ የሚኖሩ የቅድመ አባቶቻቸውን ልጆች ዘር የሆኑ ሰወችን ከ 600 አመታት በላይ በዚሁ የኖሩ አባቶቻችሁ ስለ መስቀሉ ምን ይላሉ.... በግሸን ደብረ ከርቤ ነገረ መስቀሉን እውነት ፍለጋ ያደረኩትን አሰሳ ዬቀረብኩላቸው ጥያቄ ነው ...ፍለጋየን ማጠያየቄን ጀመርኩ መረጃወችን እያሰባሰብኩ መስቀሉ ከግሸን አንባ ውስጥ በየትኛው ስፋራ አርፋል ለሚለው ጥያቄየ መልሱን ወደ ማግኘት ተጠጋሁ። ....
መረጃወቸን ከማሰባስብበት የግሸን አንባ አካባቢ ኗሪወች በቅርብ ጊዜ ስለ ተፈጸመው የመስቀሉ መግነጢሳዊ ሐይል በ ቤተክርስትያኑ ላይ ያሳየውን ታምር ነግረውኛል......
እጂግ አስደናቂውን የመስቀሉን ነገር ያልተነገሩ አማናዊ ሚስጥሮችን ያልተገለጹ እውነቶችን በፈለገ ጥበባት የዩቲቭ ቻናል ይቀርባል !
ዝንቱ ውዕቱ ፍኖተ አበው ዘበአማን!
7 163
ወደ እርሳቸው ተጠግቸ ይቅርታ ቅድም የጠየኩወት እኔም የማውቀው እና የሰማሁት እውነት ሳለለ እንጂ እንዲህ በደፈናው ለግብዘነት አይደለም አልኳቸው። እርሳቸው በጥርጣሬ አይን ይመለከቱኝ ጀመር... እንዳላመኑኝ ገብቶኛል።
ታዲያ በዚህ ጊዜ ወግ ወግን እየወለደ ስለ አቡሻሕር የሚያዉቁት ነገር ካለ ይንገሩኝ ብየ ጠየኳቸው። እርሳቸው ግን አሁንም ከጥርጣሬ መንፈስ ስላልወጡ አይ የማውቀዉ ነገር የለም አሉኝ።
ስለዚህ አቡሻህር ስለሚባለው ነገር የሚያውቅ ሰው አታገኝም ብታገኝ እንኳ አይነግሩህም አሉኝ።
በእርግጥ እኔም የማውቀዉ ነገር አለ አልኳቸው......ትኩር ብለው አይተው እየተቀመጡ እኔንም እንድቀመጥ እየጋበዙ ጀሮዋቸውን በጉጉት ሲሰጡኝ ሳይ ወሬየን ቀጠልኩ ..... እውነቸኛ የአቡሻሕር አዋቂወች በጣት የሚቆጠሩ ናቸዉ ነገር ግን የት የት እንደሚገኙ ብዙም የሚየውቅ ሰው የለም....
አንዱ እዚህው ጣና ገዳማት ውስጥ ዳጋ እስጢፍኖስ ይገኛሉ፤ ስላቸው እሳቸው እንኳ... ብለው ዝም ሲሉ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ተሰውረው እንደ ጠፉ ሰምቻለሁ አልኳቸው በመገረም አንገታቸውን እየነቀነቁ ብዙ ይባላል ብለው ተሰወረዋል አርፈዋል ይባላል በማለት ገለጹልኝ...
መስማት ጀመሩ። ሌላው ሰው ኤርትራ ወደ ሰሜኑ ደንበር አካባቢ አሉ ሲባሉ ሰምቻለሁ .. ሶስተኛው ጎንደር አካባቢ የነበሩ መምህር ሲሆኑ ካረፉ ብዙ ጊዜያቸው እንደሆኑ ነገርኳቸው። አራተኛው የት እንዳሉ አላውቅም........
ሌላው በአንድ ቦታ አካባቢ ለዘመናት እራሳቸውን መቃብር ቤት ደብቀዉ የሚኖሩ እጂግ አዋቂ እና ጠቢብ ጎልማሳ የእግዚአብሔር ሰው ሲሆኑ ራሳቸውን ደብቀዉ የሚኖሩበትም ታላቅ ሚስጥር እንዳላቸው በዘመን ውስጥ የሚገለጡ እና የአቡሻህር ሊቅ እንደሆኑ ለቅርስ ጠባቂው ስነግራቸው በመገረም የእኒህን አባት ስም ጠየቁኝ.....።
አንድ አንድ እያልን ከጉያየ የቋጠርኳትን እውንት ከጉያቸው የቋጠሯትን እውቀት..እያወጋን አመሸን!
እኒህ ጎልማሳ ሰው ጊዜና ዘመን ከሰጠን ለቤተክርስቲያን ሆነ ለሀገር አምድ ሁነው እንደሚገለጡ ተስፋ አለኝ በማለት ፈገግ አሉ!
ለጥበበኛ ሰው አንድ ቃል ትበቃለች..... የጥበብ ጭላንጭሏ መንገድ ይነገራል እንጂ በአፋ በአደባባይ አትገለጥም! ስለዚህ እናንተም ከዚህ ጽሁፍ አንድ ታላቅ እውነት እንዳለ ተረዱና እውነትና ጥበብን በቅን ልቦና ፈልጉ!
ይህ ፈለገ ጥበባት ነው ያላችሁን ሀሳስ አስተያየት Nabuti21 ላይ አድርሱኝ።
7 163
እጂግ አስደናቂ የጉዞ ማስታወሻ
የአቡሻኾር ሊቃውንትን ፍለጋ በጣና ገዳማት የገጠመኝ አስደናቂ ገጠመኝ...
በኢትዮጵያ እጂጎ ጥቂት የአቡሻኾር ሊቃውንት ሚስጥራዊ መገኛ.......
አቡሻኻር የባሕረ ሐሳብን ቀመር ብቻ ሳይሆን ስለ አዕጋረ ጸሀይ ፣ ምህዋረ ጸሀይ፣ ስለኬክሮስ፣ ኬንትሮስ፣ ስለ ሥነ ፈለክ፣ ሥነ ከዋክብት…ወዘተ የሚተነትን የጥበብ መጽሐፍ ነው። እንደ ዮሐንስ አቤል ሄሬም አይሁን እንጂ የተለያዩ አባቶችና የኅብረተሰብ ክፍሎች በተወሰነ ደረጃ ተመሳሳይነት ያለው መጽሐፍ ጽፈዋል። እነዚህም፦
· ሰዒድ ወልደ ጰጥሪቅ
· መሀቡብ ወልደ መንጋ
· ሰዒዳውያን አይሁድ /የአይሁድና የዐረብ ተወላጆች/
· ዮሐንስ አፈወርቅ
· ቄርሎስ ዘአንጾኪያ
· ኤጲፋንዮስ ዘመንፈስ ቅዱስ
· ጊዮርጊስ ወልደ አሚድ
· ማርቆስ ወልደ ቀምበር ናቸው።
በተለይም ጊዮርጊስ ወልደ አሚድ አጅግ የተቀናጀና የሚያስደስት መጽሐፍ በዘመን አቆጣጠር ላይ ጽፏል። ከሁሉም በተሟላ ሁኔታ የጻፈው ግን ዮሐንስ ወልደ አቤልሄሬም ወይም አቡሻኻር ወልደ አቤልሄሬም ነው። አቡሻኻር ማለት ወልደ ግሱጽ - የታረመ፣ የተቀጣ፣ በሥርዓት ያደገ ልጅ ማለት ነው። ይህ አባት ለሠላሳ ዘመን ሱባዔ ገብቶ ነገር ግን እግዚአብሔር ባወቀ ሠላሳውን ዓመት እንደ ሶስት ቀን አድርጎለት አቡሻኻርን ጽፏል። ለሠላሳ ዓመት በሱባዔ መቆየቱን ያወቀው እንኳን ከወጣ በኋላ ቤተሰቦቹ ናቸው የነገሩት። በተገለጸለትም መጽሐፍ ውስጥም የባሕረ ሐሳብን ቀመር በሚገባ ቀምሮታል።
አቡሻህር(አቡሻክር) ምንድን ነው?
በአለም ላይ እጂግ ርቂቅ እና ምጡቅ ስለሆነው ከእውቀቶች ሁሉ ስለ ላቀው እውቀት፣ ከጥበባትም ጥቡዕ ስለሆነው ሚስጥራዊ ጥብብን ስለያዘው ብዙም ስላልተነገረለት አቡሻህር በትቂጡ ልነግራችሁ ወደድኩ።
ይህ አቡሻሕር የሚባለው የቁጥር መጻህፍ ጭምር የያዘ ሲሆን ይህንን ማወቅ እጂግ የረቀቁ ጥበቦች ባለቤት ያደርጋል።
ብዙ ግዜ በሚዲያም ሆነ በቤተክርስትያን አውደ ምህርት የአቡሻህር ሊቁ እከሌ እየተባለ ሲጠሩ ሰምተናል ነገር ግን እውነተኞች የአቡሻህር ሊቃውንቶች በጣት የሚቆጠሩ ጥቂቶች እንደሆኑ ሚስጥር አዋቂወች ይናገራሉ።
ምክኒያቱም የዘመን አቆጣጠር አዋቂ ወይም የባህረ ሀሳብ ሊቅ ሊሆኑ ይችላሉ እንጂ የአቡሻሕር ሊቅ ወይም አዋቂ አይደሉም።
የዘመን አቆጣጠር ወይም ደግሞ የ ባህር ሀሳብ እውቀት አለምን በኬክሮስና በኬንትሮስ ከፍሎ አውድ እና አበቅቴ እንዲሁም አጾማትን ማውጣት የመሬትና የጨረቃ የፀሐይን እንዲሁም የከዋክብትን ምህዋር መለየትና ዘመንን የማራቀቅ እውቀት ነው።
ይህ ባህረ ሀሳብ ከ አቡሻህር ቅንጣቢ እውቀት የወጣ እንጂ አቡሻሕር አዋቂ አያሰኝም።
ይህንን ያልኩበት ዋና ምክኒያቴ ኢትዮጵያ ውስጥ እውነተኛ የአቡሻሕር አዋቂወች እጂግ ጥቂቶች በመሆናቸው ነው። በእርግጥ በጣት ይቆጠራሉ የሚባሉት ሰወች ብቻ እንደሆኑ ይነገራል።.......
ለምን በትቂት ሰወች ተወሰነ ከተባለ የአቡሻሕር እወቀት በመማር በመደከም ብቻ የሚመጣ አይደለም እውቀቱ በመንፈስ ቅዲስ ገላጭነት ነው የሚማሩት ይባላል...
የሚገርማችሁ ነገር እኒህ የአቡሻህር እዋቂወች ሰማያትን አይተው ከዋክብትን ተመልክተው የነፋሳትን አነፋፈስ እና የእጽዋቱን ሁኔታ ተመልከተዉ አለም ላይ እየሆነ ያለውን ወደ ፊትም የሚሆነው ነገር ያውቃሉ።
ይህም ብቻ አይደለም አቡሻህር ትምህርት መንፈስ ቅዱስ ለፈቀደላቸው ለበቁ አባቶች ብቻ ነው ትምህርቱ የሚገባው።
ስለሆነም አዋቂወች ለተንኮል የመጣን ሰውን ፊት አይተው ልቦናን እስከ ማንበብ ድረስ የሚያበቃ ጥበብ ነው ይለግሳቸዋል ይባላል...
ሰማይን አይተው የዝናባትን ሁኔታ የመዘወር ብቃትም ጥበብም አላቸው።
የነፋሳቱ ሀይል የመቆጣጠር ሀይል ታላቅ ጥበብንም ያውቃሉ።
እኒህ ሰወች ራሳቸውን የማደስ እና ከሰው የመሰውር ድንቅ ጥበብ ባለቤቶችም ናቸው። ራዕይን የማየትም ጸጋ አላቸው....
በሰማይ 4 ዓበይት እና 12 ንዑሳን ከዋክብቶች አሉ።
እኒሂ አራቱ ከዋክብት አራቱ አዝማናትን ማለትም ዘመነ ማቴወስ ማርቆስ ሉቃስና ዮሐንስን ሲያመለክቱ፤ 12ቱ ደግሞ ከ መስከረም እስከ ነሐሴ ድረስ ያሉትን ወራት የሚያመለክቱ ከዋክብት ናቸው።
ታዲያ እኒህ ዐበይትና ንዑሳን ከዋክብቶች በሰማይ ላይ በሚወጡ ወቅት እኒህ የአቢሻህር ሊቃውነት በሰማይ ያለውን የከዋክብትን አቀማመጥ ያያሉ። የሚመጣ ዘመኑንም ይተነብያ፤ በአለም ላይ የሚሆኑ እያንዳንዷን ሁኔታ በመንፈስ ቅዱስ ገላጭነት በከዋክብቶች መሪነት ማወቅ ይችላሉ።
ከዚህ ጋራ በተያያዘ በቅርቡ በአንድ ታላቅ ገዳም ላይ የገጠመኝ ታሪክ በአጭሩ ልንገራችሁ።
ከ እለታት በአንዱ ቀን ወደ ጣና ገዳም መንፈሳዊ ጉዞ ለማድረግ አስቤ የተወሰኑ ልጆች ጋራ ወደ ክቡራን ገብረኤል አቀናን።
በትንሽየ ጀልባ ተሰባስብን የጣና ሐይቅን ደረት ደረቱን እየገመስን በስተ ግራ እንጦስ ገዳምን ታከን ወደ ክቡሩ ስፍራ ክቡራን ገብርኤል ደረስን።
ከደሴቱ መሀል በበቀለ ቋጥኝ የመሰለ ተራራን እየታከክን ወደ ከፍታው ደረስን፤ ከተደላደለው ቦታም እንደደረስን ፊት ለፊት በክብ የተሰራውን የገዳሙን ቤተክርስቲያን ተሳልመን ወደ ግራ ወደ ሚገኘው እቃ ቤት ለመጓብኝት በሰልፍ ገባን።
እንደደረስን የእንኳን ደህና መጣችሁ ሰላምታቸውን የሰጡን አንድ በእድሜ ወጣት የገዳሙ ንብረት ክፍል ስማቸውን አስተዋውቀውን ወደ ውስጥ ገባን....።
ክቡራን ገብርኤል በ14ኛው ክፍለ ዘመን እንደ ተመሰረተ ጥንታዊና ታሪካዊ ታላላቅ የቤተክርስቲያኒቱን ሀብት የያዘ ድንቅ ቦታም እንደሆን እስጓብኛችን በያዙት መቋሚያ እያመለከቱ ገለጹልን ......
በእድሜ ወጣቱ አስጓብኛችን ሳይንስን ጥንቅ አድረገው የተማሩ እንደሆነ ከአነጋገራቸው እና ከሚሰጡን ቁጭት አዘል ገለጻ ለመረዳት ችያለሁ። ከእቃ ቤቱ ብዙ የብራና መጻህፍት መስቀሎች እና ስዕላትን ካሳዩን በኋላ።
እኔ አንዱ የሆነ አይኔ ያረፈበትን ታላቅ ቅርስ በማየቴ አስደንግጦኝ እስኪጨርሱና እስክ ጠይቃቸው ቸኩያለሁ....ለጉብኝት የመጡትን ልጆች ጥያቄ ካላችሁ ሲሉ የተወሰኑ ልጆች ስለ ቅርሷች አንዳንድ ጥያቄወችን ጠየቁ እሳቸውም መለሱላቸው።
ማእዛው የሚስበውን በግዙፍ በጥንታዊ ዛፎች የተዋበው ገዳም የአዋፋቱ ዝማሬ የ እጣኑ ሽታ የነፋሳቱ አነፋፋስ እጂግ የሚያስደንቀው የጣና ሃይቅ ከቦት ሲታይ የ ስጋን ሃያልነት ከተጫጫነበት የአለም ጫጫታ መንጭቆ በነፍስና በመንፍስ አለም ውስጥ ያስገባል...
ለጉብት የገቡት እንደወጡ እኔም ጥያቄ እንዳለኝ ነገሪያቸው እድሉን ሲሰጡኝ ጥያቄየን .....ጠየኩኝ
መልሳቸው የሚያስደነግጥ ነበር በሹክታ ለጠየኳቸው ከፍታ ባለው ድምጽ'' ስለ ዚህ አንተ እንዴት አወክ ? እንዴት ይህንን ጥያቄ ለጠይቀኝ ሻልክ በማለት ተቆጡኝ።
የጉብኝታችን ስአት እንዳለቀ ነግረውን የሆነ ጥግ ይዘው ከትልቅ ዋርካው ግንድ ተደግፈው ከዕቃ ቤቱ የሚወጣውን ምዕመን ይመለከታሉ።
7 163
እጂግ አስደናቂው የጉዞ ማስታወሻ .....አለም ላይ ካሉ እጂግ በጣም ጥቂት ታላላቅ የአቡሻኽር ሊቃውንትን ፍለጋ በፍለጋየ ላይ ጣና ላይ ያጋጠመኝ አስደናቂ ገጠመኝ!
በፈለገ ጥበባት የዪቱቪ ቻናል ይጠብቁን!
7 163
ከተሞች ገዝተው የሚማሩት የቆሎ ተማሪዎች በዲማ ቆይታቸው አምስትም ሆነ ስምንት ዓመት ቢቆዩ ምንም አይነት የትምህርት ክፍያ አይጠየቁም። ነገር ግን የቆይታ ጊዜ የምግብ እና የተለያዩ ወጪዎቻቸውን እራሳቸው እንዲሸፍኑ ይደረጋል።
። ዲማ ታሪካዊነቱ
በዕውቀት አበርክቶቱ ብቻ አይደለም። በጣሊያን ወረራ ወቅት የአርበኞች ማዕከል ሆኖ አገልግሏል። የመጀመሪያው የኢትዮጵያ አርበኞች ማህበር የተቆቋመበት ታሪካዊ ቦታ መሆኑንም አባ ወልደስላሴ የተባሉ የአካባቢው ታሪክ አዋቂ ይናገራሉ። በአምስት ዓመቱ የጣሊያን ወረራ ዘመንም በአባቶች ፈንታ ልጆች ተወለዱሉሽ የሚል ማህተም ተቀርፆ የጀግኖች ማህበር ተቋቁሞ አርበኞችን በተለያየ መልኩ
ይረዱ እንደነበር የታሪክ ማስረጃዎች ያመለክታሉ።
የዲማ ልዩ ክስተት በዲማ ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም ብዙዎች ሊመለከቷቸው የሚጓጉላቸው መነኩሴዎች አሉ። እማሆይ ብርሐን የተባሉት መነኩሴ በቤተክርስቲያኑ ቅጥር ግቢ ውስጥ ለረጅም ዘመናት ማለትም ለ30 ዓመታት ኖረዋል። በነዚህ ሁሉ ዘመናት ግን ባዶ ሜዳ ላይ ተቀምጠው ነው ጸሎት ሲያደርሱ የሚውሉት። ነገር ግን ዝናብ
ሲዘንብ እንኳን እርሳቸው የነበሩበት ቦታ ላይ ደረቅ ሆኖ ይታያል። ከብዙዎች አንደበት እንደተመሰከረላቸው መነኩሴዋ በአካባቢው ሲኖሩ የሚመገቡት
‹‹ቱልት›› የተባለው ቅጠል ነው። በጸሎት እና በምህላ አብዛኛውን ጊዜም ያሳልፋሉ።
እርሳቸው ካልፈለጉ ማንም ሰው ቢመጣ ሊያናግሩ አይችሉም። አሁን ላይ ግን አነስተኛ
የጭቃ ቤት በቤተክርስቲያኑ ደጀ ሰላም በስተቀኝ ተሰርቶላቸው እዛው አረፍ ይላሉ። መሬት
ላይ በተቀመጡበት ፊታቸውን ወደ መሬት አድርገው በማጎንበስ ነው የሚተኙት። ለረጅም ሰዓት በዝምታ እና
በጸሎት የሚያሳልፉት እናት የአካባቢው ክስተት ናቸው ቢባል ማጋነን አይሆንም። አስደናቂው የአኗኗር ዘይቤያቸው ለሩቅ አገር ሰዎችም ጭምር እንግዳ በመሆኑ አነስተኛ ማረፊያቸው ላይ መጥቶ የሚጎበኛቸው ሰው በርካታ ነው። ተነግሮ ከማያልቀው
የዲማ ጊዮርጊስ ገዳም ጥቂትም ቢሆን ጨለፍ አድርገን ወደ ናንተ ለማድረስ ሞከርን።
ይህ ፈለገ ጥበባት ነው ያላችሁን ሃሳብ አስተያየት @NAbuit21 ላይ አድርሱኝ።
7 163
የቤተክርስቲያን ጌጦች) ወትሮም ቢሆን ነፋስ ሲያነቃንቃቸው ጥዑመ ዜናም ይለግሳሉ። ጉሉላቱ
ላይ ደግሞ ባለ 15 ጫፍ የሆነ ከነሐስ የተሰራ መስቀል ከነግርማ ሞገሱ ይታያል። ወደ ጥንታዊው
ገዳም ውስጥ ብዙም ዘልቀን ሳንገባ በስተሰሜን አቅጣጫ በግምት 50 ሜትር ሲቀረን የመነኮሳቱን የመኖሪያ ገዳም እናገኛለን።
የመነኮሳቱ መኖሪያ ገዳም እንደ ግብር ማብያ አዳራሽ የተንጣለለ ነው።
በተለይ ሴት የቅኔ መምህሯን ለማየት እና ቅርሶቹን ለመጎብኘት በርካታ ሰዎች ወደ ስፍራው ማምራት ጀምረዋል። ወደ ገዳሙ ከመገባቱ በፊት በስተምዕራብ አቅጣጫ ከአጥር ውጭ ራቅ ብሎ በትናንሽ ጐጃዎቹ የተከበበ አንድ አሮጊ የቆርቆሮ ቤት ይገኛል። የዲማ ጊዮርጊስ መንፈሳዊ ትምህር ቤት ነው።
ጎጆዎቹ ዙሪያቸውን በሰንሰል ታጥረዋል። ፍቅር እስከ መቃብርን ካነበቡ ወይም ትረካውን ከሰሙ ይህን ጊዜ አንድ ነገር በአይነ ህሊናዎ ይመጣበዎታል። ይህም የፍቅር እስከ መቃብሩ የበዛብህ ቦጋለና የቅኔ መምህሩ የአለቃ ክንፈ የቅኔ ማዕበል መሆኑን ወዲያው ይረዳሉ። ከጎጆዎቹ አለፍ ብለን ወደ ቤተክርስቲያኑ ስንገባ አጥሩ በደቡብና በምእራብ አቅጣጫ ሁለት በሮች እንዳሉት እናያለን፡፡ ዋናው የምዕራቡ በር ነው። ይህ በር ደጀ ሰላም ይሰኛል። ሶስት ሜትር በሶስት ሜትር ስፋት አለው። አገልግሎቱ ለመውጫና መግቢያ ነው።ከላይ ባለ አንድ ደረጃ ህንፃ ይዟል። የፎቁ ርብራብ ከተጠረበ ጽድ ጣሪያው ደግሞ ከቆርቆሮ የተሰራ ነው።
በደጀ ሰላሙ የተገናኘ ሰው የእግዜር ሰላምታ ተለዋውጦ ማለፍ ባህሉ ነው። በቅጥሩ ውስጥ ዕድሜ ጠገብ የጽድ ዛፎችና ጥቂት መቃብር ቤቶች ይታያሉ፡፡ መቃብር ቤቶችን የደብሩ አገልጋይ የሆኑ ሴት መነኮሳትና አቅመ ደካሞችይኖሩባቸዋል።
በክብ ቅርፅ የታነፀው የዲማ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ግድግዳው ከድንጋይና ከሲሚንቶ የተዋቀረ ነው። በሶስት አቅጣጫዎች በሮች አሉት። በሮቹ ባለሰፋፊ የጽድ ሳንቃዎች ናቸው። ከመስታወትና ከብረት በመስቀል ቅርጽ የተሰሩ 30 የሚደርሱ መስኮቶች አሉት። የገዳሙ ውስጣዊ ገጽታ በተዋቡ ጥንታዊ ስዕሎች የተነቆጠቆጠ ነው። በጨርቅ ላይ የተሳሉ የቅዱሳን ስዕሎች በተጠረበ እንጨት ላይ ተወጥረው ለዕይታ ቀርበዋል።
ድንቅ ቅርሶች ታሪካዊው ገዳም በውስጡ የተለያዩ ሃይማኖታዊ እና ባህላዊ ቅርሶችን እንዲሁም የነገስታትን አሻራ ይዟል። ከብዙ በጥቂቱም የአፄ ዮሀንስ አራተኛ የወርቅ ዘውድ፣ የወርቅ መስቀሎችን፣ የአፄ ይሳቅ የወርቅ ጫማ፣ የበትረ ሙሴ ተምሳሌት
የሆነ የወርቅ ዘንግ በገዳሙ ይገኛሉ። የንጉስ ተክለሐይማኖት ጦር፣ በስዕልየተዋቡ በርካታ
ጥንታዊ የብራና መጽሐፍት፣ አርባአቱ ወንጌልና ገድለ
ጊዮርጊስ የተባሉ ጥንታዊ ጽሁፎች አሁንም በገዳሙ ይገኛሉ። አፄ ሚኒሊክ ለዲማ የሰጡት ውስጡ በህብረ ቀለማት ያማረ እና እስከ 70 ሰዎችን መያዝ
የሚችል ክብ ቅርጽ ያለው ድንኳን አለ። ድንኳኑ ለክብረ በዓላት እና አስፈላጊ ለሆኑ ጊዜዎች ብቻ ይወጣል። የራስ መኮንን ካባና ሌሎች የጽሁፍ መረጃዎችን እንዲሁም የወርቅ እና የብር መገልገያዎቸ አያሌ ናቸው። ይሁንና እስካሁንም የጎብኚ ያለህ እያሉ የሚጣሩ ይመስላል።
የአብነት ትምህርት በአስተዳደሩ በኩል የገዳሙን ማህበረሰብ በአራት ተከፍሎ ተመድቧል፡፡
ክፍፍሉም የሹም ሽር ቤት፣ የቄስ ቤት፣ የመሪ ቤት እና የጨዋ ቤት በመባል ተሰይሟል። የሹም ሽር ቤት የሚባለው ለደብርነት ማዕረግ ወይም በቅኔ ማህሌት እያገለገሉ ስለ ሀገር ጉዳይ ለሚቆረቆሩ የሚሰጥ ሹመት ነው፡፡ የሹም ሽር ቤት ውስጥ በወቅቱ የተሾሙትንና የተሻሩትንም ያጠቃልላል፡፡ የቄስ ቤት የሚባሉት ትምርታቸውን እየተከታተሉ ከቤተ መቅደስ በድቁና፣ በቅኔ ማህሌት፣ ሰአታት በመቆም፣ ከበሮ በመምታት መቋሚያና ጸናጽል በማቀበል ሲያገለግሉ አድገው አካለ መጠን ሲደርሱ መንኩሰው ከቤተ መቅደስ በቅዳሴ የሚያገለግሉ
ናቸው፡፡
የመሪ ቤት የሚባሉት ደግሞ ከዚህ በላይ በተመለከተው መሰረት አድገው ንጉስ ነን አንፈልግም ብለው ሚስት አግብተው ቤት ሰርተው በቅኔ ማህሌት እያገለገሉ ለአገር ጉዳይ ሲወጡ ሲወርዱ የሚኖሩ መምህራን ናቸው፡፡
ሌላኛው ደግሞ የጨዋ ቤት የሚባለው ነው። ዲማ ውስጥ የተወለደ ልጅ ሁሉ በአራት ዓመቱ እንደ ደንብ ሆኖ ከቤተክርስቲያን ተማሪ ቤት ሳይገባ አይቀርም፡፡
የጨዋ ቤት የሚባለው ግን ትምህርት ቤት ገብቶ ትምህርት እድሉ ሳይሆን ይቀርና አቋርጦ በእርሻና በንግድ የሚተዳደረውን ሰው ለመግለጽ ነው፡፡ ይህ ማህበረሰብ የጨዋ ልጅ ተብሎ ርስቱን ይዞ ቤተክርስቲያን እየደገፈ ይኖራል፡፡ ማናቸውንም የአገር ሆነ የመንደር ጉዳይእነዚህ የማህበረሰብ ክፍሎች መክረውበት ነበር የሚፈጸመው። ህዝቡ የሚተዳደረው በመረጣቸው ልጆች ስለሆነ በየ3 ዓመቱ ምርጫ እያደረገ የሚገባው በየደረጃው እየሻሩናእየሾሙ ይኖሩ ነበር፡፡ በዚህም የዲማ አስተዳደር አሳታፊ ነበር ማለት ይቻላል።ዲማ ለመንፈሳዊ ትምህርት ሃይማኖትን፣ ህግንና መንፈሳዊ ሥርዓቶችን ያስተምራል።
በስጋዊ በኩልም መልካም አስተዳደርን፣ ሀገር ጥበቃንና እንዲሁም የወገን ፍቅርንለህዝብ ሲያስተምር የኖረ ደብር ነው፡፡ በአብነት ትምህርት አሰጣጡ ዘመናዊ ትምህርት ባልተስፋፋበት ወቅት ጭምር እንደ አንድ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ከሀገሪቱ አንደኛ ጫፍ እስከ ሌላኛው ጫፍ ለሚመጡ ተማሪዎች እውቀትን ሲለግስ ኖሯል። አንጋፋው
ደራሲ ዶክተር ሀዲስ አለማየሁ እና ሌሎችም ምሁራን በዚሁ የአብነት ትምህርት ቤት ተምረዋል።
በዲማ የአብነት ትምህርት ቤት ውስጥ ስድስት የትምህርት ክፍሎች ይገኛሉ። እነርሱም
የንባብ ቤት፣ የዜማ ቤት፣ የቅኔ ቤት፣ የቅዳሴ ቤት፣ የአቋቋም ቤትና እና የትርጓሜ ቤት በመባል ይታወቃሉ። በየትምህርት ክፍሎቹ ተማሪዎችን የሚያስተምሩ ሊቃውንት ሲገኙ ብቸኛዋ ሴት የቅኔ መምህርም ትገኛለች። የአብነት ተማሪዎች የእራሳቸው የመቃብር ቤት ውስጥ ሶስት እና አራት ሆነው ይኖራሉ።
በርካቶችም አነስተኛ ማረፊያ የምትሆን ጎጆ ቤት አሰናድተው ይኖራሉ። አሁን አሁን ከቤተሰብ ገንዘብ መደጎም ጀመሩ እንጂ የቆሎ ተማሪዎች ቀለባቸውን ለምነው ነበር የሚያገኙት። ተማሪዎቹ፤ በትረ ውዳሴ ማርያም፣ቅዳሴ እና መዝሙረ ዳዊትን እንዲሁም በግዕዝ ቋንቋ በሚገባ አጥንቷል። አሁን በቅኔ ቤት አንድ ዓመት ያስቆጠረ በመሆኑ እራሱን በዕውቀት ሲገመግም አጋማሽ ላይ ይገኛል። የቅኔ ቤት የጨረሰ ተማሪ ወደ አቋቋም ቤት ነው የሚሸጋገረው። በአቋቋም ቤት ደግሞ ሙሉውን ያወቀ ተማሪ ቀጣዩ ክፍል የዜማ ቤት ነው የሚሆንለት። ጠንካራ ተማሪም ከሆነ የቅኔ ቤትን ለመጨረስ እስከ ሁለት አመት ሊፈጅበት ይችላል። ነገር ግን እንደ ዘመናዊ
ትምህርት ግማሹን ወይም አብዛኛውን ስላወቀ ብቻ ከአንዱ ክፍል ወደ ሌላው አይሸጋገርም። ይልቁንም
ሙሉ በሙሉ ከመምህሩ የሚሰጠውን ዕውቀት ተቀብሎ ብቁ እስካልሆነ ድረስ በእድሜ ቆይታ ብቻ አያልፍም። ያለዕውቀት ያለፈ ተማሪ በኋላ ላይ ማነው ያስተማረህ ተብሎ ስለሚጠየቅ እና የመምህሩ ጥንካሬ ስለሚፈተሽ ሁሉም ተማሪ በቃሉ ሸምድዶ ዕውቀቱን ሲይዝ
ወደ ሌላ ትምህርት ክፍል ይሸጋገራል። ግስ እና ታሪክ የመሳሰሉ መጻህፍትንከባህር ዳርእና ከተለያዩ
7 163
የደጋግ ቅዱሳን እግሮች አርፈውበታል። ሙኃዘ ጸሎታቸው ፈሶበታል። ድምፀ ውዳሴያቸው ተሰምቶበታል። ሊቃውንቱ ምስጢር ሊያዋድዱ አንዱ ከአንዱ ተፋጭተውበታል። የምስጢር ወርቀዘቦ የደረቡ ቅኔያት ተጎማለውበታል። የሴት ምሁራትም ቅኔ ሊዘርፉ ሰገነቱ ላይ ተገማሽረውበታል። የሊቃውንቱ ብሂል የመነኮሳቱ ክሂል ተደንቆበታል። ቅዳሴ አይታጎልም። ኪዳን አይለይም። ስብሐተ ነግህም አይቋረጥም።
ቤተ ክርስቲያን ድኅረ ፍጥረት ያልኖረችበት ዕድሜ ያለተገችበት ሥፍራ የለም። ነገር ለመመጠን የቅዱሳን ከተማ የክርስቲያኖች ባድማ ወደ ሆነችው ኢትዮጵያ እንኳ አብዝተን ስናማትር ፍርኩታዋ በበረከት ዋሻዋ በምህረት የተሞላ ነው። ጫካዋ በመዐዛ ቅዱሳን ያቁደሰድሳልል። ምድሯ ሁሉ በቅዱሳን አጽም የታጨቀ አፈር ሳይሆን እምነት ነው። እናም ኢትዮጵያ የክርስቲያን አገር ብቻ ናት ሳይሆን ራሷም ክርስቲያን ናት። የታመነች አማኝ ምድር!
➻ ጥንት በጌታዋ ደም ዛሬም በልጆቿ ደም የምትጠመቅ ፍጽምና ያላት ክርስቲያን!! እናም ኢትዮጵያ ይሏት አገር በማሕጸኗ እምነቷን የሚገልጹ አቻ የለሽ ስፍራዎችን ተሸክማለች። ከእነዚህ ስፍራዎች መካከል አንዱ ዲማ ጊዮርጊስ ነው። ዲማ ጥንተ ነገሩ ወዲህ ነው። ይህ ታላቅ ገዳም በምስራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ውስጥ በቢቸና ወረዳ ይገኛል። ዲማ የስሙ ትርጓሜ ሁለት ነገሮችን ይዟል። ድማኅ ሲል መካነ አዕምሮ የሚል ፍች ይሰጣል።
➻ ገድላቱ በዝተው የተከተቡበት። መልኮች የተገጠሙበ፤ ድርሳናቱ የተደረሱበት ጤናማ ዘመን። የገዳሙ ጥንተ መሥራች አባት አባ በኪሞስ ናቸው።
ምስጢር የሚጠየቁ ሥርዓት የሚያስጠብቁ፣ በምስጢር የሚራቀቁ ለተዋሕዶ የሚዋደቁ ሊቃውንት ከዲማ ተወልደዋል። በታሪክም በሕይወትም ከሚታወቁት መካከል:- መላከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬ፣ መምህር ወልደ ማርቆስ፣መምህር ወልደ ኢየሱስ መቅጫ፣ አለቃ አያሌው ታምሩ፣ መምህር ዘሚካኤል ይሁኔ፣ የኔታ ይባቤ ዘናዳ፣
➻ መጋቤ ሐዲስ ደጉ ዓለም ካሳ፣ የኔታ ነቅዐ ጥበብ ዘጎንደር፣ ሊቀ ሊቃውንት ያሬድ ሽፈራው፣ ሊቀ ሊቃውን ሰሎሞን ዘማርቆስ፣ ሊቀ ሊቃውንት አካለ ወልድ፣ ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ፣ ሊቀ ሊቃውንት ሥሙር አላምረው፣ መጋቤ ብሉይ አዕምሮ ዘውዴ፣ ሊቁ ማዕበል ፈጠነ፣ መጋቤ ሀዲስ መንግሥቱ አማረ፣
አንዳንዶች ‹‹የኢትዮጵያ ቅኔ ዩኒቨርሲቲ ነው›› ይሉታል። ምክንያቱም ተማሪው ከመምህሩ ጋር ሰምና ወርቁን እያስማማ ሲዘርፍ ማስተዋል በቦታው የዕለት ተዕለት ተግባር
ስለሆነ። ሌሎች ደግሞ የፍቅር እስከ መቃብር ታሪክ እትብት የተቀበረበት ስፍራ ነው ይሉታል። ምክንያቱም የሚያውቁት የሐዲስ አለማየሁ የፍቅር እስከመቃብርድርሰት ታሪክ ዋነኛ መቼት በመሆኑ ነው። ዲማ ከአዲስ አበባ በደጀን ታጥፎ ወደ
ሞጣ በሚጓዘው መንገድ ከብቸና ከተማ በስተ ምስራቅ ይገኛል።
ውብ የባህል፣የሃይማኖት እንዲሁም የተፈጥሮ ቦታ ነው ‹‹ዲማ ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም›› በምስራቅ ጎጃም ዞን እነማይ ወረዳ ከሚገኙትስመ ጥር የቱሪስተ መዳረሻዎች መካከል አንዱ ነው፡ ፡
እነማይ ወረዳ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በምስራቅ ጎጃም ዞንከሚገኙ 21ወረዳዎች ውስጥ አንዱ ነው። እነማይ ከአዲስ አበባ በ265 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል።ከባህርዳር ደግሞ በ222 ኪሎ ሜትር ርቀት አለው። ይሁንና ታሪካዊውን በይበልጥ ታዋቂ ያደረገው የሐዲስ አለማየሁ ድርሰት መሆኑ የማይካድ ነው።
የገዳሙ ትርጓሜ የገዳሙ መጠሪያ ስም በቀድሞ ዘመን ‹‹ደብረ ድማህ›› ይባልየነበረ ሲሆን ከጊዜ ቆይታ በኋላ ስያሜው ወደ ‹‹ዲማ›› ተለወጧል። ታሪክ አዋቂ
አባቶች እንደሚሉት ከሆነ ደብረ ድማህ ማለት ከግዕዝ የተወረሰ ቃል ሲሆን ትርጓሜውም(ራስ፣የሁሉ የበላይ ወይም ጭንቅላት) እንደማለት ነው። ከዚህ ትርጓሜ መረዳት እንደሚቻለውቦታው በጊዜው የጎጃም ማዕከል እንደነበረ ነው። የገዳሙ መጠሪያ ስም ‹‹ደብረ ዲማ›› ሲሆን በትርጓሜው መሰረት ገዳሙ የሁሉ የበላይ መሆኗን ለማመላከት የወጣ መሆኑን መገንዘብ ያስችላል። በሌላ በኩል ዲማ ማለት ቀይ ማለት እንደሆነ የሃይማኖት አባቶች ይናገራሉ። በጊዜው አንድ ትልቅ ቀይ ዛፍ በቦታው ስለነበረና ስሙም ከዚህ የተወሰደ መሆኑን ለማመላከት
እንደሆነም ይነገራል፡፡
ዲማ ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም የተመሰረተው በአፄ አምደ ጽዮን ዘመነ መንግስት በ1297 ዓ.ም ነው። ከአፄ ይስሃቅ ዘመነ መንግስት ጀምሮ ደግሞ በገዳምነት ተሰይሞ፤ በሚሰጠው ትምህርት አማካኝነት ዝናው የናኘ ሊሆን በቅቷል። ዲማን የመሰረቱት አባት አባ በኪሞስ የተባሉ ሰው ናቸው። በጎጃም እየተዘዋወሩ ወንጌልን በመስበክ እየጠመቁ ሳለ አንድ ቀን ከአማንያን ብዛት የተነሳ የማጥመቅን ስራ ሳይጨርሱ ጀንበር ትጠልቅባቸዋለች።
ይህ ሲሆን አምላክን ይለምኑታል። ብርሃንም ወርዶላቸው ስርዓተ ጥምቀቱን ይፈፅማሉ። ይሄ ተእምር
እንዲፈፀም ያስቻሉት አባት ከዚያ ጊዜ በኋላ ስማቸው ተከስተ ብርሃን እንደተባለ እና በገዳሙ
ታሪክ ትልቅ ቦታ እንደተሰጣቸው በድርሳናት ላይ ተፅፎ እንደሚገኝ መረጃዎች ይጠቁማሉ።ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የሀዲስ ኪዳን ሥርዓተ ህግ መሠረት አራት የአስተዳደርሥርዓቶች አሉ፡፡ እነርሱም ደብር፣ ገዳም፣ ገዳም ወደብር እና ገጠር በመባል ይታወቃሉ። የዲማ ጊዮርጊስ አስተዳደር ሥርዓት ደግሞ ገዳም ወደብር የሚባለው ዓይነት ነው።
ባህሪውም ስጋዊና መንፈሳዊ ገጽታ ያለው ሲሆን የገዳምነትንና የደብርነትን ስራ አጣምሮ ይዟል። እንደገዳምነቱም በመነኩሴ ብቻ ነው የቅዳሴ ሥነሥርዓት የሚካሄደው። አስተዳደሩንም በበላይነት ይመሩታል።እንደ ደብርነቱ ደግሞ ስጋዊ ህይወት የሚመራበት በመሆኑ ስጋዊ የአስተዳደር ሥርዓትም ጐን ለጐን ይካሄድበታል፡፡ የዲማ ገዳም ወደ ብር የሰበካ ጉባኤ በበላይነት የሚተዳደረው በመነኩሴ ሲሆን መጠሪያ ማዕረጉም ‹‹ርዕሰ መምህር›› ይባላል።
መምህሩ የሚመረጡት በህዝብ ነው፡፡ የሃይማኖት ህፀፅና ነውር ካልተገኘባቸው በስተቀር እስኪሞቱ ድረስ ወንበራቸው የፀና ነው።
የገዳሙ ቅኝት ዲማ ጊዮርጊስ ከትንሿ የገጠር ከተማ በስተደቡብ ከደልዳላ ስፍራ ላይ በአረንጓዴ እጽዋት መሀል ይገኛል። በደራሲ ሀዲስ አለማየሁ ፍቅር እስከ መቃብር ውስጥ የተጠቀሱትን መንደሮች አቀማመጥና የቤቶች አሰራር ሲመለከቱ ድንገት የዋና ገፀ ባህሪዎቹ የበዛብህና ሰብለ ወንጌል ታሪክ ትውስ ይላል። በቦታው የካህናት ዜማ እናየከበሮው ድምፅ ሲያስተጋባ በምናብ ይደመጣል። የዲማ ጊዮርጊስ ደብር ዙሪያውን የታጠረ ሲሆን ከድንጋይና ከጭቃ የተገነባ ነው። ከፍታው ሁለት ሜትር ተኩል ይደርሳል። ውፍረቱ ደግሞ ከሁለት ሜትር
በላይ እንደሚሆን ይገመታል። ይህ አጥር በክረምት ወቅት አረምና የሙጃ ሳር ስለሚበቅልበት ከርቀት ሲታይ ቁጥርነቱን ለመለየት እንደሚያስቸግር የአካባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ። መሀል ላይከነ ግርማ ሞገሱ ጉብ ብሎ የሚታየው የጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ጣሪያ ከረጃጅም የጥድ፣ የወይራና የዋንዛ ዛፎች በላይ ከፍ ያለ ነው። ጣሪያው የቆርቆሮ ክዳን ሲሆን ከጣሪያው አናት ላ ባለው ጉልላት የተንጠለጠሉት መርገፎች (በጉልላቱ እና ክፈፉ ላይ የሚሰቀሉ
