ፈለገ ጥበባት +++
Open in Telegram
+++የቀደምት ኢትዮጵያውያን ስልጣኔን ማሳየት እንዲሁም ገዳማት እና አድባራትን ማሳወቅ፡፡+++ የተረሱ አድባራትና ገዳማትን ማስታወስ ፤የ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያንን ጥበብ እውቀትን በምንችለው ሁሉ መመርመር የአባቶቻችን ልጆች በመሆን ትላንት በዛሬ እና በነገ ውስጥ ማስቀጠል ማስቻል ነው።
Show more7 163
Subscribers
-524 hours
-267 days
-7330 days
Posts Archive
7 163
የዓመቱ መስከረም 1 ቀን መቼ መቼ ትውላለች?
መስከረም አንድ ቀን መቼ እንደምትውል ለማወቅ ዓመተ ዓለምን ከመጠነ ራብዒት ጋራ ደምረን በእለታቱ መጠን በ7 አካፍለን
ቀሪው 1 ከሆነ ማክሰኞ ፤ቀሪው 2 ከሆነ ረቡእ፤ቀሪው 3 ከሆነ ሐሙስ፤ቀሪው 4 ከሆነ አርብ፤ቀሪው 5 ከሆነ ቅዳሜ፤ቀሪው 6 ከሆነ እሑድ፤ ያለ ቀሪ ከተካፈለ ሰኞ ይውላል።
የ2015 ዓ.ምየኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር 🌏
=========
👉በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር ከክርስቶስ ልደት በፊት ዘመን የተቆጠረበት ጊዜ 5,500 ዓመት ነው ።
👉ይህም ዘመን ዘመነ ፍዳ፣ዘመነ ኩነኔ፣ ዘመነ ብሉይ ይባላል ።
👉ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ጀምሮ ያለው ዘመን 2,015 ዓመት ሲሆን ይህም ዓመተ ምህረት ፣ዘመነ ሥጋዌ ፣ዘመነ ሀዲስ ፣ዘመነ መሲሕ ይባላል ።
👉ዘመነ ብሉይ እና ዘመነ ሐዲስ ሲደመሩ ውጤታቸው ዐመተ ዓለም ተብሎ ይጠራል ።
👉5,500ዓመተ ፍዳ+2,015 ዓመተ ምሕረት
=7,515 ዓመተ ዓለም
👉የዓመተ ዓለም ጥቅም ዓመተ ወንጌላውያንን ለማውጣት ይጠቅመናል።
👉የ2,015 ዓ.ም ወንጌላውያኑን ለማወቅ ዓመተ ዓለምን ለአራት ማካፈል ነው ።
ሲካፈል ቀሪው
1ከሆነ ማቴዎስ 2ከሆነ ማርቆስ 3ከሆነ ሉቃስ ያለቀሪ ከተካፈለ ዮሐንስ ነው።
👉የ2,015 ዓ.ም ወንጌላውያኑን ለማግኘት
ዓመተ ኩነኔ+ዓመተ ምህረት =ዓመተ ዓለም
5,500+2,015 =7515
7515÷4 =1878 ቀሪው 3️⃣ነው ።
ምክንያቱም 1878×4=7512 ሲሆን
7515-7512=3️⃣ነው ።
ስለዚህ የ2015ዓ.ም ወንጌላዊ ቅዱስ ሉቃስ ነው።
👉ለ4️⃣ተካፍሎ የሚደርሰው 1878 ቁጥር መጠነ ራብዒት ይባላል ።
👉መጠነ ራብኢት ማለት ለ4️⃣ተካፍሎ የደረሰ ማለት ነው ።
👉ለኢትዮጵያውያን የዘመን መለወጫ መስከረም አንድ ቀን ነው።
👉መስከረም 1️⃣ቀን ለማግኘት ዓመተ ዓለምን እና መጠነ ራብኢትን እንደምራለን ።
👉የተደመረውን ቁጥርለሰባት ቀናት ማካፈል ።
በዚህም መሠረት ለ7️⃣ቀናት ተካፍሎ የሚቀረው 1ከሆነ ማክሰኞ 2ከሆነ ረቡዕ 3ከሆነ ሐሙስ 4ከሆነ ዓርብ 5ከሆነ ቅዳሜ 6ከሆነ እሑድ ያለቀሪ ከተካፈለ ሰኞ ይሆናል ።
👉ስለዚህ የ2,015ዓ.ም መስከረም 1️⃣ቀን
7515+1878=9393 //9393÷7=1341ቀሪ 6️⃣ነው
ምክንያቱም 1341×7======9387ይሆናል ።
9393-9387===6 ነው
ስለዚህ የ2,015 ዓ.ም መስከረም 1️⃣ቀን በዕለተ ዕሑድ ይውላል ።
መስከረም 1 በዋለበት ሚያዝያ 1 ይውላል
ጥቅምት 1 በዋለበት ግንቦት 1 ይውላል
ህዳር 1 በዋለበት ሰኔ 1 ይውላል
ታሕሣሥ 1 በዋለበት ሐምሌ 1 ይውላል
ጥር 1 በዋለበት ነሐሴ 1 ይውላል።
ይህም ማለት ለምሳሌ መስከረም 1 ቀን እሁድ ከዋለ ሚያዝያ 1 ቀንም እሁድ ይውላል ማለት ነው።
7 163
ሰላም የፈለገ ጥበባት ቤተሰቦቸ
እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ፡፡
የኢትዮጵያን የዘመን አቆጣጠር በአጭሩ ....
በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር ዓመታት ሁሉ በአራት መደባት
ይዞራሉ፤ እነሱም ስለ ሐዋርያት ስሞች ዘመነ ማቴዎስ፣
ዘመነ ማርቆስ፣ ዘመነ ሉቃስ (ተጨማሪ የጳጉሜ ቀን
የሚቀበለው) እና ዘመነ ዮሐንስ ይባላሉ።
በኢትዮጵያ ታላቅ የጊዜ ቀመር መፃህፍ የሚያስረዳ ባህረ ሀሳብ የሚባል መፃህፍ አለ እወቀቱ እና ሰፊ ምርምሩ በአቡሻህር(አቡሻክር) አዋቂወች የእወቀት ልኬት የሚወሰን ነው፡፡
የኢትዮጵያ ዘመን ኣቆጣጠር የጁልያን ዘመን ኣቆጣጠር
ኣይደለም። በኣሁኑ ጊዜ በጁልያና በጎርጎርዮስ ካለንደሮች መካከል ያለው የ13 ቀናት ልዩነት ሲሆን የዓመታቱ ቍጥሮች
ልዩ ኣይደሉም።
ኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የ ኢትዮጵያ (እንዲሁም
በ ኤርትራ አብያተ ክርስትያናት) ዋና ካሌንደር ነው። አዲስ ዓመት በ ጁሊያን ካሌንደር አቆጣጠር በ ኦገስት 29 ወይም 30 የሚጀምር ሲሆን በግሪጎሪያን ካሌንደር ደግሞ ከ 1901 እ.ኤ.አ. እስከ 2099 እ.ኤ.አ. ድረስ በሴፕቴምበር 11 ወይም 12 ይጀምራል።
ለመሆኑ የኢትዮጵያ አዲስ አመት ስንት ሰአት ነው የሚገባዉ ?
አንድ አመት የሚባለው የመሬትና የፀሀይ ኡደት ነው መሬት ኡደቷን ለመጨረስ አንድ አመት ወይም 365 ከ 1/4 ቀን ይፈጅባታል
ስለዚህ ማቴወስ (12ወር *30ቀን +5ቀን ጳጉሜ)+ 6 ሰአት( 1/4 ቀን ማለት 6 ሰአት ነው)
መሬት ኡደቷን ለመጨረሳ ከ365 ቀን ትርፍ 6 ስአት ያስፈልጋታል ፡፡
ማርቆስ እንደዚህዉ እንደሉቃስ ይቆጠራል ሉቃስም ያው ነው ከእያንዳንዱ ያልተቆጠሩ 6 ስአት አሉ የማቴወስ 6 ማርቆስ 6 ሉቃስ ስድስት ሲደመር ዮሐንስ 6 አንደ ቀን ሙሉ ትሆንና ጳጉሜ 6 ቀን ትሆናለች ማለት ነው፡፡
ስለዚህ የዘመን መለወጫ ሰአቱ ስንቶ ሰአት ይሆናል ?
ይህንን ብዙ ጊዜ ካስተዋላችሁ ከነጮቹ የተወሰደውን ከለሊቱ 6 ስአት የዘመን መለወጫ ነው ተብሎ እኛው ጋም ይከበራል ግን ስተት ነው፡፡
ለምን ካላችሁኝ ኑ ላሳያችሁ.....
ቀደም ሲል እንደጠቀስኩት መሬት ኡደቷን ለመጨረስ ከ 365ቀን + 6 ስአት ትፈልጋለች ስለዚህ
ለምሳሌ ዘመኑ ማቴወስ ኑሮ ማርቆር ሊገባ ቢሆን በስንት ሰአት ሊገባ ይችላል፡፡
ማቴወስ አመቱን የሚጨረሰዉ ልክ ጳጉሜ 5 ከንጋቱ 12 ስአት ነው ነገር ግን ትረፏ 6 ስአት ስላለች በትክክለኛው ከቀትሩ 6 ስአት የማቴወስ ዘመን መለወጫ ይሆናል ማረቆስ ምሽት 12 ስአት ሉቃስ ለሊት 6 ስአት ዮሀንስ ደግሞ ከንጋቱ 12 ሰአት ይሆናል ማለት ነው፡
እንዴት የአጽዋማት እና በአላት እንደሚወጡ እንመለከታለን ብእር አዘጋጁ ወረቀትም አቅረቡ፡፡
የኢትዮጵያውያን የዘመን ስሌት....
ጠቢባን የሆኑ አባቶቻችን የዘመን ስሌትን በሚገባ ተንትነው ዘመናዊቷ አለም ከምትጠቀምበት አቆጣጠር ረቀቅ ባለ መልኩ እስከ ሳድሲት ማለትም 0.00000185 ሰከንድ ድረስ አስለተዋል።
መሬት በፀሐይ ላይ በምታደርገው ኡደት ን ተረድተው የጊዜ መለኪያ እና መቁጠሪያ አስቀመጠውልናል ....
1ኛ ሳድሲት ይህ ቁጥር 0.00000185 ሰከንድ ነው።
2ኛ ኀምሲት ይህ ቁጥር 0.00011 ሰከንድ ነው።
3ኛ ራብዒት ይህ ደግሞ 0.0067 ሰከንድ ነው።
4ኛ ሣልሲት ይህ ደግሞ 0.4 ሰከንድ ነው።
5ኛ ካልዒት ይህ ደግሞ 24 ሰከንድ ነው
6ኛ ኬክሮስ ይህ ደግሞ 24 ደቂቃ ነው።
60 ኬክሮስ=1 ዕለት ወይም 24 ሰዓት ነው። ይህ ደግሞ 1 ሰዓት 2.5 ኬክሮስ ነው ማለት ነው።
ጨረቃ በቀን ከፀሐይ 1 ኬክሮስ ከ 52 ካልዒት ከ 31 ሣልሲት በአነሰ ነው።
በቀን 1 ኬክሮስ በ30 ቀን 30 ኬክሮስ ይሆናል።
በ2 ወር 60 ኬክሮስ ይሆናል። 60 ኬክሮስ ደግሞ 1 እለት ስለሆነ።በ2 ወር 1 እለት በ12 ወር 6 እለት
ታበራለች ማለት ነው።
በ12 ወር ወይም በአንድ አመት 5 ቀንና 15 ኬክሮስ ከ1 ሣልሲት ይሆናል።...... የቀረችው 52 ካልዒትን ልቀይረው.... 52 ካልዒት×30 ቀን×12 ወር=18720 ካልዒት በአመት ይገኛል።
ይህንን ወደ ኬክሮስ ስንለውጠው 312 ኬክሮስ ይመጣል።በመቀጠል 30 ሣልሲት×30
ቀን×12 ወር 10800 ሣልሲት ይመጣል ይህንን ወደ ኬክሮስ ስንቀይረው 3 ኬክሮስ ይሆናል።
ይህ ማለት የ 52 ካልዒትየ 30+(1) ሳልሲት ጠቅላላ ስንደምረው ... 312+3=315 ኬክሮስ ይሆናል።
ይህንን ወደ እለት ስንቀይረው 5 ቀን ከ15 ኬክሮስ ይሆናል።....
ይህች 5 ቀን ተሰብስባ ጷግሜን ናት.....።
የተረፈችው 15 ኬክሮስ ለ4 አመታት ስትጠራቀም... በ4 ዓመት 4×15=60 ኬክሮስ ወይም አንድ እለት ይሆናል። በአራት ዓመት አንድ ጊዜ ጳጉሜን 6 የምትሆን በዚህ ምክንያት ነው።.....
ከላይ የ 30 ዋን ሳልሲት ሰርቸ አንዷን አላሰላሆትም....አንዷ ሣልሲት በ600 ዓመት 1 ቀን ትሆናለች።ይኽውም 1 ሣልሲት×30 ቀን×12 ወር×600 ዓመት 216000 ሣልሲት ይገኛል ይህንን ወደ
ኬክሮስ ስንቀይረው 60 ኬክሮስ ይሆናል።60 ኬክሮስ ደግሞ አንድ ቀን ወይም እለት ነው። ስለዚህም በ600 ዓመት አንድ ጊዜ ጳጉሜን 7 ትሆናለች ማለት ነው።...
ወይም በቀላል መንገድ ላሳያችሁ...
አንድ ቀን =365 እለት ከ 15 ኬክሮስ ከ 6 ካልዒት /
ወይም 365 ቀን ከ 6 ስዓት ከ 2 ደቂቃ ከ 24 ሰከንድ ነው...36o ቀን + 5 ቀን ጳጉሜ .. ይሆንና 6 ስአት ከ 2 ደቂቃ ከ 24 ሰከንድ ትተርፍለች... የተሰባሰበችው 6 ስአት በ አራተኛው አመት 24 ስአት ወይም አንድ ቀን ስትሆን ጳጉሜ 6 ትሆናለች። ትራፊ 2ደቂቃ ከ 24 ሰከንዷ ትሰበሰባለች ይህ ማለት በ 600 አመት 24 ስአት ወይም አንድ ቀን ትሞላለች።
ይህ በ 600 ኛው አመት ጳጉሜን 7 ያደርጋታል ማለት ነው.....
አበቅቴ እና መጥቅእ
አበቅቴ ማለት ተረፈ ዘመን ማለት ነው።ይህም ማለት ጨረቃ ከፀሐይ ባነሰ የምታበራበት የጊዜ መጠን ነው።ፀሐይ በዓመት 365 ቀን ከ15 ኬክሮስ ከ1 ሣልሲት
ታበራለች።ጨረቃ ደግሞ 11 ቀን አንሳ 354 ቀን ታበራለች።በሁለቱ መካከል ያለው ልዩነት አበቅቴ ይባላል።
ስለዝህ በባቶች በተገለጠላቸው መጠን 11 ጥንተ አበቅቴ ይባላል።
መጥቅዕ ማለት ትረጉሙ ደወል ሲሆን አጽዋማትን እና በዓላትን የሚያስገኝ ነው ከዚህ ላይ ተንተረሰን በዚህ ቀን ይህ ጾሜ በዚህ ዕለት ይህ በዓል ለማለት ያስችላል...።
መጥቅዕ እና አበቅቴ ተደምረው 30 መሆን ስላለባቸው መጥቅዕ 30-11=19 ይሆናል።
ስለዚህ በመጀመሪያው ዓመት 11 አበቅቴ ከሆነ በሁለተኛው አመት 22 ይሆናል በሦስተኛው 33 ይሆናል።ከ30 በላይ ሲሆን በ30 አካፍለን ቀሪውን እየያዝን አበቅቴን እናወጣለን ስለዚህ 3 ይሆናል።ከዚያ በአራተኛው 3+ 11=14 እያለ ይሄዳል።አበቅቴና መጥቅእ ሁለቱ ተደምረው 30 ስለሚሆኑ አንዱ ከተገኘ ሌላኛውን ከ30 በመቀነስ እናገኘዋለን።
አለም ከተፈጠረች ጠቅላላ ዕድሜ 5500+2015=75135አመት....ስለዚህ በሚቀጥለው ዓመት ዘመኑ ዘመነ ማን ነው የሚለውን ለማወቅ ስንፈልግ ዓመተ ዓለሙን ለ4 አካፍለን
ቀሪው 1 ከሆነ ዘመነ ማቴዎስ ፤ቀሪው 2 ከሆነ ዘመነ ማርቆስ ፤ቀሪው 3 ከሆነ ዘመነ ሉቃስ ያለ ቀሪ ከተካፈለ ዘመነ ዮሐንስ ነው።
7 163
ሁላችን ልናውቀው የሚገባ አስደናቂው የዘመን አቆጣጠራች ! ..
እጂግ አስደናቂውን የባህረ ሃሳብ ሚስጥር..ከደቂቃወች በኋላ በዩቲቭ ቻናላችን ይጠብቁን!
7 163
ሰለም!
የጳጉሜ ሚስጥራዊ ክስተቶች ?
የባህረ ሃሳባችን ረቂቅ ቀመር?
የኢትዮጵያውያን የዘመን አቆጣጠር ከ ሌላው አለም በምነስ ተለየ?
የ ጨረቃና ከዋክብት ኡደት ስለ መጭው ዘመናት ምን ይላሉ? .....ቀለል ባለ አገላለጽ ለ አድማጭ ተመልኳቾቻችን ከ አባቶቻችን የሰማነውን ይህንን ረቂቅ ሚስጥር እናቀርብላችኋለን።
7 163
ከደቂቃወች በኋላ እጂግ አስደናቂውን የጎግና ማጎግ አገራት ማንነት በእኛ ዘመን እየተከሰተ ስላለው የማጎጋውያን መነሳት እና የአርማጓዶን ጦርነት..እስክንድር የቆለፈባቸው አስፈሪ ፍጥረታት መቸ ይወጣሉ? በምድራችን ላይ የት ይገኛሉ ? ....ከ ዘመናዊ የአለም ትንታኔወችን ጨምረን ታላላቅ የብራ ና ላይ ጹሑፎች ምን ይላሉ...በዩቲቭ ቻናላችን ይጠብቁን!
7 163
እጂግ በርካታ ለምዕመን ይፋ ያልወጡ ፤ዘመን ያስረጃቸው ዘመን ተሻጋሪ ድንቅ እና ልዮ ሚስጥራትን የተሸከምችው ኢትዮጵያ በአወቅናት ልክ እንገልጣታለን....!
የታቦተ ጽዮንን መገኛ በይፋ ለአለም እንደ አስተዋወቀው እንደ ግራም ሀንኩክ ከ አውሮፖ መጥቶ '' ታቦተ ሚካኤልን ፍለጋ'' ብሎ መጻህፍ እስኪ ያ ሳትም አትጠብቅ...!
የሚስጥር መንገዷ እንጂ መዳረሻዋ አይነገርም....!
ምክኒያቱም ክብረ ነገስትን ይዘው ይሞግታሉ ከክብረ ነገስት እጂግ ቀድመው የተጻፉትን መጻህፈት ስላላዮ ስላለነበቡ። ነገር ግን የሙሴው ቅድስ ማካኤል ታቦት የሚገኘው ኢትዮጵያ ውስጥ ተከዜ ከሚመነጭበት ራስ ልዩ ስሙ አየለ(እየላ) ሚካኤል አካባቢ አለ ታዲያ ይህ ታቦት እዚህ አካባቢ አለ ማለት አዛው ቦታ አለ ማለት ሳይሆን በዋሻ ውስጥ በክብር ተቀምጧል።
ይህ እውነት ነው ታሪክን መመር መር ማወቅ መረዳት መጠየቅ ሀገርን በእውነተና ማንነቷ ለትውልድ ማሻገር ያስችላል።
በአናብረትና በአናብስት ስለ ምትጠበቀው ታቦተ ጽዮን ከዚህም በላይ እጂግ ድንቅ ነገር ብነግራችሁ በወደድኩ ግን መልካም አይሆንም ጊዜው ይግለጣት በእግዚአብሔር ፈቃድ ትገለጽ።
ታላላቅ ሚስጥራት ያላቸውን ለሙሴ ከእግዚአብሔር የተሰጠው እቃወች ጭምር ነው ...... ሰምታችኋል! ።
እኒህም ቀጸላ መንግስት፣ በትረ መንግስት፣ ሞኣ መንግስት፣ ህገ መንግስት ፣እና ታቦተ ህግ ናቸው።
ቀጸላ መንግሰት ፦ ንጉሱ ዘውድን ሲደፋ የሚደረበው ከእግዚአብሔር ለሙሴ የተሰጠው ዕቃ ነው።
በትረ መንግስት ፦ታላቅ ሀይል ያለው ንጉስ ሲነግስ የሚይዘው ታላቅ ሃያል በትረ ነው።
ህገ መንግስት፦ እንደ ኦርት ዘዳግም ያለ መጻህፍ ሲሆን በይዘቱ እና በስፋቱ ግን የተለየ ቅዱስ መጻህፍ ነው።
ታቦተ ህግ፦ ጽላተ መሴ(ጽዮን) እና የሙሴን መጻህፍት የያዘ ነው።
ሞኣ መንግሰት ፦ይህ ረቂቅ ታላቅ ሃያል ሲሆን በሀገሪቱ መከራ ፣ቸነፈር ፣ረሀብ ፣ ሰውን የሚገል የሚያሰቃይ አንባገንን መንግስት ሲነሳ ከመንበሩ በክብር ይወጣል ፤ በካህናት ምህላ ተይዞ ይጸለይበታል፤ ይህ ጠላትንም አሳፍሮ አዋርዶ ይልካል። ሀገርን ሰላም ያረጋል ምህረትንም ያወርዳል።
ታዲያ ጣሊያንን የመሰለ ሀያል ብረቱ ጠንካራ በጊዜው እንኳን በአፍሪካ በአውሮፖ የሚወዳደራት የሌላ ሃያል ሀገርን አንዲት የተንኮታኮተች የምትመስል ሀገር ከአንድም ሁለት ጊዜ አሳፍራ የላከቻት ዋናው ሚስጥር በዚህ ሞኣ መንግስት በተባለው ሀይል ባለው ሱባኤ ተይዞ ተጸልዮ ድልን ስለሚያሰጥ ነው። በአጭሩ ይህ ሞኣ መንግስት ማለት ለመፈንቅለ መንግስት የሚውል ነው..
ታዲያ ከእግዚአብሔር ለሙሴ የተሰጠው ከ3 ሺ አመት ቀፊት በቀዳማዊ ሚኒሊክ ወደ ኢትዮጵያ የመጡት አምስቱ ታላቅ ሃይል ያላቸው ዕቃወች በፍጹም በፍጹም ተለያይተው ሊኖሩ አይችሉም።
እኒህም ወደ እኛቱ ምድር የመጡበት ዋና ምክኒያት እስከ ቅርብ ጊዜ ሞኣ አንበሳ ዘእምነገድ ይሁዳ ስዮመ እግዚአብሔር የሚለው ስረወ መንግስት ከአለም ሲጠፋ ከሰሎሞን ሚኒሊክ እስከ 255 ኛው ንጉስ ጸንቶ የኖረባት ሀገር ስለሆነች ነው። በእርግጥ ይህ የዘር ሐረግ ስረው መንግስት ተቋረጧል ቢባልም ዳግም እንደሚመጣ እናምናለን።
ታዲያ ታቦተ ጽዮንን ዝዋይ ይህን ያክል፤ ጣና ቂርቆስ ይህንን ያክል፤ ዘመን ተቀምጣለች የሚባለው ነገር ፈሊጥ ነው ይላሉ አበው ለምን ቢባል ከድሮዋ እስራኤል ልጆች እስከ አሁኑ ''MOSAD'' የእስራኤል የስለላ ድርጂት በአይነ ቁራኛ ለብዙሽ አመታት
ጀምሮ ዛሬም የሰሎሞንን ቤተመቅደስ ሰረተው ሊወስዷት ይፈልጋሉና.....ስለዚህ በረቀቀ መንገድ በፈሊጣዊ ስልት ሲገልጹት አንዲህ ነው።
ሌላው ከ እናታችን ጽዮን ጋር የመጣው ቅዱስ ሚካኤል ታቦት አለ ይህንን በእኛው ሊቃውንትም ተቀባይነት እንደሌለው አምናለሁ።
ምክኒያቱም ክብረ ነገስትን ይዘው ይሞግታሉ ከክብረ ነገስት እጂግ ቀድመው የተጻፉትን መጻህፈት ስላላዮ ስላለነበቡ። ነገር ግን የሙሴው ቅድስ ማካኤል ታቦት የሚገኘው ኢትዮጵያ ውስጥ ተከዜ ከሚመነጭበት ራስ ልዩ ስሙ አየለ(እየላ) ሚካኤል አካባቢ አለ ታዲያ ይህ ታቦት እዚህ አካባቢ አለ ማለት አዛው ቦታ አለ ማለት ሳይሆን በዋሻ ውስጥ በክብር ተቀምጧል።
ይህ እውነት ነው ታሪክን መመር መር ማወቅ መረዳት መጠየቅ ሀገርን በእውነተና ማንነቷ ለትውልድ ማሻገር ያስችላል።
ከትናንት ብንዘገይ ከነገ እንድንቀድም የቀደሙትን
የሥነ ጽሑፍ ሀብቶቻችንን መቃኘት፣ ማጥናትና መጠበቅ አለብን፡፡ ሀገር የምትቆመው በዕውቀትና በእውነት ነውና፡፡
ለጠቢብ አንድ ቃል ይበቃል ይላሉ አበው ፤በዚህ ጦማር እንዳልገልጸው ሰገቸ ፤እንዳልተወው ፈርቸ ያስፈርኩትን በረቀቀ እይታ ተመልከቱ እና በቻላችሁት አቅም መርምሩ።
ይህ ፈለገ ጥበባት ነው።
7 163
በኢትዮጵያ ሸለቆወች ለ በርካታ ሺ አመታት የታፈነው እውነትና አስደናቂ ው ሚስጥር !
የሙሴ ጽላት ታቦተ ጽዮን እና ታቦተ ሚካኤል.....
እጂግ አስደናቂው የጉዞ ማስታወሻ !
ያልተነገረው የሺ አመታት አስደናቂ ሚስጥር።
የት እና ወዴት ይገኛል...
ዛሬ አንድ በብዙሀኑ ያልታወቀ ታላቅ ሚስጥርን ልገልጥላችሁ ወደድኩ...
በ ታቦተ ሚካኤልን ፍለጋ !
ወደ ኢትዮጵያ ምድር የመጣውን የቅዱስ ሚካኤልን የቃል ኪዳን ታቦት ስናስብ...ወደ አንድ ድንቅ ቦታ አብራችሁን ተጓዙ ።
የተከዜ ወንዝ መነሻ እዬላ(አየለ) ሚካኤል.....የዋሻው ነገር....!
የአቡነ ዮሴፍ ዝጊት እና አቦሀይ ጋሪያ ተራራች ጥብቅ ስፍራ የሃያ ትላልቅ ወንዞች የተከዜ ተፋሰስ ወንዞች ምንጭ፤ ያልተነገረለት ታላቁ እየለ ሚካኤል... ።
የተከዜ ወንዝ ምንጭ የሆነውን ፤ዕድሜ ጠገቡ፤ በጉያው አቅፎ የያዘው ታላቅ ዘመን አይሽሬ ማንነቱ ን ልንገለጥ ፤እንዲሁም ለ ሺ አመታት ተዳፍኖ የኖረው ከታቦተ ጽዮን እኩል ታሪክ ስላለው ከእግዚአብሔር ለ ሊዋውያኑ ወገን ሙሴ፤ ሲወረድም ከታላቁ ጠቢብ ሰሎሞን ፤አልፎ በቀዳማዊ ሚኒልክ በኩል ፤ከታቦተ ጽዮን ጋ ወደ ምድረ ኢትዮጵያ ስለ መጣው እየላ ሚካኤል......
በሰሜን ወሎ ዞን በግዳን ወረዳ በአቦሀይ ጋሪያ ጥብቅ ስፍራ ከቅዱስ ላሊበላ -አቡነ-ዮሴፍ በ43 ኪ.ሜ እና ከአቡነ ዮሴፍ አቦሀይ ጋሪያ ተራራ በ8.4 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በድብሳ ኢየሱስ አጠገብ ወደ ሚገኘው ታላቅ እድሜ ጠገብ ገዳም በወፍ በርር ቅኝት አብራችሁኝ ትጓዙ ዘንድ ተከተሉኝ......
እኒህ ታሪክን ከ ሀይማኖታችን ጋር አዋደውና ፤ በማይናድ የቃል ኪዳን ሰንድ ዘመናትን ከተሻገሩ ፤ ታሪክን አሰናስለውና አስማምተው ከያዙልን ፤ዘመን አይሽሬ የትላንትን ነጽብራቅ ከሚያሳዩን፤ ጥቂት ህያው ምስክሮቻችን አንዱ ዕድሜ ጠገቡ እየላ ሚካኤል ነው።
ታላቅ አለምን የሚያስደምም ድንቅ ሚስጥርን ይዞ ለሺ አመታት ሳይገለጥ እና ሳይታወቅ የኖረው... .. የሙሴው.. የሌላውያኑ.. የሰሎሞን የጥንቱ ታቦት ቅዱስ ሚካኤል ።
ከአክሱም ስልጣኔ ጋር የተቆራኘ ታሪክ ያለውና፤ በዘመኑ የነበሩ ነገስታት ለሀይማኖታዊ ስርዓት ይገለገሉበት የነበረ ከአክሱም ፅዮን ማሪያም ታቦት ጋር ከእየሩሳሌም እንደመጣ ብዙሃኑ ጻህፍት እንኳን ያልተረዱት ታላቅ ሚስጥር ስለ ያዘው በዘመን ውስጥ ሚስጥሩን ለትቂቶች የገለጠው ቅዱስ ቦታ.. እየላ ። ዕድሜ ጠገቡ ታቦተ ቅዱስ ሚካኤል በአካባቢው ህበረ ተሰብ እየላ (አየለ) ሚካኤል ተብሎ ስለሚጠራው ከህዝብ ጋር ኑሮ ከሀገር ጋር ያረጀው ስላልተነገረለት ታላቅ ገዳምን እናውቅ ዘንድ በውሎ ክፍለ ሀገር እንወርዳለን ...
ይህ ቤተ-ክርስቲያኑ ከክርስቶስ ልደት በፊት በ987 ዓመተ ዓለም በቀዳማዊ ሚኒልክና በንጉስ ዛግየ እንደተመሰረተ ይነገርለታል፡፡ ከ ክርስቶስ ልደት ሺ አመት ቀደም ብሎ፤ ንግስት ሳባ ልጇን ሚኒልክን ከአባቱ ከ ሰለሞን ጋር ወደ እየሩሳሌም ልካዉ እንደተመለሰ ወደ ላስታ ሸዋ ሂዶ ግዛት እንድያስፋፋና አገር እንዲጎበኝ ላከችው... ፡፡ ወጣቱ ንጉስም ታቦቱን ከጥቂት ካህናት ጋር ይዘው ሰራዊቶቻቸውን አስከትለው ጉዟቸውን ቀጠሉ፡፡ ሁለት ወር ከሳምንት ከተጓዙ በኋላ ‹‹ላስታ አላዳ›› ከተባለ ቦታ ደረሱ፡፡
ወንዙንም እንደተሻገሩ ‹‹አተርጌ›› ከተባለ ስፍራ ደረሱ፤ አተርጌን በልምላሜዋና በምንጮቿ ብዛት እንዲሁም ተስማሚ የአየር ንብረቷን በተራራ ተከቦ የተንጣለለ
እርሻዋ ማርኳቸው አዳራቸውን እዚያው ለማድረግ ተስማሙ፡፡
ድንኳናቸውን በመትከል ወጣቶቹ ነገስታት፣ ካህናቱና ወታደሮቹ በየደረጃቸው ቦታ ቦታቸውን ያዙ፡፡ ይህን የሰማ የወቅቱ የላስታ ሀገረ ገዥ የነበረው አላርሶን መኳንቱንና እግረኛ ሰራዊቱን አስከትሎ በመሄድ ለንጉሶቹ የሚገባውን ግብር አቀረበ፡፡ ንጉሶቹም በዚህ አይነት ወቅቱን ጠብቆ እንዲገበር ግዛቱን እንደያዘ እንዲቀጥል ፈቀዱለት፡፡
በአተርጌ የተደረገው እረፍት አብቅቶ ለጉዞ ዝግጅት ሲጀመር የታቦተ ሚካኤል ሊዋውያኖቹ ካህናት ሶደቅና አዛሪያስ ሊቀ-ገበዙም ጰርጤዛ በአንድነት በመሆን ታቦቱን ተሸክመው ለመሄድ ሲሞክሩ ታቦቱ ከቦታው አልንቀሳቀስም በማለቱ ወደ ንጉሶች በመቅረብ ‹‹ታቦት ጽዮን ከእየሩሳሌም
መጥታ ምድረ- አክሱም ስትደርስ አልነሳም እንዳለችው ይኸም ታቦት ልናነሳው ብንሞክር እንቢ አለን››... ብለው ተናገሩ፡፡ ተከትለውም ከነገስታቱ ጋር ሲጓዙ የነበሩት ሀምሳ ነጫጭ ጊደር ላሞች በጠባቂዎችም ለመታለብ እንቢ እንዳሏቸውና ከነጥጆቻቸው እየ ፈረጠጡ ጥለዋቸው እንደሄዱ ተናግረው ሳይጨርሱ የንቦቹም ጠባቂ ንቦቹ መረን እንደሄዱበት ይናገራል፡፡
በዚህ ጊዜ ንጉስ ሚኒልክ በሁኔታው ተከዙ፡፡ ስለሆነም ንጉሱ ተከዙ ከሚለው በመውሰድ ምንጩ ተከዜ ተባለ፡፡ በኋላ ንጉሱ ለላስታው አገረ-ገዥ ለአራርሶንና ለተከታዮቻቸው ለመላው ህዝብና ሰራዊቱ እንዲህ የሚል አዋጅ አስነገሩ፡- ‹‹ይህ ሁሉ የተፈጸመው በፈቃደ እግዚብሔር ስለሆነ ይህ ቦታ ከአሁን ጀምሮ
አተርጌ ይባል የነበረው ተለውጦ አየለነ(አስቸገረን እንቢ አለን) ፣ ሁለተኛው ምንጭ አይነ ተከዜ አካባቢ ደብሰ/ድብሳ፣ ንቦች የሔዱበት ፀድፍ ይባል የነበረው መራና ገደል፣ ማዕከሉ አየለነ ሚካኤል ሆኖ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ የአንድ ጎረምሳ ዉሎ መንገድ የአየለነ ቅዱስ ሚካኤል መተዳደሪያ ይሁን፤ ካህናቱ ሳድቅና አዛሪያስ ጰርጤዛና ሌሎቹም ከነቤተሰቦቻቸው ለአየለነ ቅዱስ ሚካኤል አገልጋዮች ሁነው ስርዓተ አይሁድን፣ ደብተራ ኦሪትን እንዲፈጽሙ ፣ላሞችና ንቦች አይነ ተከዜን ለሚንከባከቡና ለአየለነ ለታቦቱ አገልጋዮች እንዲሆኑ አዘናል›› ብለው በመናገራቸው ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ታቦተ ህጉ በሚስጥር በአካባቢው ጥቅጥቅ ባለ ጫካ በአንድ ትልቅ የኮሶ ዛፍ ቅርፊት ውስጥ ቤተ-መቅደስ እስኪሰራለት እንዲቀመጥ ተደረግ፡፡
ንግስት ሳባ በነገሰች በ31 ዓመቷ በ987 ከዚህ አለም በሞት ስትለይ ቀዳማዊ ሚኒልክ እናቱን ተክቶ አክሱም ላይ የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት ሲሆን ንጉስ ዛጉየም ማዕከሉን እየላ አድርጎ ደቡብን ሲያስተዳድር ቆይቷል፡፡ ንጉስ ዛጉየ መስዋዕተ-ኦሪት ይሰዋበት እንደነበር የሚነገርለት እንዲሁም እንደ ቤተ-መንግስትነት ይገለገሉበታል እየተባለ የሚወራለት ከ3 እስከ 5 ኪሎ ሜትር ስፋት ያለው ዋሻ በቤተ-ክርስቲያኑ አካባቢ ይገኛል፡፡
ይህ ታላቅና እድሜ ጠገብ ቤተ-ክርስቲያን በ1985 በአካባቢው ህብረተሰብና በቤተ-ክህነት ድጋፍ እድሳት የተደረገለት ሲሆን በቅጠሩም የንጉስ ዛጉየ አጽም በክብር አርፎበታል።
በቅርብ የተሰራ ከተራሮች እቅፍ ውስጥ ያለ ውብ ቤተክርስትያን አለ፤ እኔ በግል ምልከታየ ያ ለታላቁ እስራኤልን ከግብዕፅ ባርነት ያወጣቸው የሙሴው እየላ ሚካኤል ታቦተ ህግ ከዚህ ቤተክርስቲያን አለ ብየ ባላምንም ፤ በዚሁ አቅራቢያ በዋሻው ውስጥ በሚስጥር እና ልዩ በሆነ ስፍራ በክብር በ ታላላቅ አባቶቻችን ከመንበሩ እንደተቀመጡ አምናለሁ።
በእርግጥ ይህንን እውነት ለመግለጥ እና እንደ ታቦተ ጽዮን የሌዋ ዊያኑ የሙሴውን እስራኤልን ከ ግብጽ ባርነት ያወጣቸውን የ ቅዱስ ሚካኤልን ታቦት በአለም ላይ ለማግነን እንዲሁም እውነቱን ለመግለጽ ሚስጥር አዋቂ አባቶችን ዋቢ አድርጎ ሚስጥራዊ አሰሳና ፍለጋን በተገቢው መልኩ መከውን ይገባል።
7 163
እውነተን ፍለጋ!
እጂግ አስደናቂው እውነትን ለመፈለግ የተደረገ የጉዞ ማስታወሻየን ይዠላችሁ አቀርባለሁ።
ከ 3 ሺ አመት በፊት ቀደም ብሎ የተደረገ ሚስጥራዊ የ ቅርስ ጉዞ ...ያልተነገረው እውነት! ያልተገጸውን እጂግ ረቂቅ እውነት ይዠላችሁ እቀርባለሁ።
ዩቲቭ ቻናላችን በመቀላቀል ይጠብቁን!
7 163
ሚመጣው የአለም መከራ ተዘጋጁ...
እጂግ አስደናቂው ምክርና ትንቢታዊ ተግሳጽ !
ከደቂቃወች በኋላ በፈለገ ጥበባት የዩቲቪ ቻናል ይዠላችሁ እቀርባለሁ!
7 163
በሚያቃጥል እና በሚያምር የሰልፈር ፉማሮልስ እና በጨረቃ መሰል መልክአ ምድሯ ዳሎል በኢትዮጵያ በደናኪል ዲፕሬሽን ውስጥ በምድር ላይ ላሉ ሰዎች ከፍተኛውን አማካይ የሙቀት መጠን በማስመዝገብ የዓለም ክብረ ወሰን ይይዛል።
በተቃራኒው ጫፍ በኢትዮጵያ የሚገኘው የጣና ሃይቅ የጥቁር አባይ ወንዝ ምንጭ ሲሆን ይህም በአለም ረጅሙ ወንዝ ነው።
ቶፖሎጂው በረሃዎችን፣ በማዕከሉ የሚገኙ የተራራ ሰንሰለቶችን እና በደቡባዊ ክፍሎቹ የሚገኙትን ሞቃታማ ደኖችን ያጠቃልላል።
ኢትዮጵያ የምትቆጣጠረው በደጋ ተራራዎች፣ ደጋማ ቦታዎች እና ሀይቆች በታላቁ ስምጥ ሸለቆ የተከፋፈሉ እና በቆላማ ቦታዎች የተከበቡ ናቸው።
3. የማይቻሉ የምህንድስና ስራዎች የማይታወቁ ባህሪያት!
ከመሬት በታች ከተገነቡት ቤተክርስትያኖች ከአንድ የድንጋይ ብሎክ እስከ ከፍተኛ ሀውልት እስከ ሚስጥራዊው ሜጋሊትስ ድረስ እነዚህ የቴክኖሎጂ ድንቆች በአያቶቻችን እንዴት እንደተከናወኑ እንድናስብ ያደርገናል።
ከመሬት በታች ካለው የእሳተ ገሞራ አለት የተፈለፈለው የላሊበላ ቤተ ክርስቲያን ድንቅ ነው ተብሏል።
ሰዎች በቀን ይሠሩበት ነበር እና "መላእክት" በሌሊት ይቀጥላሉ ተብሎ ይታመናል.
የአክሱም ስቲል በግብፅ ከሚገኙት በርካታ ሀውልቶች ጋር የሚመሳሰል አስደናቂ የጥበብ ስራ ሲሆን በነጠላ ጡጦ የተሰራ ነው።
የቲያ አርኪኦሎጂካል ቦታ በዞኑ ውስጥ የሚገኙ ከ100 በላይ ቅርፊቶች ያሉት ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ 46 ቱ በጢያ ይገኛሉ።
ይህንን ሚስጥራዊ ቦታ እና እዚያ የተሰሩ ስራዎችን ሙሉ በሙሉ በመረዳት ግራ የሚያጋቡ አርኪኦሎጂስቶች አሉ።
4. ስነ-ምህዳር
ኢትዮጵያ በርካታ የእንስሳት፣ የአእዋፍ፣ የሁሉም አይነት ፍጥረታት ብቻ ሳትሆን የበርካታ ብሄረሰቦችም መኖሪያ ነች።
ለዘመናት እንዲኖሩ እና እንዲበለጽጉ የረዳቸው ስነ-ምህዳር ፈጥረዋል።
በሐይቁ፣ በጫካው እና በደጋማ ስፍራው ውስጥ የሚኖሩ ብዙ ልዩ ዝርያዎች በመኖራቸው የብዝሀ ሕይወት ሀብቱ አስደናቂ ነው።
በነዚህ ሥነ-ምህዳሮች ውስጥ ከ600 የሚበልጡ ሥር የሰደዱ የእፅዋት ዝርያዎች፣ 16 የአእዋፍ ዝርያዎች፣ እና 35 የአጥቢ አጥቢ እንስሳት ዝርያዎች ይገኛሉ።
እነዚህ ሁሉ ፍጥረታት በአንድ ቦታ ላይ የሚገኙ በመሆናቸው፣ ቀደምት ሰዎች ይህንን እንደ መኖሪያ ቦታ ቢመርጡ ብልህነት አይሆንም።
5. የመሬት አቀማመጥ
ኢትዮጵያ ብዙ ህዝብን ከውጪው አለም ለመደበቅ የሚያስችል በቂ የመሬት ስፋት ያላት ትልቅ ሀገር ነች።
በ 1,126,829 ስኩዌር ኪሎ ሜትር ወይም 435,071 ስኩዌር ማይል ከቴክሳስ በእጥፍ ይበልጣል።
ኢትዮጵያ በግዛቷ ሁሉ ብዙም ሰው የማይኖርባቸው ሰፊ ቦታዎች አሏት።
በዚህ ሁሉ መረጃ ዛሬም ለአለም ህዝብ ይፋ ያልወጣው ወደ ፊት በአዲሱ የአለም ምስረታቸው ላይ ከብዙ መከራ በኋላ ገና በሃያሉ እንደምትወጣ ለሺ ዘመናት የተነገራላት አገር ምናባዊቷ ዋካንዳ ኢትዮጵያ ናት እንዴም ዛሬም በህዝቦቿ የኢትዮጵያ መነሳት ተብሎ የተጠራው በሚስጥራዊው አለም የዋካናዳ ምስረታ ይባላል የሚል መላሜታዊ ሃሳብ ይነሳል።
ከ ጥቂት አመታት በፊት ለዚህ የከተማ መመስረት የተመረጠችው አገር ኢትዮጵያ መሆኑን ባህርዳር ላይ LIVECITY HUB የተሰኘ ፕሮጀክት በ20 ቢሊየን ዶላር ወጭ የቴክኖሎጂ መንደር ሊገነባ እንዳቀደ ይፋ ከተደረገ በኃላ አለምን በእጂጉ አነጋግሯል። ብዙ ጥያቄዎች ተነስተዋል?
በመጀመርያ ደረጃ ይህ ይሰራል የተባለው ቦታ ኢትዮጵያ አማራ ክልል ባህርዳር አካባቢ የኤዶም ገነትን ከሚያጠጣው አባይ ወንዝ መሆኑ በይፋዊ መግለጫ የETV ዜና ጨምሮ የአለማቀፍ የዜና አውታሮች ተዘግቦ እንደነበር የቅርብ ጋዜ ትውስታ ነው።
ይህ ጉዳይ በርካታ ጥዬቄወችንም ያስነሳል አንዳንዶቹ በቅዱስ መጻህፍ ያለችውን የህይወት ዛፍን ፍለጋ ነው ይላሉ ሌሎች ደግሞ በጣና እና በአባይ አካባቢ የሚገኘው መለኮታዊ ሚስጥርን ለመካፈል እና ለመ መርመር የታቀደ የወፊቷን ኢትዮጵያ ለማድቀቅና ለመስበር የታሰበ ነው ተብሏል....
ለጠቢብ ጥብቁ አሃቲ ቃል ይላሉ አበው
በዚህ ጉዳይ ላይ ሃሳባችሁ ምን ዬሆን በሃሳብ መስጫ ላይ አስቀምጡልኝ....
7 163
የብላክ ፖንተረሷ ዋካንዳ ማን ናት?
- ይህ የስልጣኔ ከተማ ለምን እና እንዴት የትስ ይገነባል እዉነታዉ በምን ተረጋገጠ? ማስረጃወስ
- ብዙ የተነገረላት ምናባዊቷ ዋካንዳ አስፈሪው የኢትዮጵያ መነሳት ጋር የሚያገናኘው ነገር
- የህይወትን ዛፍ ፍለጋ የሚደረግ ትንቅንቅ
ዋካንዳ በምስራቅ አፍሪካ ውስጥ ያለ ምናባዊ አገር ነው።[2] ከሰሃራ በታች ባሉ አፍሪካ ውስጥ የሚገኝ ሲሆን የልዕለ ኃይሉ ብላክ ፓንተር መኖሪያ ነው።
ይህም አለምን በአንድ ድምፅ ያነቃነቀዉ የሆሊዉዱ ፊልም ሪኮርድ ከያዙት ጥቂት ፊልሞች አንዱ የሆነዉ ዘ ብላክ ፓንተረስ ከፍተኛ የሆነ የ ኮፒ ራይት ስተት አለበት ምክኒያቱም ይህ ፉልም የታሪክ ምንጭ አንድምታዉን በመሸፈን የዛች ሉአላዊት ሀገር ማግኘት የሚገባትን ዋጋ እንዲሰጣት አላደረገምና፡፡
ደግሞስ ይህ አለምን ያነቃነቀ ፊልም የታሪክ ባለቤቷ ኢትዮጵያ ናት ብለዉ ለመቀበል ይቅርና ማስብ አይፈለጉም፡፡
እዉነታዉ ግን ይህ ነዉ በምናባዊ ፊልማቸዉ ለመደበቅ የፈለጓት ዋካንዳ ኢትዮጵያ ናት ፡፡
ይህ ፊል ሲጀምር እንዲህ ይላል አባቱን ታሪክ እንዲነግረዉ ልጁ ይጠይቀዋል፤አባቱም ታሪክ ለልጁ መናገሩን ይቀጥላል ፤"በዛች ዋካንዳ በምትባል ሀገር ቫይብሬንየም የተባለ ዉድ ማእድን እንዳለና ለቴክኖሎጂ እድገት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለዉ ይህንንም ትልቅ ሀይል ያለዉ ማእድን ከዉጭ ሀገራት ስረቆት ለመጠበቅ መሬት ስር ተቀብሮ እንደሚገኝ" ለልጁ ታሪክን ይነግረዋል ልጁም ይቀጥላል "ይህ ዛሬም ድረስ መሬት ስር እንደተቀበረ ነዉ?" ብሎ አባቱን ይጠይቃል አባቱም መልሰ አዉን ይሆናል፡፡
ይህንን የተመለከተ አንድ እንግሊዛዊ ተመራማሪ እንዲህ ይላል " the postion between Ethiopia and south sudan it should be pointed out that wakanda was concealed using a cloacking device (እፀ መሰዉር). Wakanda is very isolated and works to remani that way,almost completely untoched by outside influences". በማለት ከፊልሙ ጋ ያለዉን ምረምራዊ ግኝት ያስታረቀዋል ዋካንዳም ኢትዮጵያ እንደሆነች ያስረዳል፡፡
በደቡብ ሱዳን እና በኢትየጵያ አካባቢ አሉ ሰለሚባሉት መሬት ዉስጥ ስለተሰዉሩት ሚስጥራዊ ቅዱሳን መካናት በሌላ ጊዜ በሰፊዉ እንመለከታለን፡፡
ለመሆኑ ለሰወች ግለፅ እንዳይሆኑ ተደረገዉ በፊልሙ ላይ ብዙ ቦታ ላይ የዋካንዳ ሀሳብ መነሻ ኢትዮጵያ መሆኑን አሳይተዋል፡፡
ማስረጃወችን ከዚህ እንደሚከተለዉ አቀረብላችኀለሁ፡፡
በፊልሙ ላይ የሚታየው የሰዉየዉ body modification የሙርሲ ባህላዊ ሰዉነት የማስዋቢያ ዘዴ ይታያል፡፡
2)ላይ የሀመሮችን ባህላዊ መዋቢያ ከንፈራቸዉ ላይ ሸክላ የማስገባት ባህልን በአንድ ገፀ ባህሪ ላይ ይታያል፡፡
3) 22ኛዉ ደቂቃ 1በሌላኛዉ
ገፀ ባህሪ ላይ ስናስተዉ ወገቡ ላየ የታተቀዉ ሁሉም አይነት ኢትዮጵያን ዉስጥ የሚገኙ መስቀሎች ይታያሉ
4) ከዚህ ቀደም በዚህዉ የቴሌግራም ገፅ ላይ እንደገለፀኩት የኢትዮጵያዉያን ብዙ ቅረሶች the british liibrarys Ethiopic Gezz
book ላይ በብሪታንያ እንደተወሰዱ እና እንዳሉ መግለፄ ይታወሳል፡፡ በዚህዉ ፊልም ላይም 35ኛዉ ደቂቃ 59 ሰከንደ ጀምሮ ስታዮት የዛችን ዋካንዳ የተባለች ሀገር የጥንት ቅረሷን ለማስመለስ የብሪታኒያን ሙዜም ሰብረዉ በመግባት ሲወስዱት ይታያል፡፡
5) 1 ሰአት ከ11 ደቂቃ የላይ የሚታየዉ የቦታ አቀማመጥ የጭስ አባይ አካባቢን የቦታ አቀማመጥ ጋ ተመሳሳይ ነዉ
6) 1 ሰአት ከ 42 ደቂቃ ላይ ባህላዊዉ የሆነዉ የኢትየጵያ የሙዚቃ መሳሪያ የዋሽንት ድምፀ ይሰማል
7)በመጨረሻም 2 ኛዉ ሰአት ከ 06 ደቂቃ ላየ የሚታይ ነገረ አለ እሱም ከአሜሪካ ሰንደቃላማ በሰተቀኝ የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማን ተሰቅሎ ይታያል፡፡
ኢትዮጵያ የትውልድ አገር የጥቁር ፓንተር ዋካንዳ ነች ይባላል ። ከደማቅ ሀይቆች እስከ ጠበኛ እሳተ ገሞራዎች፣ የኢትዮጵያ ልዩ የሆነ ማንነት፣ ታሪክ እና አስደናቂ የተፈጥሮ ድንቆች በምድር ላይ ካሉት እጅግ ማራኪ ስፍራዎች አንዷ ያደርጋታል።
ኢትዮጵያ ከበረሃ፣ ደጋ እና እሳተ ገሞራዎች፣ የዱር እንስሳት ዝርያ ያላቸው የዱር እንስሳት፣ አስደናቂ የስነ-ህንፃ እና ሌሎችም መልክዓ ምድሮች መኖሪያ ነች።
በ Black Panther ውስጥ ከዋካንዳ ብሄረሰብ ጋር የሚጣጣም ቦታ እና ህዝብ ያላት አፍሪካዊ ሀገር ብትኖር ኖሮ ኢትዮጵያ ግልፅ ምርጫ ትሆን ነበር።
እንደሚታወቀው በሆሊውድ የፊልም ኢንድስትሪ ውስጥ ያለ ምክንያት የሚሰሩ የፊልም ይዘትች የሉም።
ሁሉም በእቅድና በስርአት በበርካታ ተመራማሪወች የታጀበ የእወቀትና የምርምር ክምችት ረብጣ ዶላሮች ተበጀቶ የሚሰሩ ዘመን ተሻጋሪ ሚስጥራዊ ሃሳቦችን የሚያስተላልፉበት እጂግ ግዙፍ ተቋም ነው።
በተለይ ታሪክ ነክ ዘወግ ያላቸው የሆሊወድ ፊልሞች በጥንት አፈ ታሪኮች በምድራችን ላይ የተከውኑ ሁነቶች ትንቢታዊ ንግርቶች የጥንታ ብራናዊ ክታቦች የአርኪይሎጂ መረጃወችን መሰረት ያደረጉ ናቸው።
ብዙሀኑ እንደሚስማሙት ዋካንዳ በሚል ርእስ የተሰጠው እጂግ አስደናቂው ፊልም ከፊልም በዘለለ በአለም ላይ ገናና ስለምትሆን እጂግ አስደናቂ የጥቁር አገር በሚስጥራዊ መልእክቱ እንዳስተላለፈ ይታመናል። ብዙሃኑ እንደሚሉት ዋካንድ ከዚህ ቀደም ሃያል የነበረች በትንቢታዊ ንግርት ለዘመናት የምትጠበቅ እጂግ አስደናቂ የጥቁሮች ከተማ የብላክ ፓንተር ዋካንዳ ነች። ታዲያ ምናባዊቷ አገር ማን ናት ሲሉ ብዙሃኑ ይከራከራሉ?
አስደናቂዋ ምናባዊት አገር ዋካንዳ ኢትዮጵያ መሆኗን 5 ምክንያቶች የሚከተሉት ናቸው።
1. ሚስጥራዊ ህዝብ
በታሪኳ በተለያዩ ጊዜያት ኢትዮጵያ ከውጪው ዓለም መገለሏን መርጣለች።
በእውነቱ፣ ኢትዮጵያ በጣም ሚስጥራዊ ስለነበረች ኢትዮጵያን በብልጽግና፣ እንግዳ ፍጥረታት እና ድንቅ ነገሮች የተሞላች ኃያል የክርስቲያን ሀገር እንደሆነች በግልጽ የሚያውቁትን የመጀመሪያዎቹን አውሮፓውያን ግራ እንድትጋቡ ነበር።
ፕረስተር ዮሐንስ የኢትዮጵያ ገዥ የሦስቱ ሰብአ ሰገል ዘር እና የሰፊ መንግሥት ገዥ ሁሉ ኃያል ገዥ ነው ብለው ይጠሩ ነበር።
የኢትዮጵያ ህዝብ ሚስጥሩን ወደ ልቡ የመጠበቅ እና ስውር የማታለል ዘዴዎችን በመጠቀም ትኩረትን ለመቀየር የተጋለጠ ነው።
በምሳሌነትም በመላ ሀገሪቱ በየቤተክርስቲያኑ የሚገኙት በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ “ታቦቶች” የዋናው የቃል ኪዳኑ ታቦት (10 ትዕዛዛት) ትክክለኛ ቅጂ ነው ተብሏል።
እንደዚህ ያሉ ጠቃሚ ምስጢሮችን የመጠበቅ ችሎታ ካለን ፣ ቀደም ሲል በሀገሪቱ ውስጥ ሜትሮ ወይም ቫይቨራኒም ቢወድቅ ፣ ነዋሪዎቹ ይህንን ይገልጡ ነበር? በማለት ታሪክ ከዋቂወች ይጠይቃሉ ... የዋካንዳውያን የሃይል ምንጭ ምናልባት ቪብራኒየም ወደ ኢትዮጵያ አምርቷል ከዚህም ምድርም እንደሚገኝ ይነገራል።
2. መሬት
የኢትዮጵያ የመሬት አቀማመጥ በጣም የተለያየ በመሆኑ በአለም ላይ ያሉ እያንዳንዱን ስነ-ምህዳሮች ጥቃቅን ውክልና አላት።
ከበረዶው ከተሸፈነው የራስ ዳሸን ተራሮች ጀምሮ እስከ ዳሎል ምድር ላይ ካሉት ሞቃታማ ቦታዎች እስከ አለም ረጅሙ ወንዝ እስከ ብሉ አባይ ድረስ የረቀቀ ህዝብ ምን የተሻለ ቦታ ይመርጣል?
