en
Feedback
ፈለገ ጥበባት +++

ፈለገ ጥበባት +++

Open in Telegram

+++የቀደምት ኢትዮጵያውያን ስልጣኔን ማሳየት እንዲሁም ገዳማት እና አድባራትን ማሳወቅ፡፡+++ የተረሱ አድባራትና ገዳማትን ማስታወስ ፤የ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያንን ጥበብ እውቀትን በምንችለው ሁሉ መመርመር የአባቶቻችን ልጆች በመሆን ትላንት በዛሬ እና በነገ ውስጥ ማስቀጠል ማስቻል ነው።

Show more
7 163
Subscribers
-524 hours
-267 days
-7330 days
Posts Archive
ለ ሺ አመታት የጠፋው ገዳም ተገኘ! እስልምና በአረብ ባሕረ ገብ መሬት ላይ ከመስፋፋቱ በፊት ከነበሩት ዓመታት በፊት የነበረ ጥንታዊ የክርስቲያን ገዳም በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች የባሕር ዳርቻ በአስደናቂ ሁኔታ ተገኝቷል.... ሙሉ መረጃውን ዩቲብ ቻናላችን ጋር ይለቀቃል !

እዚያ የተሠወሩ አባቶች ስላሉ ደኑን መንካት ክልክል ነው፡፡ የወደቀ ዛፍ ካላገኘን በቀር ከዛፉ ቅጠል አንቆርጥም፡፡ ይህንን ደን ሰው እንዳይመስላችሁ የሚጠብቀው፤ ነብር ነው›› አሉን፡፡ ይህ ገጽ የሁላችን ገጽ ነው አስደናቂ እውነታቸው ይፋ ያልወጡ ሚስጥሮች በተለያዩ ጥንታዊ ቦታወች በመጓዝ በመንቀሳቀስ አስደናቂ ምልከታወች የተዳፈኑ እውቶችና ጥበቦች ያልተጎበኙ ገዳማት እና ጥንታዊ ቦታወች አለም ላይ አነጋጋሪና አስደናቂ የሆኑ ሚስጥራዊ ክስቶች በተለይም ስለ ኢትዮጵያ ታሪክ፣ ባሕል፣ እምነት፣  ትውፊት ምልከታዎች ይቀርቡበታል ። ከዚህ ቀደም ስለ ዋሻ እንድርያስ አስደናቂ የጉዞ ማስታወሻየ አካፍያችኋለሁ... ከዋሻ እንድያስ ወጣንና ወደ ግራ በኩል ታጥፈን መጓዝ ጀመርን፡፡ አሁንም እየተንደረደርን ነው ወደ ታች የምንወርደው፡፡ ግራና ቀኛችን በልምላሜ የታጠረ ነው፡፡ በአካባቢው ምንነቱን ለመለየት የሚያስቸግር በጎ መዓዛ ያውዳል፡፡ ወፎች ሲዘምሩ፣ ዛፎችም ሲያሸበሽቡ ለማየት የሚመኝ ሰው ካለ ወደ ዋሻ ተክለ ሃይማኖት መውረድ ነው፡፡  እነሆ ከዚህ ቀደም በሰፊው እንደገለጽኩት  ከፊት ለፊታችን በቀለም የተዋበ  ድንቅ ሚስጥራዊ ዋሻ ገጭ ብሎ ይታያል ።   ከግንቡ በኋላ ደግሞ የቀድሞው የዋሻ ግድግዳ ይታያል፡፡ የዋሻ እንድርያስ ቅርስና ታሪክ በግራኝ ዘመን እንደጠፋ መነኮሳቱ ይናገራሉ፡፡ እንደ እኔ ግምት ግን ዋሻ ተክለ ሃይማኖት በ13ኛው መክዘ ከነበረው ‹‹የደብረ ሊባኖሳውያን› ስደት ጋር የተያያዘ ሳይሆን አይቀርም፡፡ የፓሪሱ ዜና አጭሩ መዋዕል በዚህ ዘመን ‹የደብረ ሊባኖስ መነኮሳት ከአንቆ እስከ ጋሼና ተሰደዱ› ይላል፡፡ ‹አንቆ› ወይም ‹አዕንቁ› ደቡብ ጎንደር ስማዳ ውስጥ የምትገኝ ስትሆን ‹ጋሼና› ደግሞ ከላሊበላ 50 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በጎንደርና ወሎ መለያያ ላይ ትገኛለች፡፡ ከዋሻ ተክለ ሃይማኖት ወጥተን ወደ ጣራ ኤዎስጣቴዎስ ገዳም ነው የምንሄደው፡፡ አሁን ወደ ታች ሳይሆን ወደ ላይ ነው የምንወጣው፡፡ 83.5 ሄክታር በሆነ ደን የተሸፈነው ጣራ ገዳም ኤዎስጣቴዎስ ከአዲስ ዘመን ወደ ጎንደር በሚወስደው መንገድ ምክንያት ከሁለት የተከፈለ ነው፡፡ መነኮሳት መንገዳችን በዝግታና በጸጥታ እንዲሆን መከሩን፡፡ ለምን? አልናቸው፡፡ ‹‹እዚህ ነብሮች አሉ፡፡ ወደ ገዳሙ ስትመጡ ሥርዓቱን ካልጠበቃችሁ አደጋ ያደርሳሉ›› አሉና ነገሩን፡፡ አሁን የምናደርገው ጥንቃቄ ነብሮቹም ከሚጠብቁብን በላይ ሳይሆን አልቀረም፡፡ ተራራ እንደሚወጣ ሰው ትንፋሻችን እንኳን ሲወጣ አይሰማም ነበር፡፡ ተራራውን ወጥተን በጫካዎቹ መካከል አልፈን የአቡነ ኤዎስጣቴዎስን ገዳም አገኘው፡፡ ታሪካችንን በሚገባ ስንመረምረው ከሆንነው በተቃራኒው ሆነን እንገኘዋለን፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ትውልዳቸው ሸዋ፣ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ትውልዳቸው ኤርትራ፤ ሁለቱም ግን ጎንደር ላይ በታላቅ ሁኔታ ይከበራሉ፡፡ ባይገር ማችሁ ደግሞ በዐፄ ልብነ ድንግል ዘመን ገዳሙን የመሠረቱት አቡነ ገላውዴዎስ ጎጃም ዲማ አካባቢ ‹ናጫ አቦ› ከተባለ ቦታ ነው የመጡት፡፡ እኛ እንዲህ ነን፡፡ እምነትና ምግባር እንጂ ዘር ቁብ የማይሰጠን ነበርን፡፡ ማን ሆነህ መጣህ? ምን ይዘህ መጣህ? እንጂ ከየት ዘር መጣህ? ጉዳያችን አልነበረም፡፡ ‹ለሰው ሀገሩ ምግባሩ› አይደል የሚባለው፡፡ በአካባቢው የሚገኙት አባቶች አቡነ ተክለ ሃይማኖትም ሆኑ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ በዘመናቸው ወደ ቦታው መጥተው እንደነበር ይተርካሉ፡፡ ከአቡነ ኤዎስጣቴዎስ ቤተ ክርስቲያን ባሻገር ጥቅጥቅ ያለ ደን አለ፡፡ ከቤተ ክርስቲያኑ ይጀምርና በተራራው ላይ አልፎ የተራራው አናት ይደርሳል፡፡ የገዳሙ አበ ምኔት ‹‹እዚያ የተሠወሩ አባቶች ስላሉ ደኑን መንካት ክልክል ነው፡፡ የወደቀ ዛፍ ካላገኘን በቀር ከዛፉ ቅጠል አንቆርጥም፡፡ ይህንን ደን ሰው እንዳይመስላችሁ የሚጠብቀው፤ ነብር ነው›› አሉን፡፡ ‹‹እንኳን ደኑን ነክተውት›› አሉን አበ ምኔቱ ‹‹ተቀያይሞና ተኳርፎ እዚህ ገዳም አንድ ቀን ማደር አይቻልም፡፡ አንድ ቀን ሁለት አባቶች በሥራ ምክንያት ተጋጩ፡፡ እነዚሁ አባቶችም አሉ›› አሉን በጣታቸው ወደ አባቶቹ እያመለከቱ፡፡ እነርሱም በአዎንታ ራሳቸውን ነቀነቁ፡፡ ‹‹በትንሽ ነገር ተጋጭተው ሳይታረቁ አደሩ፡፡ በማግሥቱ አንደኛው አባት ሊያጥኑ ማልደው ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲሄዱ ነብሩ በሩ ላይ ተኝቶ አላሳልፍ አላቸው፡፡ እርሳቸው በሌላኛው በር በኩል ሲሄዱ ይከተላቸዋል፡፡ ወደ በሩ ሲጠጉ ያጉረመርማል፡፡ ሲቸግራቸው ተመለሱና ከእኒያ አባት ጋር ታረቁ፡፡ ሲመለሱ በቤተ ክርስቲያኑ አካባቢ ነብሩ የለም፡፡ ድምፁን ግን በሩቁ አሰማቸው›› ብለው አስደመሙን፡፡ ይህንን አስደናቂ ገዳም እየጎበኘን ባለንበት ጊዜ ከጫካው አንድ አስገምጋሚ ድምጽ ተሰምቶን ሁላችንም በፍርሃት ዞርን...ከመካከላችን አንዳንዶቻችን ደንገጥ ደንገጥ ብለን ወዲህና ወዲያ ስንመለካከት አዩንና ‹‹እናንተ ለሰማችሁት ትፈራላችሁ፤ ትንሽ ብታመሹኮ ውኃ ለመጠጣት እዚሁ ሲመጣ ታገኙታላችሁ፡፡ እዚያ ግብር ቤቱ ጋ ውኃ ሊጠጣ ይመጣል፡፡ እኛ ዘንድ ውኃም ምግብም ክፍት ነው፡፡ የተራበ መብላት የተጠማ መጠጣት አለበት፡፡ እርሱም ሊጠጣ ይመጣል፡፡ ታድያ ጠጥቶ ማንንም ሳይተናኮል ይሄዳል፡፡ እኛኮ ከብቶቻችን ገደል እንዳይገቡ ነው እንጂ አውሬ እንዳይበላቸው አናስብም፡፡ እዚህ ቦታ ዝንጀሮና ጅብ አይገባም፡፡ ግዝት ነው፡፡ ሌባም ቢመጣ ያው ጠባቂው (ነብሩን ማለታቸው ነው) አለ፡፡›› አሉን፡፡ በገዳሙ ውስጥ እስከ ኮሌጅ ትምህርት ደርሰው በኋላ ግን የመነኑ አባቶችን ማየት የተለመደ ነው፡፡ ተራ ልብስ ለብሰው እንጨት ሲያጓጉዙ የምታገኟቸው አባቶች ያ እንጨት ከምን ከምን እንደተሠራ በታትነው የተማሩ የባዮሎጂ ምሩቅ ሊሆኑ እንደሚችሉ መጠርጠር አለባችሁ፡፡ ከአቡነ ኤዎስጣቴዎስ ቤተ ክርስቲያን ወደ እመቤታችን ቤተ ክርስቲያን እንድንሄድ  መሩን፡፡ እኛም ተከተልን፡፡ ለዚህ ገዳም ታላቁን ውለታ ከዋሉት ሰዎች መካከል እቴጌ ምንትዋብ አንዷ ናት፡፡ እቴጌ ምንትዋብ የጎንደር ዘመን ካፈራቸው ኃያላንና ጠቢባን ሴቶች መካከል አንዷ ናት፡፡ በጎንደር አካባቢና በጣና ገዳማት የሚገኙትንና እስከ ዛሬም ብርታቷንና ጽናቷን የሚመሰክሩላትን አያሌ አብያተ ክርስቲያናት ሠርታለች፡፡  ይህ ፈለገ ጥበባት ነው ያላችሁን ሃሳብ አስተያየት @Nabuti21 ላይ አድርሱኝ።

ይህ አስደናቂ የጉዞ ማስታወሻ በዩቲብ መከታተል ለማትችሉ በጹሑፍ ይቀርብላችኋል!
ይህ አስደናቂ የጉዞ ማስታወሻ በዩቲብ መከታተል ለማትችሉ በጹሑፍ ይቀርብላችኋል!

"እዚያ የተሠወሩ አባቶች ስላሉ ደኑን መንካት ክልክል ነው፡፡ የወደቀ ዛፍ ካላገኘን በቀር ከዛፉ ቅጠል አንቆርጥም፡፡ ይህንን ደን ሰው እንዳይመስላችሁ የሚጠብቀው፤ ነብር ነው''›› አሉን፡፡ ገዳሙን የሚጠብቁ ነብሮች አስደነገጡን....ይህንን አስደኛቂ የገዳም የጉዞ ታሪክ በዩቲዩብ ቻናል ይዠላችሁ እቀርባለሁ...ጠብቁ!

እግዚኦ ሰላምከ ሃባ ለሃገረ!

  '' እየኖሩ መሞት ወይስ እየሞቱ መኖር''!   አባ ሆይ ሰው ኖረ የሚባለው ምን ሲያደረግ ነው ? አልኳቸው ። ልቦናየን በእየለቱ ሰቅዞ ከሚይዘኝ መልስ ፍልጎ ካጣሁለት የህይወት ፍልስፍና አንዱን..መልስ ይሰጡኝ ዘንድ እየተማጸንኩ። በእርግና ምክኒያት ከተዳከሙ እና ከፈዘዙ አይኖቻቸው ባሻገር አስተወለው እየተመለከቱኝ ። በእውቀትና በጥበብ የታጨቀውን የአእምሮአቸውን በር ሊከፍቱ ሲዳዱ በሽበት የመላ  ጽሕማቸውን እና  የራሰቸውን ጠጉር ይዳስሳሉ። ሊቁ ሲኖዳ ከወረቅ የነጠረ ከልሜዝ የከበረ ሃሳባቸውን ለማግኘት ደጂ ፀናት ያስፈልጋል ። አባ ሲኖዳ የራስ ጠጉራቸውና ጽሕማቸውን መነካካት ከጀመሩ እንደ ልብ ከማይገኘው ወቅያኖስ ከሆነው ከተቀበረው የእወቀት ማዕድናቸው እየዘገኑ በአንደበታቸው በኩል ገጸ በረከታቸውን ሊሰጡ እንደሆን አውቃለሁ።  የ አእምሮ ማህደራቸውን የእወቀት ከረጢቱን  የሚከፍተቱ ቁልፉ ከራስ ጠጉራቸውን  እና ከ ጢማቸው ጠጉር ያለ ይመስል። ለበርካታ ጊዜያት ከመናገር አንደበታቸው የተቆጠበ ታላቁ ሊቅ ሲኖዳን የአንበታቸው በር ከከፈቱ የጥበብ ማር ከሚያዘንበው ከንፈራቸው እጂግ በሚያስደንቅ የእወቀት ሰረገላ ከ ጸርአርያም  እስከ በርባኖስ ያሉትን የአለም እንቆቅልሾች ይፈቱ ዘንዱ ይነቃሉ። አባት ሆይ ሰው መሆን ምንድን ነው ? ሰውስ ኖር የሚባለው ምን ሲያደርግ ነው? ጎተራው በእልህ ስለሞላ? አቁማዳው ስላልጎደለ? ነግዶ ስላተረፈ? ሩጦ ስለቀደመ? ማዕዱ ሙሉ ስለሆነ? ገነዘብ በከረጢቱ ስለሞላ? ለአካሉ መልካም ጨረቅን ለኑሮው የተዋቡ ቤቶች ስላሉት?  ሰው ኖረ የሚባለው መቸ ነው?... ለዘላለም በማይጸና መነበር መሾሙ በሰወች መከበቡ ?  ስለ እውነት ደስታ ምንድን ነው? ሰውስ ኖረ የሚባለው እንዴት ነው? ...አልኳቸው አረጋዊውን ሊቅ። እንደወትሮው የአንደበታቸውን በር እንዳይዘጉበኝ እየተማጸንኩ ..... ጽሕማቸውን እና የራስ ጠጉራቸውን መደባበስ ጀመሩ.....አይኖቸ ጠበቡ ጀሮወቸ ተከፈቱ ...ካቀረቀሩበት እየተቃኑ ...''ተመልከተው ዙሪያህን  እይ አለሙን'' !  አሉኝ ''እየበሉ የማይጠግቡ ጠጥተው የማይረኩ ለብሰው የተራቆቱ በተዋበ ህንጻ እየኖሩ በብረድና ቁር የሚሰቃዩ ፤ እያላቸው ያጡ፤ እየኖሩ የሞቱ፤  ቤታቸው ሙሉ ሆኑ በጎደለ ድንኮን ውስጥ የሚኖሩ የሚመስላቸው ሰወች ለምን ይመስልሃል? የሚያስፈልጋቸው ነገር ሁሉ ከበቂ በላይ ሳለ ጎደሎወቻቸው የበዙበት ምክኒያት  ስለምን ነው? ሳይደሰቱ የሚስቁ፤ ሳያጡ የሚቸገሩ ሰወች አለማችን ላይ  የበዙበት ምክኒያት ምንድን ነው?   ያላቸውን ለቀው የሌላቸውን ሲፈልጉ፤ የሚፈቀረውን  ጠልተው የሚጠላውን የሚያፈቅሩ፤ ያላቸወን ጥለው የሌላቸውን የሚያሳድዱ፤ ያሳደዱት ሲያገኙ፣ የነበራቸውን ያልነበራቸውን ያሳደዱትን ሁሉ ዋጋ የሚያጣባቸው፤ ስለምን ይመስልሃል...?  ልጀ ! እንደ ሰው ክቡር ሁኖ ተፈጥሮ እንደ እርያ መኖሩ ስለ ምን ይመስልሃል?  ስቀው የማይደሰቱ አይተው የማያስተውሉ ሰምተው የማያዳምጡት  አግኝተው በቃኝ የማይሉት ስለ ምን ይሆን? ፈልጎ ያገኘውን ስለምን ያጣዋል?  ወዶ ያፈቀረውን ስለምንስ ይጠላዋል? አንተ ከንቱ ሰው ዙሪህን ተመልከት ...የጎደላቸውን ሲያሳደዱ የሞላላቸውን የሚያጡ ሰወች ምን ባይገባቸው ነው? ህይወትን በጎደላቸው ልክ የሚመዝኑ ብኩኖች እንዴት ደስታን ያግኙ? ባላቸው ፣በሚያወቁት፣ በያዙት፣ ባገኙት፣ በሚኖሩበት ዛሬ ፣ ያልተደሰቱ በሌላቸው ፣በማያውቁት፣ ባልያዙት፣ ምኞት በሆነች ነገ  እንዴትስ ደስታ ይገኛል ?    ከስጋዊና ደማዊ ሃሳብ ውጭ  ረቂቅ እወቀትና ህይወት ጠቢባን የሚያጣጥሙት አለም እንዳለ ለማይረዳ ሆዱ አምላኩ ለሆነ ፍጡር  ደስታና እርካታ ከቁሳዊ ሃብት ማግኘትና ማጣት በዘለል መለኪያ አይኖረውም... እንግዲያውስ ሰው ኖረ የሚባለው ለልቦናው ጥበብን ለአእምሮው እውቀትን ሲያገኝ ነው።'' አሉ ሊቁ ሲኖዳ ልጀ ሆይ  ብለው  አረጋዊው ሊቁ  ከተቀመጡበት  ከበርጩሜ ወንበራቸው ግራ ቀኝ አቀርቅረው እየተመለከቱ  በቀይ አፈር ከተለቀለቀችው አንስተኛ ጎጆ አንዳች ነገርን ይፈልጉ ይመስል። ''ልጀ ሆይ በእውነት ጥበብ አትጮህምን?. ማስተዋልስ ድምጽ አትሰጥምን? ከአዳም ልጆች አንድ ሚስጥር ተሰውሯል እሱም ጥበብ ናት ....ገንዘብ ላደረገው ሰው እውቀት የሕይወት ምንጭ ናት ። ሰው ኖረ የሚባለው ሕይወቱን በእውቀትና በጥበብ ሲያጸናት ነው። ያኔ የሰው ሕይወት ጎዳናው ያማረ የተዋበ ይሆናል ..ሰው ኖረ የሚባለው በእውቀትና በጥበብ መንገድ ሲጓዝ ነው።  ያኔ ሕይወትን ከስጋዊና ደማዊ ከቁሳካላዊ ሃሳብ ባሻገር በደስታ ትኖራታለህ..ያኔ ሰው ቢበላ ይጠግባል ቢጠጣ ይረካል ቢስቅ ይደሰታል....ቢሞት እንኳ ይኖራል!  ጥበብን ስትለብሳት ያኔ እየኖርክ መሞት እንጂ እየሞትክ አትኖርም!....አሉ ሊቁ ሲኖዳ  አናብርትና አናብስት ከሚርመሰመስበት ታላቁ ገዳም ከብዙሃኑ ተሰውረው... ካልታተመው መጽሐፍ የተቀነጨበ ! ሃሳብ አስተያየት @Nabuti21 ላይ አድርሱኝ።

አባት ሆይ ሰው ኖረ የሚባለው ምን ሲያደርግ ነው? አልኳቸው ሊቁ ሲኖዳን ከ ወረቅ የነጠረ ከአልማዝ የከበረ ሃሳባቸውን ለማግኘት ደጂ እየጸናሁ....በርካቶች ለጥያቄያቸው መልስ ለማግኘት ወደ እሳቸው የሚጓዙት ታላቁ ሊቅ ደገኛው አባት ሊቁ ተጠያቁው ሰው አባ ሲኖዳን በአርምሞ የተዘጋን ያለ ፈቃዳቸው የማይከፈተውን አንደበት እንደ እጸ ተሃዲሶ የሚያድሰውን አንደበታቸውን ለማስከፈት ከ ሚኖሩበት ባዕታቸው በር ላይ ቁሜ ጠየቋቸው...መልሳቸው ለሁላችንም መልሶች ናቸው ! በዚሁ የቴሌግራም ገጽ ይዠላችሁ እቀርባለሁ ጠብቁ!

አወሮፖውያን የቀበሩት ሚስጥር ! ጥንታዊው በሴራ የተሸፈነችው ሚስጥራዊቷ የስልጣኔ ከተማ ፤ በአርኪኦሎጂወች አስደናቂ ምርምር ይፋ የወጣው የተፈራው እውነት ። ይህንን አስደናቂ መረጃ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊያወቀው ይገባል...በፈለገ ጥበባት ይቀርባል።

የሰው ልጂ መላእክትን ሲወጡ ሲወርዱ ለመመልከት ረቂቅ መናፍስትን ለማየት ለመሰወር የሚያስችለውን የአባቶቻችን ጥንታዊ ጥበብ ላጋራችሁ ነው። በ ሳይኑሱ ዓለም 5 D Extra Dimensional view በመጠቀም የኢትዮጵያን ጥንታዊ የመሰወር ጥበብ ሲመሰክሩ...የ ታላቁ ሔኖክ ዕዝራ ቅድስ ያሬድ አቡነ አረጋዊ እንዴት ተሰወሩ? እጂግ ያስደነቀኝን ጥበብ አጋራችሁ አለሁ.... እውቀት+ እምነት+ ምርምር= ሰው መሆን ዝግጁ ናችሁ?

በQuantum physics የተረጋገጠው hidden Empire የመናፍስቱ ዓለም እንዲሁም የረቀቀ የአሰራር ሁኔታ ። ምድራችን ላይ ያለውን ረቂቅ ዓለም Dark Energy እንዲሁም የመሰወር ጥበብ በሳይንስ የተረጋገጠው  የጥንት የኢትዮጵያውያን ረቂቅ ጥበብ ።መነኮሳት እንዴት በብቃት ይሰወራሉ? 5 ኛው ዳይሜንሽን (5D ) ስለሚባለው  ረቂቃኑን የማየት ጥበብ የተሰወሩ ቤተመቅደሶች እንዲሁም ፒራሚዶች ሚስጥራቸው ያልተፈታው የላሊበላና የአክሱም የመሰሉ አስደናቂ የጥበብ አሻራወች ከስጋና ደማዊ ባህሪ በላይ እንዴት ባለ እውቀትና ጥበብ ተገነቡ.....? ይህን እጂግ አስደናቂ ጥበብ በፈለገ ጥበባት የዩቲብ ቻናል ይጠብቁን።

ነብዩ ሕዝቅኤል በምዕራፍ 29 ላይ ይህንን ትንቢት ሲናገር እንዲህ ብሏል.... "የግብፅ ምድር ባድማና ውድማ ትሆናለች እኔም እግዚአብሔር እንደሆንኩ ያውቃሉ ወንዙ የእኔ ነው የሰራሁትም እኔ ነኝ ብለሀልና:: ስለዚህ በአንተና በወንዞችህ ላይ ነኝ ::የግብፅን ምድር ከሚግዶል ጀምሮ እስከ ሴኔዌ እስከ ኢትዮጲያ ዳርቻ ድረስ ውድማና ባድማ አደርጋታለሁ:: የሰው እግር አያልፍባትም የእንስሳትም ኮቴ አያልፍባትም እስከ አርባ አመት ድረስ ማንም አይኖርባትም::ባድማ በሆኑ ምድሮች መካከል የግብፅን ምድር ባድማ አደርጋታለው :: በፈረሱት ከተሞች መካከል ከተሞችዋ አርባ አመት ፈርሰ ይቀመጣሉ:: ግብፃውያንንም ወደ አህዛብ እበትናቸዋለሁ:: በአገሮችም እዘራቸዋለው ይላል'':: ግብጽ ከኢትዮጵያ የምታገኘውን ውሃ በሲዊዞ ካናል ወደ በረሀማወቹ መካከለኛ ምስራቅ የአረብ ሀገራት ትልካለች። ለዚህም ግብጽን ደግፈው የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ሰላም እምንት እና የተሰናሰለ ማንነት ሊያጠፉ ተባበሩ። አልፋ ኦ ሜጋ የሆነ አምላክ ትላንት ላይ ሆኖ ዛሬን ያውቃልና ነብዩ ሕዝቄልን አስነስቶ ትንቢት አጻፈው። ሕዝ ምዕ30 '' ሰይፍ በግብጽ ላይ ይመጣል፥ ሁከትም በኢትዮጵያ ይሆናል፤ የተገደሉትም በግብጽ ውስጥ ይወድቃሉ፥ ብዛትዋንም ይወስዳሉ፥ መሠረትዋም ይፈርሳል። ኢትዮጵያና ፉጥ ሉድም የተደባለቀም ሕዝብ ሁሉ ኩብም ቃል ኪዳንም የገባችው ምድር ልጆች ከእነርሱ ጋር በሰይፍ ይወድቃሉ። ''" እግዚአብሔርም እንዲህ ይላል ግብፅን እሚደግፉ ሁሉ ይወድቃሉ የሃይልዋ ትእቢት ይወርዳል:: ከሚግዶል ጀምሮ እስከ ሴኔዌ ድረስ በእርስዋ ላይ በሰይፍ ይወድቃሉ::..."ይላል። እንግዲህ ይህ አምላካዊ ቃል ከዚህ በፊት የተፈጸመ እንዳልሆነ እሙን ነው። ቃል በቃል ''ወንዙም የእኔ ነው የሰራሁትም እኔ ነኝ ብለሻልና'' ይላል ግብጽንም የሚደግፉ ሁሉ ይወድቃሉ ይላል ና የግብጽን ቅጣት የሃያላኑንም ውድቀት በምን አይነት መለኮታዊ ስራ ከውኖ እንደሚያሳየን እድሜ ከሰጠን እናያለን .....ይህ ሁሉ ቃል የተነገረለት ዐባይ ከ ውሃነት በዘለለ ያልተነገር የአለማችን  ማርሽ ቀያሪ ዘመመ ፖለቲካን ዘዋሪ ይሆናል።  ከ እጸ ሕይወት ስር  የሚፉልቀው ውሃ በቀን በረካታ ህሙማንን በጸበሉ እየፈወሰ ከሰማዩ ጋር ባለው የ ኮንስታሌሽንን ትስስር ቁልቁል ይፈሳል። በዚሁ የአባይ ወንዝ የተሰሩ አስደናቂ ፒራሚዶች ሲኖሩ ከ ሰማዩ ኮንስታሌሽን  መዋቅር ጋር ተመሳሳይ ቅርጽ ይዘው አባይ ወንዝን ተከትለው እጂግ በሚያስደንቅ ጥበብ መሰራታቸው ነው። ..... ይህ ፈለገ ጥበባት ነው ያላችሁን ሃሳብ አስተያየት @Nabuti21 ላይ አድርሱን።

አባይ ሰከላ ላይ ሲነሳ ግዮን በሚል ስም ይጠራል፡፡ግዮን በግዕዝ ልሳን ፏፏቴው የሚማርክ ወራጅ ወንዝ ማለት*እንደሆነ ከአካባቢው ሰዎች ይነገራሉ፡፡ ግዮን 100 ሜትር ከምንጩ ከሄደ በኋላ ዳሞቴ ከተባለች ጅረት ይቀላቀላል ፡፡ ግዮን ከዘህ በኋላ ሌሎች ገባር ወንዞችን እያስገበረ ጣና ይገባል፡፡ አባይ ከጣና ጀምሮ ከ800 ኪሜ በላይ በኢትዮጵያ ከተጓዘ በኋላ መድረሻውን በሜዲትራንን ሃይቅ ያደርጋል፡፡አባይ ማለት የናይል ወንዝ ታላቁ ገባር ወንዝ ሲሆን መነሻው ኢትዮጵያ ነው። አባይ 70 በመቶ የሚሆነው የሀገሪቱን ወንዞች የውሃ ድርሽ ሲይዝ አጠቃላይ የውሃድርሻውም ቢሆን 50 በምቶ የሚጠጋ ነው። በኢትዮጵያ ከአባይ ውጭ ያሉት ወንዞች ድምር ድርሻ 30 በምቶ ነው። ይህንን ብርቅና አስደማሚ የቱሪስት መዳረሻ በየወሩ ቢያንእስከ 4000 የሚደርሱ ሀገር ውስጥ ቱሪስት ይጎበኘዋል፡፡ የግዮን ወንዝ የተለየ የቱሪስት መስህብ እንዲሆን ካስቻሉት ጉዳዩች መካከል አንደኛ ፈዋሽ ጸበልነቱ ሲሆን ሌላው ደግሞ የዓለማችን ረጅሙ ወንዝ አባይ መነሻመሆነ ነው፡፡ የግሪኩ ሄሮዶትስ የአባይ ምንጩ ሱዳን ሲናር ግዛት እንደሆነ አትቶ ነበር፡፡ ይህ ሀሳብ እስከ 17ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ ከሞላ ጎደል ተቀባነት ነበረው፡፡ በጎንደር ስልጣኔ ወቅት የገቡ አውሮፓውያን ግን የሄሮዶትስን ሀሳብ አጨናገፉት፡፡ ፖርቹጋላዊው ፔድሮ ፔዝ የአባይ ምንጭ ጣና ነው ሲሉ፤ እስኮትላንዳዊው ጀምስ ብሩስ ደግሞ በበቅሎ ከጎንደር አስከ ሰከላ ግሽ ተራራ ስር ተጉዞ የዐባይ መነሻ ሰከላ እንደሆነች በማስታወሻው አሰፈረ፡፡ ማስታወሻው ሲታተም ሰፊ ተቀባይነት አግኝቶ የአባይ መነሻ ግሽ ተራራ እንደሆነ በ18ኛው መቶ ክፍለዘመን ጀምሮ ተስተጋባ፡፡ ሌላው በዚህ የዐባይ(ዓባይ) ወንሽ ምክኒያት የተነገረ ወደ ፊት የሚፈጸም ረቂቅ ትንቢት አለ... የነብዩ ኢሳኢያስ ትንቢት በግብጽ ምድር ላይ ይፈጸም ዘንድ ጊዜው አሁን መቸ ይሆን ? ይህ የአባይ ወንዝ ጉዳይ ወቅታዊ ዘመን አመጣሽ ጊዜ የወለደው ሙግት የሚመስላቸው በርካታ ሰወች አሉ። ሰወች በጥንቷ ምስር በአሁኗ ግብጽ እና በኢትዮጵያ ኑሯቸውን ከመሰረቱበት እለት ጀምሮ አባይ የሽ ዘመናት ቁርሾ ነበር። ከ 700 መቶ አመት በፊት በታላቁ የጊዮርጊስ ወልደ አሚድ የብራና መጻህፍ እንደተጻፈው ከ ሺ አመትት ቀደም ብሎ በአባይ ምክኒያት በኢትዮጵያና ግብጽ ስለነበረው ቁርሾ በግልጽ ይናገራል። ''እስመ ምፅአተ ማዮሙ ለግብጽ እም ኢትዮጵያ ወእም ድሕረዝ አመከርዎ ለፈረኦን መኳንንቲሁ ከመ ይፈንዎ ለሙሴ ይፅብዖሙ ለሰብአ ኢትዮጵያ ወይቤሎሙ ኦሆ.....'' ግብፃውያን ውሃን የሚያገኙት ከ ኢትዮጵያ ብቻ ነውና ከዚህ በኋላ የፈርኦን መኳንንት ሙሴን ወደ ኢትዮጵያ እንዲልከውና ኢትዮጵያን እንዲበቀላቸው ፈረኦንን አግባቡት... እሱም በነገራቸው ተስማምቶ ለሙሴ እንዲህ አለው ሙሴ ሆይ በአገራችን ላይ የደረሰው ውርደት ሁሉ ተመልከት መከራውን ያደረሱብን ኢትዮጵያውያን ናቸው አገራችንን ወረሩ ሰወቻችንን ማረኩ አገራችንን አጠፉ ወንዙንም ወደ ግብጽ እንዳይወርድ ዘጉ መለሱትም.... ይህ መልእክት ከክርስቶስ ዘመን በፊት በነበረው የግብጹ ጨካኙ ፈርኦን ኢትዮጵያን ያጠፋ ዘንድ ወንዙንም ከምንጩ ለመቆጣጠር ያለው ጽኑ ፍላጎት ነበር...ታላቁ ሙሴም 20ሺ ፈረሰኞችን አስከትሎ ኢትዮጵያን ሊወጋ ህዝቦቹንም ሊማርክ የተገደበውን ውሃም ሊለቅ ከአሳዳጊው ከ ፈርኦን ዘንድ ተላከ። ሙሴም የትልቁ ውሃ ወንዝ እሲኪ ሞላ ድረስ ሲጠብቅ ቆየና በጡብ አስገንብቶ ኢትዮጵያን አጥግቦ ወደ ግብጽ እንዲፈሰ ቸርነታቸውን ጠይቆ በቃል ኪዳን ተስማሙ። ሙሴም የእግዚአብሔር ፈቃድ ሆነና የዮቶርን ልጂ አግብቶ የበግ እረኛ ሆኖ በኢትዮጵያ ተራሮች ላይ ኖረ ... .... ይህ ከ ሶስት ሽ ዘመናት ቀደሞ የነበር የኢትዮጵያን አባይ ለመውረስ የፈርኦን ስሪት ግብጽ የሺ ዘመናት ፈላጎት ዛሬም ድረስ እብሪተኝነቷ አልቅ ብሏታል ከሃያላኑ ጋ ሴራን ታሴራለች ። ኢትዮጵያ ጠሏ የልእለ ሃያሏ ሀገር አሜሪካ ጫና እና የምዕራባውያኑ የሴራ ፖለቲካ ለግብጽ መደገፍ የአለም የመገናኛ አውታር ጀሮ አሙቋል እንድትፈርስ የሚፈልጉት የአረብ አውሮፖና የአሜሪካ ሀገራትን ሴራ በግልጽ አሳይተዋል። ይህ ያልተዘጋ አጀንዳ ጉዳይ ከክርስቶስ ልደት በፊት ጀምሮ የዐባይ ጉዳይ ግብጽና ኢትዮጵያን ጦር ሲያማዝዝ ዘገር ሲያስነቀነቅ የነበር ጉዳይ ነው። በወቅቱ የኢትዮጵያ የወሀ ሀብቷ እጂግ ከበቂ በላይ የሆነ እና በመልካምድር ሀብቷ የበለጸገች ከመሆኗ የተነሳ ያለ ተቃውሞ የአባይ ወንዝ ለሽ አመታት ወደ በርሃማዋ ግብጽ እየወረደ ያረሰርሳታል። የኢትዮጵያ አፈር ግብጽን ጠፍጥፎ እንዳቆማትም እሙን ነው... ዐባይ ወይም ግዮን ብዙ ትንቢት የተነገረለት ታላቅ ወንዝ ነው። ከዚህ ቀደም የአባይ ወንዝን የኢትዮጵያውያኑ ነገስታት ከአንድም ሁለት ሶስቴ ገደበወት የግብጽን መከራ አጽንተወት ነበር። የአረብ አብዮት ግብጽን ሲያጠግባት ሰይፏን ሞርዳ ዘገራን ንቅንቃ ኢትዮጵያንም ልትወገ ዐባይንም ከስሩ ለመቆጣጠር በርካታ ጊዜ ሞክራ ደል ተነስታለች። በወቅቱ የነበሩ ኢትዮጵያውን ነገስታት ንጉስም ጻድቅም አንዳንዶች ካህንም ነበሩ። እንደ እነ ንጉስ ዳዊት ያሉ ሃያላን ጠቢባን ነገስታት የአባይን ወንዝ በተለየ ጥበብ ገድበው አሁን ግሸን ማርያም ያለውን ግማደ መስቀል ከግብጽ ወደ ኢትዮጵያ እንዲሚመጣ እና በክብር እንዲቀመጥም የሆነውም በዚህ በአባይ ወንዝ ምክኒያት ነው።... ታድያ ይህ ጉዳይ ታላቁ ነብይ ኢሳኢያስ በትንቢቱ ነገሮናል በ አባይ ምክኒያት በግብጽ ምድር ላይ በዚህ ዘመን ስለሚደርሰው የእግዚአብሔር መልስ በመጻህፍ ቅዱስ ላይ ትንቢት የጻፉ በርካታ ነብያት አሉ። ኢሳኢያስ ምዕ 19 "ውሆችም ከባህር ይደርቃሉ::ወንዙም ያንሳል ደረቅም ይሆናል:: ወንዞችም ይገማሉ:: የግብፅ መስኖዎችም ያንሳሉ ይደርቃሉም:: ደንገልና ቄጤማ ይጠወልጋሉ:: በአባይ ወንዝ ዳር ያለው መስክ በአባይም ወንዝ ዳር የተዘራ እርሻ ሁሉ ይደርቃል ይበተንማል አይገኝምም: አሳ አጥማጆች ያዝናሉ::በአባይም ወንዝ መቃጥን የሚጥሉ ሁሉ ያለቅሳሉ::በውሆችም ላይ መረብ የሚጥሉ ይዝላሉ:: ይላል የእግዚአብሔር ቃል... በመጻህፍ ቅዱስ ከኦሪት እስከ ዮሐንስ ራዕይ ከተነገሩት ትንቢቶች የተፈጸሙ ወደ ፊትም የሚፈጸሙ አሉ። ይህ የኢሳኢያስ ትንቢትም ወደ ፊት የሚፈጸም መሆኑን ያሳያል። የፈርኦን ስሪት ግብጽ አሁን ባለችበት ሁኔታ አለም ላይ የኢትዮጵያን ስም በማጠልሸት እንዲሁም በእምነት እሷን ከመሰሉ መሀመዳውያን አረቦች እንዲሁም ኢትዮጵያ ጠል ከሆኑ ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ ላይ ከፍተኛ ዘመቻ መጀራቸው ይታወቃል ኢትዮጵያ አሁን ላለችበት የመከራ በዛት ምክኒያቶች ናቸው  ። በእውነትም የዚህ ትንቢት ቃል እንዳይፈጸም የሰጉ ይመስላሉ... ወንዙም የእኔ ነው የህልወና መሰርቴ የዘመናት ሀብት ቅርሴ ነው አትንኩብኝ ብላለች። ለዚህም የልእለ ሀያሏ ሀገር አሜሪካ ድጋፏ ነበር ለነገሩ ከ ሺ አመት በፊትም ከ ታላቋ ባቢሎንን ጋር በማበር ነበር ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ለማጥፋት የምትዳዳው በታራኳ አንድም ጊዜ ባይሳካላትም...

ዐባይ ወንዝ ሚስጥር ከ ኤዶም ገነት ..... ብዙሃኑ ዐባይ ውሃ ብቻ አይደለም ይላሉ ለዚህም ምክኒያት.. ከ አዶም ገነት የሚነሳው የአለምን የፖለቲካ አሰላለፈ የቀየረው በግብጽ ላይ  ትንቢት የተነገረለት ታላቁ ዐባይ እና ያልተሰማው  አስደናቂው ሚስጥር.... ወንዝም ገነትን ያጠጣ ዘንድ ከዔድን ይወጣ ነበር፤ ከዚያም ለአራት ክፍል ይከፈል ነበር።   የአንደኛው ወንዝ ስም ፊሶን ነው፤ እርሱም ወርቅ የሚገኝበትን የኤውላጥ ምድርን ይከብባል፤ የዚያም ምድር ወርቅ ጥሩ ነው፤ ከዚያም ሉልና የከበረ ድንጋይ ይገኛል።   የሁለተኛውም ወንዝ ስም ግዮን ነው፤ እርሱም የኢትዮጵያን ምድር ሁሉ ይከብባል። የሦስተኛውም ወንዝ ስም ጤግሮስ ነው፤ እርሱም በአሦር ምሥራቅ የሚሄድ ነው፤ አራተኛውም ወንዝ ኤፍራጥስ ነው። አራቱ የገነት ወንዞች ኤፍራጥስ፣ ጤግሮስ፣ ግዮን ፌሶን ናቸው።  በመጀመሪያ የተዘረዘሩት በዘፍ 2፡10–14 ነው።  የተጸነሱት ከኤደን ገነት ወደ አራቱ የምድር ማዕዘኖች በኮምፓስ በአራቱም አቅጣጫ እንደሚፈስሱ ነው። በዚህ ጉዳይ የተለያዩ የአለም ምሁራን አወዛጋቢ እና አከራካሪ ሃሳቦች ይነሱበታል። ከእነዚህም እስከ ሙሉ ሃይሉና ሞገሱ ከጥንት ከፈርኦን ጀምሮ ዛሬም የአለምን ህዝብ የፖለቲካዊ ውሳኔወችን የሚተላለፊበት ። የአለምን የ ፖለቲካ አሰላለፈ የቀየር እጂግ አስደናቂው ወንዝ የኢትዮጵያው ግዩን ነው ። ይህ ምንጭ ዛሬ ከገነት ከመጣ ጀምሮ እንደ ቅዱስ ውሃ ከታየ፣ ጥንት ሰማያዊ ወደብ የነበረው  እንጂ ሌላ አልነበረም.....ይላሉ ።  የመጀመሪያው አውሮፓውያን የብሉ ናይልን ምንጭ የጎበኙ እና የሰነዱ ፖርቱጋላዊው ኢየሱሳዊ ቄስ ፔድሮ ፓኤዝ ናቸው።  የጉብኝቱ ቀን እንደ ኤፕሪል 21፣ 1613 ወይም 1615 ወይም 1618 በተለያየ መልኩ ተሰጥቷል። ጀምስ ብሩስ በህዳር 1770 ወደ ምንጩ በመጣ ጊዜ በተለይ የበሬዎችን መስዋዕትነት አምልኮ ጠቅሷል፡- “የዳሞት አገዎች ለአባይ መለኮታዊ ክብር ይሰጣሉ።  ወንዙን ይሰግዳሉ፣ እናም በሺዎች የሚቆጠሩ ከብቶች ቀርበዋል፣ እናም መንፈሱ በእሱ ምንጭ ይኖራል ተብሎ ይታሰባል… ሁሉም ነገዶች… በየዓመቱ ከወንዙ ምንጭ አጠገብ ይሰበሰባሉ፣ ወንዙንም ጠርተው ይሠዉታል ይላል።    አፍሪካውያን ራሳቸው  ገነትን ከሚያጠጡ ማይ አፍላጋት ከማህጸናቸው እንደሚቀዳ ስለእነዚህ ነገሮች መኖር ሲያውቁ የአፍሪካን ሕዝቦች፣ ወንዞች፣ ሐይቆች፣ ፏፏቴዎች፣ ተራሮች እና ጅረቶች 'ግኝት' ለአውሮፓውያን አሳሾች አሳልፈው በመስጠት የታሪክ መፋለስ እንዲገጥመን ሁነናል። ነገር ግን በተለይ የነጭ አባይ ምንጭን በተመለከተ እንደ ስፔኬ ያሉ ምዕራባውያን አሳሾች በአባይ ወንዝ የውሃ ፍሰት ላይ ሃይማኖታዊ ግንኙነቶችን መስርተዋል  ይላል።     ሙሴ እና እንደ አብርሃም እና እንደ ያዕቆብ ያሉ ሌሎች የመጽሐፍ ቅዱስ ሰዎች  ጋር ከአባይ በረከት ተቋድሰዋል ከአባይ ወንዝ ጠጥተዋል።.... ስለዚህም የብሉ አባይ ምንጭ ላይ ውሃው መጀመሪያ ላይ ብዙ መስዋዕት ከተፈጸመበት ምንጭ የመጣ ቢሆንም ዛሬ ግን ከሰማይ የሚመጣው የግዮን ወንዝ ምድራዊ መገኛ ነው ተብሎ የሚታመንበት የክርስቲያኖች ኮስሞሎጂ አካል ነው።  የነጭ አባይ ምንጭ እና ተከታታዮቹ ፏፏቴዎች ግን ዛሬ በክርስትና ውስጥ ትልቅ ሚና ቢኖራቸውም ቀደምት ተመራማሪዎች እና ኋለኞቹ ሚስዮናውያን በሰሩት ሃይማኖታዊ ታሪክ እና ምርምር የተነሳ የግዩን መግነጢሳዊ ሃያልነቱን ይገልጻሉ። ታላላቅ የወንዞች ሸለቆዎች ለሥልጣኔ እድገት ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል፡ በሜሶጶጣሚያ፣ ሕንድ፣ ቻይና እና ግብፅ።  ነገር ግን መደበኛ የበጋ ፍሰቱ እና በሁለት በረሃማ ቦታዎች መካከል ያለው ጠባብ ለም መሬት ያለው የአባይ ወንዝ ባህሪ ያለው ሌላ ወንዝ አለም ላይ የለም ።  እ.ኤ.አ. በ 1790 ጄምስ ብሩስ ከአምስት ሺህ ዓመታት በላይ ታሪክን ጠቅለል አድርጎ እንዲህ ሲል ተናግሯል- አባይ ከምንጩ እስከ ባህር ድረስ ባለው ረጅም ጉዞ ውስጥ በየግዛቱ የተለየ ቋንቋ ይነገርበት የነበረ ስም ማግኘቱ ምንም አያስደንቅም;  ነገር ግን አንድ አስደናቂ ነገር አለ፣ በድምፅ እና በፊደሎች ውስጥ ያለው ስም በእውነት የተለያየ ቢሆንም ትርጉሙ ግን አንድ ነው… በአገው መካከል… ግዚር ፣ ገፋ ፣ ሴይር ይባላል።  ከእነዚህ ስሞች መካከል የመጀመሪያው አምላክን የሚያመለክት ነው;  አባ፣ ወይም አብ፣ አባት ተብሎም ይጠራል … በቅንነት እና ግብዝነት በሌለው አምልኮ፣ በእነዚህ ስር ወይም እንደዚህ ባሉ አቤቱታዎች፣ ወደ አባይ ወንዝ ወይም በዚያ ወንዝ ውስጥ የሚኖረውን ሃያል መግነጣሳዊ  መንፈስ እንዳለ ይታወቃል።   ውሃ ለሃይማኖታዊ እና መለኮታዊ መስተጋብር መካከለኛ ነው;  አንዳንድ ውኃዎች መንፈሳዊ ባሕርያት አሏቸው፣ ሌሎች የውኃ ዓይነቶች ግን የመለኮት ስራ መገለጫ  ናቸው።  "በዓለም ዙሪያ ያሉ ሰዎች በማንኛውም ጊዜ ከውሃ ጋር የተያያዙ የተለያዩ ሃይማኖታዊ ትርጉሞችን አላቸው። አከራካሪ ሃሳብ የያዘው የዐባይ ወንዝና አስደናቂው የምንጩ ሁኔታ ዛሬም ድረስ ታሪኩን ለሚያጠኑ አስደናቂ ሚስጥሩን ያካፍላል። እጂግ መለኮታዊ  ሚስጥራት ከሚከወኑበት የአለማችን ጥቂት ተፈጥሮወች በዋናነት የዐባይ ወንዝ ሲሆን የመነሻ ምንጩ ጉዳይ እጂግ አስደናቂና አነጋጋሪ ያደርገዋል።  ይህንን የመሰለ የአለም የፖለቲካ መነጋገሪያ ጥብቁ  ጉዳይ የሆነው ታላቁ የግዩን ወንዝ ምንጭ አብረን እንጎበኝ... የሰከላ የታላቁ የዐባይ ወንዝ ማህጸን  በአማራ ክልል በምዕራብ ጎጃም ዞን ከባህርዳር 174 ከሎ ሜትር እርቀት ላይ ትገኛለች፡፡ ከአዲስ አባባ ተነስተው በደብረ ማርቆስ ወደ ባህር ደር በሚወስደው አስፓልት መንገድ 432 ኪ/ሜ ወደ ሰሜን ከተጓዙ በኋላ ቲሊሊ ላይ ይደርሳሉ፡፡ ከቲሊሊ ምስራቃዊ አቅጣጫ 32 ኪ/ሜ መንገድ በመጓዝ ሽንጣሙን ግሽተራራ ያገኙታል፡፡ የግሽ ተራራ ከባህር ወለል 2800 ሜትር ከፍታ አለው ሞገሱ የበዛለት አስደናቂ ተፈጥሮ ያለው ሲሆን በዚሁ አካባቢ የሚኖሩ ሰወች እንደሚናገሩት ከሆነ ከዚህ አካባቢ ከ አዳም የተሰወረች እጸ ህይወት አለች ተብሎ በመታመኑ ብዙሃኑ የ ውጭ አገር ዜጎች በአጽኖት ይከታተላሉ። የ ዐባይ አሰያየም ...አቡነ ዘርዓ ብሩክ "ዓባይ" እና "ግሽ ዓባይ" የሚሉ ስሞች እንዳወጡ አንድ ቀን አባታችን የንጉስ ጭፍሮች ሲያሳድዷቸው ግዮን ደረሱ። እንደደረሱባቸው ሲያውቁ ዳዊታቸውንና ለወንጌል ስብከት ሲጠቀሙባቸው የነበሩ 7 መጻሕፍት ሁሉ ለግዮን ወንዝ አደራ ሰጡዋት። ከ5 አመት በኋላ ሲመለሱ" ኦ ግዮን ግሥኢ መፃሕፍትየ -- ግዮን ሆይ መጻሕፍቴን ግሺ መልሺልኝ " (ግሽ ዓባይ -- የሚባልም ከዚህ የተነሳ ነው።) ቢሉአት አንድም የውሃ ጠብታ ሳይኖርባት ዳዊታቸውን ብትመልስላቸው ለደቀ መዝሙራቸው ዘሩፋኤል አሳዩት ሁለቱም የእግዚአብሔርን ሥራ አደነቁ። ከዛም በኋላ ግዮንን ባረክዋትና "ይኩን ፈውስ ዓብይ በውስቴትኪ -- በውስጥሽ ታላቅ ድኅነት ይደረግብሽ" አሉ። ከዛ ጊዜ ጀምሮ መካኖች ይወልዱ፣ ድዉዮች ይድኑ ጀመር "ወእም አሜሃ ተሰምየት ዓባይ ይእቲ ፈለግ -- ከዛ ጊዜ ጀምሮ ይህች ዓባይ ተብላ ተጠራች።

ይህ ድንቅ ምስጢር በ ጹሑፍ ይቀርባል👆👆

ይህ ድንቅ ሚስጥር በጸሑፍ ይቀርባል !