en
Feedback
Apostolic church of Ethiopia, Bole Hermon Branch

Apostolic church of Ethiopia, Bole Hermon Branch

Open in Telegram

"፤ እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ አምላካችን እግዚአብሔር አንድ እግዚአብሔር ነው፤" (ኦሪት ዘዳግም 6: 4)

Show more
3 848
Subscribers
+724 hours
+577 days
+17630 days
Posts Archive
የተወደዳችሁ ቅዱሳን ነገ የእግዚአብሔር ሰው በእግዚአብሔር በረከት ሙላት ወደ እኛ ስለሚመጣ ከበረከቱ እንድትካፈሉ በማለዳ ለመገኘት ጊዜ ይሁንላችሁ። @ACEBoleHermon

የተወደዳችሁ በጾም ጸሎቱ ምክንያት ዛሬ አዳር ጸሎት አይኖርም ። ተባረኩ

የተወደዳችሁ ቅዱሳን እንኳን አደረሳችሁ። " እግዚአብሔር እንደ ሰጠን ሁሉ፥ የእግዚአብሔርን ቸርነትና የእግዚአብሔርን ምስጋና፥ እንደ ምሕረቱና እንደ ቸርነቱም ብዛት ለእስራኤል ቤት የሰጠውን ትልቅ በጎነት አሳስባለሁ....በጭንቃቸው ሁሉ እርሱ ተጨነቀ፥ የፊቱም መልአክ አዳናቸው፤ በፍቅሩና በርኅራኄውም ተቤዣቸው፥ በቀደመውም ዘመን ሁሉ አንሥቶ ተሸከማቸው። ኢሳ63: 7-9 ....በቀደመው ዘመን አንስቶ የተሸከማችን የተባረከ ነው። ሃሌሉያ!! መሸከም...እግራችን እንዳይሰናከል... እንቅፋቱን አላመነውም! መሄድ ሲያቅተን ...የርሱ ዱካ ብቻ እየታየ .. የእኛ ዱካ የለበትም... በርሱ ትከሻ ላይ ነንና!! ዘመን ሲሻገር ይሄን የሚያዩ አይኖች የተባረኩ ናቸው። ምስጋናውን ያበዙለታል!! “ በእግዚአብሔር የተወደደ በእርሱ ዘንድ ተማምኖ ይኖራል፤ ቀኑን ሁሉ ይጋርደዋል፥ በትከሻውም መካከል ያድራል።” ዘዳ 33፥12 በርሱ ትከሻ መዋል ማደር ስለሆነልን በዘመናችን ሁሉ ጠላት ፈልጎ አጥቶናአል !!! ሃሌሉያ!! ውዶች ሆይ:- “እንደ ዕድሜህ እንዲሁ ኃይልህ ይሆናል።” ዘዳ 33፥25 በተጨመረልን ዘመንና እድሜ፦ መጨመር ይሆንልን ዘንድ እዳ አለብን!! በዚህም ሃሌሉያ!! "....ስለዚህም ምክንያት ትጋትን ሁሉ እያሳያችሁ በእምነታችሁ በጎነትን ጨምሩ፥ በበጎነትም እውቀትን፥ በእውቀትም ራስን መግዛት፥ ራስንም በመግዛት መጽናትን፥ በመጽናትም እግዚአብሔርን መምሰል፥ እግዚአብሔርንም በመምሰል የወንድማማችን መዋደድ፥ በወንድማማችም መዋደድ ፍቅርን ጨምሩ። እነዚህ ነገሮች ለእናንተ ሆነው ቢበዙ፥ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እውቀት ሥራ ፈቶችና ፍሬ ቢሶች እንዳትሆኑ ያደርጉአችኋልና፤.." 2ጴጥ1፥5-8 በተሰጠን ዘመን የመጨመር፣ የማደግ፣ የመለወጥ ፣ የመብዛትና ሃሳቡን የማገልገል ዘመን ይሆንልን ዘንድ ከዛሬ ነሃሴ 18 - ጳጉሜ 1 2018, በሚኖረን "ጸጋውን ለመቀበል ወደ ጸጋው ዙፋን እንቅረብ" በሚል መሪ ቃል ከጸሎቱ ከምልጃው እንዳንጎድል ለመገኘት እንትጋ። " አቤቱ፥ ጠላቶችህን የሰደቡትን የቀባኸውን ዘመን የሰደቡትን አስብ። መዝ89:51 እኛንም ዘመናችንንም እናስቀባ! እናስባርክ!!! ከቅባቱ የተነሳ ቀንበር ይሰበራልና!! የመቀባት ዘመን ይሁንላችሁ። ACEBoleHermon

የተወደዳችሁ መዘምራን ሰላም ለናንተ ይሁን ዛሬ በሚኖረን አዳር ጸሎት ማንም ሰው እንዳይቀር በአጽንዖት አሳስባለሁ። ተባረኩ!! መጋቢ ወንደሰን

📌 የተራራው ስብከት ክፍል 8 " የሚያስተራርቁ ብፁዓን ናቸው፥ የእግዚአብሔር ልጆች ይባላሉና።" ማቴ5:9 @ACEBoleHermon

📌 የተራራው ስብከት ቅኔ በእህት ኤልሳቤጥ ቢያድግልኝ @ACEBoleHermon

የተወደዳችሁ ቅዱሳን ሰላም ይብዛላችሁ። " ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወረደ ጊዜ ኃይልን ትቀበላላችሁ፥ በኢየሩሳሌምም በይሁዳም ሁሉ በሰማርያም እስከ ምድር ዳርም ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ ....." ሐዋ 1:8 የተቀበልነው መንፈስ ለተጠራንበት ሥራ ለወንጌል የሚለይ ነውና በዚህ መንፈስ ኃይል ወንጌልን ከኢየሩሳሌማችን ( ከአጥቢያችን ) ከቤተሰዎቻችን ጀምረን የክብሩን ወንጌል ብርሃን ለመመስከርና ለማወጅ :- ፊታችን እሁድ የወንጌል ቀን ስለሆነ፤ እንደተመካከርነው (ለወጣቶች ይድረሳችሁ) በኮንፈረንሱ ምክንያት ጎፋ ስለነበራችሁ እያንዳንዱ ሰው አንድ ነፍስ ይዞ እንዲመጣ ከጸሎት ጋር የመከሩን ጌታ ለምነናል! እኛም አምነናል። " ለምነኝ፥ አሕዛብን ለርስትህ የምድርንም ዳርቻ ለግዛትህ እሰጥሃለሁ። " መዝ 2:8 ጌታ ኢየሱስ ለብዙ ህዝብ ጉባኤ ያድርጋችሁ! ያፍራችሁ!! ተባረኩ!!! @ACEBoleHermon