en
Feedback
BAHIR DAR UNIVERSITY (ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ)

BAHIR DAR UNIVERSITY (ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ)

Open in Telegram

Bahir Dar University (BDU) is a public University established in 2000 by merging two former higher education institutions: Bahir Dar Polytechnic Institute (1963) and Bahir Dar Teachers’ College (1972).

Show more
9 368
Subscribers
+1024 hours
+637 days
+40630 days
Posts Archive
ጳጉሜ 2 ቀን 2018 ዓ.ም የምዝገባ ጥሪ ማስታወቂያ ለባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በ2018 ዓ.ም ጀማሪ መርሃ ግብር መደበኛ ተማሪዎች በሙሉ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በ2018 ዓ.ም የ1ኛ አመት ትምህርታች
ጳጉሜ 2 ቀን 2018 ዓ.ም     የምዝገባ ጥሪ ማስታወቂያ ለባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በ2018 ዓ.ም ጀማሪ መርሃ ግብር መደበኛ ተማሪዎች በሙሉ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በ2018 ዓ.ም የ1ኛ አመት ትምህርታችሁን አጠናቃችሁ የዲፓርትመንት ምደባ እየጠበቃችሁ ላላችሁ(ማለትም Other Social Science, Other Natutral and Health Science and Engineering and Technology Band)  ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ቀን ከመስከረም 06-07/2019 ዓ.ም  ብቻ መሆኑን አውቃችሁ  ከዚህ በታች በተገለጸው ግቢ ሪፓርት እንድታርጉ Band/department Campus Other Natural and Health Science Peda/CoBE Other Social Science Gish Abay Engineering & Technology Band Selam በተጨማሪም የዲፓርትመንት ምደባ የሚካሄደው በተማሪዎች የመምረጫ ሲስተም(SIMS) ስለሆነ የመምረጫ ሲስተሙ  ክፍት የሚሆነው ከመስከረም 05-08/2019 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 ሰዓት ስለሆነ ባላችሁበት ሆናችሁ በኦንላይን መማር የምትፈልጉትን የትምህርት መስክ መምረጥ የምትችሉ መሆኑን  እናሳውቃለን። ማሳሰቢያ፤ §  ዲፐርትመንት ምደባ የሚጠናቀቀው መስከረም 08/2019 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 መሆኑን አውቃችሁ እንድትመርጡ፡፡ §  በሲስተም ያልመረጠን ማንኛውንም ተማሪ የማናስተናግድ መሆኑን አውቃችሁ እያንዳንዱ ዲፓርትመንት የሚቀበሉትን የተማሪ ቁጥር/ኮታ በትክክል አይታችሁ እንድትመርጡ በጥብቅ እንገልፃለን:: §  ከተጠቀሰው የምዝገባ ጊዜ በፊትም ሆነ ዘግይቶ የሚመጣን ተማሪ የማንቀበል መሆኑን እናሳውቃለን፡፡ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራርና አልሙናይ ማኔጅመንት ዳይሬክቶሬት

ጳጉሜ 2 ቀን 2018 ዓ.ም የምዝገባ ጥሪ ማስታወቂያ ለባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ነባር ቅድመ ምረቃ እና ድህረ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች በሙሉ 1) የቅድመ ምረቃ 3ኛ ዓመትና ከዚያ በላይ እንዲሁም የነባር
ጳጉሜ 2 ቀን 2018 ዓ.ም     የምዝገባ ጥሪ ማስታወቂያ ለባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ነባር  ቅድመ ምረቃ እና ድህረ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች በሙሉ 1)    የቅድመ ምረቃ  3ኛ ዓመትና ከዚያ በላይ እንዲሁም የነባር  የድህረ ምረቃ ተማሪዎች ፤ 2)    የትምህርት ክፍል ምደባቸውን ያወቁ 2ኛ አመት ተማሪዎች(Anesthesia, Comprehensive Nursing, , Law, Midwifery, Pharmacy, Pre-medicine and Veterinary Medicine) የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የመጀመሪያው ወሰነ ትምህርት ምዝገባ የሚካሄደው ከመስከረም 07-08/2019 ዓ.ም መሆኑን እየገለጽን ምዝገባ የሚካሄደው ፕሮግራሙ በሚገኝበት ካምፓሶች መሆኑን እንገልጻለን።   ማሳሰቢያ፤ §  ከተጠቀሰው የምዝገባ ጊዜ በፊትም ሆነ ዘግይቶ የሚመጣን ተማሪ የማንቀበል መሆኑን እናሳውቃለን፡፡ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራርና አልሙናይ ማኔጅመንት ዳይሬክቶሬት

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ የታዳጊ ህጻናት ሳመር ካምፕ የመዝጊያ መርሃ ግብር በደመቀ ሁኔታ ተካሄደ ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም.፣ ባሕር ዳር  ዩኒቨርስቲ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ ለሁለት ወራት በተለያዩ የስፖርት ዘርፎች ሲያሰለጥናቸው የቆየውን 753 ታዳጊ ህጻናት የሳመር ካምፕ ስልጠና የመዝጊያ ስነ-ስርዓት ወላጆች፣ ዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ እና እንግዶች በተገኙበት በደመቀ ሁኔታ ተካሂዷል። በመርሃ ግብሩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ ዲን አቶ ሲሳይ አዱኛ፣ የሳመር የስፖርት መርሃ ግብሩ ታዳጊዎች አካላዊ እድገታቸውን እንዲያሻሽሉ፣ የስፖርት ክህሎታቸውን እንዲያጎለብቱ፣ በቡድን የመስራት ባህላቸውን እንዲጠናከር እና ክረምቱን በጤናማና አስደሳች መንገድ እንዲያሳልፉ አስተዋፅኦ ማድረጉን ገልጸዋል። በተጨማሪም ልጆች ለዲጂታል ዓለም አሉታዊ ተጽዕኖዎች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ትልቅ ሚና መጫወቱን ጠቁመዋል። አቶ ሲሳይ አክለውም፣ በመርሃ ግብሩ የተሳተፉ ህጻናት ደስተኛ፣ ጤናማ እና በራሳቸው የሚተማመኑ እንዲሁም አዳዲስ ጓደኞችን አፍርተው ወደ መደበኛ ትምህርት ቤታቸው ከፍ ባለ ተነሳሽነት የሚመለሱ እንደሆነ ገልጸዋል። ስፖርት አካዳሚው በበጋ ወራት 236 ታዳጊዎችን በእግር ኳስና በአትሌቲክስ ማሰልጠኑን ጠቅሰው፣ በዚህ ዓመት በዋናው ግቢ 480 እና በዘንዘልማ ግቢ 37 ታዳጊዎች በተለያዩ የስፖርት ዘርፎች ስልጠና ማግኘታቸውን ገልጸዋል። በአጠቃላይ 753 ታዳጊዎች እንደየ እድሜአቸው ተመጣጣኝ ስልጠና እንዳገኙም አመልክተዋል። ከሰለጠኑት ህጻናት መካከል ተሰጥኦና ፍላጎት ያላቸው በልዩ መርሃ ግብር ተመርጠው ከሰኞ እስከ አርብ ከትምህርት በኋላ እንዲሁም ቅዳሜና እሁድ በቀጣይ ስልጠና እንደሚሳተፉ ተገልጿል። የአካዳሚው ዲን ስኬታማ የሆነው የሳመር ካምፕ መርሃ ግብር በአሰልጣኞች፣ በአስተባባሪ ኮሚቴዎች፣  እንዲሁም በወላጆች ትብብር መሳካቱን ገልጸው፣ ልጆቻቸውን በእምነት ለአካዳሚው ለሰጡ ወላጆች ልባዊ ምስጋና አቅርበዋል። በእለቱም ታዳጊ ህጻናቱ በተለያዩ የስፖርት ዘርፎች ያገኙትን ክህሎትና ብቃት በአስደናቂ የስፖርት ትርኢቶች ለታዳሚዎች በማቅረብ የመዝጊያ መርሃ ግብሩን አድምቀውታል።

ቀን፡ 01/13/2018 ዓ.ም ክፍት የኃላፊነት ቦታ ማስታወቂያ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የመካከለኛ አመራር ምርጫና አሰያየምን ለመደንገግ ባወጣዉ ማሻሻያ መመሪያ ቁጥር 05/2012 መሰረት ለሶሻል ሳይንስ ፋካሊቲ ሪጅስትራር ኃላፊ (በምክትል ዲን ማዕረግ) የኃላፊነት ቦታ በመመሪያው በወጣው መስፈርት መሰረት ብቁ አመልካቾችን አወዳድሮ መሾም ይፈልጋል፡፡ ክፍት የኃላፊነት ቦታ፡ የሶሻል ሳይንስ ፋካሊቲ ሪጅስትራር ኃላፊ (በምክትል ዲን ማዕረግ) የማወዳደሪያ መስፈርት፡- 1ኛ. የትምህርት ማዕረግ/ደረጃ፡ ሌክቸረርና ከዚያ በላይ ያለው/ያላት 2ኛ. በከፍተኛ ትምህርት ተቋም፣ በኢንዱስትሪ፣ በምርምር ተቋማትወይም መሰል ተልዕኮ ባላቸው ተቋማት በልዩ ልዩ ኃላፊነት ዕርከን ያገለገለ/ችና ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረከተ/ች፤ 3ኛ. በሚያመለክቱበት አካዳሚክ ክፍልና ዘርፍ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ የከፍተኛ ትምህርት ተደራሽነት፣ ፍትኃዊነት፣ጥራት፣ ተገቢነትና ዓለምአቀፋዊነትን ለማሳካት፣ አካዳሚክ ክፍሉን የልህቀት ማዕከል ለማድረግ፣ ተጨማሪ ሀብት ለማስገኘት፣ እንዲሁም ዓለማቀፋዊና አገራዊ ጉድኝቶችን ለመፍጠርና ቸማስፋት በሚደረገው ሂደት አስተዋጽኦ ለማበርከት የሚያስችል ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ማዘጋጀትና ማብራሪያ መስጠት የሚችል/ምትችል፤ 4ኛ. የአካዳሚክ ክፍሉ ማህበረሰብ፣ የአካዳሚክ ኮሚሽኑ አባላት እንዲሁም የሚመለከታቸው ተጋብዘው በሚገኙበት መድረክ በአጀንዳዎች ላይ በአካል ተገኝቶ/ታ ማብራሪያና ገለጻ መስጠት የሚችል/ምትችል፤ አመልካቾች፡- ይህ ማስታወቂያ በዩኒቨርሲቲው ድህረ- ገጽ፣ ፌስቡክና ማስታወቂያ ሰሌዳዎች ከተገለጸበት ጳጉሜ 01 /2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 10 (አስር) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ የትምህርትና የስራ ልምዳቸውን ማስረጃ ፎቶ ኮፒ እንዲሁም ያዘጋጁትን ከአምስት ገጽ ያልበለጠ ስትራቴጂያዊ ዕቅድ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ ለበለጠ መረጃ፡ በሚከተሉት ስልክ ቁጥሮች +251 2 20 9653 ወይም +251 583 20 6059 ደውሎ ማነጋገር ይቻላል፡፡ ኢንፎርሜሽንና ስትራቴጂክ ኮሚኒኬሽን ም/ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

🎉 የ2018 ዓ.ም የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የስፖርት አካዳሚ የክረምት ስፖርት ካምፕ የማጠቃለያ ፕሮግራም ግብዣ! 🎉 የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የስፖርት አካዳሚ የክረምት ስፖርት ካምፕ ከሐምሌ ፩- ነ
🎉 የ2018 ዓ.ም የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የስፖርት አካዳሚ የክረምት ስፖርት ካምፕ የማጠቃለያ ፕሮግራም ግብዣ! 🎉 የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የስፖርት አካዳሚ የክረምት ስፖርት ካምፕ ከሐምሌ ፩- ነሐሴ ፴ ቀን ፳፻፩፰ ድረስ ለታዳጊ ወጣቶችና ህፃናት ሲሰጥ የቆየው የክረምት የስፖርት ስልጠና በታላቅ ስነ-ስርዓት ይዘጋል። ስለሆነም ይህንን የመዝጊያ መርሃ ግብር በጋራ ለማክበር በሚደረገው በዚህ የማጠቃለያ ስነ-ስርዓት ላይ የሰልጣኝ ወላጆች፣ የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ እና የስፖርት ቤተሰቦች በሙሉ እንድትገኙልን በአክብሮት እንጋብዛለን። 🗓 አርብ ነሐሴ 29 ቀን 2018 ዓ.ም ⏰ ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ 🏟️ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የስፖርት አካዳሚ ስታዲየም 🌐 www.bdu.edu.et/sport 📧 sport.academy@bdu.edu.et

Bahir Dar University Sport Academy Holds Outcome-Based Curriculum Validation Workshop Bahir Dar University Sport Academy successfully held an Outcome-Based Curriculum (OBE) Validation Workshop on Friday, 28 August 2026, at the Sport Academy Hall. The workshop brought together relevant academic and professional stakeholders to review, critically examine, and provide constructive feedback on the proposed curricula of: 🎓 BSc in Sport Sciences 🎓 BEd in Health, Physical Education and Sports The validation focused on strengthening the relevance, quality, coherence, and practical orientation of the curricula in line with Outcome-Based Education (OBE) principles and the changing needs of sport, education, coaching, management, and the wider community. The valuable contributions, professional insights, and constructive recommendations provided during the workshop will serve as an important input for further refinement and improvement of the curricula. As the Bahir Dar University Sport Academy continues to advance its vision of becoming a Center of Excellence in Sport Education, Coaching and Management for Community Impact and Global Recognition, curriculum quality remains at the heart of our commitment to preparing competent, ethical, innovative, and socially responsible sport professionals.

ማስታወቂያ ለኤክስቲንሽን እና ርቀት ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ የውሃ ሀብት ማኔጅመንት ስልጠና  ተጠናቀቀ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣ ነሐሴ 23 ቀን 2018 ዓ.ም. — በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የBDU-Iሀር ፕሮጀክት፣ የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ የውሃ ሀብት ማኔጅመንት ስልጠና  ተጠናቀቀ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣ ነሐሴ 23 ቀን 2018 ዓ.ም. — በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የBDU-Iሀር ፕሮጀክት፣ በሃይድሮ(ጂኦ)ሎጂ ንዑስ ፕሮጀክት (SP3) አዘጋጅነት “የውሃ ሀብት ማኔጅመንት፡ መሳሪያዎች፣ ቴክኒኮች እና ምርጥ ልምዶች” በሚል ርዕስ ለአምስት ቀናት የተሰጠው ስልጠና በስኬት ተጠናቋል። ከነሐሴ 18 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም. የቆየው ስልጠና፣ የውሃ ሀብትን በተገቢው ለመጠቀም፣ ለመጠበቅና በዘላቂነት ለማስተዳደር የሚያስችሉ ዕውቀቶችን፣ መሳሪያዎችንና ተግባራዊ ክህሎቶችን ለተሳታፊዎች ለማጋራት ያለመ ነበር። በስልጠናው ከተለያዩ የውሃና ተያያዥ ዘርፎች የተውጣጡ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል። በተለይም ከአማራ ብሔራዊ ክልል ሜትሮሎጂ ተቋም፣ ከውሃና ኢነርጂ ቢሮ፣ ከግብርና ቢሮ፣ ከአማራ ክልል ልህቀት፣ ዲዛይንና ቁጥጥር ኮርፖሬሽን፣ ከውሃ ግንባታ ቢሮ፣ ከዓባይ ተፋሰስ ባለሥልጣን እና ከባሕር ዳር ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት የተውጣጡ ባለሙያዎች በመርሃ ግብሩ ተሳትፈዋል። ስልጠናው በንድፈ ሀሳብ ትምህርት ብቻ ያልተገደበ ሲሆን፣ የመስክ ጉብኝትና ተግባራዊ ልምምድንም ያካተተ ነበር። ተሳታፊዎች በባሕር ዳር ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት የውሃ ማሰራጫ ጋን እና በምዕራብ አማራ ሜትሮሎጂ ጣቢያ በመገኘት በተግባር የውሃ ሀብት አያያዝና አጠቃቀም ላይ ያሉ ሁኔታዎችን ተመልክተዋል። ከአማራ ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮ የውሃ ሀብት ተፋሰስ ጥናትና ምርምር ባለሙያ አቶ በሪሁን መኮነን፣ ስልጠናው በሙያቸው ላይ የነበሩ የዕውቀትና የክህሎት ክፍተቶችን በንድፈ ሀሳብና በተግባር ለመለየትና ለመሙላት እድል መፍጠሩን ገልጸዋል። አቶ በሪሁን አክለውም፣ በስልጠናው ያገኙት ዕውቀት በቀጣይ የውሃ ሀብትን፣ በተለይም የከርሰ ምድር ውሃን በሳይንሳዊ መርህ ለማጥናትና በተሻለ መንገድ ለማስተዳደር ትልቅ አቅም እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል። ከአማራ ክልል ልህቀት፣ ዲዛይንና ቁጥጥር ኮርፖሬሽን የሃይድሮሎጂስት መሐንዲስ አቶ እያያ ደጀን በበኩላቸው፣ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አለም አቀፍ ተቋም ከመሆኑ ባሻገር አለም አቀፋዊነቱን ይበልጥ ለማስፋት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም የባሕር ዳር ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎትን የውሃ ማሰራጫ ጋን እና የምዕራብ አማራ ሜትሮሎጂ ተቋምን በመጎብኘት በተግባር ያገኙት ልምድ፣ በቀጣይ የተሻለ የውሃ ሀብት አስተዳደር ለመፍጠር የሚያግዙ ጥናትና ምርምሮችን ለማካሄድ ጠቃሚ ግብዓት እንደሆነላቸው አቶ እያያ ጠቁመዋል። በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ ላይ የBDU-IUC ፕሮጀክት ዳይሬክተር ዶ/ር ተስፋዬ ሽፈራው በሰጡት የመዝጊያ ንግግር፣ የስልጠናው መጠናቀቅ በተለያዩ የውሃ ዘርፍ ተቋማት መካከል የሙያ ልምድ ልውውጥንና ትብብርን ለማጠናከር ጠቃሚ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል። ዶ/ር ተስፋዬ አክለውም የውሃ ሀብትን በተቀናጀ፣ በሳይንሳዊና በዘላቂነት ለማስተዳደር የባለሙያዎችን ዕውቀትና ክህሎት ማጎልበት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፣ በስልጠናው የተገኘው ዕውቀትና ተግባራዊ ልምድ ወደ ሥራ በመተርጎም ተጨባጭ ውጤት እንዲመጣ አሳስበዋል። በተጨማሪም፣ ያለንን ፀጋ፣ የተፈጥሮ ሀብት፣ ዕውቀትና ክህሎት በአግባቡ በመጠቀምና በተቀናጀ መንገድ በመሥራት፣ ማኅበረሰቡን ተጠቃሚ ማድረግና ያለንን አቅም በተለይም ለጣና ተፋሰስ ዘላቂ ልማት ማዋል እንደሚገባ ዶ/ር ተስፋዬ አስገንዝበዋል። የስልጠናው ውጤት በተሳታፊዎች የሥራ አፈጻጸም ላይ ብቻ ሳይወሰን፣ በተቋማት መካከል ቀጣይ የጋራ ምርምር፣ የልምድ ልውውጥና የትብብር ሥራዎችን ለማስፋት መሠረት እንዲሆንም ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል።

Bahir Dar University and IMPACT Initiatives/REACH Explore Partnership Opportunities Bahir Dar, August 27, 2026 BDU hosted an introductory meeting with a delegation from IMPACT Initiatives/REACH to explore partnership opportunities, with a particular focus on evidence-based research and data collection in the Amhara region. The meeting opened with a welcome address by Dr. Manendante Mulugeta, Director of External Relations and Partnerships at BDU, who provided an overview of the University for the visiting delegation. Following his remarks, Eleni Dawit, Projects and Partnerships Support Officer at IMPACT Initiatives/REACH, presented an overview of IMPACT Initiatives and its REACH initiative. Laura Harrison, Country Representative for IMPACT Initiatives/REACH, expressed her delight in visiting Bahir Dar University, describing it as one of Ethiopia’s established public universities with a strong academic and research profile spanning a wide range of disciplines and an extensive portfolio of local and international partnerships. She also reflected on IMPACT Initiatives/REACH’s broader mission of improving decision-making by aid actors in crisis contexts, explaining that in Ethiopia, REACH’s work includes multi-sector assessments, cash and markets assessments, rapid needs assessments, nutrition and public health assessments, climate risk assessments, and humanitarian situation monitoring. She went on to propose several possible areas of collaboration, including harmonizing research approaches, jointly developing project proposals, coordinating through national and regional networks, engaging government stakeholders, and exploring short-term staff exchanges, and reflected at length on how the partnership could support improved data collection and access in the Amhara region. In his remarks, Dr. Mengesha Ayene, President of Bahir Dar University, warmly thanked the IMPACT Initiatives/REACH delegation for visiting and for taking the initiative to explore collaboration with the University. He described the timing of the discussion as significant and stressed the importance of identifying areas of mutual interest in light of the current dynamics in the region. He welcomed further clarity on the specific areas where BDU and IMPACT Initiatives/REACH could combine their strengths, and he highlighted joint proposals and research alignment, capacity building and operations, and the formalization of next steps as priority areas for the partnership going forward. Following these remarks, participants and delegates from both institutions engaged in an open discussion, reflecting on which areas of collaboration hold the strongest potential, how the two institutions should coordinate their work, and what framework and process would best serve to formalize and operationalize a future partnership. The meeting concluded with both sides reaffirming their commitment to continuing the conversation and working together to define concrete next steps toward a formal partnership between Bahir Dar University and IMPACT Initiatives/REACH.

Bahir Dar University Sport Academy is validating its programs! Join us for the upcoming Outcome-Based Curriculum Validation W
Bahir Dar University Sport Academy is validating its programs!  Join us for the upcoming Outcome-Based Curriculum Validation Workshop as we review and enhance our academic programs to ensure excellence in sports education and training. 📅 Date: Friday, 28th August ⏰ Time: 2:00 PM 📍 Venue: Sport Academy Hall Featured Curriculums: 🏃‍♂️ BSc in Sport Sciences 📚 BEd in Health, Physical Education and Sports We Educate, Coach, and Manage for Excellence We Empower Champions, and Build Futures. 🌐 Website: www.bdu.edu.et/sport 📧 Email: sport.academy@bdu.edu.et

Ethiopian Students Shine at GFSSM 2026, Securing Second Place Four Ethiopian students. An international team of Eight countries. Five days of intense competition. And a remarkable second-place finish. From August 13–17, the Global Future Space Scholars Meet (GFSSM) brought together talented young minds from eight countries for an ambitious five-day challenge focused on the future of human civilization in space. Among them were four students from BDU STEM Incubation Center — Nahom Ziyn, Natnael Belete, Nobel Desalegn, and Yohanan Daniel — who proudly represented Ethiopia as members of the international company Helio Energy. With 38 members from different countries, Helio Energy quickly distinguished itself through its creativity, energy, resilience, communication, facilitation, and exceptional teamwork. Led by Company President Nahom Ziyn, the team faced the demanding task of bringing together ideas from dozens of different minds and transforming them into a unified and compelling vision — all within a remarkably short period of time. From the early stages of the competition, the Ethiopian students made a strong impression on their teammates. Their arrival was described by fellow members as bringing a renewed sense of hope, creativity, resilience, and energy, strengthening the team's belief that Helio Energy had a genuine chance of reaching the top. That belief ultimately translated into an outstanding performance. Helio Energy delivered a strong proposal, demonstrated effective communication and facilitation, and maintained remarkable team cohesion throughout the competition, earning Second Place overall at GFSSM 2026. The achievement was further highlighted during the final company bidding speeches, where Ethiopian representation became a particularly memorable moment. The four Ethiopian students stood before the international audience in beautiful Ethiopian cultural dress, proudly carrying their country's identity onto the global stage. The final presentations brought additional recognition to the team, with Nahom Ziyn and Natnael Belete receiving awards for their brilliant final presentation speeches, further demonstrating the strength of Helio Energy's communication and presentation skills. The achievement is a remarkable milestone for the four Ethiopian students, who are currently studying at STEM Incubation Center and are preparing to enter Grade 12 in September. More importantly, it reflects the strength of an international team that successfully transformed diverse perspectives into one shared vision. The Ethiopian students extend their deepest regards and appreciation to the entire Helio Energy team for the dedication, trust, and teamwork that made this achievement possible, as well as to their team leader, Dr. Alemu Tesfaye, whose leadership and support played an important role in making this remarkable experience possible. From eight countries to one united team, Helio Energy proved that great ideas become even greater when different minds work together. Congratulations to Helio Energy on an outstanding Second Place finish at GFSSM 2026

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የውሃ ሀብት ማኔጅመንት ስልጠና በይፋ ተጀመረ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣ ነሐሴ 24 ቀን 2018 ዓ.ም. — በባሕር ዳርዩኒቨርሲቲ የBDU-Iሀር ፕሮጀክት፣ የሃይድሮ(ጂኦ)ሎጂ ንዑስ ፕሮጀክት (SP3) አዘጋጅነት “የውሃ ሀብት ማኔጅመንት፡ መሳሪያዎች፣ ቴክኒኮች እና ምርጥ ልምዶች" በሚል ርዕስ የሚሰጠው የአምስት ቀናት ስልጠና በይፋ ተጀምሯል። ከነሐሴ 24-28 ቀን 2018 ዓ.ም. የሚቆየው ስልጠና፣ ከተለያዩ የውሃ ዘርፍ ተቋማት የተውጣጡ ባለሙያዎችን በማሰባሰብ የውሃ ሀብትን በተገቢው ለመጠቀም፣ ለመጠበቅና በዘላቂነት ለማስተዳደር ያላቸውን ዕውቀትና ተግባራዊ ክህሎት ለማጎልበት ያለመ ነው፡፡ በስልጠናው የአማራ ብሔራዊ ክልል ሜትሮሎጂ ተቋም፣ የአማራ ብሔራዊ ክልል የውሃና ኢነርጂ ቢሮ፣የአማራ ብሔራዊ ክልል የግብርና ቢሮ፣የአማራ ብሔራዊ ክልል  የጥናትና ዲዛይን ኢንተርፕራይዝ፣ የአማራ ብሔራዊ ክልልውሃ ግንባታ ቢሮ፣ የአባይ ቤዝን ባለሥልጣን እና የባሕር ዳር ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ጽ/ቤት ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት ለተሳታፊዎች “እንኳን ደህና መጣችሁ" ያሉት የBDU-IUር ፕሮጀክት ዳይሬክተር ዶ/ር ተስፋየ ሽፈራው፣ ፕሮጀክቱ የመምህራን፣ የተመራማሪዎችና የተማሪዎችን አቅም ለማጎልበት ስልጠናዎችን፣ የምርምርና የእውቀት ልውውጥ ስራዎችን እንዲሁም ከአጋር ተቋማት ጋር የጋራ የአካዳሚክ ትብብር ስራዎችን ማከናወኑን ገልጸዋል። በተለይም በሃይድሮ(ጂኦ)ሎጂ ንዑስ ፕሮጀክቱ በውሃ ሀብት ጥናትና ምርምር፣ በሃይድሮሎጂና ሃይድሮጂኦሎጂ መረጃ አሰባሰብና ትንተና፣ በምርምርና በላቦራቶሪ አቅም ግንባታ ላይ የተለያዩ ተግባራት መከናወናቸውን ዶ/ር ተስፋየ አስረድተዋል። የውሃ ሀብት ለሰው ልጅ ህልውናና ለሀገራዊ ልማት ወሳኝ መሆኑን ያነሱት ዳይሬክተሩ፣ ያለንን የውሃ ሀብት በአግባቡ፣ በቁጠባና በዘላቂነት መጠቀም እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ በፕሮጀክቱ የተገኙ ውጤቶችና የተፈጠሩ የትብብር እድሎችም ከፕሮጀክቱ የጊዜ ገደብ ባሻገር ቀጣይነት እንዲኖራቸው ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የBDU-IUC የሃይድሮ(ጂኦ)ሎጂ ንዑስ ፕሮጀክት (SP3) መሪ ዶ/ር መከተ ደሴ በበኩላቸው፣ የንዑስ ፕሮጀክቱ ዋና ትኩረት በውሃ ሀብት ጥናት፣ ምርምርና አስተዳደር ዙሪያ የሙያ አቅምን ማጠናከር መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የውሃ ሀብት አስተዳደር በትክክለኛ መረጃና በሳይንሳዊ ምርምር ላይ መመስረት እንዳለበት ያስገነዘቡት ዶ/ር መከተ፣ ሰልጣኞች የሚያገኙትን ዕውቀትና ክህሎት በሙያዊ ስራቸው በመተግበር ለውሃ ሀብት ጥበቃና ዘላቂ አስተዳደር ተጨባጭ አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በተጨማሪም ሰልጣኞች በንቃት እንዲሳተፉና ልምድና ዕውቀታቸውን እንዲለዋወጡ አሳስበዋል፡፡የስልጠናው ይዘት ከመረጃ አሰባሰብና ትንተና እስከ የውሃ ሀብት ዕቅድና አስተዳደር የሚዘልቅ ነው፡፡ የከርሰ ምድር ውሃ ደረጃና ጥራት ክትትል፣ የውሂብ ትንተናና ትርጓሜ፣ የመስክ ጣቢያዎች ጉብኝት፣ የዲጂታል መሳሪያዎችና የርቀት ዳሰሳ ቴክኒኮችን ለሃይድሮሎጂ ጥናት መጠቀም ከሚሸፈኑ ጉዳዮች መካከል ይገኛሉ፡፡ በተጨማሪም የውሃ ሚዛንና የገጸ ምድር-ከርሰ ምድር ውሃ መስተጋብር በMODFLOW እና WetSpass-M ሶፍትዌሮች በተግባር ይተነተናል፡፡ የግድቦች የውሃ ምደባና አጠቃቀም፣ በጣና ሐይቅ አካባቢ ያሉ ሁለገብ ግድቦች፣ በቆጋ የመስኖ ልማት ላይ የመስኖ እጥረት (Deficit Irrigation) አስተዳደር እና የውሃ መሠረተ ልማት ንብረት አስተዳደርም የስልጠናው አካል ናቸው፡፡ በመሆኑም ስልጠናው ንድፈ ሀሳብን ከመስክ ልምምድና ከዘመናዊ ቴክኖሎጂ ጋር በማጣመር፣ ተሳታፊዎች የውሃ ሀብት መረጃን በትክክል እንዲተነትኑ፣ በሳይንሳዊ ማስረጃ ላይ የተመሠረተ ውሳኔ እንዲያሳልፉ እና በውሃ ዘርፍ የሚከሰቱ ተግዳሮቶችን በተገቢ መሳሪያና ቴክኒክ እንዲፈቱ የሚያስችል አቅም ይገነባል። ከስልጠናው የሚገኘው ዕውቀትና ክህሎት ወደ ምርምር፣ ልማትና ሙያዊ ተግባር በመቀየር፣ የውሃ ሀብታችንን በቁጠባ፣ በጥበቃና በዘላቂነት ለዛሬና ለመጪው ትውልድ ማስተላለፍ የሁሉም የጋራ ኃላፊነት መሆኑን ተገልጿል።