የEiABC ግቢ ጉባኤ
Open in Telegram
ይህ የEiABC ግቢ ጉባኤ ኦፊሻል የቴሌግራም ቻነል ነው። በዚህ ቻነል የግቢ ጉባኤ መልክዕክቶች ሌሎችም ክርስትናችንን ሊያጠነክሩ የሚችሉ ትምህርቶች በቀጥታ ይተላለፋሉ። ቻነሉን ይቀላቀሉ። 👇👇👇👇👇👇👇 👉 @eggmk1984 👈 👉 @eggmk1984 👈 👆👆👆👆👆👆👆 ሀሳብ አስታያየት ካላችሁ @Eiabcgbigubae_bot @eiabcgebigubae
Show more856
Subscribers
-324 hours
No data7 days
+1130 days
Posts Archive
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን !!!
ሐምሌ ፮ [6] ቀን ስንክሳር
👉እዚህ ይጫኑ👈
የEiABC ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል
ሰላም የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እንደምን አላቹህ?
ይህ Google form በ EIABC ጊቢ ጉባኤ የንስሐ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ሲሆን ዓላማውም:
በአገልግሎት ሂደቱ ላይ መስተጓጐል ሲፈጥሩ የነበሩ ችግሮችን መንስኤ (ምክንያት) ከራሳቸው ከተማሪዎች መገንዘብ እና መለየት ነው።
የሚሰጡን መረጃ በምስጢር የሚጠበቅ ሲሆን እናንተ ከፈቀዳችሁ ብቻ ከእናንተ ጋር ለመገናኘት ይውላሉ።
ስለትብብርዎ እናመሠግናለን።
https://forms.gle/o4r9TcJPzJoX4B5A6
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን !!!
ሐምሌ ፭ [5] ቀን ስንክሳር
👉እዚህ ይጫኑ👈
የEiABC ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን !!!
ሐምሌ ፬ [4] ቀን ስንክሳር
👉እዚህ ይጫኑ👈
የEiABC ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን !!!
ሐምሌ ፫ [ 3 ] ቀን ስንክሳር
👉እዚህ ይጫኑ👈
የEiABC ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን !!!
ሐምሌ ፪ [ 2 ] ቀን ስንክሳር
👉እዚህ ይጫኑ👈
የEiABC ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን !!!
ሐምሌ ፩ [ 1 ] ቀን ስንክሳር
👉እዚህ ይጫኑ👈
የEiABC ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን !!!
ሰኔ ፴ (30) ቀን ስንክሳር
👉እዚህ ይጫኑ👈
የEiABC ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን !!!
ሰኔ ፳፱ (29) ቀን ስንክሳር
👉እዚህ ይጫኑ👈
የEiABC ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል
ሰላም ውድ የEiABC ግቢ ጉባኤ አባላት፡
የአዲስ አበባ ማእከል ልማት ተቋም የቅዱስ አግናጥዮስ የክረምት ት/ት እና ስልጠና ለታዳጊ እና ወጣት ልጆች በማዘጋጀት እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡ በመሆኑም የትሩፋት አገልጋዮች ይህንን የበረከት አገለግሎት ለመደገፍ የሚከተለውን ቅጽ በመሙላት በትሩፋት አገልግሎቱን እንድትደግፉ በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን!!!
https://docs.google.com/forms/d/1L1LXtEiwpDQXk5r1O-GaRAgzKbpdtwNqp3jSQZJiFCA/edit
"መልካም ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ፥ ብርሃናችሁ በሰዎች ፊት ይብራ።" ማቴዎስ 5፥16
ውድና የተከበራችሁ የ2018 የEiABC ግቢ ጉባኤ ተመራቂ እኅቶቻችንና ወንድሞቻችን፣
በቅድሚያ በእግዚአብሔር ረድኤትና ጥበቃ ይህን የተባረከ የምረቃ ቀን ለማየት ስለበቃችሁ ከልብ እንኳን ደስ አላችሁ። በትምህርታችሁ ያሳያችሁት ትጋት፣ በመንፈሳዊ ሕይወታችሁ የጸናችሁበት ጽናት እና በግቢ ጉባኤው ያደረጋችሁት አገልግሎት ዛሬ በደስታ የምናከብረው ፍሬ ሆኗል። ጌታ እስከዚህ ያደረሳችሁ እንደሆነ ወደፊትም በጸጋው እንደሚመራችሁ እናምናለን።
ባለፉት ዓመታት በአርክቴክቸር፣ በኮንስትራክሽን ማኔጅመንት እና በከተማ ፕላኒንግ ትምህርታችሁ ጠንክራችሁ በመማር ይህን ውጤት አስመዝግባችኋል። ከዚህ ጎን ለጎንም በግቢ ጉባኤው ውስጥ በጸሎት፣ በቅዳሴ፣ በጉባኤያት እና በልዩ ልዩ መንፈሳዊ አገልግሎቶች በመሳተፍ በእምነታችሁ ጸንታችሁ ቆይታችኋል።
የEiABC ግቢ ጉባኤ ዋና ዓላማ ተማሪዎች በግቢ ቆይታቸው መንፈሳዊ ብስለት እንዲያገኙ፣ ከግቢ ከወጡ በኋላም በእምነታቸው ጸንተው በአጥቢያ ቤተ ክርስቲያናቸው ውስጥ በተማሩበት ሙያና በሰጣቸው ጸጋ እግዚአብሔርን እንዲያገለግሉ ማዘጋጀት ነው። ዛሬ የምረቃችሁ ቀን የዚህ ዓላማ አንዱ ፍሬ መሆኑን እናምናለን።
🔴 የግቢ ጉባኤው አደራ
🔹 በእምነታችሁ ጽኑ። የግቢ ጉባኤው ትምህርትና መንፈሳዊ ሕይወት በምረቃ አይጠናቀቅም፤ በምትሄዱበት ሁሉ በቤተ ክርስቲያን ተጠግታችሁ በእምነታችሁ ጸንታችሁ ኑሩ።
🔹 "ጌታ የሰጣችሁን የሙያ እውቀት ለቤተ ክርስቲያን ክብር እና ለሕዝቡ ጥቅም አውሉ።
የተማራችሁት ሙያ የሥራ መተዳደሪያ ብቻ ሳይሆን እግዚአብሔርን የምታገለግሉበት ጸጋም ነው።
የአርክቴክቸር ባለሙያዎች ውብ፣ ጠንካራ እና ለአምልኮ የሚመቹ ቤተ ክርስቲያናት፣ መንፈሳዊ ማዕከላት እና ሌሎች የቤተ ክርስቲያን ተቋማት በማቀድና በመንደፍ ቤተ ክርስቲያንን ማገልገል ትችላላችሁ።
የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ባለሙያዎች የቤተ ክርስቲያን የግንባታ ፕሮጀክቶች በጥራት፣ በጊዜ እና በታማኝነት እንዲጠናቀቁ በመምራትና በመቆጣጠር ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረግ ትችላላችሁ።
የከተማ ፕላኒንግ ባለሙያዎች ቤተ ክርስቲያን ለወደፊት የሚያስፈልጓትን የመሬት አጠቃቀም፣ የልማት ዕቅድ፣ የመንፈሳዊ ማዕከላት አቀማመጥ እና ዘላቂ ልማት በሙያዊ ዕውቀታችሁ በመደገፍ ማገልገል ትችላላችሁ።
ስለዚህ የተማራችሁትን እውቀት ለግል ስኬታችሁ ብቻ ሳይሆን፣ ለቤተ ክርስቲያን እድገት፣ ለሀገር ልማት እና ለማኅበረሰብ ጥቅም እንድታውሉ በክርስቶስ ፍቅር አደራ እንላለን።
🔹 የብርሃን ምስክሮች ሁኑ። በሥራ ቦታችሁ፣ በማኅበረሰብ እና በምትኖሩበት ሁሉ በታማኝነት፣ በቅንነት፣ በትሕትና እና በክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ሌሎችን አብሩ።
ውድ ተመራቂዎቻችን፣ ዛሬ ከግቢ ብትመረቁም ከክርስቶስ ትምህርትና ከቤተ ክርስቲያን ፈጽሞ እንዳትለዩ አደራ እንላለን። የተማራችሁትን እውቀት በሙያችሁ፣ ያገኛችሁትን ጸጋ በአገልግሎታችሁ፣ ያጸናችሁትን እምነት ደግሞ በሕይወታችሁ እየገለጣችሁ ለቤተ ክርስቲያን፣ ለሀገር እና ለማኅበረሰብ በረከት ሁኑ።
እግዚአብሔር በሄዳችሁበት ሁሉ ይጠብቃችሁ፤ ጥበቡንና ጸጋውን ያብዛላችሁ፤ የቤተ ክርስቲያኑን እና የሀገራችንን ተስፋ የምታለመልሙ ብቁ አገልጋዮች ያድርጋችሁ።
እንኳን ደስ አላችሁ!
የEABC ግቢ ጉባኤ
✨✨ልዩ የምርቃት መርሐግብር✨✨
🗓️ ሰኔ 21፥ 2018
⏰ ጥዋት 3፡00 ሰዓት
📌 ማኅደረ ስብሐት ልደታ ለማርያም እና ደብረ መድኃኒት መድኃኒዓለም ቤተክርስቲያን
✨✨ልዩ የምርቃት መርሐግብር✨✨
🗓️ ሰኔ 21፥ 2018
⏰ ጥዋት 3፡00 ሰዓት
📌 ማኅደረ ስብሐት ልደታ ለማርያም እና ደብረ መድኃኒት መድኃኒዓለም ቤተክርስቲያን
Repost from EiABC ቤተ-መጽሐፍት
እንኳን አደረሳችሁ
ሰኔ 12
✨በዚህች ቀን ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል አፎምያን ከሰይጣን እጅ ያዳነበት ቀን ነው።
✨ዳግመኛም በዚህ ዕለት ቅዱስ ሚካኤል ባሕራንን የሞቱን ደብዳቤ ወደ ሕይወት የቀየረበት ዕለት ነው።
✨ይህ ዕለት ጻድቁ ንጉሥ ቅዱስ ላሊበላ ያረፈበትም ቀን ነው።
አፎምያን ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ የታደጋት ቅዱስ ሚካኤል እኛንም በጥበቃው አይለየን አሜን!
💫 መልካም በዓል💫
ኃይልን በሚሰጠን በክርስቶስ ሁሉን እንችላለን። ፊልጵ 4፥13በዛሬ ዕለት Exit ፈተና ያላችሁ ውድ የግቢ ጉባኤያችን ተመራቂ ተማሪዎች ሰላም ለእናንተ ይሁን😊 በዚህ የፈተናችሁ ሰዓት እግዚአብሔር ለአእምሯችሁ ጥበብን ፣ ለልባችሁ ሰላምን መረጋጋትን ያድላችሁ። ይህን ወቅት ድካማችሁ ወደ ብርታት፣ ትጋታችሁም ወደ ውጤት የሚለወጥበት ፣ የበረከትን ፍሬ የምታጭዱበት ጊዜ ያድርግላችሁ። ስትጀምሩ እና ስትፈጽሙ በጸሎት ይሁን። መልካም እድል።
🕰 አርብ ከ 11:45 ጀምሮ
📍በደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ( አዲሱ ሚካኤል - አውቶቢስ ተራ )
ሰብሰብ ብለን ከእኅት ወንድሞቻችን ጋር በመገኘት የበረከቱ ተካፋይ እንሁን።
