የEiABC ግቢ ጉባኤ
Open in Telegram
ይህ የEiABC ግቢ ጉባኤ ኦፊሻል የቴሌግራም ቻነል ነው። በዚህ ቻነል የግቢ ጉባኤ መልክዕክቶች ሌሎችም ክርስትናችንን ሊያጠነክሩ የሚችሉ ትምህርቶች በቀጥታ ይተላለፋሉ። ቻነሉን ይቀላቀሉ። 👇👇👇👇👇👇👇 👉 @eggmk1984 👈 👉 @eggmk1984 👈 👆👆👆👆👆👆👆 ሀሳብ አስታያየት ካላችሁ @Eiabcgbigubae_bot @eiabcgebigubae
Show more856
Subscribers
-324 hours
No data7 days
+1130 days
Posts Archive
ብጹዕ አቡነ ጴጥሮስ ሰማዕተ ኢትዮጵያ
ብጹዕ አቡነ ጴጥሮስ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ስለ ሀገር ነፃነትና ስለ ሃይማኖት ጽናት ሲባል ሕይወትን አሳልፎ የመስጠት ታላቅ የጀግንነትና የሰማዕትነት ምሳሌ ናቸው። በ፲፱፳፰ ዓ.ም. አረመኔው የኢጣልያ ፋሺስት ሀገራችንን በግፍ በወረረበት ወቅት፣ ብጹዕነታቸው እንደ የቤተክርስቲያን አባትነታቸው ሕዝቡን በጸሎትና በትምህርት በማጽናት ብቻ ሳይሆን፣ ከግርማዊ ንጉሠ ነገሥቱ ጋር በመሆን እስከ ማይጨው ዘመቻ ድረስ በመሄድ አርበኞችን አበራታተዋል። በወቅቱ ጠላት የመርዝ ጋዝ ጥቃት በመክፈቱ ምክንያት ሠራዊቱ ወደ ኋላ ሲያፈገፍግ ከንጉሡ ጋር ወደ አዲስ አበባ ተመልሰው ነበር።
ይሁን እንጂ በጠላት የወረራ ግፍ ክፉኛ ያዘኑት አቡነ ጴጥሮስ በአዲስ አበባ በሰላም ለመቀመጥ አልፈቀዱም። ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም በመሄድ ለሀገርና ለነፃነት መሞት ቅዱስ ተግባር መሆኑን በመስበክ አርበኞች እንዲጋደሉ ማሳሰብና ማትጋት ጀመሩ። በእርሳቸው ስብከት የተነሳሱት እንደ ደጃዝማች አበራ ካሣ፣ ደጃዝማች ፍቅረ ማርያም እና ደጃዝማች ባልቻ አባ ነፍሶ ያሉ የአርበኞች ጦር አዲስ አበባ ላይ የተቀመጠውን የጠላት ኃይል ለማጥቃት ቢንቀሳቀሱም፣ የመረጃ ልውውጥ ክፍተት በመኖሩና በአንድ ጊዜ ባለመድረሳቸው ምክንያት ሳይሳካ ቀርቷል። አቡነ ጴጥሮስ ግን አዲስ አበባን ትተው ወደ ገጠር መሸሽ አልፈለጉም።
ከተማዋ ውስጥ ቀርተው ሕዝቡን ለማንቃት ቢሞክሩም በባንዳዎች መብዛት ምክንያት እንዳሰቡት መንቀሳቀስ ስላልቻሉ፣ ሐምሌ ፳፪ ቀን ፲፱፻፳፰ ዓ.ም. ለራስ ኃይሉ እጃቸውን ሰጡ፤ እርሳቸውም ወዲያውኑ ለግራዚያኒ አሳልፈው ሰጧቸው። በጣሊያን የጦር ሹማምንት በተሰየመው ችሎት ቀርበው "ለምን አምፁ?" ተብለው ሲጠየቁ፣
"እኔ ኢትዮጵያዊ ነኝ፥ ስለ ሀገሬና ስለ ቤተክርስቲያኔ እቆረቆራለሁ። እኔን ለመግደል እንደወሰናችሁ አውቃለሁ፤ በእኔ ላይ የፈለጋችሁትን አድርጉ፤ ግን ተከታዮቼን አትንኩ"በማለት ፍጹም የጽናትና የጀግንነት መልስ ሰጥተዋል። ለሞት የተፈረደባቸው ብጹዕነታቸው ከተገደሉበት ቦታ ከመድረሳቸው በፊት ለሕዝቡ ባስተላለፉት ሕያው መልእክት ውስጥ የፋሺስት መንግሥት ግፈኛ በመሆኑ ሕዝቡ እንዳይገዛለት፣ ነፃነቱንና ሃይማኖቱን እንዲከላከል፣ እንዲሁም የኢትዮጵያ መሬት ጠላትን ብትቀበል የተረገመች እንድትሆን አውግዘዋል። ሐምሌ ፳፪ ቀን ፲፱፳፰ ዓ.ም. ከቀኑ ፭፡፲፭ ላይ ስምንት ወታደሮች በተኮሱባቸው ጥይት ሳይሞቱ በመቅረታቸው፣ ሌላ ወታደር በሦስት የሽጉጥ ጥይት ራስ ቅላቸውን መትቶ ገድሏቸዋል። አስከሬናቸውም ሕዝቡ እንዳይወስደው በምሥጢር ከአዲስ አበባ ውጭ እንዲቀበር ተደረገ። አቡነ ጴጥሮስ በልጅነታቸው ከመምህራቸው ከዓለቃ ተጠምቀ የተቀበሉትን "በሰማዕትነት እለፍ" የሚል አደራ እስከ መጨረሻዋ የሕይወት እስትንፋሳቸው ድረስ ጠብቀዋል። ሀገራችን ነፃነቷን ከተቀዳጀች በኋላ ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፱፻፴፰ ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ እምብርት የመታሰቢያ ሐውልት ቆሞላቸዋል። በተጨማሪም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በቅድስና ማዕረግ "ቅዱስና ሰማዕት" ብሎ ያጸደቀላቸው ሲሆን፣ የከፈሉት ታላቅ መስዋዕትነት ለትውልድ ሁሉ የጀግንነትና የፍቅር ሕያው ምስክር ሆኖ ይኖራል። የሰማዕቱ የአቡነ ጴጥሮስ ረድኤት አይለየን!!!
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን !!!
ሐምሌ ፳፫ (23) ቀን ስንክሳር
👉እዚህ ይጫኑ👈
የEiABC ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን !!!
ሐምሌ ፳፪ (22) ቀን ስንክሳር
👉እዚህ ይጫኑ👈
የEiABC ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል
ዛሬ ሐምሌ ፳፩ የግቢ ጉባኤያችን የንስሐ ወር በይፋ ተጀምሯል። እኛም በዚህ ወር ራሳችንን አዘጋጅተን፣ በጾም፣ በጸሎትና በስግደት ሆነን ወደ ቃለ እግዚአብሔር ማዕድና ወደ ንስሐ አባቶቻችን ልንቀርብ ይገባል።
የንስሐ አባትን በተመለከተ፦
በግቢ ጉባኤ የተመደበላችሁን የንስሐ አባት በዚህ ወቅት ማግኘት የማትችሉ አባላት፣ የቤተሰባችሁን የንስሐ አባት ወይም ቀደም ሲል የነበራችሁን መንፈሳዊ አባት ማነጋገር ትችላላችሁ። የንስሐ አባት የሌላችሁም ከደብራችሁ መንፈሳዊ አባት በመያዝ መያዝ ያስፈልጋል።
ዋናው ነገር የትም ብንሆን ከንስሐ አባት መሪነትና ምክር እንዳንወጣ ነው።
ማንኛውንም ጥያቄ ካላችሁ እኛን ማግኘት ትችላላችሁ፦
👉 ሙሉነህ አበበ
0915852875 | @mule_yemariam_lij
👉 እሱባለው
0910212621 | @Bell_1221
ንስሐ ንዑስ ክፍል
EIABC ግቢ ጉባኤ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን !!!
ሐምሌ ፳፩ (21) ቀን ስንክሳር
👉እዚህ ይጫኑ👈
የEiABC ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል
በጣም ብዙ ምሳሌ መጥቀስ አስረጅ ታሪክ ማቅረብ የሚቻል ቢሆንም ለዛሬ ማንሳት የፈለግነው ግን ከመላእክት ወገን አንዱን በተራዳኢነቱ በመታዘዙ ለሰው ልጆች ባለው ቅርበትና አጋዥነት በብዙ ቅዱሳን ሰማዕታት የተጋድሎ የምስክርነት ሥራ ውስጥ በርኅራኄውና በቁጣው በፍቅሩና በአስፍሪነቱ የሚጠቀሰው ቅዱስ ገብርኤል ለቅዱስ ቂርቆስና ለእናቱ ለቅድስት ኢየሉጣ ያደረገውን ተራዳኢነት ነው፡፡
ይህ ገናና መልአክ ጥንት በሥነ ፍጥረት ዓለመ መላእክትን ያረጋጋ ነው፤ሦስቱን ሕፃናት ከእቶን እሳት ያወጣ መልአክ ነው ፤ይህ መልአክ ኤልሳቤጥን በእርጅናዋ ዘመን እንድትወልድ ያበሠረ ነው፤ይህ መልአክ ካህኑ ዘካርያስን አንደበቱን የዘጋ ነው፤ ይህ መልአክ ድንግል ማርያምን ለዛ ባለው ቃል በትሁት ማንነት ቀርቦ ያናገረ የልዑል ክርስቶስን መወለድ ያበሠረ የተስፋ ቃሉ ፍጻሜ መድረሱን ያስረዳ አብሣሬ ትስብእት ፍጡነ ረድኤት የሆነ መልአክ ነው፡፡
ወደ መነሻ ታሪካችን ስንመለስ ሐምሌ 19 ቀን ይህ መልአክ ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስንና እናቱን ቅድስት ኢየሉጣን ከእሳት ማዳኑ የሚዘከርበት ዕለት ነው፡፡ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ሀገሩ ሮም አንጌቤን ነው፡፡ አባቱ ቆዝሞስ እናቱ ኢየሉጣ ሲሆኑ ቅድስት ኢየሉጣ ከአዝማደ ነገሥት ነበረች፡፡ዲዮቅልጥያኖስ በነገሠ በ20 ዓመት (በ303 ዓ.ም) በአባ አባጋግዮስ ምክንያት ‹‹አብያተ ክርስቲያናት ይትዐጸዋ አብያተ ጣዖታት ይትረኃዋ ››የሚል አዋጅ ሲታወጅ ብዙ ክርስቲያኖች እንደ ሽንኩርት ተላጡ እንደ ጎመን ተቀረደዱ በሰይፍ ተቆረጡ በእሳት ተቃጠሉ ብዙ መከራ ደረሰ ብዙዎቹም ተሰደዱ፡፡ በዚህ ጊዜ ቅዱስ ቂርቆስ የሦስት ዓመት ሕፃን ሆኖ ከናቱ ጋር ወደ ጠርሴስ ሸሹ፡፡
ይሁን እንጅ በዚያም መስፍነ ብሔሩ እለእስክንድሮስ ክርስቶስን ካጂ ለጣኦት ስገጂ አላት፡፡‹‹ዐይን እያለው ለማያይ ጆሮ እያለው ለማይሰማ በቃልህ አዝዘህ በእጅህ አበጅተህ ላቆምከው ምስል አልሰግድም እስኪ ይህንን ህፃን ጠይቀው›› አለችው፡፡መስፍኑም ቅዱስ ቂርቆስን ‹‹አንተ ሕፃን ብዙ ወርቅ እሰጥሃለሁ ለዚህ ጣዖት ስገድ›› አለው፡፡መንፈስ ቅዱስ ያደረበት ነበርና ‹‹አንሰ ኢይሰግድ ለአማልክቲከ ርኩሳን ዘኢይክሉ አድኅኖ ርእሶሙ…ራሳቸውን ማዳን ለማይችሉ ርኩሳን ጣዖቶችህ አልሰግድም›› አለው፡፡(መዝገበ ታሪክ ክፍል 2)
በዚህ ጊዜ ተበሳጭቶ በብረት ጋን ውኃ አፍልታችሁ ዝፍት ተይ ጨምራችሁ በዚያ ጣሏቸው ብሎ አዘዘ፡፡ዝፍት ተይ ጨምረው በብረት ጋን ውኃ አፍልተው ‹‹ድምፃ ለጽሕርት ከመ ነጎድጓደ ክረምት ››ይላል የውኃው መፍለቅለቅ ፍላቱ እንደ ክረምት ነጎድጓድ እስከ 42 ምዕራፍ ድረስ እስኪሰማ ይጮህ ነበር ፡፡በዚያ ሊጥሏቸው ሲወስዷቸው ቅድስት ኢየሉጣ ልቧ ታወከ ፈራች ልጇ ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ግን ‹‹ፍርሃቷን አርቅላት›› እያለ ለእናቱ ይጸልይ ነበር፡፡
እንዲህም አላት ‹‹ጥብዒኬ እምየ እምዝ ዳግመ ኢይረክበነ ሞት…ሁለተኛ ሞት አያገኘንምና እናቴ ሆይ በርች ጨክኚ..አናንያን አዛርያን ሚሳኤልን ያዳነ እኛንስ ያድነን የልምን ? ››እያለ አጽናናት፡፡በዚህ ጊዜ ጨክነው ተያይዝው በእሳት ወደፈላው የጋን ዉኃ ገብተዋል፡፡ቅዱስ ዳዊት መላእክቱን ስላንተ ያዝዛቸዋል ያለው እንደነሱ ላለው ሕያው ምስክሮቹ ነውና ከመላእክት አንዱ ፍጡነ ረድኤት ቅዱስ ገብርኤል ፈጥኖ መጣ በበትረ መስቀሉ እሳቱን ሲመታዉ 42 ምዕራፍ እስኪሰማ የፈላው ዉሃ እንደ ጥዋት ጤዛ ቀዘቀዘ ቅድስት ኢየሉጣና ሕፃኑ ቂርቆስ በሰላም ከእሳቱ ወጡ፡፡
‹‹መንክር እግዚአብሔር በላዕለ ቅዱሳኒሁ›› እንዳለ ቅዱስ ዳዊት ..እግዚአብሔር በቅዱስ ቂርቆስ እና በእናቱ ቅድስት እየሉጣ ላይ የሠራው ተአምር እጅግ የሚደንቅ ተአምር እንደሆነ እንረለልን፡፡
አምላከ ቅዱስ ቂርቆስ ወኢየሉጣ በእደ መልአኩ ይጠብቀን አሜን፡፡
እስመ ለመላእክቲሁ ይኤዝዞሙ በእንቲአከ/ መላእክቱን ስላንተ ያዛቸዋል. (መዝሙር ፺፥፲፩)
ዲ/ን ይትባረክ
ክፍል 1
ይህንን ቃል የተናገረው ቅዱስ ዳዊት ነው፡፡የቅዱሳን መላእክትን ተልእኮ ከቅዱሳን ሰዎች ጋራ ያላቸውን ግንኙነት፤አምላካችን እግዚአብሔር ስሙን ለሚጠሩ ስለ ስሙ ለሚጋደሉ በዐላውያን በመናፍቃን ዘንድ ሕያው ምስክር ሆነው መከራን የሚቀበሉ ሰዎችን ለመርዳት ለመታደግ ለማገልገል ለማጽናት ለማበርታት መላእክቱን እንደሚያዛቸው መላእክቱም እንደሚታዘዙ የታዘዙበትን ተልእኮም እንደሚወጡ ሰማዕታቱ በኀይለ እግዚአብሔር በእደ መላእክት ተደግፈው በክንፈ መላእክት ተጠልለው ለቅድስና ለክብረ ቅዱሳን እንደሚበቁ ለተስፋው ቃል ፍጻሜ እንደሚደርሱ የድል አክሊል እንደሚቀዳጁ ሲያመላክት…..
‹‹እስመ ለመላእክቲሁ ይኤዝዞሙ በእንቲአከ ከመ ይዕቀቡከ በኩሉ ፍናዊከ ወበእደዊሆሙ ያነሥኡከ ከመ ኢይትዐቀፍ በዕብን እግርከ….መላእክቱን ስላንተ ያዝዛቸዋልና በሥራህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ በእጃቸው ያነሱህ ዘንድ እግርህ በድንጋይ እንዳትሰናከል…›› ይላል፡፡ (መዝ ፺፥፲፩-፲፫፤ዘፀ ፳፫፥፳ ማቴ ፬፥፮)
መላእክት ስለ ሰው ልጆች የታዘዙበት ጥላ ከለላ የሆኑበት አቅፈው ደግፍው ለክብር ያበቁበት ስለ ሰው ልጆች ታዝዘው በመዓትም በምሕረትም በቁጣም በትሕትናም የተገለጹበት ወዳጅን ረድተው ጠላትን ቀጥተው የተገለጡበት ታሪክ በመጽሐፍ ቅዱስ በብዙ ቦታ ተጠቅሷል በብዙ ቅዱሳን ሕይወት ውስጥ ታይቷል፡፡(ዘፀ ፳፫፥፳ ማቴ ፬፥፮፤፩ኛ.መቃ ፲፫፥፳፩፤ኢያ ፭፥፲፫፤ኢሳ ፷፫፥፱…….)
Repost from ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል
በጣም ብዙ ምሳሌ መጥቀስ አስረጅ ታሪክ ማቅረብ የሚቻል ቢሆንም ለዛሬ ማንሳት የፈለግነው ግን ከመላእክት ወገን አንዱን በተራዳኢነቱ በመታዘዙ ለሰው ልጆች ባለው ቅርበትና አጋዥነት በብዙ ቅዱሳን ሰማዕታት የተጋድሎ የምስክርነት ሥራ ውስጥ በርኅራኄውና በቁጣው በፍቅሩና በአስፍሪነቱ የሚጠቀሰው ቅዱስ ገብርኤል ለቅዱስ ቂርቆስና ለእናቱ ለቅድስት ኢየሉጣ ያደረገውን ተራዳኢነት ነው፡፡
ይህ ገናና መልአክ ጥንት በሥነ ፍጥረት ዓለመ መላእክትን ያረጋጋ ነው፤ሦስቱን ሕፃናት ከእቶን እሳት ያወጣ መልአክ ነው ፤ይህ መልአክ ኤልሳቤጥን በእርጅናዋ ዘመን እንድትወልድ ያበሠረ ነው፤ይህ መልአክ ካህኑ ዘካርያስን አንደበቱን የዘጋ ነው፤ ይህ መልአክ ድንግል ማርያምን ለዛ ባለው ቃል በትሁት ማንነት ቀርቦ ያናገረ የልዑል ክርስቶስን መወለድ ያበሠረ የተስፋ ቃሉ ፍጻሜ መድረሱን ያስረዳ አብሣሬ ትስብእት ፍጡነ ረድኤት የሆነ መልአክ ነው፡፡
ወደ መነሻ ታሪካችን ስንመለስ ሐምሌ 19 ቀን ይህ መልአክ ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስንና እናቱን ቅድስት ኢየሉጣን ከእሳት ማዳኑ የሚዘከርበት ዕለት ነው፡፡ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ሀገሩ ሮም አንጌቤን ነው፡፡ አባቱ ቆዝሞስ እናቱ ኢየሉጣ ሲሆኑ ቅድስት ኢየሉጣ ከአዝማደ ነገሥት ነበረች፡፡ዲዮቅልጥያኖስ በነገሠ በ20 ዓመት (በ303 ዓ.ም) በአባ አባጋግዮስ ምክንያት ‹‹አብያተ ክርስቲያናት ይትዐጸዋ አብያተ ጣዖታት ይትረኃዋ ››የሚል አዋጅ ሲታወጅ ብዙ ክርስቲያኖች እንደ ሽንኩርት ተላጡ እንደ ጎመን ተቀረደዱ በሰይፍ ተቆረጡ በእሳት ተቃጠሉ ብዙ መከራ ደረሰ ብዙዎቹም ተሰደዱ፡፡ በዚህ ጊዜ ቅዱስ ቂርቆስ የሦስት ዓመት ሕፃን ሆኖ ከናቱ ጋር ወደ ጠርሴስ ሸሹ፡፡
ይሁን እንጅ በዚያም መስፍነ ብሔሩ እለእስክንድሮስ ክርስቶስን ካጂ ለጣኦት ስገጂ አላት፡፡‹‹ዐይን እያለው ለማያይ ጆሮ እያለው ለማይሰማ በቃልህ አዝዘህ በእጅህ አበጅተህ ላቆምከው ምስል አልሰግድም እስኪ ይህንን ህፃን ጠይቀው›› አለችው፡፡መስፍኑም ቅዱስ ቂርቆስን ‹‹አንተ ሕፃን ብዙ ወርቅ እሰጥሃለሁ ለዚህ ጣዖት ስገድ›› አለው፡፡መንፈስ ቅዱስ ያደረበት ነበርና ‹‹አንሰ ኢይሰግድ ለአማልክቲከ ርኩሳን ዘኢይክሉ አድኅኖ ርእሶሙ…ራሳቸውን ማዳን ለማይችሉ ርኩሳን ጣዖቶችህ አልሰግድም›› አለው፡፡(መዝገበ ታሪክ ክፍል 2)
በዚህ ጊዜ ተበሳጭቶ በብረት ጋን ውኃ አፍልታችሁ ዝፍት ተይ ጨምራችሁ በዚያ ጣሏቸው ብሎ አዘዘ፡፡ዝፍት ተይ ጨምረው በብረት ጋን ውኃ አፍልተው ‹‹ድምፃ ለጽሕርት ከመ ነጎድጓደ ክረምት ››ይላል የውኃው መፍለቅለቅ ፍላቱ እንደ ክረምት ነጎድጓድ እስከ 42 ምዕራፍ ድረስ እስኪሰማ ይጮህ ነበር ፡፡በዚያ ሊጥሏቸው ሲወስዷቸው ቅድስት ኢየሉጣ ልቧ ታወከ ፈራች ልጇ ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ግን ‹‹ፍርሃቷን አርቅላት›› እያለ ለእናቱ ይጸልይ ነበር፡፡
እንዲህም አላት ‹‹ጥብዒኬ እምየ እምዝ ዳግመ ኢይረክበነ ሞት…ሁለተኛ ሞት አያገኘንምና እናቴ ሆይ በርች ጨክኚ..አናንያን አዛርያን ሚሳኤልን ያዳነ እኛንስ ያድነን የልምን ? ››እያለ አጽናናት፡፡በዚህ ጊዜ ጨክነው ተያይዝው በእሳት ወደፈላው የጋን ዉኃ ገብተዋል፡፡ቅዱስ ዳዊት መላእክቱን ስላንተ ያዝዛቸዋል ያለው እንደነሱ ላለው ሕያው ምስክሮቹ ነውና ከመላእክት አንዱ ፍጡነ ረድኤት ቅዱስ ገብርኤል ፈጥኖ መጣ በበትረ መስቀሉ እሳቱን ሲመታዉ 42 ምዕራፍ እስኪሰማ የፈላው ዉሃ እንደ ጥዋት ጤዛ ቀዘቀዘ ቅድስት ኢየሉጣና ሕፃኑ ቂርቆስ በሰላም ከእሳቱ ወጡ፡፡
‹‹መንክር እግዚአብሔር በላዕለ ቅዱሳኒሁ›› እንዳለ ቅዱስ ዳዊት ..እግዚአብሔር በቅዱስ ቂርቆስ እና በእናቱ ቅድስት እየሉጣ ላይ የሠራው ተአምር እጅግ የሚደንቅ ተአምር እንደሆነ እንረለልን፡፡
አምላከ ቅዱስ ቂርቆስ ወኢየሉጣ በእደ መልአኩ ይጠብቀን አሜን፡፡
Repost from ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል
እስመ ለመላእክቲሁ ይኤዝዞሙ በእንቲአከ/ መላእክቱን ስላንተ ያዛቸዋል. (መዝሙር ፺፥፲፩)
ዲ/ን ይትባረክ
ክፍል 1
ይህንን ቃል የተናገረው ቅዱስ ዳዊት ነው፡፡የቅዱሳን መላእክትን ተልእኮ ከቅዱሳን ሰዎች ጋራ ያላቸውን ግንኙነት፤አምላካችን እግዚአብሔር ስሙን ለሚጠሩ ስለ ስሙ ለሚጋደሉ በዐላውያን በመናፍቃን ዘንድ ሕያው ምስክር ሆነው መከራን የሚቀበሉ ሰዎችን ለመርዳት ለመታደግ ለማገልገል ለማጽናት ለማበርታት መላእክቱን እንደሚያዛቸው መላእክቱም እንደሚታዘዙ የታዘዙበትን ተልእኮም እንደሚወጡ ሰማዕታቱ በኀይለ እግዚአብሔር በእደ መላእክት ተደግፈው በክንፈ መላእክት ተጠልለው ለቅድስና ለክብረ ቅዱሳን እንደሚበቁ ለተስፋው ቃል ፍጻሜ እንደሚደርሱ የድል አክሊል እንደሚቀዳጁ ሲያመላክት…..
‹‹እስመ ለመላእክቲሁ ይኤዝዞሙ በእንቲአከ ከመ ይዕቀቡከ በኩሉ ፍናዊከ ወበእደዊሆሙ ያነሥኡከ ከመ ኢይትዐቀፍ በዕብን እግርከ….መላእክቱን ስላንተ ያዝዛቸዋልና በሥራህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ በእጃቸው ያነሱህ ዘንድ እግርህ በድንጋይ እንዳትሰናከል…›› ይላል፡፡ (መዝ ፺፥፲፩-፲፫፤ዘፀ ፳፫፥፳ ማቴ ፬፥፮)
መላእክት ስለ ሰው ልጆች የታዘዙበት ጥላ ከለላ የሆኑበት አቅፈው ደግፍው ለክብር ያበቁበት ስለ ሰው ልጆች ታዝዘው በመዓትም በምሕረትም በቁጣም በትሕትናም የተገለጹበት ወዳጅን ረድተው ጠላትን ቀጥተው የተገለጡበት ታሪክ በመጽሐፍ ቅዱስ በብዙ ቦታ ተጠቅሷል በብዙ ቅዱሳን ሕይወት ውስጥ ታይቷል፡፡(ዘፀ ፳፫፥፳ ማቴ ፬፥፮፤፩ኛ.መቃ ፲፫፥፳፩፤ኢያ ፭፥፲፫፤ኢሳ ፷፫፥፱…….)
ብቸኝነት ማለት በዙሪያህ የሚሆኑ ሰዎችን ማጣት ማለት አይደለም ብቸኝነት ማለት በልብህ ውስጥ እግዚአብሔርን አጥተህው የምትኖርበት የነፍስ ባዶነት ነው እንጂ። ክርስቶስ በአንተ መርከብ ውስጥ ካለ በምድረ በዳ ብቻህን ብትሆን እንኳ ፈጽሞ ብቸኛ አይደለህም እርሱ ዓለምን ሁሉ የሚተካ ታላቅ ወዳጅ ነውና።
አባ እንጦንስ
