en
Feedback
Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

Open in Telegram

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

Channel Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council (@eiasc1) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 11 190 subscribers, ranking 8 052 in the Religion & Spirituality category and 3 002 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 11 190 subscribers.

According to the latest data from 09 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -72 over the last 30 days and by -2 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 16.51%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 9.93% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 1 846 views. Within the first day, a publication typically gains 1 111 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 10 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

11 190
Subscribers
-224 hours
-227 days
-7230 days
Posts Archive
ዳሸን ባንክ ከጠቅላይ ምክር ቤቱ ጋር በመተባበር ለአቅመ ደካማ ወገኖች ማዕድ አጋራ። •••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ጳጉሜ 5/2018 ዓ.ል| ረቢዑል አወል 28 /1448 ዓ.ሒ بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ •••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• አዲስ አበባ | ​ዳሸን ባንክ ማህበራዊ ሀላፊነትን መሠረት በማድረግ ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ጋር በመተባበር ለ100 አቅመ ደካማ ወገኖች ማዕድ አጋራ። ​በጠቅላይ ምክር ቤቱ ቅጥር ግቢ በተከናወነው የማዕድ ማጋራት መርሐ ግብር ላይ የተገኙት የጠቅላይ ምክር ቤቱ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝደንት ሸይኽ አብዱልከሪም ሸይኽ በድረዲን ማዕድ ማጋራት የመተሳሰብ፣ የመረዳዳትና የበጎነት ተግባራትን በማጠናከር ለማህበራዊ አብሮነት ግንባታ አስተዋፅኦ ያደርጋል ብለዋል። አቅመ ደካሞችን መመገብና መንከባከብ ኢስላማዊ እሴት መሆኑን ያስታወሱት ሸይኽ አብዱልከሪም ሸይኽ በድረዲን ዳሸን ባንክ ከጠቅላይ ምክር ቤቱ ጋር በመቀናጀት ለአቅመ ደካሞች ማዕድ ማጋራቱ ለማህበራዊ ኃላፊነት የሰጠውን ከፍተኛ ትኩረት ያሳያል ብለዋል። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ሥራ አስፈጻሚ አባል እና የማህበራዊ ጉዳዮች ኃላፊ ዶክተር ኢብራሂም አህመድ በበኩላቸው ዳሸን ባንክ ድጋፍ የሚፈልጉ ወገኖችን ማዕድ ለማጋራት ጠቅላይ ምክር ቤቱን በአጋርነት ስለመረጠ ያላቸውን ምስጋናቸው ገልጸው ማዕድ ማጋራት በእስልምና አስተምህሮም ሆነ በማንኛውም በጎ ባህል ውስጥ ከፍተኛ መንፈሳዊ ዋጋ ያለው ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። ​አቅመ ደካሞችንና ድጋፍ የሚሹ ወገኖቻችንን መንከባከብ የአንድ ወገን ወይም የኃይማኖት ተቋም ኃላፊነት ብቻ ሳይሆን የሁሉም ሰው የሞራል እና የዜግነት ግዴታ ነው ያሉት ዶክተር ኢብራሂም አህመድ ሁሉም ሰው በሚችለው አቅም ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን ወገኖች በማገዝ የመረዳዳትና የመደጋገፍ ባህላችንን አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ብለዋል። የዳሸን ባንክ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት ቺፍ ኦፊሰር አቶ አምዱ ሠማን በዚሁ ወቅት እንደገለጹት ባንኩ ማኅበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት እና የሕዝብ አጋርነቱን ለማረጋገጥ ከፍተኛ በጀት በመመደብ በየዓመቱ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን ወገኖች እንደሚደግፍ አንስተዋል። ​ዳሽን ባንክ በሸሪክ የወለድ አልባ መረሀ ግብሩ ከጠቅላይ ምክር ቤቱ ጋር በመቀናጀት ይህን መሠል የማዕድ ማጋራት ተግባር ማከናወኑ የተጠቃሚዎችን ችግር ከማቃለሉ በተጨማሪ በመረዳዳት የተጠናከረ ማህበረሰብ ለመገንባት ወሳኝ ሚና እንዳለው ገልጸዋል። ዳሸን ባንክ በቀጣይም በጎ ተግባራት ዙሪያ ከጠቅላይ ምክር ቤቱ ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ የተጠቀሰ ሲሆን የእርዳታው ተጠቃሚ የሆኑ ወገኖችም ለተደረገላቸው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በማዕድ ማጋራት መርሃ ግብሩ ላይ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ስራ አስፈጻሚ አባልና የህዝብ ግንኙነትና ሚዲያ ዘርፍ ኃላፊ ዑስታዝ ፋሪስ ጀማል እና የዳሸን ባንክ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። ••••••••••••••••••••••••••••••••••••• የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት ይከታተሉን | Follow us፡ ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council ቴሌግራም | t.me/eiasc1 ትዊተር | https://x.com/eiasc1

በአይን ሞራ ግርዶሽ ተጠቂ ለሆኑ ዜጎች ነጻ የህክምና አገልግሎት ሊሰጥ መሆኑ ተገለጸ:: •••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ጳጉሜ 4/2018 ዓ.ል| ረቢዑል አወል 27 /1448 ዓ.ሒ بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• አዲስ አበባ | ​የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የልማት ክንፍ የሆነው አወሊያ ዕርዳታና ልማት ድርጅት ከአል በስር ኢንተርናሽናል ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር ነጻ የአይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና ሊሰጥ ነው። ነጻ ህክምናው በአይን ሞራ ግርዶሽ ምክንያት በከፊልና ሙሉ በሙሉ ለሙሉ የእይታ እክል ላጋጠማቸው ወገኖች የሚሰጥ ሲሆን ለህክምናው አስፈላጊ የሆኑ ቅድመ ዝግጅቶች ከወዲሁ መጠናቀቃቸውን የአወልያ እርዳታ እና ልማት ድርጅት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሐጅ ሰዒድ አስማረ ተናግረዋል። የመጀመሪያው ዙር ነጻ የህክምና አገልግሎት በአዲስ አበባ ከተማ በአወሊያ ጤና ጣቢያ ከመስከረም 4 እስከ መስከረም 7 /2019 እንደሚሰጥም ዋና ስራ አስኪያጁ ገልጸዋል። ​የህክምናው ተጠቃሚ መሆን የሚፈልጉ የአዲስ አበባ እና አካባቢዋ ነዋሪዎች በተጠቀሱት ቀናት በአወሊያ ጤና ጣቢያ በመገኘት የነጻ ህክምና አገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑም ሐጅ ሰዒድ አስማረ ጥሪ አቅርበዋል። ​ነጻ የአይን ሞራ ግርዶች ህክምናው በቀጣይም በጅማ እና በወሎ አካባቢዎች እንደሚሰጥ ተመላክቷል። ••••••••••••••••••••••••••••••••••••• የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት ይከታተሉን | Follow us፡ ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council ቴሌግራም | t.me/eiasc1 ትዊተር | https://x.com/eiasc1

በጠቅላይ ምክር ቤቱ የኡለማ ጉባዔ ዘርፍ ምክትል ፕሬዝዳንት ሸይኽ ጁነይድ ሐምዛ የተመራ ልዑክ ለስራ ጉዳይ ጎዴ ከተማ ገባ። •••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ነሀሴ 29 /2018 ዓ.ል| ረቢዑል አወል 22 /1448 ዓ.ሒ بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ •••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ጎዴ | በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የኡለማ ጉባዔ ዘርፍ ምክትል ፕሬዝዳንት ሸይኽ ጁነይድ ሐምዛ ዩሱፍ የተመራው የስራ ልዑክ በሶማሌ ክልል ጎዴ ከተማ ገባ። ​ ልዑኩ በጎዴ ኡጋዝ ሚራድ ኤርፖርት ሲደርስ በሶማሌ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የዳዕዋ ዘርፍ ተጠሪ ሸይኽ አብዱሽኩር ሸይኽ አብደላ፣ የጎዴ ከተማ እስልምና ምክር ቤት ሰብሳቢ ሸይኽ ኢስማኢል ሙዓሊም እንዲሁም የሃይማኖት አባቶችና የአካባቢው አመራሮች ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። ​ልዑኩ ጎዴ ከተማ የገባው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ዑለማ ጉባዔ ከቡኒያን ዓለም አቀፍ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር በጎዴ ከተማና በሸበሌ ዞን ለሚገኙ አንድ መቶ ኢማሞችና አሳቲዞች የሚሰጠውን የአቅም ግንባታ ስልጠና በማስተባበር ውጤታማ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የስራ አቅጣጫ እና መመሪያ ለመስጠት ነው። ጠቅላይ ምክር ቤቱ ከቡኒያን ዓለም አቀፍ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር ከዚህ በፊትም በተለያዩ ከተሞች ለኢማሞችና ለኡስታዞች ተመሳሳይ የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠቱ ይታወሳል። •••••••••••••••••••••••••••••••••••••• የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት ይከታተሉን | Follow us፡ ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council ቴሌግራም | t.me/eiasc1 ትዊተር | https://x.com/eiasc1

የጨረታ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በጊቢው ውስጥ ሊያስገነባ ላሰበው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቻርጅ ማድረጊያ የመኪና ማቆሚያ ግንባታ ብቁ ተጫራቾችን ማወዳደር ይፈልጋ
+1
የጨረታ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በጊቢው ውስጥ ሊያስገነባ ላሰበው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቻርጅ ማድረጊያ የመኪና ማቆሚያ ግንባታ ብቁ ተጫራቾችን ማወዳደር ይፈልጋል በመሆኑም ከስር በተያያዘው ሰነድ ላይ በዝርዝር የቀረቡ መስፈርቶችን የምታሟሉ ተጫራቾች በጨረታው እንዲሳተፉ እንጋብዛለን። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት

የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ 15ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እና 18ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በጋራ እያካሄደ ነው ። •••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ነሀሴ 26/2018 ዓ.ል| ረቢዑል አወል 19/1448 ዓ.ሒ بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ •••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• አዲስ አበባ | የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ከምስረታው 15ኛ ዓመት በዓል ጋር በማያያዝ 18ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን እያካሄደ ይገኛል። ​ጉባኤው በይፋ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ያከናወናቸውን ተግባራትና ያመጣቸውን ስኬቶች የሚዘክረው ይህ ጉባዔ ፤ "15 ዓመታት - እምነትን በቀጣይነት፣ ሰላምን ህብረብሔራዊ ልማት በኢትዮጵያ" በሚል መሪ ሀሳብ በልዩ ልዩ መርሃ ግብሮች እየተከናወነ ነው። በዚሁ ታሪካዊ መርሃ ግብር ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የየሃይማኖት ተቋማት መሪዎች እና የጉባኤው የበላይ ጠባቂ አባቶች ፣ሚኒስቴሮች እና የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ተወካዮች፣የክልል ቤተ እምነት ዋና ጽሕፈት ቤቶች እና ከክልል ጉባኤዎች የተወከሉ የጠቅላላ ጉባኤ አባላት እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጥሪ ተደርጎላቸዋል እንግዶች እየተሳተፉ ይገኛሉ። የዕለቱ የክቡር እንግዳ የኢፌዲሪ ፕረዚዳንት ክቡር አቶ ታዬ አጽቀስላሴ የእምነት አባቶች የሀገራችን አያሌ ዘመናት የአብሮነትና የመተባበር ና የሰላም ዕሴትን ምዕመናን ሲያስተምሩ መቆየታቸውን ተናግረዋል። የእምነት አባቶች በጨለማ ብርሀንን ፣በተከፋፈሉ ልቦች ውስጥ አንድነትን የሚያመጡ በመሆኑ መከፋፈልን እንደስኬት የሚቆጥሩ አካላትን እንዲያወግዙ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል። ከኢትዮጵያዊነት ባህል ውጪ የሆኑ ቅጥፈት ፣ እብለትን ፣ሌብነትን ና ለሰዎች ደንታቢስነትን እንዲታረሙ ማስተማር የተቋማቱ ቀዳሚ ተግባር መሆን እንደሚኖርበት አሳስበዋል። የኢፌዲሪ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አቶ ሙሀመድ ኢድሪስ አባል ቤተ ዕምነቱ ተቋማቱ የሀገራችንን ሰላምና አብሮነት ላይ ላለፉት አስራ አምስት አመታት በመስራት ታሪካዊ ድል ማስመዝገቡን ተናግረዋል። ተቋማቱ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ስኬት ያደረጉት አስተዋፅኦ በምሳሌነት ጠቅሰዋል።በቀጣይም በትብብርና በአንድነት በመቆም በጋራ ጉዳዮች ላይ በማተኮር ውጤታማ ስራ እንዲሰሩ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ጠቅላይ ፀሐፊ ሊቀ ትጉኅን ታጋይ ታደሰ ሁሉም ሃይማኖቶች የሚሰብኩት ሰላም በመሆኑ ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም ሁሉም የበኩሉን አስተዋፅኦ እንዲያበረክት የአደራ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ችግሮችን ለመፍታት በጋራ መስራት አማራጭ የሌለው መፍትሄ መሆኑ በመታመኑ የሃይማኖት አባቶች በጋራ እየሰሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ የሃይማኖት አባቶች ያላቸውን ተሰሚነትን ተጠቅመው በተለያዩ አካባቢዎች ግጭቶች እንዳይፈጠሩ በማድረግ፣ ጥያቄዎች ካሉ ደግሞ በውይይት መፍታት እንደሚቻል በማሳየት ስራዎች መስራቱን ገልጸዋል፡ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት የጠቅላላ ጉባዔና የሥራ አመራር ቦርድ አባል ዑስታዝ ሀሰን ዓሊ ባደረጉትን ንግግር ፣አባል የሃይማኖት ተቋማቱ ከመንፈዊ አገልግሎታቸው ጎን ለጎን በጋራ ሀገራዊ የሰላም ፣ የልማት ስራ ባሻገር በሃይማኖት ተቋማትና የሃይማኖት አባቶች መካከል የእር በእርስ ግንኙነት እንዲጠናከር ማድረጉን ተናግረዋል። ጉባዔው በአባል ቤተ እምነቶች መካከል ለግጭት መንስዔ የሆኑ ጉዳዮችን በውይይት በመፍታት ፣ማሕበራዊ እድገትን የሚያፋጥኑ የልማት ሥራዎችን በትብብር በመስራት ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በ መርሃ ግብር ላይ ጉባኤው ባለፉት 15 ዓመታት በሀገሪቱ ሰላም፣ አብሮነት እና ህብረብሔራዊ ልማት እንዲጸና ያከናወናቸው አዎንታዊ ተግባራት የሚገመገሙ ሲሆን፣ በቀጣይ አቅጣጫዎችና በ18ኛው መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔዎች ላይም ምክክር ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል። •••••••••••••••••••••••••••••••••••••• የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት ይከታተሉን | Follow us፡ ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council ቴሌግራም | t.me/eiasc1 ትዊተር | https://x.com/eiasc1

ጋዜጠኛ አብዱረሂም አህመድ ከህዝበ ሙስሊሙ እውቅናና ሽልማት ተበረከተለት። ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ነሀሴ 25/2018 ዓ.ል| ረቢዕ አል አወል 18/1448 ዓ.ሒ بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ •••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• አዲስ አበባ| በሙስሊሞች መብት መከበር ዙሪያ ትኩረት አድርጎ ለበርካታ ዓመታት እየሰራ የሚገኘው ጋዜጠኛ አብዱረሂም አህመድ ለህዝበ ሙስሊሙ መብት መከበር ላበረከተው እና እያበረከተ ላለው ጉልህ አስተዋጽኦ ከህዝበ ሙስሊሙ እውቅናና ሽልማት ተበረከተለት። ደረሳው ሰዒድ በሚል ስያሜ በሚሰራቸው ኢስላማዊ የኪነ ጥበብ ስራዎቹ የሚታወቀው ጋዜጠኛ አብዱረሂም አህመድ አሁን ላይ ሀሩን ሚዲያ በሚል ስያሜ በመሰረተው የሚዲያ ተቋሙ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍል የሙስሊሞች መብት እንዲከበር እየሰራ ይገኛል። በዛሬው ዕለት ሳፋየር አዲስ በተካሄደው የዕውቅናና ሽልማት ፕሮግራም ላይ ጋዜጠኛ አብዱረሂም አህመድ የምስክር ወረቀት፣ የዋንጫ እና ልዩ ልዩ ስጦታዎች ተበርክተውለታል። በመርሃ ግብሩ ላይ የሚዲያን ሃያልነት እና ህዝበ ሙስሊሙ በዘርፉ ያለው ክፍተት የተገለጹ ሲሆን ለህዝበ ሙስሉሙ መብት መከበር እየተንቀሳቀሱ ያሉበእንደ ሃሩን ሚዲያ ያሉ ተቋማት እንዲጠናከሩ ሁሉም ድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ ተላልፏል። በበጎ ፈቃደኛ ሙስሊሞች አስተባባሪነት እውቅና የተበረከተለት አብዱረሂም አህመድ የተሰጠው እውቅና በሚዲያ ዘርፉ የተሰማሩ ተቋማትን የሚያበረታታ መሆኑን ገልጸዋል። በእውቅናና የሽልማት መርሃ ግብሩ ላይ መሻይሆች፣ ዱዓቶች፣ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ ባለሃብቶች፣ የበጎ አድራጎት ተቋማት አመራሮችና የሚዲያ ባለሙያዎች፣ የስራ ባልደረባዎቹ ተገኝተዋል። •••••••••••••••••••••••••••••••••••••• የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት ይከታተሉን | Follow us፡ ቨቨዠፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council ቴሌግራም | t.me/eiasc1 ትዊተር | https://x.com/eiasc1

ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት ከክቡር ዶክተር ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ የተሰጠ የሀዘን መግለጫ "እኛ የአላህ ነን፤ ወደ እርሱም ተመላሾች ነን።" ( አል-በቀራህ፡ 156)
ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት ከክቡር ዶክተር ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ የተሰጠ የሀዘን መግለጫ "እኛ የአላህ ነን፤ ወደ እርሱም ተመላሾች ነን።" ( አል-በቀራህ፡ 156) ​የፈርስት ሂጅራ ፋውንዴሽን መስራች አባል እና አመራር የነበሩት የተከበሩ ሀጂ ነጅብ ሙሀመድ ወደ አኺራ በመሻገራቸው የተሰማኝን ጥልቅ ሀዘን እገልጻለሁ። ​ሀጂ ነጅብ ሙሀመድ ህይወታቸውን ሙሉ ለእስልምና እና ለህዝበ ሙስሊሙ ሲታገሉ ያሳለፉ፣ በሰብዓዊ እና በማህበረሰባዊ የልማት ስራዎች ላይ ግንባር ቀደም ተሳታፊ የነበሩ ታላቅ ሰው ነበሩ። ሀጂ ነጅብ ሙሀመድ በፈርስት ሂጅራ ፋውንዴሽን መስራችነታቸው እና አመራርነታቸው የኢስላማዊ እሴቶችን ለማስፋፋት፣ የታሪክ እና የቅርስ ጥበቃን ለማሻሻል እንዲሁም የህዝበ ሙስሊሙም አንድነት ለማጠናከር ሰርተዋል። ይህ በጎ ተግባራቸው በታሪክ እና በምእመናን ልብ ውስጥ ሲታወስ የሚኖር ነው። ​ለሟቹ ወንድማችን አላህ (ሱ.ወ) ሰፊ እዝነቱን እና ምህረቱን ለግሶ ጀነተል ፊርደውስን እንዲያጎናጽፋቸው እንዲሁም ለቤተሰቦቻቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው አላህ መፅናናትን እና ሰብርን እንዲሰጥ እየተመኘሁ ህዝበ ሙስሊሙ በየመስጂዶቹ ሶላተል ገይብ (የሩቅ ሶላት) እንዲሰግድላቸው ጥሪዬን አቀርባለሁ። ​የክቡር ዶክተር ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ - የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት

ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የተሰጠ የሀዘን መግለጫ ​"ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን" ​"ሁላችንም የአላህ ነን፤ ወደ እርሱም ተመላሾች ነን።" በሀገረ አሜሪካ ሙስሊም ኢትዮጵያ
ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የተሰጠ የሀዘን መግለጫ ​"ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን" ​"ሁላችንም የአላህ ነን፤ ወደ እርሱም ተመላሾች ነን።" በሀገረ አሜሪካ ሙስሊም ኢትዮጵያዊያንን ያሰባሰበው የፈርስት ሂጅራ ፋውንዴሽን መሥራችና ለአርባ ዓመታት በመሪነት ያገለገሉት ሐጂ ነጂብ ሙሐመድ ወደ አኺራ ተሻግረዋል። ሐጂ ነጂብ ከፈርስት ሂጅራ መሥራችነት ባሻገር ለኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች መብት መከበር በተለያዩ መልኩ ታግለዋል፤ ከቅድመ ድምጻችን ይሰማ ትግል ወቅት ጀምሮ የህዝበ ሙስሊሙን ጥያቄዎች በድፍረት ለመንግስት ግልጽ አድርገዋል። የድምጻችን ይሰማ የመብት ማስከበር ትግል 2004 ላይ ሲጀመርም በሚዲያዎችና በሰላማዊ ሰልፎች ላይ በመገኘት የህዝበ ሙስሊሙን የመብት ጥያቄዎች ትክክኛነት አስረድተዋል። የመንግሥትን የሀሰት ፕሮፓጋንዳና ስም ማጥፋት በማክሸፍም ግንባር ቀደም ሚና ተጫውተዋል። የሐጂ ነጂብ ሙሐመድ ሰላተል ጀናዛ በኒውሃምፕሻየር MCC መስጂድ ኦገስት 30/2016 በ1:30 PM የሚሰገድ ሲሆን ስርዓተ ቀብራቸው ደግሞ በአል ፊርደውስ መታሰቢያ ጋርደን ይፈጸማል። ቤተሰቦቹ በፈርስት ሂጅራ ፋውንዴሽን ታዕዚያ የሚቀመጡ ሲሆን ሐጂ ነጂብ ሙሐመድ የአራት ልጆች አባትና የአምስት የልጅ ልጆች አያት ነበሩ። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በሐጂ ነጂብ ሙሐመድ ህልፈተ ሕይወት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን እየገለፀ አሏህ ሱብሀነሁ ወተዓላ ለሟቹ ምሕረቱን ለግሶ ማረፊያቸውን ጀነት እንዲያደርግላቸው እንዲሁም ለቤተሰቦቻቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መፅናናትን እንዲሰጥ ይመኛል። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ነሀሴ 24/2018 ዓ.ል ረቢዑል አወል 17/1448 ዓ.ሒ

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝደንት ለባሌ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት የቢሮ ግንባታ የመሰረት ድንጋይ አስቀመጡ። •••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
+3
የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝደንት ለባሌ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት የቢሮ ግንባታ የመሰረት ድንጋይ አስቀመጡ። ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ነሀሴ 23/2018 ዓ.ል| ረቢዕ አል አወል 16/1448 ዓ.ሒ بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ •••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ባሌ ሮቤ| የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት የክቡር ዶክተር ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ የባሌ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ለሚገነባው ባለ አምስት ወለል ሕንፃ የመሰረት ድንጋይ አስቀመጡ። ​በ1 ሺህ 7 መቶ 50 ካሬ ሜትር የቦታ ስፋት ላይ የሚያርፈው ይህ ዘመናዊ ሕንፃ ግንባታው ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ ለምክር ቤቱ ቢሮዎች እንዲሁም ለተለያዩ ተያያዥ አገልግሎቶች የሚውል መሆኑ ተገልጿል። ​የህንጻ ግንባታው የዞኑ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ለአገልግሎት አሰጣጡ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠርና ተቋማዊ አቅሙን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያደርገውን እንቅስቃሴ እንደሚያግዝ ተመላክቷል። በመርሃ ግብሩ ላይ የፌዴራል፣ የክልል እና የከተማ መጅሊስ ስራ አስፈጻሚ አባላትና ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። •••••••••••••••••••••••••••••••••••••• የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት ይከታተሉን | Follow us፡ ቨቨዠፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council ቴሌግራም | t.me/eiasc1 ትዊተር | https://x.com/eiasc1

በጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝደንት ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ የተመራው ልዑክ ተፈጥሯዊውን የሶፍ ዑመር ዋሻ ጎበኘ። ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ነሀሴ 22 /2018 ዓ.ል| ረቢዕ አል አወል 15/1448 ዓ.ሒ بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ •••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ባሌ ሮቤ| በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት የክቡር ዶክተር ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ የተመራው ልዑክ በታዋቂው መንፈሳዊ አባት ሸይኽ ሱፊ ዑመር አሕመድ ስም የሚጠራውንና በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በጻፉት የመደመር ትውልድ መፅሀፍ ሽያጭ የለማውን ሶፍ ዑመር ዋሻ ጎበኘ። ​ታሪካዊውና ተፈጥሯዊው የቱሪዝም መዳረሻ ሶፍ ዑመር ዋሻ ለሀገር እና ለህዝብ እየሰጠ ያለውን ኢኮኖሚያዊና ባህላዊ ጥቅም ለማሳደግ ሰፊ የመሰረተ ልማት ግንባታ ስራዎች ተሰርተዋል። ሶፍ ዑመር ዋሻ ተፈጥሯውዊ እና ባህላዊ እሴቱ ተጠብቆ ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ጎብኚዎች ምቹ እንዲሆን የተሰሩ ስራዎች የአካባቢውን የቱሪዝም ፍሰት ማሳደግ እንደቻሉ በጉብኝቱ ተመላክቷል። በጉብኝቱ ላይ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት ሸይኽ አብዱልከሪም ሸይኽ በድረዲን፣ ምክትል ፕሬዝደንቶች ሸይኽ ሀሚድ ሙሳ እና ሸይኽ ጁነይድ ሃምዛ፣ የአዲስ አበባ ከተማ እና የኦሮሚያ ክልል መጅሊስ የስራ አስፈፃሚዎች፣ ዱዓቶች፣ የወጣት ካውንስል አመራሮች እና ታዋቂ ግለሰቦች ተሳትፈዋል። •••••••••••••••••••••••••••••••••••••• የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት ይከታተሉን | Follow us፡ ቨቨዠፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council ቴሌግራም | t.me/eiasc1 ትዊተር | https://x.com/eiasc1