en
Feedback
Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

Open in Telegram

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

Channel Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council (@eiasc1) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 11 287 subscribers, ranking 8 059 in the Religion & Spirituality category and 2 961 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 11 287 subscribers.

According to the latest data from 27 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -74 over the last 30 days and by -2 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 17.17%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 9.89% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 1 938 views. Within the first day, a publication typically gains 1 116 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 28 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

11 287
Subscribers
-224 hours
-267 days
-7430 days
Posts Archive
"ጠቅላይ ምክር ቤቱ ለቅዱስ ቁርአን ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት መድረሳዎች እንዲስፋፉና ውጤታማ ስራ እንዲሰሩ በትጋት ይሰራል።" - ሸይኽ ጁነይድ ሀምዛ ━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━ ሐምሌ 21 /2018 ዓ.ል | ሰፈር 14/1448 ዓ.ሂ بِسْمِ ٱللَّٰهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ ━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━ ጅግ ጅጋ | የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ከሶማሌ ክልል እስልምና ከፍተኛ ምክር ቤት እና በኢትዮጵያ የሳውዲ ዓረቢያ ኤምባሲ የባህል አታሼ ቢሮ ጋር በመተባበር የቁርአን ሂፍዝ ውድድር በጅግጅጋ ከተማ እየተካሄደ ነው። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የኡለማ ጉባዔ ዘርፍ ምክትል ፕሬዝደንት ሸይኽ ጁነይድ ሐምዛ ዩሱፍ በቁርአና ውድድሩ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር ጠቅላይ ምክር ቤቱ ለቅዱስ ቁርአን ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት መድረሳዎች እንዲስፋፉና ውጤታማ ስራ እንዲሰሩ በትጋት እየሠራ ይገኛል ብለዋል። ​ጠቅላይ ምክር ቤት የሙስሊሙን አንድነት ለማጠናከርና ለማስጠበቅ የሚያደርገውን እንቅስቃሴ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ምክትል ፕሬዝደንቱ በአጽንኦት ገለፀዋል። ማጣሪያ ውድድሩ በሦስት ዘርፎች ተከፍሎ እየተካሄደ የሚገኝ ሲሆን 'በሀፍስ' አቀራር የሙሉ ቁርአን ሂፍዝ፣ 'በወርሽ' አቀራር የሙሉ ቁርአን ሂፍዝ እንዲሁም የአምስት ፣ የአስር ና የሀያ ጁዝ የቁርአን ንባብ 'በተጅዊድ እና በተላዋ' በሰባት አይነት የአቀራር ዜዴዎች ይከናወናል። ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት ይከታተሉን | Follow us፡ ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council ቴሌግራም | t.me/eiasc1 ትዊተር | https://x.com/eiasc1

የኢስላማዊ ዩንቨርስቲ እና ኮሌጅ መምህራንን የምርምር አቅም የሚያሳድግ የሳይንሳዊ ምርምር ዘዴዎች ስልጠና ተሰጠ። ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ሐምሌ 20/2018 ዓ.ል| ሰፈር 12/1448 ዓ.ሂ بِسْمِ ٱللَّٰهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• አዲስ አበባ | ​የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የዑለማዎች ጉባኤ የትምህርትና ሥርዓተ ትምህርት ዘርፍ ከአሜሪካው የሚኒሶታ ኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲ እና ከዳማው ኢማም ቡኻሪ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ለኢስላማዊ ኮሌጅ መምህራን ሲሰጥ የቆየውን ሳይንሳዊ የምርምር አቅም ማሳደጊያ ስልጠና አጠናቀቀ። ​የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት የክቡር ዶክተር ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ በስልጠናው ማጠቃለያ ባደረጉት ንግግር ስልጠናውን የሰጡትን አካላት አመስግነው አክለውም ስልጠናው ኢስላማዊ ዩንቨርስቲና ኮሌጆች እየተሰጠ ያለውን ትምህርት ጥራት ለማረጋገጥ የጎላ ፋይዳ አለው ብለዋል። ​የጠቅላይ ምክር ቤቱ ዑለማዎች ጉባኤ የትምህርትና ሥርዓተ-ትምህርት ዘርፍ ኃላፊ ዶክተር አብዱላህ ኸድር በበኩላቸው በስልጠናው ላይ ከስምንት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተውጣጡ መምህራን እና የድህረ ምረቃ ተማሪዎች መሳተፋቸውን ገልጸዋል። ስልጠናው ቀደም ሲል የነበረውን ውጤታማ የዩኒቨርሲቲ መማር ማስተማር ሂደት የሚያስቀጥል፣ የምርምር ጥናት አዘጋጃጀት አቅምን የሚያጎለብትና የምርምርን ፋይዳ የሚያሳድግ እንደሆነም አስረድተዋል። ስልጠናው የኢስላማዊ ትምህርት ተቋማትን የመማር ማስተማር ሂደት ለማዘመን፣ የትምህርት ጥራት ለማሳደግ እና ዘመናዊ ጥናትና ምርምርን ለማበርከት ከፍተኛ ጥቅም እንዳለው ሰልጣኞች በሰጡት አስተያዬት ጠቁመዋል። ሰላጣኞቹ አያይዘውም የመምህራንን የምርምር ክህሎት ለማሳደግ ጠቅላይ ምክር ቤቱ ከአጋር አካላት ጋር በመቀናጀት የጀመረውን ስልጠና አጠናክሮ እንዲቀጥልም አደራ ብለዋል። ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት ይከታተሉን | Follow us፡ ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council ቴሌግራም | t.me/eiasc1 ትዊተር | https://x.com/eiasc1

የጠቅላይ ምክር ቤቱ የኡለማ ጉባዔ ምክትል ፕሬዝደንት በጅግጅጋ ከተማ የሥራ ጉብኝት አካሄዱ። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━ ሐምሌ 17/2018 ዓ.ል | ሰፈር 10/1448 ዓ.ሂ بِسْمِ
+4
የጠቅላይ ምክር ቤቱ የኡለማ ጉባዔ ምክትል ፕሬዝደንት በጅግጅጋ ከተማ የሥራ ጉብኝት አካሄዱ። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━ ሐምሌ 17/2018 ዓ.ል | ሰፈር 10/1448 ዓ.ሂ بِسْمِ ٱللَّٰهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ ━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━ ጅግ ጅጋ| የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የኡለማ ጉባዔ ዘርፍ ምክትል ፕሬዝደንት ሸይኽ ጁነይድ ሐምዛ ዩሱፍ በጅግጅጋ ከተማ የስራ ጉብኝት አደረጉ። ​ምክትል ፕሬዝደንቱ በጉብኝታቸው በሶማሌ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት እየተገነባ የሚገኘውን መስጂድ የግንባታ ሂደት አሁናዊ ደረጃ ከሰወራ ኃላፊዎች ጋር ሆነው ተመልክተዋል። ​ሸይኽ ጁነይድ በጉብኝታቸው ወቅት ባደረጉት ንግግር የክልሉ መጅሊስ እያከናወናቸው ያሉት የልማት እና የዳዕዋ ሥራዎች አበረታች ውጤት እያስመዘገቡ መሆናቸውን ገልጸው ለክልሉ መጅሊስ አድናቆት እንዳላቸው አመላክተዋል። ​የሶማሌ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዝደንት ሸይኽ አህመድ ሙሀመድ አሊ በበኩላቸው ፌዴራል መጅሊሱ እያደረገ ያለው ያልተቋረጠ ድጋፍና ክትትል የክልሎችን የመፈጸም አቅም እየገነባ መሆኑን ገልጸዋል። ሸይኽ ጁነይድ ሐምዛ በነገው ዕለትም በክልሉ እየተከናወኑ የሚገኙ ሌሎች የልማትና ስራዎችን በመጎብኘት ከክልሉ መጅሊስ አመራሮች ጋር ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል። ••••••••••••••••••••••••••••••••••• የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት ይከታተሉን | Follow us፡ ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council ቴሌግራም | t.me/eiasc1 ትዊተር | https://x.com/eiasc1

ለመጅሊስ አመራሮችና ለዱዓቶች የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት ተጀመረ። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━ ሐምሌ 14/2018 ዓ.ል | ሰፈር 7 /1448 ዓ.ሂ بِسْمِ ٱللَّٰهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ ━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━ ሻሸመኔ | የኢትዮጵያ እስልምና ጠቅላይ ምክር ቤት ዑለማእ ጉባዔ ከኦሮሚያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤትና ከቡኒያን ዓለም ዓቀፍ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር ለክልልና ለዞን መጅሊስ የሥራ ኃላፊዎችና ዱዓቶች የአቅም ግንባታ ስልጠና በሻሸመኔ መስጠት ጀምሯል። በስልጠናው ላይ ከኦሮሚያ፣ ከደቡብ ኢትዮጵያ፣ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ እና ከሲዳማ ክልል መጅሊሶች የተወጣጡ የሥራ ኃላፊዎችና ዱዓቶች እየተሳተፉ ይገኛሉ። የጠቅላይ ምክር ቤቱ የዑለማእ ጉባዔ ምክትል ጽህፈት ቤት ኃላፊ ዶክተር ሙሀሙድ ሁሴን በስልጠናው መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር በሻሸመኔ ከተማ በተጀመረው የአቅም ግንባታ ስልጠና በእስላማዊ እውቀት፣ በዳዕዋ፣ በሰላም ግንባታ፣ በማኅበራዊ ኃላፊነት እና በአመራር ክህሎት ላይ ትኩረት ማድረጉን ተናግረዋል። ሰልጣኞች ከስልጠናው የሚያገኙትን እውቀትና ክህሎት በመጠቀም የሕዝበ ሙስሊሙን የሰላም፣ የልማት፣ የአንድነት እና የአብሮነት ኢስላማዊ እሴቶችን በማጠናከር ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚጠበቅባቸውም ኃላፊው አክለው ገልጸዋል። ጠቅላይ ምክር ቤቱ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በመተባበር እየሰጠ የሚገኘው የአቅም ግንባታ ስልጠና በቀጣይ ሳምንትም እንደሚቀጥል ተመላክቷል። ••••••••••••••••••••••••••••••••••••• የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት ይከታተሉን | Follow us፡ ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council ቴሌግራም | t.me/eiasc1 ትዊተር | https://x.com/eiasc1

የኢትዮጵያ ዑለማዎች ጉባኤ ለኮሌጅ መምህራን የሰጠው የማስተማር ብቃት ማበልጸጊያ ስልጠና ተጠናቀቀ። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ ሐምሌ/13/2018 ዓ.ል| ሰፈር 6/1448 ዓ.ሂ بِسْمِ ٱللَّٰهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ ━━━━━━━━━━━━━━━━ አዲስ አበባ | የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የዑለማዎች ጉባኤ የትምህርትና ሥርዓተ ትምህርት ዘርፍ ከሱና ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ለኢስላማዊ ኮሌጅ መምህራን ሲሰጥ የቆየውን ሥልጠና አጠናቀቀ። ሥልጠናው ውጤታማ የዩኒቨርሲቲ የመማር ማስተማር ሂደት" በሚል መሪ ሃሳብ የተዘጋጀ ሲሆን በስልጠናው መክፈቻ ላይ የተገኙት የዑለማ ጉባኤ ጽፈት ቤት ኃላፊ ሸይኽ ዓሊ መሐመድ ትምህርትን በስልጠና በመደገፍ ከዘመኑ ጋር አብሮ መራመድና የትምህርት ጥራትን ከፍ ማድረግ ይገባል ብለዋል። ኃላፊው አክለውም ስልጠናው በአፍሪካና በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ልምድ ያላቸው የአረብኛ ቋንቋና የስርዓተ ትምህርት ሊቃውንት የተሳተፉበት የተሳተፉበት መሆኑን በመጥቀስ እንዲህ ዓይነቱ የስልጠና መድረክ ጠቀሜታው ከፍተኛ እንደሆነ አብራርተዋል። የጠቅላይ ምከር ቤቱ ዑለማእ ጉባኤ የትምህርትና ሥርዓተ-ትምህርት ዘርፍ ኃላፊ ዶክተር አብዱላህ ኸድር በሰጡት ማብራሪያ ስልጠናው መምህራን የማስተማር ማስተማር ሂደቱን ይበልጥ ውጤታማና ጥራቱን የጠበቀ ለማድረግ ያግዛቸዋል ብለዋል። በመጨረሻም የጠቅላይ ምክር ቤቱ ሥራ አስፈጻሚና የመስጂዶች ጉዳይ ዘርፍ ተጠሪ ሸይኽ እድሪስ አሊ ለሠልጣኞች ባስተላለፉት መልዕክት ሙያን በሥልጠና ማበልጸግ ከዘመኑ ጋር መራመድ መሆኑን ነው ያሉ ሲሆን ሰልጣኞች ባገኙት ዕውቀት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡም አደራ ብለዋል። ስልጠናው በአፍሪካ ዩኒቨርሲቲ የዐረብኛ ቋንቋ ተመራማሪና የሥርዓተ-ትምህርት ባለሙያ ፕሮፌሰር አል-ሲዲቅ አዳም በረካት የተሰጠ ሲሆን ሸይኽ እድሪስ አሊ እና የሙስሊም ወጣቶች ዓለም አቀፍ ጉባኤ (WAMY) ተወካይ ለሠልጣኞች የሜዳሊያና የምስክር ወረቀት አበርክተዋል። •••••••••••••••••••••••••••••••••• የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት ይከታተሉን | Follow us፡ ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council ቴሌግራም | t.me/eiasc1 ትዊተር | https://x.com/eiasc1

ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የተሰጠ የሀዘን መግለጫ ​ ​«ሁላችንም የአላህ ነን፤ ወደ እርሱም ተመላሾች ነን።» (ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን) ​በእኔ፣ በኢትዮጵያ እስልምና
ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የተሰጠ የሀዘን መግለጫ ​ ​«ሁላችንም የአላህ ነን፤ ወደ እርሱም ተመላሾች ነን።» (ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን) ​በእኔ፣ በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት እና በመላው የኢትዮጵያ ህዝበ ሙስሊም ስም፣ ለተከበሩት የሀገረ ኳታር አሚር ሸይኽ ታሚም ቢን ሀማድ አል ታኒ፣ ለኳታር መንግሥት እና ለኳታር ሕዝብ፣ በክቡር አሚር ሸይኽ ሀማድ ቢን ኸሊፋ አል ታኒ ህልፈተ ሕይወት የተሰማኝን ልባዊ እና ጥልቅ ሐዘን እገልጻለሁ። ​ክቡር አሚር ሸይኽ ሀማድ ቢን ኸሊፋ አል ታኒ ለኳታር ብቻ ሳይሆን ለሀገራት ሁሉ ሰላም በተለይም በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ የሚነሱ ግጭቶችን ለመፍታት ታላቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ አርዓያ መሪ ነበሩ። ​የኢትዮጵያ ሙስሊሞችና መላው ሕዝብ ለሟቹ አሚር ታላቅ ክብርና መልካም ትውስታ ያለው ሲሆን ክቡር አሚር የኢትዮጵያ እና የኳታር ታሪካዊ ግንኙነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ከማድረግ አንጻር ከፍተኛ ሚና ነበራቸው። በሁለቱ ሀገራት ህዝቦች መካከል ያለው ሃይማኖታዊና ሰብዓዊ ትስስር ሁለንተናዊ በሆነ መንገድ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም ደማቅ አሻራ አሳርፈዋል። ​ለክቡር አሚር ሸይኽ ሀማድ ቢን ኸሊፋ አል ታኒ ምሕረቱንና እዝነቱን እንዲለግሳቸውና ማረፊያቸውን በጀነት እንዲያደርግላቸው አላህን እንማጸነዋለን። ለተከበረው የሀገረ ኳታር መንግስትና ህዝብ እንዲሁም ለወዳጆቻቸው ሁሉ አላህ መጽናናትንና ሰላምን እንዲሰጥ ዱዓችን ነው። ​ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት እና የኡለማ ጉባኤ ፕሬዝደንት

ለኢማሞችና ለዑስታዞች የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━ ሐምሌ 03/2018 ዓ.ል | ሙሐረም 24/1448 ዓ.ሂ بِسْمِ ٱللَّٰهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ ━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━ አሶሳ | የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ዑለማእ ጉባዔ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤትና ከቡኒያን ዓለም ዓቀፍ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ ዑለማዎችና ዑስታዞች በአሶሳ ከተማ የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ። በአቅም ግንባታ ስልጠናው ላይ 50 ኢማሞችና 50 ዑስታዞች የተሳተፉ ሲሆን ስልጠናው በእስላማዊ እውቀት፣ በዳዕዋ፣ በሰላም ግንባታ፣ በማህበራዊ ኃላፊነት እና በአመራር ክህሎት ላይ ትኩረት ያደረገ ነው። በስልጠናው ማጠናቀቂያ ላይ ንግግር ያደረጉት የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሸይኽ ኢብራሂም ሙሐመድ ስራጅ ሰልጣኞች ከስልጠናው ያገኙትን እውቀትና ክህሎት ተግባራዊ በማድረግ ማህበረሰቡን በብቃት እንዲያገለግሉ አደራ ብለዋል። ኢማሞችና ዑስታዞች የሕዝበ ሙስሊሙን ሰላም፣ አንድነት እና ኢስላማዊ የስነ ምግባር እሴቶችን በማጠናከር ውጤታማ ሥራ እንዲሰሩም ጠይቀዋል። ከሚመለከታቸው ባለ ድርሻ አካላት ጋር በመተባበር በቀጣይም የኢማሞችና የዑስታዞች አቅም ለማጠናከር መጅሊሱ እንደሚሰራም ፕሬዝደንቱ ልጸዋል። በምርቃት መርሀ ግብሩ ላይ የክልሉ መጅሊስ ምክትል ፕሬዚዳንት ሸይኽ ዑመር ሐጅ አኑር፣ ሸይኽ ሷሊህ ሙሐመድ እና ሌሎች የመጅሊሱ አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል ••••••••••••••••••••••••••••••••••••• የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት ይከታተሉን | Follow us፡ ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council ቴሌግራም | t.me/eiasc1 ትዊተር | https://x.com/eiasc1

የጠቅላይ ምክር ቤት የኦዲትና ኢንስፔክሽን ኮሚሽን ለኮሚሽነሮች እና ለባለሙያዎች ሲሰጥ የነበረውን ስልጠና አጠናቀቀ። •••••••••••••••••••••••••••••••• ሰኔ 30 /2018 ዓ.ል| ሙሀረብ 22/1448 ዓ.ሒ سْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ •••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• አዳማ | የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የኦዲትና ኢንስፔክሽን ኮሚሽን በአዳማ ከተማ ለክልል እና ለከተማ አስተዳደር መጅሊስ የኦዲትና ኢንስፔክሽን ኮሚሽነሮች እና ባለሙያዎች ሲሰጥ የነበረውን ስልጠና አጠናቀቀ። በሥልጠናው በተግባር ልምምድ ታግዞ ሲሰጥ የቆዬ ሲሆን ሰላጣኞቹ በስልጠናው ባገኙት ክህሎት መሰረት የኦዲት እና ኢንስፔክሽን መመሪያ እንዲሁም ዓመታዊ ዕቅድ አዘጋጅተው ለጠቅላይ ምክር ቤቱ የኦዲትና ኢንስፔክሽን በማቅረብ አስገምግመዋል። ስልጠናው ባለ 7 ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት የተጠናቀቀ ሲሆን በማንኛውም ደረጃ የሚሰበሰብ ገቢና ወጪ የፋይናንስ ሕግና እና ሥርዓትን ተከትሎ እንዲከናወን አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግ በስልጠናው ማሳረጊያ ቃል ተገብቷል። የሕገ መጅሊሱ ማስፈጸሚያ ደንቦችና መመሪያዎች ሳይሸራረፉ ሥራ ላይ እንዲውሉ ተቋማዊ ኃላፊነትን መወጣት እንደሚገባም በአቋም መግለጫው ላይበተካቷል። የጠቅላይ ምከወር ቤቱ የኦዲትና ኢንስፔክሽን ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ሸይኽ ኢልያስ አወል በስልጠነው ማጠቃለያ ላይ እንደገለጹት የስልጠናው ዓላማ በመጅሊስ መዋቅሮች ውስጥ ግልጽነትን እና ተጠያቂነት ማስፈን ነው። ሰልጣኞች ከስልጠናው ያገኙትን እውቀትና ክህሎት በአግባቡ ተግባራዊ በማድረግ ለተቋሙ ስኬት አዎንታዊ ሚና እንዲጫወቱም ሸይኽ ኤሊያስ አወል አደራ ብለዋል። ••••••••••••••••••••••••• የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤትን ሕዝብ ግንኙነትና ሚዲያን ይከታተሉ | Follow us፡ ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council ቴሌግራም | t.me/eiasc1 ትዊተር | https://x.com/eiasc1

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ዑለማእ ጉባዔ የሞሮኮ ንጉስ ሙሀመድ ስድስተኛ የአፍሪካ ዑለማ ፋውንዴሽን ጋር በትምህርትና ልማት ዘርፍ በጋራ ለመስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ። ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ሰኔ 30/2018 ዓ.ል| ሙሀረም 22 /1447 ዓ.ሒ بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• አዲስ አበባ | የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የዑለማእ ጉባዔ ከሞሮኮ ንጉስ ሙሀመድ ስድስተኛ የአፍሪካ ዑለማእ ፋውንዴሽን ጋር በትምህርትና ልማት ዘርፍ በጋራ ለመስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ። በጠቅላይ ምክር ቤቱ የተደረገውን የፊርማ ሥነ ሥርዓት የዑለማእ ጉባዔ ዘርፍ ምክትል ፕሬዝዳንት ሸይኽ ጁነይድ ሐምዛ ዩሱፍ እና የሞሮኮ ንጉስ ሙሀመድ ስድስተኛ የዒማሞችና ዱዓቶች ማሰልጠኛ ኢኒስቲትዩት ዳይሬክተር ዶክተር አብዱሰላም ላዛር ተፈራርመዋል። በፊርማ ስነ-ሥርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት ምክትል ፕሬዝደንት ሸይኽ ጁነይድ ሀምዛ የሞሮኮ ንጉስ ሙሀመድ ስድስተኛ የአፍሪካ ዑለማ ፋውንዴሽን የዒማሞችን አቅም ለማጎልበት የመግቢያ ፈተና ያለፉ ሃያ ስምንት ዒማሞችን ሙሉ ወጪያቸውን ሸፍኖ ለማስተማር ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል። ፋውንዴሽኑ በቀጣይም የምዘና ሌሎች ዒማሞችን በማወዳደር የትምህርት እድሉ ተጠቃሚ እንዲያደርግ የዑለማእ ጉባዔው በትኩረት እንደሚሰራ ምክትል ፕሬዝደንቱ አክለዋል የሞሮኮ ንጉስ ሙሀመድ ስድስተኛ የአፍሪካ ዑለማ ፋውንዴሽን እና ጠቅላይ ምክር ቤቱ የጋራ በሆኑ ሃይማኖታዊ እና ልማታዊ ስራዎች ላይ በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን ዶክተር አብዱሰላም ተናግረዋል። ••••••••••••••••••••••••••••••••••• የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤትን ሕዝብ ግንኙነትና ሚዲያ ዘርፍ ይከታተሉ | Follow us፡ ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council ቴሌግራም | t.me/eiasc1 ትዊተር | https://x.com/eiasc1