የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
Open in Telegram
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
Show more2 765
Subscribers
+424 hours
+127 days
+5330 days
Posts Archive
+9
የጻድቁ አባታችን አቡነ አረጋዊ የተሰወሩበት ዓመታዊ ክብረ በዓል በደብራችን በታላቅ ድምቀት እየተከበረ ይገኛል ከበዓሉ በረከት ያሳትፈን።
ደብሩሰ ለአባ አረጋዊ ትመስል ደብረ ሲና ትመስል ደብረ ሲና
ዘኀደረ በላዕሌሃ እግዚአብሔር ሐጹረ የዐውዳ ወጽጌ ረዳ በትእምርተ መስቀል{፪×}
የአባ አረጋዊ ደብር እግዚአብሔር በላዩ ያደረ ደብረ ሲናን ትመስላለች እነሆ በጽጌ ረዳ ትእምርተ መስቀል ተከብባለች፡፡
ጻድቁ አቡነ አረጋዊ
ጥቅምት ዐሥራ አራት በዚህች ቀን ታላቁና የከበረው አባታችን አቡነ አረጋዊ (ዘሚካኤል) የተሰወሩበት ነው።
እኚህ አባት ከ9 ቅዱሳን አባቶች አንዱ ሲሆኑ
አባታቸው ይስሐቅ የሮም ንጉስ ነበሩ፡፡ እናታቸው ንግስት እድና ይባሉ ነበር፡፡ የመጀመሪያ ስማቸው ዘሚካኤል ነው፡፡ ጥበብ መንፈሳዊ ሲማሩ አድገው ወደ እስክንድርያ ገዳም ገቡ፡፡ አበምኔቱ አባ ጳኩሚስ በፈቃደ እግዚአብሔር የመጡ መሆናቸውን አውቀው መዓረገ ምንኩስና ሰጥተዋቸዋል፡፡
የንጉሳዊ የቅንጦት ኑሮ ንቀው ትተው ገዳም ገብተው በምንኩስና ተወስነዋል፡፡ አባታችን በተጋድሏቸውም ከአባ እንጦንስ፣ ከአባ ጳውሊ እና ከአባ መቃርስ ቀጥሎ በአራተኛ ማዕረግ አበ መነኮሳት ሆነው ተመርጠዋል።
በገዳመ ዳውናስ 7 ዓመት ከቆዩ በኋላ ወደ ሮም ተመልሰው ሲያስተምሩ የሀገራችን ኢትዮጵያን ዜና ሰምተው ለመምጣት በ480 ዓ.ም ከአባ ፍሬምናጦስ በኋላ መንገድ ጀመሩ፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም በክንፉ ተሸክሞ አክሱም አድርሷቸዋል፡፡
ተመልሰውም ሄደው ስለ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ መስክረዋል፡፡ ሐዋርያ ሳይላክላት በሃይማኖት በምግባር ጸንታ ትኖራለች ብለው ለሰባቱ ዘመዶቻቸው አበው መነኮሳት ነገሯቸው፡፡ ስምንቱም ጓዛቸውን ጠቅልለው በሮም ነግሶ የነበሩ ይስሐቅን (አባ ገሪማን) ጨምረው ንጉስ አልአሜዳ በነገሰ በአምስተኛ ዓመት ማለትም በ480 ዓ.ም ወደ ኢትዮጵያ ዘጠኝ ሆነው መጥተዋል፡፡
አባ አረጋዊ እናታቸው ቅድስት እድናን ደቀ መዝሙራቸውን ማትያስን አስከትለው እግረ መንገዳቸውን እያስተማሩና ድውያንን እየፈወሱ ደብረ ዳሞ ደርሰዋል፡፡
ከእግረ ደብር ሆነው አሁን ይህን ተራራ በምን ልወጣው እችላለሁ እያሉ ሲያወጡ ሲያወርዱ በንግግሩ ሐሰት የሌለበት አምላካችን በነቢዩ ዳዊት ላይ አድሮ በመዝሙር 90/91፥11-16 ላይ “በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዛቸዋልና፤ እግርህም በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸው ያነሡሃል። በተኵላና በእባብ ላይ ትጫማለህ፤ አንበሳውንና ዘንዶውን ትረግጣለህ። እንዳለው የታዘዘ ዘንዶ መጥቶ ስድሳ ክንድ በሚያህል ጅራቱ ጠምጥሞ ቅዱስ ሚካኤል ሰይፈ እሳት ይዞ እየጠበቃቸው ከተራራው አናት አድርሷቸዋል፡፡
ወዲያው ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ ብለው አመስግነዋል፡፡ ቦታውም ደብረ ሃሌ ሉያ ተብሏል፡፡ በዚያ ዕለት ግማሽ ህብስት በልተው ጠገቡ፤ ከዚያ በኋላ ግን ምድራዊ ሕብስት አልተመገቡም፡፡ በሰንበተ ክርስታያን ከቅዳሴ በኋላ ሕብስተ ሰማያዊ እያመጡላቸው ይመገቡ ነበር እንጂ፡፡ ኋላም ዜና ጽድቃቸውን ሰምተው ከስድስት ሺህ ያላነሱ ደቀ መዛሙርት ተሰብስበውላቸዋል፡፡
ዘጠና ዘጠኝ ዓመት ሲሞላቸው ጌታ በመንፈቀ ሌሊት ተገልጾ ምድራዊ መንግስትህን ትተህ ስላገለገልከኝ ህልፈት ሽረት የሌለባት ሰማያዊ መንግስቴን አወርሰሃለሁ ብሎ ቃልኪዳን ሰጣቸው፡፡ በስምህ የተማጸነውን እስከ አስራ አምስት ትውልድ ድረስ እምርልሃለሁ አንተም ከሞት ገጽ ትሰወራለህ ብሎ ተስፋቸውን ነገራቸው፡፡ እሳቸው መነኮሳቱን ሰብስበው ከእንግዲህ በሥጋ አታዩኝም ብለው ነግረዋቸው አበምኔት ሾመውላቸው በዚህች ዕለት በዚያው በደብረ ዳሞ ተራራ በስተምስራቅ አቅጣጫ ተሰውረዋል፡፡
የአባታችን የጻድቁ አቡነ አረጋዊ በረከታቸው በሁላችንም ላይ ይደር። አሜን
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
+5
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት ጉባኤው፦
1.ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ
2.ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ
3.ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ
4.ብፁዕ አቡነ ማርቆስ (ዘሲያትል)
5.ብፁዕ አቡነ ፊሊጶስ
6.ብፁዕ አቡነ ኤጲፋንዮስ
7.ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕን በአጀንዳ አርቃቂነት ሰይሟል።
ወገኖቻችንና ልጆቻችን የምናስተላፈው ወቅታዊ መልእክታችን ይህ ነው፡፡ በመጨረሻም በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሁለንተናዊ አገልግሎትና የስራ አፈጻጸም ላይ ለመምከርና ለመወሰን ኃላፊነት ያለው ቅዱስ ሲኖዶስ በዛሬው ዕለት መደበኛና ዓመታዊ ጉባኤውን የጀመረ መሆኑን ለሕዝበ ክርስቲያኑ እናበስራለን፡፡
እግዚአብሔር ጉባኤያችንን ይባርክ!
እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን::
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም
ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ጥቅምት ፲፪ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
©የቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባሕር ዳርና የሰሜን ጐጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፤
ዓመቱን ጠብቆ ስለ አጠቃላይ ተልእኮአችን ለመወያየት በዚህ ጉባኤ የሰበሰበን አምላካችን ስሙ የተመሰገነ ይሁን፤
“ወይእዜኒ ግብኡ ኀበ ኖላዊሃ ወዓቃቢሃ ለነፍስክሙ፤ አሁንም ወደ እረኛችሁና ወደ ነፍሳችሁ ጠባቂ ተመለሱ” (1 ጴጥ 2÷!5)
ሁሉን የሚችል አምላካችን እግዚአብሔር በፍቅሩና በፍቅሩ መነሻነት ብቻ ፍጥረታትን በሙሉ እንደፈጠረ ቅዱስ መጽሐፍ ያስተምረናል፤ ከፈጠረም በኋላ የክብሩ ተሳታፊ እንዲሆኑ ወዶ ክብሩን አድሎአቸዋል፡፡ እግዚአብሔር ለፍጡራኑ ካደላቸው ነገሮች አንዱ በየዓይነታቸው ጠባቂና መሪ እያደረገ በፍጡራን ላይ ፍጡራንን መሾሙ ነው፤ ይህ ስጦታ በሰማይም ሆነ በምድር ላሉ ፍጥረታት የተሰጠ የሱታፌ መለኮት ስጦታ ነው፡፡
ይህም በመሆኑ ሁሉም ፍጡራን አራዊትም ሆኑ እንስሳት ይብዛም ይነስ ጠባቂና መሪ እንዳላቸው እናስተውላለን፤ በተለይም የፍጥረታት ቁንጮ የሆኑ መላእክትና ሰዎች መሪና ሹም እንዳሏቸው የማንክደው ሓቅ ነው፡፡ ቅዱስ መጽሓፍም ይህንን ደጋግሞ ያስረዳል፤ የእነዚህ ሁሉ ላዕላዊ ጠባቂና መሪ ደግሞ እግዚአብሔር ነው፤ እግዚአብሔር በፍጡራን ላይ ፍጡራንን ጠባቂዎች አድርጎ ሲሾም ፍጡራንን የክብሩ ተሳታፊ ለማድረግ እንጂ የእሱ ጥበቃ አንሶ ወይም ድጋፍ ሽቶ አይደለም፡፡ ስለሆነም ፍጹምና ላዕላዊ የሆነ ጥበቃው ሁሉንም ያካለለ ነውና ከእሱ ቊጥጥርና ጥበቃ ውጭ አንድም ነገር እንደሌለ የምንስተው አይደለም ፡፡
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት
የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
በአምሳለ እግዚአብሔር በተፈጠረውና በክብር መልዕልተ ፍጡራን በሆነው ሰው ላይ በዚህ ዓለም የተሾሙ ሁለት አካላት አሉ፤ እነሱም የመንፈስና የዓለም መሪዎች ናቸው፡፡ በተለይም የመንፈስ መሪዎችና ጠባቂዎች የተባሉት በመንፈስ ቅዱስ ተሹመን በዚህ ክርስቶሳዊ ጉባኤ የተሰበሰብነው እኛ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ነን፡፡
ይህ ጉባኤ በሀገር ውስጥና በውጭ ለሚገኙና በሚሊዮኖች ለሚቆጠሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን መሪና ጠባቂ ነው፤ ከዚያም ባሻገር እንደ ቃሉ እስከ ዓለም ዳርቻ ድረስ ቃሉን በመስበክ ፍጥረተ ሰብእን በሙሉ የመጥራት ተልእኮ ለእኛ የተሰጠ የቤት ስራ ነው፡፡ ከዚህ አኳያ የተሰጠን ኃላፊነት እጅግ በጣም ታላቅ እንደመሆኑ የሚጠበቅብን ውጤትም በዚያው ልክ ትልቅ ነው፤ ብዙ ከተሰጠው ብዙ ይፈለግበታል ያለው የጌታችን አስተምህሮም ይህንን ያስታውሰናል፡፡
ሁላችን እንደምንገነዘበው አሁን የምንገኝበት ዘመን የጸላኤ ሠናያት መንፈስ በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ ከምንም ጊዜ በበለጠ ጦሩን ሰብቆ የተነሣበት ጊዜ ነው፤ አሁን ያለው ዓለም በሀገራችንም ሆነ በሌላው ክፍለ ዓለም ላሉ ኦርቶዶክሳውያን ከባድ ፈተና ደቅኖብናል፡፡ ክፉው መንፈስ የሰውን አእምሮ በማዛባት ምእመናንን በቅዱስ መጽሐፍና በሕገ ተፈጥሮ ከተመደበላቸው የጋብቻ ሕግ በማስወጣት እንስሳት እንኳ የማይፈጽሙት ነውረ ኃጢአት እንዲፈጽሙ በመገፋፋት ላይ ይገኛል፡፡ በአማንያን ልጆቻችን ላይም በረቀቀ ስልት ግድያ፣ እገታ፣ አፈና፣ የመብት ተጽዕኖ እና አድልዎ በማድረግ እንደዚሁም በአስመሳይ ስብከትና አምልኮ ጣዖትን በማለማመድ ሕዝቡ ሳይገባውና ሳይጠነቀቅ ከእግዚአብሔር መንግሥት እንዲወጣ እያደረገ ነው፡፡
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት
የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
ክፉው መንፈስ በተራቀቀና በተራዘመ ስልት ሊውጠን በተነሣ ልክ እኛም ከእሱ እጥፍ በሆነ መለኮታዊ ኃይል ልንመክተው ካልቻልን በፈጣሪም ሆነ በትውልድ እንደዚሁም በታሪክ ፊት በኃላፊነት መጠየቃችን አይቀርም፡፡ መከላከል የምንችለውም ችግሩን በውል ከመረዳት አንሥቶ ሕዝቡን በደምብ በማስተማርና በመጠበቅ እንደዚሁም ለመሪነታችን ዕንቅፋት ከሚሆኑን ዓለማዊ ነገሮች ራሳችንን በማራቅ ነው፡፡ ሕዝቡም በዚህ ዙሪያ ሊያደምጠንና ሊከተለን የሚችለው መስለን ሳይሆን ሆነን ስንገኝለት ነው፡፡ ሕዝቡ ሊከተለን የሚችለው እሱን በብቃት ለመጠበቅ ዓቅሙም ተነሣሽነቱም ቁርጠኝነቱም እንዳለን ሲመለከት፣ እንደዚሁም ከዕለት ተዕለት ተግባራችንና አኗኗራችን የሚያየው ተጨባጭ እውነታ ኅሊናውን ሲረታ እንደሆነ አንርሳ፡፡
የምናስተምረው ሌላ የምንሰራው ሌላ ከሆነ ግን ከሕዝቡ አእምሮ መውጣታችን እንደማይቀር መገንዘብ አለብን፤ በመሆኑም በሰብእናችን፣ በአስተዳደራችን፣ በአመራራችንና በጥበቃችን ሁሉ እንደቃሉና እንደቃሉ ብቻ ለመፈጸም መትጋትና በቁርጥ መነሣት ጊዜው አሁን ነው እንላለን፡፡ ይህ ሲሆን በምእመናንና በእኛ መካከል ያለው ግንኙነት አስተማማኝና እንከን የለሽ ይሆናል፤ ይህ ከሆነ እውነትም የመሪነት፣ የእረኝነትና የመልካም ተምሳሌነት ኃላፊነታችንን በትክክል ተወጥተናል ማለት እንችላለን፡፡
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት
የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
የሰው ልጆች በዚህ ዓለም ሲኖሩ የተሟላ ሰላምና ጣዕመ ሕይወት ሊኖራቸው የሚችለው በመንፈሳዊ ኑሮአቸው የተሻለ ነገር ስላገኙ ብቻ አይደለም፡፡ ሰዎች ከሥጋዊ ክዋኔም ጭምር የተፈጠሩ እንጂ እንደመላእክት ሥጋ የሌላቸው መንፈስ ስላይደሉ ለኑሮአቸውና ለሥጋዊ ክዋኔአቸው የሚሆን ነገር ያስፈልጋቸዋል፡፡ በዚህም ዓለማዊው አስተዳደር የተመቻቸ መደላድል ሊፈጥርላቸው ግድ ነው፤ ዓለማዊው አስተዳደርም የመለኮትን ተልእኮ ለመፈጸም የተሾመ ሹመኛ እንደመሆኑ የእግዚአብሔርን ሕዝብ በትክልል መምራት ይጠበቅበታል፡፡ ምንም ቢሆን የተቀበለው ኃላፊነት የእግዚአብሔር ነውና በሚሰራው ሁሉ በሿሚው አምላክ ከመጠየቅ አያመልጥም፡፡
እኛም በዚህ ዓለም የእግዚአብሔር ወኪሎች ስለሆንን ቢሰሙንም ባይሰሙንም ዓለማውያን ሹማምንትን የማስተማርና የመምከር ኃላፊነት አለብን፡፡ ይህ የሁለታችን ኃላፊነት እንደ እግዚብሔር ፈቃድ ስንፈጽም የሕዝብ ሰላምና በረከት፣ ፍቅና አንድነት፣ ዕድገትና ልማት በአስተማማኝ ሁኔታ ይረጋገጣል፡፡ ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ በሀገራችንም ሆነ በአካባቢያችን እየሆነ ያለው ይህ አይደለም፤ አለመግባባት በዝቶአል፣ ማኵረፍና መቀያየም ሰፍቶአል፤ ነገሩ ሁሉ ግራ የሚያጋባና የተመሰቃቀለ ሆኖ ይታያል፡፡ ችግሩ ከሕዝብ አልፎ የአምልኮ ስፍራዎችንና የአምልኮው ፈጻሚዎችን ዒላማ ያደረገ እግዚአብሔርን መዳፈር እየተለመደ መጥቶአል፤ ይህ ለአንድ ሀገር ወይም ሕዝብ የውድቀት ምክንያት ከሚሆን በቀር ከቶውኑም የዕድገት ምልክት ሊሆን አይችልም፡፡
ከሁሉም በላይ የሚያሳዝነው ደግሞ ይህ ክፉ ድርጊት እየተፈጸመ ያለው በእኛው ልጆች በኢትዮጵያውያን መሆኑ ነው፤ ስለሆነም በከተማም፣ በጫካም፣ በገጠርም በየትኛውም ስፍራ የምትገኙ ልጆቻችን ምንም ይሁን ምን ሀገርንና ሕዝብን ከመጉዳት ተቆጠቡ፡፡ በተለይም ከቤተ ክርስቲያንና ከሀገር እንደዚሁም ሕዝቡን ከሚያገለግሉ ካህናትና ሲቪል ሰራተኞች እባካችሁ እጃችሁን አንሡ፤ ቤተ ክርስቲያን እኮ የእናንተና የሕዝቡ ሁሉ እናት ናት፤ በእናታችሁ ላይ መጨከንን እንዴት ተለማመዳችሁት? አሁንም ንስሐ ግቡ ያለፈው ይበቃል፡፡ ልብ በሉ ከእግዚአብሔር ጋር መጣላት አይበጅም፤ ሰውን መጉዳትና እግዚአብሔርን መዳፈር አቁሙ፤ የእግዚአብሔር ገንዘብ የሆነውን ሥርዓተ አምልኮም ያለቦታው አታውሉ፤ ጥያቄአችሁን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ዕድል ስጡ፡፡ በእግዚአብሔር ስም ለመላው ኢትዮጵያውያን
+5
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤው በዛሬው ዕለት ስብሰባውን ጀምሯል።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በነገው ዕለት ይጀመራል !
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የጥቅምት 2017 ዓ.ም ምልዓተ ጉባኤ በነገው ዕለት በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ይጀመራል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በዓመት ሁለት ጊዜ ጥቅምት 12 እና በዓለ ትንሣኤ በዋለ በ25ተኛው ቀን ምልዓተ ጉባኤውን የሚያከናውን መሆኑ ይታወቃል።
ምልዓተ ጉባኤው በዛሬው ዕለት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በሚደረገው የጸሎት መርሐግብር የሚከፈት ሲሆን ከነገ ጀምሮ ቅዱስ ሲኖዶስ በልዩ ልዩ ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያንና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ እንደሚወያይ ይጠበቃል። በዛሬው ዕለት የመክፈቻ የጸሎት መርሐ ግብር በቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ተከናውኗል።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የጥናት መጽሔት ዝግጅት የማስጀመሪያ መርሐ ግብር አካሔደ
____
(ቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ/ጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓ.ም)
የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የጥናት መጽሔት ዝግጅት የማስጀመሪያ መርሐ ግብር ዛሬ ጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓ.ም አካሔደ። መርሐ ግብሩን ያዘጋጀው የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ጥናትና ምርምር ክፍል ሲሆን የክፍሉ ሓላፊ መምህር ግርማ ባቱ ይህ መርሐ ግብር የጥናት መጽሔቱ የማስጀመሪያ መርሐ ግብር መሆኑንና የመጽሔቱ ስያሜ "መጽሔተ ተዋሕዶ- Journal of Tewahedo) መባሉን እና ለጊዜው በግእዝ፣ በአማርኛና በእንግሊዝኛ ቋንቋ እንደሚታተም ገልጸዋል።
መምህር ግርማ ባቱ አክለውም ይህ የጥናት መጽሔት ክፍል በዩኒቨርሲቲው ፕሬዚደንት ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ መልካም ፈቃድና አሳሳቢነት የተጀመረ ሲሆን በብፁዕነታቸው የሚመራ የአማካሪ ቦርድ እና በፕ/ር አባ ኃይለ ገብርኤል ግርማ የሚመራ ኤዲቶሪያል ቦርድ መቋቋሙን አሳውቀዋል።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት እና የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ ዩኒቨርሲቲያችንን የሚመጥኑ የምርምር ሥራዎችን በየመስካቸው የማስጀመር መርሐ ግብሩ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዚዳንቱ ፕ/ር አባ ኃይለ ገብርኤል ግርማ ይህ የጥናን መጽሔት ጥናት ብቻ ሳይሆን ችግር ፈቺ እንዲሆንም እንሠራለን ብለዋል።
በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ የምሥራቅ አፍሪካ አሁጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኃን የበላይ ሓላፊ እና ብፁዕ አቡነ ዲዮናስዮስ የምሥራቅ ጎጃምና የጀርመንና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ በተለያዩ ተቋማት ብዙ መልካም ፕሮግራሞች ተጀምረው ወዲያው ይጠፋሉ ይህም እንዲያ እንዳይሆንና እንዲያድግ እናሳስባለን ብለዋል።
በዚህ መርሐ ግብር ላይ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዚዳንቶች፣ መምህራንና ሠራተኛች እና ጥሪ የተደረገላተው እንግዶች ተገኝተዋል።
©የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ሕዝብ ግንኙነት
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ቀን:- 10/2/2017 ዓም
የጥቅምት አብነ አረጋዊ ዘማሪያን ስለማሳወቅ፤
በቅድሚያ መንፈሳዊ ሰላምታችን እያቀረብን ከዚህ በታች ስማችሁ የተዘረዘረውን አባላት የ2017 ዓ/ም የጥቅምት አብነ አረጋዊ አገልግሎት ላይ ዘማሪያን መሆናችሁን በአክብሮት ማሳወቅ እንወዳለን!!!
1 መምህር ተስፋዬ ተሾመ
2 አቶ ካሳሁን እሸቱ
3 ወ/ሮ ቤተልሔም ገነነው
4 መ/ር ወንደሰን መኮንን
5 ኢ/ር ዳዊት አበበ
6 ዮሴፍ አምሐ
7 አቶ እንግዳወርቅ አረፋይኔ
8 አቶ አፈወርቅ በላቸው
9 መ/ር ስለሺ ይርጋ
10 ወ/ሮ ሰላማዊት ይልማ
11 አቶ አሸናፊ ኀ/ጊዮርጊስ
12 አበራ መላኩ
13 አቶ ሙሉጌታ ሰማን
14 ምእራፍ እንዳሉ
15 ጌቱ ጉዲሳ
16 ሰላማዊት በላይ
17 ቤተልሔም ታደለ
18 ቤተልሔም ይልፋሽዋ
19 ሰለሞን ክብረት
20 ከተማ ደገፉ
21 እንቁ ታደሰ
22 አቶ ኢሳያስ ባደግ
23 ሮቤል አሰፋ
24 ዳንኤል ታደሰ
25 አ/ቶ ዳንኤል ጌታቸው
26 ዮሴፍ ከበደ
27 ሚኬኤሌ ዘብሬ
28 ወ/ሮ ትግስት አማረ
29 ዲ/ን ዘላለም ታከለ
30 አ/ቶ ወርቅነህ ባህሩ
31 ሜሮን ብርሃኑ
32 ናትናኤል ቴዎድሮስ
33 ዲ/ን ቡሩክ ይብራህ
34 ይርጋለም አሸናፊ
35 አበባ አሸናፊ
36 ሚኬኤሌ ፍቅረማርያም
37 ብርሐኑ ንጉሴ
39 አየለች ደጉ
40 ለተእግዚ አረፋይኔ
41 በቀለች ማሞ
42 ካሰች ግደይ
43 አብርሐም ተመስገን
44 የዚች አለም ሲሳይ
45 አሰገደች ታደሰ
46 ቢኒያም ሰይፉ
47 ሰላማዊት ሸዋንግዛው
48 ሔለን ማሙሽ
49 ኤደን ጥበቡ
50 ምትኩ አሰፋ
51 ሳራ ፍቅሩ
52 ያዕቆብ ተስፋዬ
53 መ/ር ፍቃዱ ኪሮስ
54 ተስፋዬ በዙ
55 አለም ንጉሴ
56 ማቲዎስ ወ/ገብርኤል
57 ኀ/ሚካኤል ገ/አሳይ
58 ነአምን ኤልያስ
59 ሰላም ወርቁ
60 የአብስራ አክሊሉ
61 ሰላም ታደለ
62 መሠረት አሰፋ
63 ኤልያስ አስፋው
64 ረድኤት ከድር
65 እዮብ ታደለ
66 አዲስ ሀይሉ በቀለ
67 ተስፋለም ጣዕሙ
68 ፊሊሞን አብርሃ
69 ሔዋን አብርሃም
70 ሜሮን ተክላይ
71 ሩት ሞገስ
72 አብርሐም አስራት
73 ሔርሜላ አወጣኸኝ
74 ልድያ አሰፋ
75 ዳግማዊት መሰረት
76 ረድኤት ኃይሉ
77 መቅደስ ቀጸላ
78 እጸገነተ ፍቅሬ
79 መሰረት አለሙ
80 ፍቅርተ ታዬ
81 ዲ/ን ዘካሪያስ ኩሙሳ
82 ሰለሞን መብራቱ
83 ዲ/ን ብሩክ ሲሳይ
84 ብሌን ተስፋዬ
85 ብሌን መሀመድ
86 አቤኔዘር ልደቴ
87 ሚኪያስ ተስፋዬ
88 ኤርሚያስ በድሉ
89 ብሩክ ተ/ሀይማኖት
90 ቤዛ አሰግድ
91 አይናለም ደጀኔ
92 ዲ/ን እስጢፋኖስ ኪሮስ
93 ስመኝ ፀጋዬ
94 ማራማዊት ሽፈራው
95 ሰላማዊት ገ/ሚካኤል
96 ትእግስት ወርቅነህ
97 አፎምያ ታደሠ
98 ላምሮት በላይ
99 ዮርዳኖስ ገ/ሚካኤል
100 ዲ/ን አላዛር ፍቅሩ
101 ብሩክ ብርሀኑ
102 ቆንጂት ወ/ሰንበት
103 ፍቅርተ ካሳሁን
104 ማስረሻ
105 ቤተልሔም ዳዊት
106 ያዕቆብ ግሩም
እግዚአብሔር አገልግሎታችን ይባርክ!!!
የአባላት ጉዳይ ክፍል!!!
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
ቅዳሜ ጥቅምት 9/2017 ዓ.ም ኦርቶዶክሳዊ የንባብ ሕይወት ትምህርት መሰጠቱ የሚታወቅ ነው።
ስለዚህም ከላይ በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ከመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ከማቴዎስ ወንጌል በቀን አንድ ምዕራፍ ያንብቡ መልካም የንባብ ጊዜ
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
+6
የሰንበት ትምህርት ቤታችን ፍኖተ ብርሃን የሥራ አመራር እና ንዑሳን አመራር አባላት በአገልግሎት ዙሪያ ሰፊ የውይይት መርሐ ግብር አከናወኑ።
ቅዱስ እግዚአብሔር አገልግሎታችንን ይቀበልልን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
4_5807722990321801221.docx0.15 KB
በቅዳሜ መደበኛ የአባላት ትምህርት ይሰጣል
የንባብ ልምድ እንዲኖረው አቅደዋል እንግዲህያውስ ይበርቱ ኦርቶዶክሳዊ የንባብ ሕይወት ዛሬ ቅዳሜ ጥቅምት 9
በመምህር ዲ.ን ኤልያስ ጥላሁን ይሰጣል
ቦታ:-በፀበል ቤት አዳራሽ
ሰዓት:- 11:45 ከዚህ ትምህርት በኃላ የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት አባላት ከላይ በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት መጽሐፍ ቅዱስን አንብበን እንጨርሳለን መልካም የንባብ ጊዜ ይሁንልን አሜን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቅዳሜ የትምህርት መርሐግብር ጥቅምት 09 /2017 ዓ.ም 11:45 ሰዓት ላይ ቀጠሮዎትን በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ያድርጉ ''ኦርቶዶክሳዊ የንባብ ሕይወት'' ይምጡ ይማሩ በብዙ ያተርፋሉ።
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
+8
በሰንበት ት/ት ቤታችን በጎ አድራጎት ክፍል ከ250 በላይ ለሚሆኑ ነዳያን የምገባ መርሐግብር ያከናወነ ሲሆን በተጨማሪም
የሰንበት ት/ት ቤታችን አባላትንና ምዕመናንን በማስተባበር ባሳለፍነው እሑድ ጥቅምት 03 ቀን 2017 ዓ.ም ለ50 ሰንበት ተማሪዎች እና የካህናት አባቶቻችንን ልጆች የደብተር፣ ቦርሳና እስክሪብቶ የልገሳ መርሐ ግብር ተከናወነ።
እግዚአብሔር ከሁላችንም ጋር ይሁን
የሰንበት ትምህርት ቤታችን በጎ አድራጎት ክፍል እያከናወነ ያለውን በጎ ስራ ለመደገፍ የምትፈልጉ እንዲሁም ለሌሎች የበጎ አድራጎት ስራ መረጃዎችም
0912 41 97 72
09 66 25 87 38
09 31 14 44 44 በመደወል ማነጋገር ይቻላል።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
