en
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

Open in Telegram

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

Show more
2 757
Subscribers
+124 hours
+17 days
+4230 days
Posts Archive
''ናርዶስ ''    ቁጥር 2 በሰ/ት/ቤታችን የተዘጋጀች ዲጂታል መጽሔት ሰሙነ ሕማማትን ትኩረት በማድረግ የተዘጋጀ በመሆኑ ሁላችንም እንድናነብ ተጋብዘናል። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን  https://finotebirhan.com

''ናርዶስ '' ቁጥር 2 በሰ/ት/ቤታችን የተዘጋጀች ዲጂታል መጽሔት ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን  https://finotebirhan.com

በዓለ ሆሣዕና በደብራችን ጽ/ጽ/ሐ/ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ዋለ። ጌታችን አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቤተ ፋጌ ወደ ኢየሩሳሌም በአህያና ውርንጫይቱ ላይ ተቀምጦ
+9
በዓለ ሆሣዕና በደብራችን ጽ/ጽ/ሐ/ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ዋለ። ጌታችን አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቤተ ፋጌ ወደ ኢየሩሳሌም በአህያና ውርንጫይቱ ላይ ተቀምጦ በገባ ጊዜ ሕዝቡ ሲዘምሩና ሲያመሰግኑ የአይሁድ አለቆች በመቆጣታቸው አመስጋኙ ሕዝብ ዝም ሲሉ ሕጻናቱ የዘንባባ ዝንጣፊ ይዘዉ ''ሆሣዕና በአርያም'' እያሉ  በደስታ ያመሰገኑበት እነዚህ ሕጻናት ዝም ቢሉ እነዚህ አፍ የሌላቸው ድንጋዮች ያመሰግኑኛል ብሎ የተናገረበት  ''እም አፈ ደቂቅ ወሕፃናት አስተዳሎከ ስብሐተ በእንተ ጸላዒ ከመ ትንሥቶ ለጸላዒ ወለገፋዒ ከህፃናት አንደበት ምስጋናን አዘጋጀህ የጠላት ዲቢሎስ ምክሩን ታፈርስበት ዘንድ'' ተብሎ የተነገረበት ታላቁ የሆሣዕና በዓል በአዲስ አበባ ሀገረስብከት ስር  ከሚገኙ 66 ደብራት ከተውጣጡ 2500 በላይ ሕጻናት በተገኙበት  በደብራችን ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት አዘጋጅነት የተከበረ ሲሆን በዕለቱም የደብራችን ዋና አስተዳዳሪ መልአከ ብርሃን አዕምሮ ምስጋናው የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የትምህርት ክፍል ኃላፊ መጋቤ ሃይማኖት ቀሲስ ይታገሱ ደሴ እንዲሁም ከተለያዩ ቦታዎች የተጋበዙ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ሕብረት ተወካዮችና አመራሮች በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ዋለ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

በዓለ ሆሣዕና በደብራችን ጽ/ጽ/ሐ/ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ዋለ። ጌታችን አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቤተ ፋጌ ወደ ኢየሩሳሌም በአህያ እና ውርንጫይቱ ላይ ተቀምጦ በገባ ጊዜ ሕዝቡ ሲዘምሩና ሲያመሰግኑ የአይሁድ አለቆች በመቆጣታቸው አመስጋኙ ሕዝብ ዝም ሲሉ ሕጻናቱ የዘንባባ ዝንጣፊ ይዘዉ ''ሆሣዕና በአርያም'' እያሉ ያመሰገኑበት እነዚህ ሕጻናት ዝም ቢሉ እነዚህ አፍ የሌላቸው ድንጋዮች ያመሰግኑኛል ብሎ የተናገረበት ''እም አፈ ደቂቅ ወሕፃናት አስተዳሎከ ስብሐተ በእንተ ጸላዒ ከመ ትንሥቶ ለጸላዒ ወለገፋዒ ፡  ከህፃናት አንደበት ምስጋናን አዘጋጀህ የጠላት ዲቢሎስ ምክሩን ታፈርስበት ዘንድ'' ተብሎ የተነገረበት ታላቁ የሆሣዕና በዓል በአዲስ አበባ ሀገረስብከት ከሚገኙ 66 ደብራት ከተውጣጡ 2500 በላይ ሕጻናት በተገኙበት በደብራችን ተከብሮ ዋለ።

ምስጋና ዘፍኖተ ብርሃን ሆሣዕና የሚለው ቃል በዕብራይስጥ “ሆሼዕናህ” የሚል ሲሆን ትርጉሙም “እባክህ አሁን አድን”  ማለት ነው፡፡ ይህ ቃል በዘመነ ብሉይ በቀደምት ነቢያት ዘንድ የተለመደ ቃል ነው፡፡ “አቤቱ እባክህ አሁን አድን፣ አቤቱ እባክህ አሁን አቅና፣ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ቡሩክ ነው”፡፡  የሚል /መዝ.፻፲፯፥፳፭—፳፮/፡፡  የሆሣዕና በዓል በልዩ ሁኔታ በሰላም አክብረን አጠናቀናል !!! ተመስገን ከሁሉ አስቀድሞ ለአምላካችን ለቅዱስ እግዚአብሔር ምስጋና አምልኮ እና ውዳሴ ይድረስው እናታችን ድንግል ማርያም አሳዳጊያችን እና ጠባቂያችን ቅዱስ ሚካኤል እንዲሁም ጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ምስጋና ይድረሳችሁ !!! በመጽሐፉ ከጭቃም ይሠራው የነበረ ዕቃ በሸክላ ሠሪው እጅ ተበላሸ፥ ሸክላ ሠሪውም እንደ ወደደ መልሶ ሌላ ዕቃ አድርጎ ሠራው” ት.ኤርምያስ 18፥4 እንዲል የህጻናቱን በዓል በዓለ ሆሣዕናን በደመቀ እና በተቃና ሁኔታ አክብረናል እግዚአብሔር ይመስገን.... *የሰንበት ት/ቤታችን አባላት በሙሉ  በተለይም * የሆሣዕና ዝግጅት ዐብይ ኮሜቴ አባላት * የሰንበት ት/ት ቤቶች አንድነት ህብረት * የህጻናት እና የማዕከላውያን አዘጋጆች * የሰንበት ት/ት ቤታችን የወላጅ ኮሜቴ አባላት እና ወላጆች * አገልግሎቱ እንዲቃና በጸሎት በጉልበት በሀሳብ  ስታግዙን  የነበራችሁ *   በጠቅላላው ልዪ ልዩ የጊቢያችን ማኅበራት *ለተስፋ ተክለ ሃይማኖት ማህበራት ህብረት *ለምንወዳችሁ እና ለምናከብራችሁ ይልቁን ቤተክርስቲያን በስስት ለምታያችሁ እና ጠበቃዋ ለሆናችሁ በሦስቱም መውጫ በር ላይ ያላችሁ የአጥቢያችን ወጣቶች እና ምዕመናን *ለልደታ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያና ለጎማ ቁጠባ ፖሊስ ጣቢያ *ለወረዳ 07 የአስተዳደር እና የጸጥታ አካላት  በሙሉ ጊዜያችሁን ጉልበታችሁን  ገንዘባችሁን ሳትሰስቱ እና ሳትቆጥቡ ስትሰጡ ለበዓሉ ድምቀት ለሆናችሁ ምዕመናን እና ምዕመናት በሙሉ ዋጋ ከፋይ አስራት ተቀባይ የለመነቱን የማይነሳ የነገሩትን የማይረሳ ቸሩ መድኃኔዓለም አምላካችን ዋጋቹሁን ይክፈላችሁ!!! ከዓይን ጥቅሻ ይልቅ ፈጥና የምትደርስ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በሕይወታችሁ በቤታችሁ ትግባ ስሙ ሲጠራ ልባችን ወከክ እግራችን ሸብረክ የሚለው ጠባቂያችን አሳዳጊያችን  ቅዱስ ሚካኤል ከልጅነታችን እስከ ሽምግልናችን በጥባቆቱ አይለየን!! "ለጌታ ያስፈልጉታል" እንድንባል ይርዳን  !!! እንዲህ ማማራችን እና መዋባችን በእርሷ ነውና ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ከውስጥም ከውጭም ጠላት ይጠብቅልን!!! የሆሣዕና በዓል የህጻናቱ ነውና ተተኪዎቻችንን በጤና በጸጋ ይጠብቅልን !!ሀገራችንን ኢትዮጵያን በሰላም እና በፍቅር በአንድነቷ አጽንቶ ያቆይልን የዓመት ሰው ይበለን!!! አሜን          ሚያዚያ 5/2017ዓ.ም                  ካሣሁን እሸቱ    የጽ/ጽ/ሐ/ጎላ /ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ          የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት                ም/ሰብሳቢ ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com 

ሆሳዕና በአርያም ሆሳዕና ማለት ቃሉ ሆሼዕና ከሚለው ከዕብራይስጥ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙ  መድኃኒት፣ አቤቱ አሁን አድን ፣አቤቱ አሁን አቅና ማለት ነው፡፡ ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘጠኙ ዓበይት በዓላት አንዱ ሲሆን ቅዱስ ያሬድ ኢትዮጵያዊው ሊቅ በሰየመው የዐቢይ ፆም ሳምንታት ስያሜ  ስምንተኛ ሳምንት ሆኖ ተሰይሟል። ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቤተ ፋጌ ወደ ኢየሩሳሌም በአህያ ውርንጭላ ላይ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም መግባቱን በማሰብ ዛሬም ድረስ በታላቅ ክብር ቤተክርስቲያን በዓሉን ታከብራለች። ጌታችንም ከደቀ መዛሙርቱ ሁለቱን ጠርቶ እንዲህ አላቸው  “በፊታችሁ ወዳለችው መንደር ሂዱ ያን ጊዜም የታሰረች አህያ ከውርንጭላዋ ጋር ታገኛላችሁ፤ ፍቱና አምጡልኝ” አላቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም እንዴት የሰው ንብረት ዘርፈን  እናመጣለን? ብለው ፈሩ ያንጊዜ  “ምን ታደርጋላችሁ? የሚላችሁ ቢኖር ጌታቸው ይሻቸዋል በሉ፤ ያን ጊዜ ይሰዱአችኋል” አላቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም ሄደው ጌታችን ኢየሱስ እንዳዘዛቸው አደረጉ፡፡ “አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ እጅግ ደስ ይበልሽ፤ አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ እልል በዪ፤ እነሆ ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው፤ ትሑትም ሆኖ በአህያ በአህያይቱም ግልገል በውርንጫይቱ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል፡፡” ትን.ዘካርያስ 9፥9 ተብሎ በነቢያት የተነገረው ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ጌታችንም በአህያ ውርንጭላ ላይ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም በሚገባ ጊዜ ሕዝቡም ልብሶቻቸውን በመንገድ ላይ እያነጠፉ ፤ ዘንባባ ይዘው የዛፎችንም ጫፍ ጫፍ እየቆረጡ “ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ቡሩክ ነው፤ ሆሣዕና በአርያም” እያሉ ይጮሁ ነበር፡፡ ያን ጊዜ የሕዝቡና የሕጻናቱ የደስታ ጩኸትና ምስጋና ያስቆጣቸው ፈሪሳዊያን ዝም እንዲያሰኛቸው ጌታችንን ጠየቁት እርሱም መልሶ “እነርሱ ዝም ቢሉ ድንጋዮች ያመሰግኑኛል” ብሎ መለሰላቸው። ''እም አፈ ደቂቅ ወሕፃናት አስተዳሎከ ስብሐተ በእንተ ጸላዒ ከመ ትንሥቶ ለጸላዒ ወለገፋዒ ፡  ከህፃናት አንደበት ምስጋናን አዘጋጀህ የጠላት ዲቢሎስ ምክሩን ታፈርስበት ዘንድ''     ጌታችን በአህያ ላይ ለምን ተቀመጠ? • ትህትናን ለማስተማር • የሰላም ዘመን ነው ሲል • ለፈለጉኝ ሁሉ የቅርብ አምላክ ነኝ ሲል ነው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ቤተ መቅደስ ሲገባ ሕዝቡ ዘንባባ ይዘው “ቡሩክ ዘይመጽእ በስመ እግዚአብሔር፤ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ የተባረክ ነው።’’ በማለት ስለተቀበሉት ይህን በማሰብ እስከ አሁን ድረስ ቤተ ክርስቲያናችን ዘንባባ ለሕዝበ ክርስቲያኑ በመስጠት እንዲሁም በአራቱም ማዕዘናት ከአራቱም የወንጌል ክፍል ዕለቱን የሚመለከቱ ምንባባት እየተነበበ በዓሉ ይከበራል፡፡ በሰሙነ ሕማማት ጸሎተ ፍትሐት ስለማይፈጸም በዚሁ እለት ጸሎተ ፍትሐት ይከናወናል ፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

የነገውን የሆሣዕና በዓል ዝግጅት ከጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን በቀጥታ ስርጭት በእነዚህ የሶሻል ሚድያ አማራጮች ከ 5 ሰዓት ጀምሮ ይከታተሉን ቲክቶክ:- https://www.tiktok.com/@f
የነገውን የሆሣዕና በዓል ዝግጅት ከጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን በቀጥታ ስርጭት በእነዚህ የሶሻል ሚድያ አማራጮች ከ 5 ሰዓት ጀምሮ ይከታተሉን ቲክቶክ:- https://www.tiktok.com/@finotebirhan?is_from_webapp=1&sender_device=pc ዩቲዩብ:- https://www.youtube.com/@finotebirhan12 ፌስቡክ:- https://web.facebook.com/Fbirhan

እንኳን ለሆሳዕና በዐል በሰላም አደረሳችሁ ለሆሳዕና በዐል ታሳቢ የተደረገው ዝግጅት ተጠናቀቀ ነገ ከ 4 - 11 ሰዓት ከ 66 - 77 ሰንበት ትምህርት ቤቶች በጋራ የምስጋና ቀናችንን የምናከብር ያከናውናሉ ።

"ሆሳዕና በአርያም " ሆሳዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው ሆሳዕና በአርያም እያሉ ይጮሁ ነበር ( ማቴ 21÷9 ) "አቤቱ እባክህ አሁን አድን !
"ሆሳዕና በአርያም " ሆሳዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው ሆሳዕና በአርያም እያሉ ይጮሁ ነበር ( ማቴ 21÷9 ) "አቤቱ እባክህ አሁን አድን !

እንኳን ለሆሣዕና በዓል ዋዜማ በሠላም አደረሰን! #ማስታወቂያ እንደ እግዚአብሔር አምላክ ፈቃድ ከአራት ወራት በላይ ስንዘጋጅበት የነበረው የሆሣዕና በዓል መርሐግብር ዋዜማ ላይ ደርሰናል። ለዚህ ያደረሰን አምላከ ቅዱሳን ስሙ ይክበር ይመስገን። ከዚህ ሁሉ ዝግጅት በኃላ በጥሩ ሁኔታ ለእንግዶች እና ለምዕመናን ይደርስ ዘንድ ቀሪ የምናከናውናቸው ተግባራት ላይ በትጋት እንድንሳተፍ እንጠይቃለን። የቀሩ ስራዎች 1. የምግብ ዝግጅት ማከናወን 2. የግቢና አዳራሽ ጽዳት ማከናወን 3. የድንኳን ተከላ ማካሄድ 4. የወንበር መደርደርና ማስተካከል በእነዚህና በመሳሰሉት አገልግሎቶች ላይ የተከበራችሁ ወንድምና እሕቶቻችን ተገኝታችሁ እንድታግዙ እንጠይቃለን። የሆሣዕናው ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በሠላም ያስጀመረንን በመልካም እንዲያስፈጽመን በጸሎት አስቡን። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

02 ቀን ቀረው! #ሆሳዕና_በአርያም መልሶም፡— እላችኋለሁ፥ እነዚህ ዝም ቢሉ ድንጋዮች ይጮኻሉ፡ አላቸው። (ሉቃስ 19:40) #አቤቱ_እባክህ_አሁን_አድን!
02 ቀን ቀረው! #ሆሳዕና_በአርያም መልሶም፡— እላችኋለሁ፥ እነዚህ ዝም ቢሉ ድንጋዮች ይጮኻሉ፡ አላቸው። (ሉቃስ 19:40) #አቤቱ_እባክህ_አሁን_አድን!