የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
Open in Telegram
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
Show more2 636
Subscribers
+324 hours
+187 days
+5730 days
Posts Archive
ምስጋና ዘፍኖተ ብርሃን
የከተራ የጥምቀት እና የቃና ዘገሊላ በዓል በሰላም አክብረን አጠናቀናል !!! ተመስገን ከሁሉ አስቀድሞ ለአምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔር አምልኮ እና ውዳሴ ይድረስው እናታችን ድንግል ማርያም አሳዳጊያችን እና ጠባቂያችን ቅዱስ ሚካኤል እንዲሁም ጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ምስጋና ይድረሳችሁ !!
የሰንበት ት/ቤታችን አባላት በሙሉ
ህጻናት (የነገ ተስፍዎች) ማዕከላውያን (ተረካቢዎቻችን) ወጣቶች ( የሰ/ቤቱ ጠበቃዎች) የባለ ትዳር ጉባኤ አባላት ( ጥላዎቻችን )ልዪ ልዪ የአገልግሎት ክፍላት ልብሰ ስብሐት ልዪ ልዪ አገልግሎት ላይ የተሳተፋችሁ አባላት ለእህት ሰ/ት/ቤታችን ለደብረ አሚን ተክለ ሀይማኖት መካዕ ደናግል ሰንበት ት/ቤት ለደብራችን አገልጋዪች በጠቅላላ ለልዪ ልዪ የጊቢያችን ማህበራት ለምንወዳችሁ እና ለምናከብራችሁ በሶስቱም መውጫ በር ላይ ላላችሁ የአካባቢው ወጣቶች ለል/ክ/ከ ለወረዳ 07 አስተዳደር እና ለጸጥታ ክፍል ስራተኞች በሙሉ ጊዜያችሁን ጉልበታችሁን ሳትሰስቱ እና ሳትቆጥቡ ስትሰጡ ለበዓሉ ድምቀት ለሆናችሁ ምዕመናን እና ምዕመናት በሙሉ ዋጋ ከፋይ አስራት ተቀባይ የለመነቱን የማይነሳ የነገሩትን የማይረሳ ቸሩ አምላካችን ዋጋቹሁን ይክፈላችሁ !! ከዓይን ጥቅሻ ይልቅ ፈጥና የምትደርስ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በህይወታችሁ በቤታችሁ ትግባ ስሙ ሲጠራ ልባችን ወከከ እግራችን ሸብረክ የሚለው ጠባቂያችን ቅዱስ ሚካኤል ከልጅነታችን እስከ ሽምግልናችን በጥባቆቱ አይለየን ከቁጥር ሳያጎድለን አምና ብለን ለማውጋት ያብቃን !! እንዲህ ማማራችን እና መዋባችን በእርሷ ነውና ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ይጠብቅል !! ሀገራችንን በሰላም እና በፍቅር በአንድነቷ አጽንቶ ያቆይልን የዓመት ሰው ይበለን!!!
ነጻ በምታወጣ በኢየሩሳሌም ከተማ
ከጽዮን ልጆች ጋራ መዝሙራችን እንዲሰማ
አንድ ሆነን በቀኝ እንድንቆም ከበኩራት ማኅበር ጋራ አንድ ሆንን ዛሬ እናገልገል አንድ ሆነን ዛሬ እንስራ።
ጥር 12/2016ዓ.ም
የጽ/ጽ/ሐ/ጎላ /ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ
የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
ጽሕፈት ቤት
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
