የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
Open in Telegram
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
Show more2 640
Subscribers
+124 hours
+27 days
+5230 days
Posts Archive
የወጣት ጉዞ የመጨረሻ ቀን ክፍያ ነሐሴ 23 ነው
ክፍያውን በጽ/ቤት እንዲሁም የሰንበት ት/ቤታችን ልማት ሱቅ ያገኛሉ
👉 ባለትዳር አባላት እፀገነት ጋር ትኬቱ ይገኛል
#ደብረ_ታቦር
ነሐሴ ዐሥራ ሦስት በዚች ቀን ክብር ይግባውና የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታላቅና ክቡር በዓል ነው።
በዚች ቀን መድኃኒታችን ሦስቱን ደቀ መዛሙርቶቹን ጴጥሮስን፣ ያዕቆብንና ዮሐንስን ይዞ ወደ ታቦር ተራራ ላይ አወጣቸው። መልኩም በፊታቸው ተለወጠ ልብሱም እንደ በረዶ ነጭ ሆነ። ስለ እነርሱም ጌታችን የሰው ልጅ በጌትነቱ ሲመጣ እስከሚያዩት ድረስ በዚህ ከቆሙት መካከል ሞትን የማይቀምሱት አሉ አለ።
ሰዎች ሁሉ እርሱ ለሙሴ ጌታውና ከሞት ያስነሣው እንደሆነ ለኤልያስም ፈጣሪው እንደሆነና ካሳረገበትም ያወረደው እርሱ እንደሆነ ያውቁ ዘንድ እነሆ ከጌታ ከኢየሱስ ጋራ እየተነጋገሩ ሙሴና ኤልያስ ወደርሱ መጡ።
ስለዚህም ጴጥሮስ ጌታችንን እንዲህ አለው አቤቱ በዚህ ትኖር ዘንድ ትወዳለህን ሦስት ሰቀላዎችንም አንድ ላንተ፣ አንድ ለሙሴ፣ አንድ ለኤልያስ እንሠራ ዘንድ።
እንኳን አደረሳችሁ
🌑 ሀዘን ዜና
እህታችን እፁብድንቅ አየለ በሰንበት ት/ቤታችን በሕጻናት ክፍል ስታገለግል ቆይታ ባደረባት የልብ ሕመም በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ስትረዳ ቆይታ በትላንትናው ዕለት አርፋለች
👉 ዛሬ ነሐሴ 11 ቀብር ደብረ ኢሚን አቡነ ተክለሃይማኖት በ8:30 ይፈጸማል
👉 ለቤተሰቧቿ መጽናናትን ይስጥልን የምንችል አባላት በቦታው እንገኝ
🌑 ሀዘን ዜና
እህታችን እፁብድንቅ በሰንበት ት/ቤታችን በሕጻናት ክፍል ስታገለግል ቆይታ ባደረባት የልብ ሕመም በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ስትረዳ ቆይታ በትላንትናው ዕለት አርፋለች
👉 ቀብር ደብረ ኢሚን አቡነ ተክለሃይማኖት በ8:30 ይፈጸማል
👉 ለቤተሰቧቿ መጽናናትን ይስጥልን የምንችል አባላት በቦታው እንገኝ
👉 በዚህ ሳምንት የቅዳሴ ማርያምን ትርጓሜ በPDF እናቀርብሎታለን መልካም ንባብ
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
