en
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

Open in Telegram

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

Show more
2 765
Subscribers
+424 hours
+127 days
+5330 days
Posts Archive
የተከበራችሁ የባለ ትዳር ጉባኤ አባላት በሙሉ አምላካችን በሰላም በፍቅር በጤና ጠብቆ ከዘመነ ዮሐንስ ወደ ዘመነ ማቴዎስ ስላሸጋገረን ክብርና ምስጋና ይድረሰው።          🌹 ዕድሜ ለንስሃ ፤ዘመን ለፍስሐ የተሰጠን የንስሃ ፍሬ አፍርተን መንግስቱን እንድወርስ ነውና ፈጣሪያችን ልንማጸነው ይገባል። የ 2017 ዓ.ም የመጀመሪያው የባለ ትዳር ጉባኤ የፊታችን እሑድ መስከረም 19 ከ5:30-7:00 የሚከናወን በመሆኑ ሁላችሁም እንድትገኙ በክብር ተጠርተዋል።                  የባለ ትዳር ጉባኤ ክፍል። ሠላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

የቅዱስ መስቀል ደመራ በዓል ፍፁም መንፈሳዊ በሆነ መልኩ ተከብሮ መዋል ይችል ዘንድ ሁሉም ባለድርሻ አካል የሚጠበቅበትን ሁሉ እንዲያደርግ ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ  አቡነ አብርሃም ጥሪ አቀረቡ። ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የባህርዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የ፳፻፲፯ ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓልን በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁና የቅድመ ጥንቃቄ መልእክት አስተላለፉ። ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ በዚሁ መልዕክታቸው ለመላው ሕዝበ ክርስቲያን እንኳን  ለ፳፻፲፯ ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ ካሉ በኋላ በዓሉ በድምቀት፣ባማረና በሰመረ መልኩ ተከብሮ መዋል ይችል ዘንድ ሕዝበ ክርስቲያኑ በንቃትና በሕብረት በመሆን ከጸጥታ አካላትና ቤተክርስቲያኒቱ ለዚሁ ዓላማ ካቋቋመቻቸው የኮሚቴ አባላት ጭምር በመተባበር እንዲሰራ አደራ ብለዋል። የመንግሥት የጸጥታ ተቋማት በዓሉ ያለ አንዳች የጸጥታ ችግር ተከብሮ መዋል እንዲችል ከጠቅላይ ቤተክህነት ዐቢይ ኮሚቴ ጋር በጥምረት እየሰራ እንደሚገኝ የጠቀሱት ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ በበዓሉ ወቅት ለሚደረግ ፍተሻ ፍፁም ክርስቲያናዊ ትብብር እንዲያደርግ አደራ ብለዋል።የጸጥታ አስከባሪዎችም ጨዋነት በተምላና ክብርን በሚገልጽ አግባብ የፍተሻ ሥርዓቱን እንዲያከናውኑ  አሳስበዋል። ከበዓላችን መንፈሳዊ ሥርዓት ውጪ የሆኑ መልዕክቶች፣ አለባበሶች እንዲሁም የቤተክርስቲያኒቱ መገለጫ ከሆኑ ዓርማዎች ውጭ እንዳይዙ በዓሉ ሃይማኖታዊና መንፈሳዊ እንደመሆኑ ቤተክርስቲያኒቱን ከማይገልጹ ሆታዎችና ጭፈራዎች እንዲርቁ በአጠቃላይ ያልተፈቀዱ ነገሮችን ሁሉ የመስቀል ደመራ በሚከበርባቸው ቦታዎች ሁሉ  ይዞ መገኘት ፍጹም መንፈሳዊ የሆነውን በዓላችንን የሚያደበዝዘው ስለሆነ ጥንቃቄ ማድረግ  ይገባል ብለዋል። አያይዘውም ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ወጣት የሰንበት ትምህርት ቤት ልጆቻችን ከሚያቀርቡት መንፈሳዊ ትርኢትና ዝማሬ ጎን ለጎን አካባቢያቸውን በመቆጣጠር በዓላችንን በሰላም እንዳናከብር የሚያደርጉ ሁኔታዎች እንዳይፈጠሩ በጥንቃቄ መጠበቅ ይኖርባቸዋል ብለዋል። በሌላ መልኩም የሌሎች እምነት ተከታዮችም በነበረውና በኖረው የመከባበርና የመደማመጥ የአብሮነት ስሜት በዓሉ በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን እንዲወጡ የአደራ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። የበዓሉ ዝግጅት በየደረጃው በተቋቋሙት የበዓል አዘጋጅ ኮሚቴዎች ጥረት በጥሩ ሁኔታ በማጠናቀቅ ላይ መሆኑን የገለፁት ብፁዕነታቸው ከንጉሰ ነገስት አጼ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግስት ወዲህ ተደርጎ በማያውቅ ሁኔታ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር  ለሦስተኛ ጊዜ የመስቀል ደመራ በዓልን በድምቀት ማክበር የሚያስችል የስቴጅ፣የድምጽ ማጉያና የክብር እንግዶች ማስተናገጃ ቦታዎችን በማዘጋጀት የሚያደርገውን ተሳትፎ ያደነቁት  ብፁዕ አቡነ አብርሃም የከተማ አስተዳደሩ እያደረገ ላለው ከፍተኛ አስተዋጽኦ በራሳቸውና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክን ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በመጨረሻም በዓሉን ስናከብር ፍቅር ሰላምንና አንድነትን እንዲሁም መግባባትን መርህ ባደረገ አግባብ መሆን አለበት ያሉት ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ በዓሉ ሥጋዊ ፈቃዶቻችንን የምንፈጽምበት ሳይሆን ንስሐ ያልገቡ ንስሐ የሚገቡበት የተጣሉ የሚታረቁበት የተለያዩ አንድ የሚሆኑበት የተራራቁ የሚቀራረቡበት ፍፁም የደስታና የሰላም በዓል ሆኖ እንዲከበር ማድረግ ይኖርብናል በማለት መልዕክታቸውን አጠናቀዋል። ዘገባው የኢኦተቤ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው። ©የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

የተወደዳችሁ የሰንበት ት/ት ቤታችን አባላት ያለፈው ቅዳሜና እሑድን በደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ቤ/ክ  የመስቀል ጥናት ስታጠኑ የነበራችሁ አባላት  ከዛሬ  ማክሰኞ  ጀምሮ ልብሰ ስብሐት የሚሰጥ በመሆኑ መጥታችሁ እንድትወስዱ እያሳሰብን  ሐሙስ መስከረም 16/2017ዓ.ም  የምንችል አባላት  5:00 ላይ በደብራችን ጎላ ተገናኝተን አብረን የምንሄድ ይሆናል በሰዓቱ ጎላ መገኘት የማትችሉ  አባላት ግን ግዴታ 6:00 ላይ መንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ  ቤ/ክ መድረስ ይኖርብናል። ሠላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

22ቱ የእግዚአብሔር ኅቡዕ ስሞች(ሃያ ሁለቱ ዓሌፋት) ================================== 1.     አሌፍ ፡ ብሂል አምላክ ፈጣሬ ኩሉ ዓለም ዓለምን ከነጓዟ ካለመኖር ወደ መኖር አምጥቶ የፈጠረ እግዚአብሔር ማለት ነው። 2.    ቤት፡ ብሂል ባዕል እግዚአብሔር እግዚአብሔር ሁሉን መስጠት የሚችል ቸር ለጋስ ባለጸጋ ማለት ነው። 3.    ጋሜል፡ ብሂል ግሩም እግዚአብሔር እግዚአብሔር ሊመረመር የማይችል ግሩም ድንቅ ማለት ነው። 4.    ዳሌጥ፡ ብሂል ህልው እግዚአብሔር እግዚአብሔር በጌትነቱ ዙፋን ለዘለዓለም ይኖራል ማለት ነው። 5.   ፡ ብሂል ህልው እግዚአብሔር እግዚአብሔር በአንድነቱ በሦስትነቱ ለዘለዓለም ይኖራል ማለት ነው። 6.   ዋው፡ ብሂል ዋህድ እግዚአብሔር እግዚአብሔር በመንግሥት በሥልጣን በአገዛዝ በባህርይ አንድ አምላክ የሆነ ማለት ነው። 7.    ዛይ፡ ብሂል ዝኩር እግዚአብሔር እግዚአብሔር በሥራው ሁሉ እየታሰበ ሲመሰገን የሚኖር ፈጣሪ ማለት ነው። 8.    ሔት፡ ብሂል ሕያው እግዚአብሔር እግዚአብሔር በመንግሥቱ ሽረት በባሕርዩ ኅልፈት የሌለበት ለዘለዓለም ሕያው የሆነ ማለት ነው። 9.   ጤት፡ ብሂል ጠቢብ እግዚአብሔር እግዚአብሔር ጥበብን የሚገልጽ ከጥበበኞች ይልቅ ጥበበኛ የሆነ አምላክ ማለት ነው። 10.  ዮድ፡ ብሂል የማነ እግዚአብሔር በእግዚአብሔር ቀኝ ያለ እሱ ኃያልና ጽኑዕ የሆነ ማለት ነው። 11.    ካፍ፡ ብሂል  ከሃሊ እግዚአብሔር ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የሌለ ሁሉን ማድረግ የሚቻለው አምላክ ማለት ነው። 12.  ላሜድ፡ ብሂል ልዑል እግዚአብሔር እግዚአብሔር ልዑለ ባሕርይ የሆነ ማለት ነው። 13.  ሜም፡ ብሂል ምዑዝ እግዚአብሔር እግዚአብሔር ንጹሕ ባሕርይ የሆነ አምላክ ማለት ነው። 14.  ኖን፡ ብሂል ንጉስ እግዚአብሔር እግዚአብሔር የነገሥታት ንጉሥ የገዥዎች ገዥ የሆነ አምላክ ማለት ነው። 15.  ሳምኬት፡ ብሂል ሰፋኒ እግዚአብሔር እግዚአብሔር ሁሉን የሚገዛ አምላክ ማለት ነው። 16.  ዔ፡ ብሂል ዐብይ እግዚአብሔር  እግዚአብሔር ታላቅና ገናና የሆነ አምላክ ማለት ነው። 17.  ፌ፡ ብሂል ፍትው እግዚአብሔር እግዚአብሔር ተወዳጅ የሆነ አምላክ ማለት ነው። 18.  ጻዴ፡ ብሂል ጻድቅ እግዚአብሔር እግዚአብሔር ሐሰት የሌለበት እውነተኛ አምላክ ማለት ነው። 19.  ቆፍ፡ ብሂል ቅዱስ እግዚአብሔር እግዚአብሔር ለልበ ቅኖችና ለየዋሃኖች ቅርብ የሆነ አምላክ ማለት ነው። 20. ሬስ፡ ብሂል ርዑስ እግዚአብሔር እግዚአብሔር ክብሩ ከእርሱ ለእርሱ የተገኘ የሁሉ ጌታ ማለት ነው። 21.  ሳን፡ ብሂል ስቡህ እግዚአብሔር  እግዚአብሔር በሥራው ሁሉ የተመሠገነ ማለት ነው። 22. ታው፡ ብሂል ትጉህ እግዚአብሔር እግዚአብሔር እንቅልፍ የሌለበት ትጉህ፤ ድካም የማይሰማው ጽኑዕ የሆነ ፈጣሪ ማለት ነው።          ምንጭ :- መዝሙረ ዳዊት ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

https://youtu.be/5rLqRj0ho-g?si=nclQAFTxCM8mInb7 በሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት የተዘመሩ የመስቀል መዝሙራት በሊንኩ ገብተው ያዳምጡ።

"ስለዚህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ወደ ፊት ሁለት አይደሉም። እግዚአብሔር ያጣመረውን እንግዲህ ሰው አይለየው።" ማቴ 19 ÷6 በዛሬው እለት መስከረም 12 /2017 ዓ.ም ጋብቻችሁን በቅድስት ቤተክርስ
"ስለዚህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ወደ ፊት ሁለት አይደሉም። እግዚአብሔር ያጣመረውን እንግዲህ ሰው አይለየው።" ማቴ 19 ÷6 በዛሬው እለት መስከረም 12  /2017 ዓ.ም ጋብቻችሁን በቅድስት ቤተክርስቲያን ሥርዓት የፈጸማችሁት የሰንበት ትምህርት ቤታችን የፍኖተ ብርሃን አገልጋዮች ወንድማችን ወርቅነህ ባህሩ  እና  የትዝታ ወንድሙ የአብርሃምን እና የሳራን ጋብቻ የባረከ አምላክ ጋብቻችሁን ይባርክላችሁ።  ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በክንፉ ከልሎ በፍቅርና በጤና ይጠብቃችሁ ዘንድ መልካም ምኞታችን ነው!!!      እንኳን ደስ አላችሁ  ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

"ስለዚህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ወደ ፊት ሁለት አይደሉም። እግዚአብሔር ያጣመረውን እንግዲህ ሰው አይለየው።" ማቴ 19 ÷6 በዛሬው እለት መስከረም 12 /2017 ዓ.ም ጋብቻችሁን በቅድስት ቤተክርስ
"ስለዚህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ወደ ፊት ሁለት አይደሉም። እግዚአብሔር ያጣመረውን እንግዲህ ሰው አይለየው።" ማቴ 19 ÷6 በዛሬው እለት መስከረም 12  /2017 ዓ.ም ጋብቻችሁን በቅድስት ቤተክርስቲያን ሥርዓት የፈጸማችሁት የሰንበት ትምህርት ቤታችን የፍኖተ ብርሃን አገልጋዮች ዲ/ን ብሩክ ይብራ  እና  ቤተልሔም ፀጋዬ የአብርሃምን እና የሳራን ጋብቻ የባረከ አምላክ ጋብቻችሁን ይባርክላችሁ።  ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በክንፉ ከልሎ በፍቅርና በጤና ይጠብቃችሁ ዘንድ መልካም ምኞታችን ነው!!!      እንኳን ደስ አላችሁ  ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ሰላም ለምቅዋምከ ዘልዑል ማዕረጋ ፤ እምተቅዋመ አዕላፍ እንግልጋ ፤ ሚካኤል መንፈስ ዘእንበለ ሥጋ፤ ታድኅን ዘተመንደቡ ለማዕከለ ባሕር እምፁጋ፤ ወለእለ በበድው ካዕበ ትባልህ በጸጋ። በፈጣሪ ፊት ከአ
ሰላም ለምቅዋምከ ዘልዑል ማዕረጋ ፤ እምተቅዋመ አዕላፍ እንግልጋ ፤ ሚካኤል መንፈስ ዘእንበለ ሥጋ፤ ታድኅን ዘተመንደቡ ለማዕከለ ባሕር እምፁጋ፤      ወለእለ በበድው ካዕበ ትባልህ በጸጋ። በፈጣሪ ፊት ከአዕላፍ መላእክት መቆሚያ ይልቅ ከፍታ ለአላት መቆሚያህ ሰላም እላለሁ። ተፈጥሮህም ከነፋስ የኾነ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ  በክፋት ማዕበል እየተንገላቱ የሚጨነቁና በበረኃ የሚሠቃዩትን በፍጹም ረድኤትህ ደርሰህ የምታድናቸው አንተ ነህ።    የቅዱስ ሚካኤል ጸሎቱና በረከቱ አማላጅነቱም ለዘለዓለሙ ከእኛ ጋር ይኑር። አሜን ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ጼዴንያ ማርያም በዚህች ቀን ቅዱስ ሉቃስ የሳላትና ሥጋን የለበሰችው  ከፊቷም ወዝ የሚወጣትና ድውያንን የምታድነው የድንግል ማርያም ስዕለ አድኅኖ ወደ ጼዴንያ ከወዳጇ ከብጽዕት ማርታ ዘንድ ገብታለች:: ቅድስት ማርታ ሃብት ንብረቷን በአብርሃማዊ ተግባር (በምጽዋትና እንግዳን በመቀበል) ላይ ያዋለች ክብርት ሴት ናት:: ለእመ ብርሃን ካላት ፍቅር የተነሳ እንቅልፍ አልነበራትም ተግታ ታገለግላትም ነበር ስዕሏን እንዲያመጣላት የላከችው ኢትዮዽያዊው መነኩሴ አባ ቴዎድሮስ የስዕሏን ተአምራት ባየ ጊዜ ለራሱ ለመውሰድ ሞክሮ ነበር:: ነገር ግን ከሁሉም በተሻለ የምትወዳት ቅድስት ማርታ ነበረችና በድንቅ ተአምር  በዚህች ቀን ወደ ጼዴንያ ገብታለች:: ቅድስት ማርታም ያለ ዕረፍት ስታገለግላት ኑራ ዐርፋለች::   ተቀጸል ጽጌ / አጼ መስቀል ከ1500 ዓመት በፊት አበባን ተቀዳጅ የሚል ትርጉም ያለው የ‹‹ተቀጸል ጽጌ›› ክብረ በዓል መከበር የተጀመረው በአፄ ገብረ መስቀል ዘመን ሲሆን፣ ዝማሬውን ያዘጋጀው ደግሞ ቅዱስ ያሬድ ነበር ክረምት በሚወጣበት መስከረም 25 ቀን የአበባው በዓል ሲከበር ቅዱስ ያሬድ ንጉሠ ነገሥቱን ‹‹ተቀጸል ጽጌ ገብረ መስቀል ሐፀጌ›› - አፄ ገብረ መስቀል ክረምቱ አልፎልሃልና አበባን ተቀዳጅ፣ አበባን ተላበስ እያለ ያወድሰው የነበረው በዓላዊ ትውፊት እየተቀባበለ እስከ 15ኛው መ/ክ/ዘ ደርሶ ነበር፡፡ በአፄ ዳዊት ዘመን የጌታችን ግማደ መስቀሉ መስከረም 10 ቀን ከግብፃውያን እጅ በመቀበላቸው ግማዱም በንጉሡ ምክንያት በመምጣቱ ‹‹አፄ መስቀል›› እየተባለ መከበር ሲጀምር፣ የ25ኛው ቀን የአበባው በዓልም በ15 ቀን ወደኋላ በማፈግፈግ ከርሱ ጋር ባንድነት እንዲከበር በመወሰኑ እስካሁን በመከበር ላይ ይገኛል፡፡ በቀድሞ ግዜ እስከ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዘመን (1923-1967) የ1966ቱ መስከረም 10 ድረስ በዓሉ በንጉሡ ፊት በገነተ ልዑል ቤተ መንግሥት፣ በኋላም በኢዮቤልዩ ቤተ መንግሥት ይከበር ነበር፡፡ በዘመነ ደርግ ተቋርጦ የነበረው የአበባው በዓል ተቀጸል ጽጌ ከ1980ዎቹ አጋማሽ ጀምሮ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ አማካይነት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ዐውደ ምሕረት በመንፈሳዊ ሥነ ሥርዓትና ለምእመኑ አበባ እየታደለ መከበር ጀምሮ እንደቀጠለ ነው፡፡ ‹‹የክረምቱ ወራት አልፎ መጸዉ ብሎም በጋው ሲተካ፣ ምድር በልምላሜ ፀጋ ተውባ አረንጓዴ ልብስ ተጎናጽፋ፣ በዕፅዋት አበባ ደምቃ፣ የመንፈስ ደስታ የምታድልበት፣ ሰማይ በከዋክብት አጊጦና አሸብርቆ የሚታይበት በመሆኑ የአበባ በዓል ስም ከግብር የተስማማለት ነው፡፡ ቅዱስ እግዚአብሔር በዕለቱ ከሚታሰቡ ቅዱሳን በረከት ያድለን። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

🌻ተቀጸል ጽጌ 🌻 በዐፄ ዳዊት ዘመን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት ግማደ መስቀሉ ወደ ኢትዮጵያ የገባበትና የ “ተቀጸል ጽጌ”(አበባን ተቀዳጅ) በዓል ዛሬ መስከረም ፲ ቀን ይከበራል፡፡
🌻ተቀጸል ጽጌ 🌻                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                     በዐፄ  ዳዊት ዘመን  ኢየሱስ  ክርስቶስ  የተሰቀለበት ግማደ  መስቀሉ  ወደ ኢትዮጵያ የገባበትና   የ “ተቀጸል  ጽጌ”(አበባን  ተቀዳጅ)  በዓል ዛሬ መስከረም ፲ ቀን  ይከበራል፡፡

እናስተዋውቅዎ """""""""""""""""""" ጥንታዊው እና ታሪካዊው የርዕሰ አድባራት እንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ወኤልያስ ቤተክርስቲያን በ1872 ዓ.ም በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ተመሰረተ። የ
+3
እናስተዋውቅዎ """""""""""""""""""" ጥንታዊው እና ታሪካዊው የርዕሰ አድባራት እንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ወኤልያስ ቤተክርስቲያን በ1872 ዓ.ም በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ተመሰረተ። የኪነ ሕንፃ ግንባታው አምስት ዓመታትን የፈጀ ሲሆን ከ1872 እስከ 1877 ዓ.ም ተሰርቶ ሲጠናቀቅ በግብጻዊው ጳጳስ አቡነ ማቴዎስ ተባርኮ ቅዳሴ ቤቱ ተከብሯል። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

የተከበራችሁ የሰንበት ት/ት ቤታችን አባላት ከዚህ ቀደም ለበዓለ ደመራ ክብረ በዓል ከትርኢት አቅራቢዎች ውጪ ያሉ አገልጋዮች ከደብራችን በዕለቱ ልብሰ ስብሐት በመልበስ ወደ መስቀል አደባባይ እናመራ የነበረ ሲሆን አሁን ግን ከሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በተሰጠን አቅጣጫ መሰረት በዕለቱ የሚወጡ ዘማርያንም ቢሆኑ በአንድነት በደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ቤ/ክ የመዝሙር ጥናት ቅዳሜና እሑድ ከ ቀኑ 10:00-12:00 ስለሚከናወን ተገኝታችሁ ካላጠናችሁ  ስለተከለከለ በዕለቱ የማትሳተፉ መሆኑን አጥብቀን እናሳውቃለን። የሰ/ት/ቤታችን አባላት ጉዳይ ክፍል ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

የሐዘን መግለጫ የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባል የሆነው የወንድማችን ዳንኤል ተስፋዬ አባት ስላረፉ ስርዓተ ቀብራቸው ነገ ዛሬ መስከረም 09/2017 ዓ.ም ከቀኑ 6:00 ላይ በደብረ አሚን ተክለሃይማኖት ቤ/ክ ስለሚፈጸም የምትችሉ አባላት ቀብሩ ላይ እንድንገኝ ይሁን እንዲሁም መኖሪያ ቤታቸው በመገኘት እንድናጽናናቸው ይሁን።  የአባታችንንነፍስ ይማርልን። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

የኦርየንታል ኦርቶዶክስ እና የምሥራቅ ኦርቶዶክስ አቢያተ ክርስቲያናት የነገረ መለኮት ውይይት ከ34 ዓመታት በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ በካይሮ መካሄድ ጀመረ  ! መስከረም 7 ቀን 2016 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ) +++ ጉባኤው “የክርስቶስ ፍቅር ግድ ይለናል” (2ኛ ቆሮንቶስ 5፡14) በሚል መሪ ቃል በእምነት እና  እና በአገልግሎት እና በማኅበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተካሂደዋል፤ ጉባኤው ትናንትና እና ዛሬ በግብጽ ቅዱስ ቢሾይ ገዳም “ሎጎስ” የስብሰባ ማዕከል መካሄድ የጀመረ ሲሆን በኦሪየንታል ኦርቶዶክስ አቢያተ ክርስቲያናት እና በምሥራቅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን መካከል ይፋዊ የነገረ መለኮት ውይይት በዚህ ስብሰባ ተካሂዷል። ዓላማው ከ30 ዓመታት በላይ የተቋረጠውን ይፋዊ የሥነ-መለኮት ንግግር እንደገና ለመቀጠል እና እንደገና ለመገምገም መሆኑን የግብጽ ቤተ ክርስቲያን አስታውቃለች። ጉባኤው የተከፈተው በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ታዋድሮስ ዳግማዊ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር እና በፓትርያርክ አቡነ በርተሎሜዎስ ቀዳማዊ፣ መልእክት ነው። በስብሰባው ላይ በሁለቱ አቢያተ ክርስቲያናት ቤተሰቦች ላይ የሚነሱ ልዩ ልዩ የአስተምህሮ ጉዳዮች ወደ አንድ ወጥ አቋም ለመድረስ በማለም በዚሁ ልክ ውይይት መደረጉ ነው የተገለጸው። የምሥራቃውያን ኦርቶዶክስ አቢያተ ክርስቲያናት ልዑካንን ጨምሮ በጉባኤው  የአሌክሳንድርያ ኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ፓትርያርክ (አስተናጋጅ ቤተ ክርስቲያን)፣ የአንጾኪያ እና የመላው ምሥራቅ ፓትርያርክ (ሶርያ )፣ የአርመን ኦርቶዶክስ፣ የኦርቶዶክስ የኢትዮጵያ የኤርትራ አቢያተ ክርስቲያናት መወከላቸውን የግብፅ ቤተ ክርስቲያን ገልጻለች። ©ተ.ሚ.ማ ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

አስቸኳይ የስራ ማስታወቂያ ..................................... የስራ መደብ:- ኤዲተር የት/ደ:- ኤዲቲንግ ፎቶሾፕ የተማረ/ች የስራ ልምድ :- በማተሚያ ቤት የሰራ/ች ብዛት :- 1(አንድ) ቦታ:- ተክለሃይማኖት ስልክ:-0931144444 ደሞዝ:- በስምምነት ማሳሰቢያ:- የሰንበት ት/ትቤታችን አባላት የሆናችሁና የስራ ዕድል ሲመጣልን እንድናገናኝዎ የምትፈልጉ ወይም ይህ መረጃ የሚያደርሳቸውና የሚያስፈልጋቸውን አባላት የምታውቁ ከታች በተቀመጡ ስልኮች በመደወል እንዲያስመዘግቡ በትህትና እንጠይቃለን። 0966-25-87-38 ዮሐንስ ትዳሩ 0912-41-97-72 ዮናስ እርዳው የበጎ አድራት ክፍል ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com