en
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

Open in Telegram

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

Show more
2 632
Subscribers
+124 hours
+227 days
+5430 days
Posts Archive
የቅዱስ ፓትርያርክ የጾመ ፍልሰታ መልእክት በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! በሀገር ውስጥና በተለያዩ ክፍለ ዓለማት የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት በሙሉ! በማሕፀነ ማርያም በፈጸመው እውነተኛ ተዋሕዶ የሰው ልጅን ከኃሣር ወደ ክብር የመለሰ እግዚአብሔር አምላካችን፣ እንኳን ለሁለት ሺሕ አሥራ ስድስት ዓመተ ምሕረት ጾመ ቅድስት ማርያም በደኅና አደረሰን አደረሳችሁ! ‹‹ተፈሥሒ ኦ ምልእተ ጸጋ፣ ተፈሥሒ እስመ ረከብኪ ሞገሰ በኀበ እግዚአብሔር፡- ምልእተ ጸጋ ሆይ ደስ ይበልሽ፤ በእግዚአብሔ ዘንድ ሞገስን አግኝተሻልና ደስ ይበልሽ›› ሉቃ. 1÷ 28-30" የክብር አምላክ እግዚአብሔር የሰው ልጅን ከወደቀበት ዐዘቅተ ኵነኔ የሚያድንበት ዕድል እንዳዘጋጀ በብሉይ ኪዳን በስፋት ተገልጿል፤ የማዳን ሥራውም ከሰው ወገን ከሆነች ቅድስት ድንግል በሚወለደው መሲሕ እንደሚፈጸም አስረድቶአል፤ የማዳን ቀኑ በደረሰ ጊዜም መልእክቱን በፊቱ በሚቆመው በቅዱስ ገብርኤል በኩል ልኳል፤ ቅዱስ ገብርኤልም የተነገረውን መልእክት ለድንግል ማርያም አድርሶአል፡፡ ቅዱስ ገብርኤል ለድንግል ማርያም እንዲነግር ከታዘዘባቸው መካከል ‹‹ጸጋን የተመላሽ ደስተኛይቱ ሆይ÷በእግዚአብሔር ዘንድ ሞገስን አግኝተሻልና ደስ ይበልሽ›› የሚል አስደናቂ መልእክት ይገኝበታል፡፡ የተወደዳችሁ ሕዝበ ክርስቲያን! ከእግዚአብሔር መንጭቶ በቅዱስ ገብርኤል በኩል ለድንግል ማርያም የተነገረ ይህ መልእክት፣ የቅድስት ድንግል ማርያምን ክብር ከመግለጽ ባሻገር ለሰው ልጆች ሁሉ ያለው ፋይዳ በእጅጉ የላቀ ነው፤ ‹‹ጸጋ›› የሚለው ቃል እንደ ቅዱስ መጽሐፍ አስተምህሮ ያልተወሰነ፣ ገደብና ቅድመ ሁኔታ የሌለው ስጦታን ሲያመለክት ‹‹ሞገስ›› የሚለው ቃል ደግሞ ተወዳጅነትን ተደማጭነትን ተሰሚነትን የሚያመለክት የክብርና የባለሟልነት መግለጫ ቃል ነው፡፡ እነዚህ ቃላት ከእግዚአብሔር ዘንድ በቅዱስ ገብርኤል በኩል ለቅድስት ድንግል ማርያም ተነግረዋል፤ የእግዚአብሔር ቃል የማይለወጥ ነውና ቃላቶቹ ለድንግል ማርያም ቃል ኪዳን ሆነው የተሰጡ ናቸው፤ የተሰጡበትም ምክንያት ሰውን ለማዳን ሥራ እንዲውሉ እንጂ ለሌላ አይደለም፡፡ ምክንያቱም የእግዚአብሔር የማይናወጥ ፈቃድ ሰውን ማዳን ነውና፤ በመሆኑም ቅድስት ድንግል ማርያም ከእግዚአብሔር በተሰጣት በዚህ ገደብ የሌለው ቃል ኪዳኗ ሰውን ልትታደግ በቅታለች፤ይህም በቃና ዘገሊላ ባደረገችው ምልጃ በጭንቀት የተዋጡትን ሰርገኞች እንዴት እንደታደገች በቅዱስ ወንጌል ተጽፎ እናገኘዋለን፤ ቅድስት ድንግል ማርያም ቀድሞውኑም ከፍ ያለ ሞገስ ተሰጥቶአታልና የሰርጉ አሳላፊዎችን ‹‹የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ›› በማለት ስታዝዝ እናያለን፤ ይህ ለሰው ልጆች ሁሉ የተሰጠ አስደናቂ የትድግና ስጦታ ነው፡፡ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን! የድንግል ማርያም የጸጋ ስጦታ በብሥራተ ገብርኤል ተገልጾ፣ በቃና ዘገሊላ ተተግብሮ በዕለተ ስቅለት ‹‹እነሆ ልጅሽ፣ እነኋት እናትህ›› በሚል መለኮታዊ ማኅተም የታተመ ነው፤ ይህ ቃል እሷ እናታችን መሆኗን፤ እኛም ልጆችዋ መሆናችንን ያረጋገጠ ማኅተመ ቃል ኪዳን ነው፤ የቃል ኪዳኑ ይዘት እሷ በአማላጅነቷ እንደ ልጅ ልትንከባከበን እኛም እንደ እናት  ልናከብራትና ልንማፀናት የሚገባን መሆኑን ያሳያል፤ የእናትነትና የልጅነት ማረጋገጫ የሆነ ይህንን የቃል ኪዳን ማኅተም ሊሰርዝም ሆነ ሊፍቅ ሊደመስስም የሚችል ኃይል የለም፡፡ ይህ ጸጋና ሞገስ በምድር ብቻ ሳይሆን በሰማይም የሚቀጥል እንጂ የሚገደብ አይደለም፤ ሞት፣ ቦታና ዘመንም አይወስኑትም፤ ምክንያቱም የእግዚአብሔር ቃል ኪዳን በሞት በቦታና በዘመን አይገደብምና ነው፤ ‹‹ኪዳኑንም ለዘለዓለም ያስባል›› ተብሎ የተገለጸውም ለዚህ ነው፤ (መዝ. )111÷5) መንፈስ ቅዱስም በእሷ አንደበት ‹‹እነሆ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ነሽ ይሉኛል›› በማለት የተናገረው ይህንን ለማስረዳት እንደሆነ ማስተዋል ያሻል፡፡ በእግዚአብሔር  ተሰጥቶ፣ በቃል ኪዳን ታትሞ፣ በቅዱስ ገብርኤል ተብራርቶ፣ በጌታችን ተረጋግጦና በሐዋርያት በኩል የተላለፈልን፣ ሰውን ማዳን ግቡ የሆነ የድንግል ማርያም ምልጃ ጥንታዊት፣ ሐዋርያዊት፣ በሁሉ ያለች፣ አንዲትና ቅድስት ኦርቶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ለሁለት ሺሕ ዓመታት ያህል አምና እና ተቀብላ ስትጠቀምበት ኖራለች፤ አሁንም በዚሁ ትቀጥላለች፡፡ በኦርቶዶክሱ ዓለም ዛሬ የሚጀመረው የጾመ ማርያም ሱባዔም የዚሁ ጭብጥ ማሳያ ነው፤ ዋናው መልእክቱም ድንግል ማርያም በተሰጣት ጸጋና ሞገስ በጸሎቷ ከእግዚአብሔር ዘንድ ምሕረትንና ይቅርታን የምታሰጠን ስለሆነች እሷን በመማፀን ወደ እግዚአብሔር እንቅረብ የሚል ሆኖ ይመሰጠራል፡፡ የተወደዳችሁ ሕዝበ ክርስቲያን ልጆቻችን! ጾም ፈቃደ ሥጋን በማድከምና ፈቃደ ነፍስን በማጎልበት ምሕረተ እግዚአብሔር መሻታችንን የምናሳይበት መንፈሳዊ ማመልከቻ ነው፤ ጾም ከጥንት ጀምሮ የነበረ ከእግዚአብሔር ጋር የሚያገናኝ ድልድይ ነው፤ ቀደምት አበው በጾም ምክንያት ከጥፋት ድነዋል፤ የለመኑትንም አግኝተዋል፤ ምስጢርም ተገልጾላቸዋል፤ ዲያብሎስም ድል አድርገውበታል፡፡ እኛም ዛሬ ጾምን ስንጾም በሀገራችንም ሆነ በአካባቢያችን ብሎም በዓለም ዙሪያ ሁሉ ስጋትን እየጫረ ያለው የጥፋት እንቅስቃሴ እግዚአብሔር እንዲያስቆምልን ከልብ በመጸለይ ሊሆን ይገባል፤ ይህንንም ስናደርግ በጸሎት ብቻ ሳይሆን ንስሐ በመግባትና ቅዱስ ቁርባንን በመቀበል እንደዚሁም የሰላም የፍቅርና የዕርቅ ሰው ሆኖ በእግዚአብሔር ፊት በመቆም ሊሆን ይገባል፡፡ ችግሮችንና አለመግባባቶችን በሰላማዊ መንገድ በውይይትና በምክክር ለመፍታት የሚደረገው ጥረትም በእጅጉ ሊደገፍ ይገባል፤ ግጭትና ጦርነት ከሚያጠፋን በቀር ሊያተርፍልን የሚችል አንዳች ጥቅም የለም፡፡ በመሆኑም በየትኛውም የሀገራችን አካባቢ ያላችሁ ልጆቻችን እባካችሁ ለሰላም ለውይይትና ለሰው ልጆች መብት መከበር ቅድሚያ ስጡ፤ ግድያ፣ ዕገታ፣ አብያተ ሃይማኖትን መዳፈር፣ ዘረፋና ቅሚያ፣ የሴት ልጅን መድፈርና ሰውን ማንገላታት አቁሙ፤ እነዚህ ድርጊቶች ሰብአዊነትን ዝቅ የሚያደርጉ፣ እግዚብሔርን የሚያስቆጡ፣ በታሪክም የሚያሳፍሩ ናቸው፤ እነዚህን ሳናርም   የምንጾመው ጾም ትርጉም ስለሌለው ንስሐ ገብተን ከእንደዚህ ያለው ድርጊ ርቀን ጾሙን መጾም ይገባል፤ ይህን ስናደርግ ጾማችን በእግዚአብሔር ፊት ዋጋ ይኖረዋል፡፡ በመጨረሻም የኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ በተለይም በጾመ ማርያም ሱባዔ በንስሐና በጸሎት የሚያሳልፉ ሕዝበ ክርስቲያን ስለ ሃይማኖት መጠበቅ፣ ስለሀገር ሰላምና አንድነት፣ እንደዚሁም ስለሕዝቦች ደኅንነትና ጤንነት አጥብቀው እንዲጸልዩ በእግዚአብሔር ስም መልእክታችንን እናስተላልፋለን፡፡ መልካም የሱባዔ ወቅት ያድርግልን እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ! ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ነሐሴ 1 ቀን 2016 ዓ.ም ዋሽንግተን ዲሲ - ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ የቴሌግራም ቻናላችን https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

በሰንበት ትምህርት ቤታችን የብርሃን መንገድ ለልጆቻችን በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ልዩ ጉባኤ ተከናወነ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። h
+4
በሰንበት ትምህርት ቤታችን የብርሃን መንገድ ለልጆቻችን በሚል ርዕስ የተዘጋጀው  ልዩ ጉባኤ ተከናወነ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

በሰንበት ትምህርት ቤታችን የተዘጋጀው የብርሃን መንገድ ለልጆቻችን / ወላጆች ልዩ ጉባኤ ተከናወነ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። ht
+4
በሰንበት ትምህርት ቤታችን የተዘጋጀው የብርሃን መንገድ ለልጆቻችን / ወላጆች ልዩ ጉባኤ ተከናወነ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

መደበኛ የቅዳሜ ትምህርት (ክርስቲያናዊ ሕይወት)በሚል ርዕስ በመ/ር ያሬድ ጥላሁን ክፍል ሦስት ሐምሌ 27/2016 ይሰጣል አባላት ትምህርት መማሯን ማረጋገጫ ከሰ/ት/ቤቱ የሚፈልጉ ከሆነ ተከታታይ የሚ
መደበኛ የቅዳሜ ትምህርት (ክርስቲያናዊ ሕይወት)በሚል ርዕስ በመ/ር ያሬድ ጥላሁን ክፍል ሦስት ሐምሌ 27/2016 ይሰጣል አባላት ትምህርት መማሯን ማረጋገጫ ከሰ/ት/ቤቱ የሚፈልጉ ከሆነ ተከታታይ የሚሰጠውን ትምህርት ይማሩ  በጊዜ በመገኘት የድርሻችንን እንወጣ። ቦታ በጸበል ቤት አዳራሽ ሰዓት 11:30 ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ውሉደ ፍኖተ ብርሃን ሆይ የእህታችሁን የሣምራዊት ዓለሙን የህክምና ወጪ ለመቻል ከመረባረብ ጀምሮ ሁል ጊዜ ከጎኗ ባለመለየት ስታበረታቱ በመቆየ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።    ውሉደ ፍኖተ ብርሃን ሆይ የእህታችሁን የሣምራዊት ዓለሙን የህክምና ወጪ ለመቻል ከመረባረብ ጀምሮ ሁል ጊዜ ከጎኗ ባለመለየት ስታበረታቱ በመቆየታችሁ ኋላም በዕረፍቷ እኔን ወንድማችሁን እና መላ ቤተሠቡን ለማጽናናት በብዙ በመድከማችሁ እጅግ የከበረ ምስጋናዬን በልዑል እግዚአብሔር ስም እያቀረብኩ ዛሬ የእህታችሁ የ40 ቀን መታሠቢያ ነውና ከአቡነ ዘበሠማያት ጋር ነፍሰ ወለተ መስቀልን ማርልን እያላችሁ በጸሎት አስቡልኝ።           እግዚአብሔር ይስጥልኝ። ወንድማችሁ እንግዳወርቅ አረፋይኔ + + + + + + + + የእህታችን ሣምራዊት አለሙ ዛሬ የ40 ቀን መታሰቢያ ነው ሰማይን ያለ ባለ ምድርን ያለካስማ አጽንቶ ያቆመ የአባቶቻችን አምላክ ቅዱስ እግዚአብሔር የእህታችንን ነፍስ ይማርልን በደጋጎቹ በአብርሃም በይስሐቅ በያዕቆብ አጠገብ ያስቀምጥልን። ቸርና መሐሪ የሆነ አምላካችን ለነፍሷ ዘለዓለማዊ እረፍትን ይስጥልን። ኑ እናንት የአባቴ ብሩካን ተርቤ አብልታችሁኛል ተጠምቼም አጠጥታችሁኛል ታርዤ አልብሳችሁኛልና ዓለም ሳይፈጠር ጀምሮ የተዘጋጀላችሁን መንግስቴን ውረሱ ብሎ በቀኝ ከሚያደርጋቸው ጻድቃን ይደምርልን።                 ፍኖተ ብርሃን ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

የመጥሪያ ካርድ የብርሃን መንገድ ለልጆቻችን / ወላጆች ለልጆቻችሁ ስለወደፊቱ የብርሃን መንገድ ለማዘጋጀት በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ልዩ ጉባኤ ተዘጋጀ ወላጆች በጎ አድራጊዎች የቤተ ክርስቲያ
+1
የመጥሪያ ካርድ የብርሃን መንገድ ለልጆቻችን / ወላጆች ለልጆቻችሁ ስለወደፊቱ  የብርሃን መንገድ ለማዘጋጀት በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ልዩ ጉባኤ ተዘጋጀ ወላጆች በጎ አድራጊዎች የቤተ ክርስቲያን የቁርጥ ቀን ልጆች ወዴት አላችሁ? በያላችሁበት ቦታ ሆናችሁ በሚገጥማችሁ ሐዘን እና ደስታ ሁሌም የምታስታውሱት ቤተክርስቲያንን ነው ማንኛውም ጉዳይ በገጠመን ጊዜ መሸሸጊያችን በልቅሷችን ሳቃችንን የምትመልስ በስብራታችን ማንነታችንን የምትጠግን ቤተክርስቲያናችን ትጣራለች ያኔ ጥንት ባሰብናት ጊዜ አለቀስን ብረሳሽ ቀኜ ትርሳሽ ባላስብሽ ምላሴ ከትናጋዬ ይጣበቅ ብላችሁ መሐላ የማላችሁ ቃል ኪዳን የገባችሁ ልታስታውሳችሁ እናታችሁ  ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የብርሃን መንገድ ለልጆቻችን በሚል ቃል ልዩ መንፈሳዊ ጉባኤ  ሐምሌ 28/2016ዓ.ም ከ9:30_12:30 አዘጋጅታ ትጠራችኋለች የመልአኩ የቅዱስ ሚካኤል ወዳጆች ይህ መጥሪያ እጃችሁ ከደረሰ ቅዱስ ሚካኤል ከእናንተ ጋር ለእናንተ መልእክት እንዳለሁ አስባችሁ በቀኑ እና በሰዓቱ እንድትባረኩ ዕጣ እንደወጣለት፤ ሎተሪ እንደ ደረሰው እድለኛ በደስታ  እንዲገኙ ሐምሌ 28 ከቀኑ 9:30 እንዳይቀሩ ተጠርተዋል።                የፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

መደበኛ የቅዳሜ ትምህርት (ክርስቲያናዊ ሕይወት )በሚል ርዕስ ክፍል ሦስት ትምህርት በመ/ር ያሬድ ጥላሁን ይሰጣል እኛ አባላትም በጊዜ በመገኘት የድርሻችንን እንወጣ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ
መደበኛ የቅዳሜ ትምህርት (ክርስቲያናዊ ሕይወት )በሚል ርዕስ ክፍል ሦስት ትምህርት  በመ/ር ያሬድ ጥላሁን ይሰጣል እኛ  አባላትም በጊዜ በመገኘት የድርሻችንን እንወጣ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc

የመጥሪያ ካርድ የብርሃን መንገድ ለልጆቻችን / ወላጆች ለልጆቻችሁ ስለወደፊቱ  የብርሃን መንገድ ለማዘጋጀት በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ልዩ ጉባኤ ተዘጋጀ ወላጆች በጎ አድራጊዎች የቤተ ክርስቲያን የቁርጥ ቀን ልጆች ወዴት አላችሁ? በያላችሁበት ቦታ ሆናችሁ በሚገጥማችሁ ሐዘን እና ደስታ ሁሌም የምታስታውሱት ቤተክርስቲያንን ነው ማንኛውም ጉዳይ በገጠመን ጊዜ መሸሸጊያችን በልቅሷችን ሳቃችንን የምትመልስ በስብራታችን ማንነታችንን የምትጠግን ቤተክርስቲያናችን ትጣራለች ያኔ ጥንት ባሰብናት ጊዜ አለቀስን ብረሳሽ ቀኜ ትርሳሽ ባላስብሽ ምላሴ ከትናጋዬ ይጣበቅ ብላችሁ መሐላ የማላችሁ ቃል ኪዳን የገባችሁ ልታስታውሳችሁ እናታችሁ  ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የብርሃን መንገድ ለልጆቻችን በሚል ቃል ልዩ መንፈሳዊ ጉባኤ  ሐምሌ 28/2016ዓ.ም ከ9:30_12:30 አዘጋጅታ ትጠራችኋለች የመልአኩ የቅዱስ ሚካኤል ወዳጆች ይህ መጥሪያ እጃችሁ ከደረሰ ቅዱስ ሚካኤል ከእናንተ ጋር ለእናንተ መልእክት እንዳለሁ አስባችሁ በቀኑ እና በሰዓቱ እንድትባረኩ ዕጣ እንደወጣለት፤ ሎተሪ እንደ ደረሰው እድለኛ በደስታ  እንዲገኙ ሐምሌ 28 ከቀኑ 9:30 እንዳይቀሩ ተጠርተዋል።                የፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

በዩቲዩብ ሊንኩ በመግባት ዝማሬውን ያዳምጡ

" የስሙ ምስክር " | አዲስ ዝማሬ | ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የፍኖተ ብርሃን ሰ... https://youtube.com/watch?v=89NGmkNBgX4&si=wAJnATSzRJxcNky1

የመጥሪያ ካርድ የብርሃን መንገድ ለልጆቻችን / ወላጆች ለልጆቻችሁ ስለወደፊቱ  የብርሃን መንገድ ለማዘጋጀት በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ልዩ ጉባኤ ተዘጋጀ ወላጆች በጎ አድራጊዎች የቤተ ክርስቲያን የቁርጥ ቀን ልጆች ወዴት አላችሁ? በያላችሁበት ቦታ ሆናችሁ በሚገጥማችሁ ሐዘን እና ደስታ ሁሌም የምታስታውሱት ቤተክርስቲያንን ነው ማንኛውም ጉዳይ በገጠመን ጊዜ መሸሸጊያችን በልቅሷችን ሳቃችንን የምትመልስ በስብራታችን ማንነታችንን የምትጠግን ቤተክርስቲያናችን ትጣራለች ያኔ ጥንት ባሰብናት ጊዜ አለቀስን ብረሳሽ ቀኜ ትርሳሽ ባላስብሽ ምላሴ ከትናጋዬ ይጣበቅ ብላችሁ መሐላ የማላችሁ ቃል ኪዳን የገባችሁ ልታስታውሳችሁ እናታችሁ  ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የብርሃን መንገድ ለልጆቻችን በሚል ቃል ልዩ መንፈሳዊ ጉባኤ  ሐምሌ 28/2016ዓ.ም ከ9:30_12:30 አዘጋጅታ ትጠራችኋለች የመልአኩ የቅዱስ ሚካኤል ወዳጆች ይህ መጥሪያ እጃችሁ ከደረሰ ቅዱስ ሚካኤል ከእናንተ ጋር ለእናንተ መልእክት እንዳለሁ አስባችሁ በቀኑ እና በሰዓቱ እንድትባረኩ ዕጣ እንደወጣለት፤ ሎተሪ እንደ ደረሰው እድለኛ በደስታ  እንዲገኙ ሐምሌ 28 ከቀኑ 9:30 እንዳይቀሩ ተጠርተዋል። የፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

የመጥሪያ ካርድ የብርሃን መንገድ ለልጆቻችን / ወላጆች ለልጆቻችሁ ስለወደፊቱ የብርሃን መንገድ ለማዘጋጀት በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ልዩ ጉባኤ ተዘጋጀ ወላጆች በጎ አድራጊዎች የቤተ ክርስቲያ
የመጥሪያ ካርድ የብርሃን መንገድ ለልጆቻችን / ወላጆች ለልጆቻችሁ ስለወደፊቱ  የብርሃን መንገድ ለማዘጋጀት በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ልዩ ጉባኤ ተዘጋጀ ወላጆች በጎ አድራጊዎች የቤተ ክርስቲያን የቁርጥ ቀን ልጆች ወዴት አላችሁ? በያላችሁበት ቦታ ሆናችሁ በሚገጥማችሁ ሐዘን እና ደስታ ሁሌም የምታስታውሱት ቤተክርስቲያንን ነው ማንኛውም ጉዳይ በገጠመን ጊዜ መሸሸጊያችን በልቅሷችን ሳቃችንን የምትመልስ በስብራታችን ማንነታችንን የምትጠግን ቤተክርስቲያናችን ትጣራለች ያኔ ጥንት ባሰብናት ጊዜ አለቀስን ብረሳሽ ቀኜ ትርሳሽ ባላስብሽ ምላሴ ከትናጋዬ ይጣበቅ ብላችሁ መሐላ የማላችሁ ቃል ኪዳን የገባችሁ ልታስታውሳችሁ እናታችሁ  ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የብርሃን መንገድ ለልጆቻችን በሚል ቃል ልዩ መንፈሳዊ ጉባኤ  ሐምሌ 28/2016ዓ.ም ከ9:30_12:30 አዘጋጅታ ትጠራችኋለች የመልአኩ የቅዱስ ሚካኤል ወዳጆች ይህ መጥሪያ እጃችሁ ከደረሰ ቅዱስ ሚካኤል ከእናንተ ጋር ለእናንተ መልእክት እንዳለሁ አስባችሁ በቀኑ እና በሰዓቱ እንድትባረኩ ዕጣ እንደወጣለት፤ ሎተሪ እንደ ደረሰው እድለኛ በደስታ  እንዲገኙ ሐምሌ 28 ከቀኑ 9:30 እንዳይቀሩ ተጠርተዋል።                የፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

የመጥሪያ ካርድ የብርሃን መንገድ ለልጆቻችን / ወላጆች ለልጆቻችሁ ስለወደፊቱ  የብርሃን መንገድ ለማዘጋጀት በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ልዩ ጉባኤ ተዘጋጀ ወላጆች በጎ አድራጊዎች የቤተ ክርስቲያን የቁርጥ ቀን ልጆች ወዴት አላችሁ? በያላችሁበት ቦታ ሆናችሁ በሚገጥማችሁ ሐዘን እና ደስታ ሁሌም የምታስታውሱት ቤተክርስቲያንን ነው ማንኛውም ጉዳይ በገጠመን ጊዜ መሸሸጊያችን በልቅሷችን ሳቃችንን የምትመልስ በስብራታችን ማንነታችንን የምትጠግን ቤተክርስቲያናችን ትጣራለች ያኔ ጥንት ባሰብናት ጊዜ አለቀስን ብረሳሽ ቀኜ ትርሳሽ ባላስብሽ ምላሴ ከትናጋዬ ይጣበቅ ብላችሁ መሐላ የማላችሁ ቃል ኪዳን የገባችሁ ልታስታውሳችሁ እናታችሁ  ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የብርሃን መንገድ ለልጆቻችን በሚል ቃል ልዩ መንፈሳዊ ጉባኤ  ሐምሌ 28/2016ዓ.ም ከ9:30_12:30 አዘጋጅታ ትጠራችኋለች የመልአኩ የቅዱስ ሚካኤል ወዳጆች ይህ መጥሪያ እጃችሁ ከደረሰ ቅዱስ ሚካኤል ከእናንተ ጋር ለእናንተ መልእክት እንዳለሁ አስባችሁ በቀኑ እና በሰዓቱ እንድትባረኩ ዕጣ እንደወጣለት፤ ሎተሪ እንደ ደረሰው እድለኛ በደስታ  እንዲገኙ ሐምሌ 28 ከቀኑ 9:30 እንዳይቀሩ ተጠርተዋል። የፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

አቡነ ጴጥሮስ ሰማዕት (ኢትዮጵያዊ) በዚህች ዕለት ኢትዮጵያዊው ሰማዕት ብጹዕ አቡነ ጴጥሮስ በሰማዕትነት አረፉ፡፡ የ20ኛው ክፍለ ዘመን ታላቅ ሰማዕት የሆኑት አቡነ ጴጥሮስ በ1875 ዓ.ም በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሰላሌ አውራጃ ፍቼ ከተማ ተወለዱ፡፡ አቡነ ጴጥሮስ በሰማዕትነት እንደሚሞቱ አስቀድመው መምህራቸው በትንቢት ነግረዋቸው ነበር፡፡ ‹‹አለቃ ተጠምቀ›› የተባሉ ቅድስናን ከሊቅነት ጋራ አስተባብረው የያዙ የቅኔ መምህራቸው አንድ ቀን አቡነ ጴጥሮስን ጠርተው «ኀይለ ማርያም አንተ ወደፊት ጳጳስ ትሆናለህ፤ በወቅቱም አረመኔ በዚህች ሀገር ይሠለጥናል፡፡ ታዲያ ያኔ አንተ ለነፍስህ ሳትሳቀቅ በሰማዕትነት እለፍ፤ ሰማዕትነት ክፍልህ ነው፣ አደራ›› ብለዋቸው ነበር፡፡ ይኸውም ትንቢት ደርሶ አቡነ ጴጥሮስ በሰማዕትነት ለማረፍ በቅተዋል፡፡ ብፁዕ አባታችን የጵጵስና ስማቸውን ከማግኘታቸው በፊት መመህር ኀይለ ማርያም ይባሉ ነበር፡፡ በልጅነታቸው ወላጆቻቸው ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም በመውሰድ በሃይማኖትና በምግባር ተኮትኩተው እንዲያድጉ አድርገዋቸዋል፡፡ የቤተ ክርስቲያኗን ሥርዓተ ትምህርት ከንባብ እስከ ቅኔ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች በመዘዋወር ብሉያትን ሐዲሳትን ዜማን ጨምሮ ሌሎች የሊቃውንት ትምህርቶች ተምረዋል፡፡ በ1910 ዓ.ም ወደ ደብረ ሊባኖስ በመምጣት ሥርዓተ ምንኩስናን ፈጸሙ፡፡ ከዚያም መምህርነት ተሹመው ደብረ መንክራት ምሑር ኢየሱስ ገዳም ሄደው ለ6 ዓመታት ካስተማሩ በኋላ በ1916 ዓ.ም እንደገና በዝዋይ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ገዳም በመምህርነት ተሹመው ለ3 ዓመታት አገልግለዋል፡፡ በ1919 ዓ.ም ወደ አ.አ በመምጣት የመንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ መምህርና በቤተ መንግሥት የግርማዊ ቀዳማዊ ኀይለ ሥላሴ የንስሓ አባት ሆኑ፡፡ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ በራሷ ተወላጅ ጳጳሳት ልጆቿ እንድትመራ ከ1600 ዓመታት በኋላ ስለተፈቀደላት ከዚህ በኋላ በሃይማኖታቸውና በስነ ምግባራቸው የተመሰከረላቸው አምስት ደጋግ አባቶች ሲመረጡ አንዱ አቡነ ጴጥሮስ ነበሩ፡፡ በዚህም መሠረት ኢትዮጵያ ለመጀመርያ ጊዜ የራሷን ጳጳስ ስትሾም አቡነ ጴጥሮስ ግንቦት 18 ቀን 1921 ዓ.ም ጵጵስና ተሾሙ፡፡ ከዚህም በኋላ ብፁዕ አባታችን ‹‹አቡነ ጴጥሮስ ጳጳስ ዘምሥራቀ ኢትዮጵያ ተላዌ አሠሩ ለአቡነ ኢየሱስ ሞዐ›› ተብለው በያኔው መንዝና ወሎ ሀገረ ስብከት ተሾሙ፡፡ ብፁዕ አባታችንም ቅድስት ቤተ ክርስቲያንንና ቅድስት ሀገራችን በጸሎታቸው፣ ሕዝቡን በትምህርታቸው እየጠበቁ በተጋድሎ እየኖሩ ሳለ አረመኔው የኢጣሊያ ፋሺስት በ1928 ዓ.ም በኢትዮጵያ ላይ የግፍ ጦርነትን አውጆ ሕዝቡን በግፍ ይገድል ቤተ ክርስቲያንን ያቃጥል ጀመር፡፡ በየገዳማቱ እጅግ በርካታ ካህናትና መነኮሳት ተገደሉ፣ ብርቅዬ የቤተ ክርስቲያን ቅርሶች ተዘረፉ፡፡ አቡነ ጴጥሮስም ይህንን ግፍ በማየታቸው ከሀገራችን አርበኞች ጋር በመሆን በጸሎታቸው ሊዋጉት ተነሡ፡፡  ‹‹ሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም አቡነ ጴጥሮስ ተይዘው ወደ ግራዚያኒ ቀረቡ፡፡  ‹‹ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ቁመታቸው ረዘም፣ ፊታቸው ዘለግ ያለ፣ መልካቸው ጠየም ያለ፣ ዐዋቂነታቸውና ትሕትናቸው ከገጻቸው የሚነበብ ሲሆን በዚህ ጊዜ ለብሰውት የነበረው ልብሰ ጵጵስና ጥቁር ካባ ያውም በጭቃ የተበከለ ነበር፡፡ በዚህ ሁኔታ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ወደ ችሎት ቀረቡ፡፡ አቡነ ጴጥሮስም በእኔ ላይ የፈለጋችሁትን አድርጉ፡፡ ተከታዮቼን ግን አትንኩ» አሉ፡፡ ‹‹ይህንንም ብለው በጥይት ተደብድበው ሲገደሉ እንዲመለከት ተጋብዞ ለተሰበሰበው ሕዝብ የሚከተለውን ሕያው መልእክት አስተላለፉ፡-     "አረማዊ የሆነው የፋሺስት መንግሥት ቤተ ክርስቲያንን ለማቃጠል፣ ሕዝበ ክርስቲያንን ለመግደል፣ ሃይማኖትን ለማጥፋት፣ ታሪካችንን ለማበላሸት የመጣ ነው፤ እንጂ በጎ ለመሥራት ስላልመጣ ለዚህ ለግፈኛ አትገዙ፡፡ ስለ ውድ ሃገራችሁ፣ ስለ ቀናች ሃይማኖታችሁ ተከላከሉ፡፡ ነጻነታችሁ ከሚረክስ ሞታችሁ ስማችሁ ቢቀደስ ታላቅ ዋጋ ያለው ክብር ታገኛላችሁ፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለዚህ ለጠላት እንዳይገዛ አውግዣለሁ፤ የኢትዮጵያ መሬት ጠላትን ብትቀበል የተረገመች ትሁን፡፡ በፈጣሪዬ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም የተገዘተች ትሁን" ብለው አወገዙ፡፡ ቀጥሎም ብፁዕነታቸው በፍጥነት ችሎት ላይ እንዳሉ ሕዝቡ ሁሉ ስለ እርሳቸው እያዘነ ሳለ መስቀላቸውን አውጥተው እየጸለዩ ሕዝቡን ባረኩ፡፡ በዚያን ጊዜ አቡነ ጴጥሮስ የሞታቸው ሰዓት መድረሱን ዐውቀው ሰዓታቸውን ከኪሳቸው አውጥተው ተመለከቱ፡፡ የሞታቸውን ፍርድ ያነብ የነበረው ኢጣሊያዊው  ታላቅ ፍርሃትም በፊቱ ላይ ይታይ ነበር፡፡ የሞታቸው ፍርድ ከተነበበ በኋላ የፈረዱባቸውን ዳኞች ጸልየው በመስቀላቸው ባረኳቸው፡፡ ከዚህ በኋላ ሐምሌ 22/1928 ዓ.ም ብጹዕ አቡነ ጴጥሮስን በመድፍ እሩምታ በመደብደብ ሰማዕት ሆነዋል። የብጹዕ አባታችን አቡነ ጴጥሮስ በረከታቸው ይደርብን። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

በደብራችን ጽ/ጽ/ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የተዘጋጀውን ሀገር አቀፍ
+4
በደብራችን  ጽ/ጽ/ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል  ቤ/ክ  ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት  በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የተዘጋጀውን ሀገር አቀፍ  የማጠቃለያ የ4ኛ እና የ6ኛ  ክፍል ምዘና  በዛሬው እለት ማለትም በ 21/11/2016 ዓ.ም ተከናወነ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com