ማዳኑን አውሩ | ᴘʀᴏᴄʟᴀɪᴍ ʜɪꜱ ꜱᴀʟᴠᴀᴛɪᴏɴ
Open in Telegram
Thank you for your interest to join Our Telegram channel. ▫️The primary function of this channel is : ☞To proclaim our savior JESUS CHRIST through a lifestyle of praise and worship. መዝሙረ ዳዊት 96 2፤ እግዚአብሔርን አመስግኑ ስሙንም ባርኩ፥ ዕለት ዕለትም ማዳኑን አውሩ።
Show more1 241
Subscribers
No data24 hours
+57 days
+1030 days
Posts Archive
“እንደሚበርር ወፍ እንዲሁ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ኢየሩሳሌምን ይጋርዳታል፤ ይከልላታል፥ ይታደጋታል፥ አልፎም ያድናታል።”
( ኢሳይያስ 31፥5)
እንደዚህ ቃል ጌታ ለግል ህይወታችን፡ ለቤተሰባችን፡ ለወገኖቻችን እንዲሁም ለኢትዮጰያ ጌታ እንዲያደርግ እንፀልይ፡፡
መጋቢ አስፋው፡፡
✍እኔ የኮሮና ዜና የለኝም!!
**********************
❝እኔ ቃልህን ሰጥቻቸዋለሁ፤ እኔም ከዓለም እንዳይደለሁ ከዓለም አይደሉምና ዓለም ጠላቸው።ከክፉ እንድትጠብቃቸው እንጂ ከዓለም እንድታወጣቸው አልለምንም።እኔ ከዓለም እንዳይደለሁ ከዓለም አይደሉም።❞
—ዮሐንስ 17: 14-16
ይህ ቃል እንዴት ደስ እንደሚል ተመልከት፦ ኢየሱስ ከአለም እንዳልሆነ ሁሉ አንተም ከአለም አይደለህም!!
ወዳጄ፦
✍የሺዎች ሞት አሳዝኖሀል አይደል?ታዲያ እንዴት የቢልዮኖች ሞት አያሳዝንህም?
✍ሺዎች በኮሮና ሞቱ ብለሀል አይደል?ቢልዮኖች እኮ ኢየሱስን ባለማመናቸው ሞተዋል፡፡
✍እግዚአብሔር ሰውን ሞተ የሚለው በልጁ ያላመነውን እንጂ በኮሮና የሞተውን አይደለም፡፡
✍ባለማመኑ የሞተው እሱና በማመንህ ሕያው የሆንከው አንተ እኩል አብዝታችሁ የምትጮሁለት የጋራ ርዕስ የላችሁም!!
✍መልካም እረኛ ያለው በግ እና በአውሬዎች ተከቦ የሚኖር እረኛ የሌለው በግ እኩል ስለ ሞት አያወሩም!!
✍በተንዠረገገ ዛፍ ጥላ ስር ያረፈ እና በሚያቃጥል በረሀ የሚንከራተት እኩል ስለመቃጠል አያወሩም!!
✍እረኛው በእረፍት ውሀ ዘንድ የሚመራው በግና እረኛ አጥቶ በምድረበዳ የሚዋትት በግ እኩል ስለ ውሀ ጥም አያወሩም!!
✍ተስፋ ያለውና ተስፋ የሌለው እኩል አሁንስ ተስፋዬ ማነው አይሉም!!
✍በብርሃን ውስጥ ያለና በጨለማ ውስጥ ያለ እኩል በዳበሳ አይንፏቀቁም!!
✍አድራሻውን የሚያውቅ እና አድራሻውን የማያውቅ እኩል አይቅበዘበዙም!!
✍በጌታ የተወደዳችሁ ወዳጆቼ በየቀኑ ሽብርና ፍርሀት እንደሚያሰሙን የዜና አውታሮች በኮሮና የሞቱ ሰዎች ይሄን ያህል ደረሱ ፤ ዛሬ ጨመረ፤ ገና ያሻቅባል እያላችሁ ባትዘግቡ ደስ ይለኛል!!
✍እግዚአብሔር ያላወራለትን እናንተ አታውሩለት!!
✍እግዚአብሔር ዜና ያለላደረገውን አንተ ዜና አታድርገው!!
✍ 2፡00 ጠብቀህ ከምትሰማው ዜና በላይ የምታሰማው ዜና አለህ!!
✍አለም ስለሞት ብትነግርህ አይግረምህ!!ያላትን ነው የምትናገረው!!ሕይወት ያለው አንተ ጋር ነው!!አለም እየሞትኩ ነው ስትልህ አንቺን ሊያድን እንዲሁ ወዶሽ የሞተ መድኃኒት-ለአለም አለልሽ በላት!!
✍ደጋግመህ ስለ ኢየሱስ አውራ፣ አሁንም አሁንም ስለ ኢየሱስ አውራ፣ መላልሰህ ስለ ኢየሱስ አውራ፣ ሳትሰለች ስለ ኢየሱስ አውራ፣ ቆየት ብለህም ስለ ኢየሱስ አውራ፣ ከእንቅልፍህ ስትነቃ ስለ ኢየሱስ አውራ፣ ስትበላም ስለ ኢየሱስ አውራ፣ ልታወራ ስትል ስለ ኢየሱስ አውራ፣ ስታወራም ስለ ኢየሱስ አውራ፣ ወሬህን ስትጨርስም ስለ ኢየሱስ አውራ፣ ልትተኛም ስትል ስለ ኢየሱስ አውራ!!አውራ!!አውራ!!አውራ!!.......አውራ ዜና ኢየሱስ ነው!!
✍የምትዘግቡትን ዛሬ ምረጡ፡፡ እኔና ቤቴ ግን ኢየሱስን እንዘግባለን!!
#ሄኖክ_አሸብር
ሰላም ነው ከጌታ ጋር
#Telegram_worship_channel
Join for more @hymnsofmes
#ስሲተጉ_የሚያገኛቸው
#Telegram_worship_channel
Join for more @hymnsofmes
*STAY AT HOME*
👉 1) Q: When the flood arrived ... Where were Noah and his family?
*A: At home*
👉 2) Q: When the three angels visited Abraham where was he?
*A: At home*
👉 3) Q: When the two angels went to Sodom and Gomorrah, where was Lot?
*A: At home*
👉 4) Q: When the angel killed the firstborn in Egypt, where were the Israelites?
*A: At home*
👉 5) Q: Where were the apostles of Jesus when they received the Holy Spirit?
*A: At home*
👉 6) Q: Where was Paul when he was visited by Ananias?
*A: At home*
👉 7) Q: Where was Rahab when the walls of Jericho fell?
*A: At home*
👉8. At the Annunciation when the Angle visited Mary she was at Home.
👉9. When the Angle visited Joseph in a dream he was at Home.
👉 10. Q: And now, where should we stay to protect ourselves from the Corona virus?
*A: At home*
*Really, Really, let's stay at Home!*
Bible Verse: *"Come, my people, enter your home, and shut your doors behind you; hide yourselves for a little while until the wrath is past."*
(Isaiah 26:20)
🙏selam
God bless you
@hymnsofmes
ጌታቸው በመጣ ጊዜ
(song by Pastor Tamirat H.)
ሉቃስ 12:
37 ጌታቸው በመጣ ጊዜ ሲተጉ የሚያገኛቸው እነዚያ ባሪያዎች ብፁዓን ናቸው፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ታጥቆ በማዕድ ያስቀምጣቸዋል ቀርቦም ያገለግላቸዋል።"
Join👇🏻
@hymnsofmes
ሰላም ለእናንተ ይሁን የአባቴ ብሩካን
ስለ ጊዜው ስናስብ ምን ይሰማናል?
ውስጣችን ለራሳችን ምን መልስ ይሰጠዋል?
ይህስ በሽታ ለምን በረታብን?
ለዚህ ጥያቄ መልስ የሚመስለኝ በሽታው በርትቶ ሳይሆን የእኛ አቋም ወርዶ ነው የሚመስለኝ።
በዚህ በሽታ ሰይጣን ያሰበው፦
1-ሰው ወደ ቤተክርስቲያን እንዳይሄድ
2-ሰላም በሰው ልጅ መካከል እንዳይኖር
3-እኛ ክርስትያኖች ዝም እንድንል
የ እግዚአብሄር ሀሳብ ደግሞ ፦
ፖለቲካን፣ብሄርን፣ክፋትን ትተን መናገር የሚፈልገውን እንድንሰማው ነው
እውነቱን ለመናገር እንደ መንፈሳዊ ሰው በሽታው በጌታ አይን ቀላል ነው ። በስጋ ካየነው ግን ይሄ ኢቦላ ያልጨረሰው ማህበረሰብ ኮሮና አይጨርሰውም
ልብ ካልን ግን በስጋም በመንፈስም ሰይጣን ተስፋ የለውም ግን ተስፋ አይቆርጥም
እንፀልይ፣ እንበርታ ጌታ አብዝቶ ይባርካችሁ ተባረኩ!
https://t.me/hymnsOfmes
በጌታ የተወደዳችሁ ወገኖች ጌታ ያቀረበልንን ጥሪ ከዚህ በታች አቀርብለችኃለሁ፡፡ “ሕዝቤ ሆይ፥ ና ወደ ቤትህም ግባ፥ ደጅህን በኋላህ ዝጋ፤ ቍጣ እስኪያልፍ ድረስ ጥቂት ጊዜ ተሸሸግ።”
( ኢሳይያስ 26፥20)
ጥሪው እንዲህ ይላል፡፡
1. ና ወደ ወደ ቤትህ ግባ የሚል ሲሆን ይህም እግዚአብሔር ወደ ደጁ፡ ወደ ፊቱ፡ ወደ መገኘቱ፡ ወደ ክብሩ ጸዳል ወደ ህይወት ምንጭ ፡ ወደ እረፍት ነው የሚጠራን፡፡ ስለዚህ ዛሬ በፀሎት ወደ ቤቱ ( ፊቱ) በያለንበት እንቅረብ፡፡
አዝማች፡ ወደ መገኘቱ እገባለሁ እያልን አንዘምር፡፡
2. ደጅህን ዝጋ ብሎናል፡፡ ማለትም ከቤተሰብ ጋር ወይም ብቻችንንም ብንሆን ሀሳባችንን ሰብስበን ወደ አእምሮአችን ለሚመጡት ሀሳቦች ልባችንን ዝግ አድርገን ለመንፈስ ቅዱስ ድምፅ ክፍት በመሆን በጌታ ፊት እንድንሆን፡፡ ተጨማሪ ጥቅስ፡፡ “እግዚአብሔር አምላክ የሚናገረውን እሰማለሁ፤ ሰላምን ለሕዝቡና ለቅዱሳኑ ልባቸውንም ወደ እርሱ ለሚመልሱ ይናገራልና።”
— መዝሙር 85፥8
3. ቁጣ እስኪያልፍ ተሸሸግ፡፡ ማለት በተለያዩ ጊዜያት የሚነሱ ቁጣዎች ሲኖሩ በቶሎ ወደ ጌታ ጉያ ለመሸሸግ በጸሎት እና በእምነት መሸሽ እንዳለብን ነው፡፡
“ስለዚህ ቅዱስ ሁሉ በምቹ ጊዜ ወደ አንተ ይለምናል፤ ብዙ የጥፋት ውኃም ወደ እርሱ አይቀርብም።”
(መዝሙር 32፥6)
ወገኖች በእርግጥ ወደ እርሱ ከሸሸን ደሙን ከተሸፈንን አጥፊው ወደ እኛ አይገባም፡፡ አሜን
“እግዚአብሔር ግብፃውያንን ይመታ ዘንድ ያልፋልና፤ ደሙንም በጉበኑና በሁለቱ መቃኖች ላይ ባየ ጊዜ እግዚአብሔር በደጁ ላይ ያልፋል፥ አጥፊውም ይመታችሁ ዘንድ ወደ ቤታችሁ እንዲገባ አይተውም።”
(ዘጸአት 12፥23)
ተባረኩ፡፡ መጋቢ አስፋው ከታቦር MKC
ቃልኪዳን ጥላሁን - (ሊሊ) - ትችላለህ 2012 Kalkidan Tilahun - Tichlaleh - 2020
Join @homproject
@hompeoject
My God:- 'Always and at all places Let me be like You and fear You. Make me different from the world and Let them see You through me. Let me crucify my body for the world; Let me travel following You. > I look by faith unto You; O Lord. I am waiting, watching for Your victory.'
(Baweraw Ayalkim )
Danny T.
Join @homproject for more new songs
