ማዳኑን አውሩ | ᴘʀᴏᴄʟᴀɪᴍ ʜɪꜱ ꜱᴀʟᴠᴀᴛɪᴏɴ
Open in Telegram
Thank you for your interest to join Our Telegram channel. ▫️The primary function of this channel is : ☞To proclaim our savior JESUS CHRIST through a lifestyle of praise and worship. መዝሙረ ዳዊት 96 2፤ እግዚአብሔርን አመስግኑ ስሙንም ባርኩ፥ ዕለት ዕለትም ማዳኑን አውሩ።
Show more1 241
Subscribers
No data24 hours
+57 days
+1030 days
Posts Archive
በእሾህ መካከል የተዘራው ዘር ምሳሌ ትርጉም : ምንድነው ?
😁[በፍጥነት ለመለሰ የ 50 ብር የሞባይል ካርድ ሽልማት ይኖረዋል ]
መድኃኒቴ፣ እረኛዬ፤ ጌታዬ ሰው የሆነበት ያ! ጊዜ ለእኔም ልደቴ ነው። ለተቀበሉት በስሙ ላመኑት ለእነርሱ የልጅነት ስልጣን እንደሰጣቸው ሁሉ ዛሬም በስሙ ላመኑ የእግዚአብሔር ልጅ የመሆን ስልጣን ይኖራቸዋል። ልደቱንም በእሩቅ እንደ ባህል ከማክበር ይልቅ የልደቱን ጌታ በማወቅ እና ልደቱ ልደትህ እንደሆነ በመረዳት መኖር ይሁንልን።
ኢየሱስ ብቸኛው መንገድ ፤ እውነት ፤ ህይወትም ነው።
መልካም የጌቻችን ልደት መታሰቢያ በዓል ይሁንላችሁ። 🙏🏾🤎
@hymnsofmes
☞ #ዳሰሳ መዝሙረ ዳዊት ምዕ:119 : ቁጥ. 145 -152
☞ ረቡዕ | ታህሣሥ 12 / 2015 ዓ.ም
☞ መዝሙረ ዳዊት ምዕ :119 ከመዝሙሮች ሁሉ ረዥሙ (176 ቁጥሮችን ያዘ ክፍል እንደሆነ እናያለን) እናም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ #ረጅሙ_ምዕራፍ ነው። አንዳንድ ፀሐፊዎች " #የመዝሙር_ኤቨረስት" በማለት ይገልፁታል ፤ ም/ቱም ወደ እግዚአብሔር ቃል ከፍታ ሲወስደን ስለምንገነዘብ ነው።
☞ ( የኤቨረስት ተራራ ከባህር ጠለል በላይ ከፍተኛው / ረዥሙ የምድር ተራራ እንደሆነ ይታወቃል ።)
_________________________________________
☞ እናም ከእኔ ጋር የምንመለከተው መዝሙር 119 : (ከ ቁጥር 145-152) ይህም ክፍል የዚያ የቃሉ ተራራ ጫፍ አንደኛው ክፍል እንደሆነ አምናለው።
💬 በዚህ ክፍል መዝሙራዊው አሁንም በጸሎት ውስጥ ሆኖአል ፣ እናም
☞ #እንዴት_እንደጸለየ፣
☞ #ለምን_እንደጸለየ፣
☞ #መቼ_እንደጸለየ እና
☞ #የፀለየው_ጸሎቱ ስለ ምን እንደሆነ ፍንጭ ሲሰጠን እንመለከታለን።
💬ከዚህም ባለፈ በዋናነት የምንማረው #በጸሎት እና #በእግዚአብሔር_ቃል መካከል ስላለው ወሳኝ ግንኙነት ነው።
💬 (ምዕ 119፡ ቁጥ : 145)
በዚህ ክፍል ላይ ፤ የዳዊት ጸሎቶች በፍጹም ና በሙሉ ልብ እንጂ በግማሽ ልብ የሚቀርቡ እንዳልሆኑ እንመለከታለን። እንዲሁም በሙሉ ልቡ እና በትህትና ለእግዚአብሔር ፤ለቃሉ ና ለሥርዓቱ ለመገዛት ያለውን ቁርጠኝነት እናያለን። ስለዚህ አንድ ሰው በሙሉ ልቡ ሲጸልይ በጣም #ውጤታማ በሆነ መንገድ ይጸልያል ማለት ነው።
💬 (ምዕ 119፡ ቁጥ : 146)
በዚህ ክፍል ደግሞ ዳዊት #ለመዳን ሲጸልይ እናያለን። #ፀሎቱም #ከስሕተት_የዳነ፣ #ከኃጢአት_የዳነ፣ #የራሱን_ፍላጎት_ከመከተል_የዳነ እንዲሆን ነው።
🤔ስንቶቻቻችን እንሁን ዕለት ተዕለት ይህ ፀሎት ልንፀልይ እንደሚገባ የምናምን_____? መልሱን ለኛው...
💬 (ምዕ 119፡ ቁጥ : 147 -148)
መዝሙረኛው ሲቀጥል ፤ ለመጸለይ በማለዳ / ጎህ ሳይቀድ (አ.መ.ት) የተስፋው ምንጭ በሆነው በእግዚአብሔር ቃል ላይ በመታመን አምላኩን ሲያስብ ና ሲያሰላስል መጸለይን ሲቀጥል እናያለን።
🔎 በአዲሱ መደበኛ ትርጉም " ቃልህን አሰላስል ዘንድ ፤ #ዐይኔ_ሌሊቱን_ሙሉ_ሳይከደን_ያድራል። " ብሎ ይናገራል። (አያስገርምም?)
☞ 🟡 ይህንን ክፍል ሳነበው ወደ ልቤ የመጣውን ሃሳብ ልንገራችሁ፤
🌐 Skillademia የተባለ የ social media statistics አጥኚ ተቋም ፤ በ 2021/22 G.C ይዞ ባወጣው report መሰረት ዕድሜያቸው ከ 15 -30 የሚገኙ 85 % ያህል ሰዎች በ ቀን ውስጥ ቢያንስ ለ 8:00 ሰዓት ያህል Instagram,TikTok, Facebook etc.. በመጠቀም #ጊዜያቸውን_ያጠፋሉ ይላል። አስቡት ይህ ማለት የእንቅልፍ ና የስራ ወይም የት/ት ጊዜያትን ሳያካትት ነው። ምንም እንኩዋን ይህንን ጥናት Europe ላይ ቢያደርጉም የእኛ #የኢትዮጵያውያን ተሞክሮ ከዚህ ቢበልጥ እንጂ እንደማይተናነስ ሀገር ያወቀው ፣ ፀሀይ የሞቀው ጉዳይ ነው።
💬 ስንቶቻቻን ነን ይህንን የዳዊትን ከቃሉ ጋር ያለውን ህብረት #የምንናፍቀው ?
#ለመሆንም_የምንለማመደው?
☞ የተወዳችሁ ሆይ ፤ ይህ ክፍል ወደ ቃሉ ተራራ ጫፍ እየወሰደን እንዳለ አልጠራጠርም።
💬 እግዚአብሔርን በጣም የምንወደው ከሆነ ከእግዚአብሔር ጋር ጊዜ እናጠፋለን። እግዚአብሔር ደግሞ ራሱን በቃሉ በኩል በሙላት ስለገለጠ ከቃሉ ጋር ጊዜ አጠፋን ማለት ከእግዚአብሔር ጋር ጊዜ ወስደናል ማለት ነው።
💬(ምዕ 119፡ ቁጥ : 149 -150)
መዝሙራዊው እግዚአብሔር እንዲራራለት ፣ ህይወትን አብዝቶ እንዲሰጠው እና እርሱ በፈቀደው ህግ ህያው እንዲያደርገው ጸለየ። ምክንያቱም ዳዊት በዙሪያው ያሉትን ጠላቶች / ኃጢአቶችን ያውቃል ።
💬(ምዕ 119፡ ቁጥ : 151 -152)
ከአምላካችን ጋር ከመገናኘት የሚለየን በውስጣችን ያለው #የተደበቀ_የኃጢአት_ዓለም_ቅርብ_ነው። ነገር ግን እንደ ዳዊት ወዲያውኑ ወደ #ምሽጋችን_በመዞር፣ “ጌታ ሆይ፣ አንተ ቅርብ ነህ” በሚለው ቃል #መተማመን ና #መታደስን ማግኝት እንችላለን። ም/ቱም የምናመልከው ጌታ ምንም እንኳን ስሙ ቅዱስ የሆነ ልዑል ጻድቅና አስፈሪ አምላክ ቢሆንም ግን ከልጆቹ ጋር በመስቀሉ ደም #ተቀራርቦ ይገኛልና።
💬በስተመጨረሻም (ምዕ 119 : ቁጥ 152)
"ከጥንት አውቀዋለሁ። " በሚለው ሐረግ ውስጥ፤
ለዳዊት፤ የእግዚአብሔር #ቃሉ_ከፍጡራን ጋር የሚሠራበት የዘወትር አገዛዝ መንገዱ እንደ ነበረ ዘግይቶ የገባው ወይም አሁን መማር ያለበት ነገር እንዳልሆነ ያስገነዝባል። ስለ እግዚአብሔር ቃል ከጥንትም ስለሚያውቅ ሁል ጊዜ ይረዳው ነበር፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር ብዙ ጊዜ በቃሉ በኩል ለአባቶቹ መልካም አድርጎ አይቷል። (መዝ 22: 4-5 )መመልከት እንችላለን።
☞ 🛑 በተመሳሳይ ጎን በአዲስ ኪዳን ላይም ጳውሎስ ለጢሞቴዎስም በሰጠው አደራ
"2ኛ ጢሞቴዎስ 3
15፤ ከሕፃንነትህም ጀምረህ ክርስቶስ ኢየሱስን በማመን፥ መዳን የሚገኝበትን ጥበብ ሊሰጡህ የሚችሉትን ቅዱሳን መጻሕፍትን አውቀሃል።"
እያለ ሲያሳስበው እንደምንመለከተው ፤
🙏🏾 #እኔም_ይህን_ጽሁፍ_ሳበቃ ፤እግዚአብሔር ካከበረው ፤ ራሱን በሙላት ከገለጠበት ፤ መዳን ከሚገኝበት ና ዘውትር ጥበብን ከሚሰጠን ከቃሉ ጋር ያለንን ህብረት ያድስልን ስል በትህትና እየፀለይኩ ነው።
@hymnsofmes
እወዳቹ አለሁ 🙏🏾
መኩዬ ፤ በኢየሱስ_አምኛለሁ_አልጸጸትም ብላ ወዳገለገለችው ጌታ ሄዳለች።😭
መልካም እረፍት መኩዬ😭
ለቤተሰቦችሽና ለጓደኞችሽ መጽናናትን እመኛለሁ።😭
#እግዚአብሔር_መልካም_ነው።
@hymnsofmes
