en
Feedback
FDRE MINISTRY of JUSTICE/ EXTERNAL

FDRE MINISTRY of JUSTICE/ EXTERNAL

Open in Telegram
2 425
Subscribers
+224 hours
+237 days
+6230 days

Data loading in progress...

Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
December '24
December '24
+211
in 3 channels
November '24
+30
in 3 channels
Get PRO
October '24
+92
in 1 channels
Get PRO
September '24
+98
in 1 channels
Get PRO
August '24
+90
in 3 channels
Get PRO
July '240
in 0 channels
Get PRO
June '240
in 1 channels
Get PRO
May '240
in 0 channels
Get PRO
April '24
+82
in 1 channels
Get PRO
March '24
+79
in 0 channels
Get PRO
February '24
+207
in 0 channels
Get PRO
January '240
in 0 channels
Get PRO
December '230
in 2 channels
Get PRO
November '230
in 0 channels
Get PRO
October '230
in 0 channels
Get PRO
September '230
in 0 channels
Get PRO
August '230
in 0 channels
Get PRO
July '230
in 0 channels
Get PRO
June '230
in 0 channels
Get PRO
May '23
+42
in 0 channels
Get PRO
April '23
+52
in 0 channels
Get PRO
March '23
+71
in 0 channels
Get PRO
February '23
+55
in 0 channels
Get PRO
January '23
+95
in 0 channels
Get PRO
December '22
+91
in 0 channels
Get PRO
November '22
+64
in 0 channels
Get PRO
October '22
+78
in 0 channels
Get PRO
September '22
+118
in 0 channels
Get PRO
August '22
+90
in 0 channels
Get PRO
July '22
+69
in 0 channels
Get PRO
June '22
+81
in 0 channels
Get PRO
May '22
+152
in 0 channels
Get PRO
April '22
+174
in 0 channels
Get PRO
March '22
+108
in 0 channels
Get PRO
February '22
+41
in 0 channels
Get PRO
January '22
+1 447
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
21 December+4
20 December+8
19 December+3
18 December+6
17 December+4
16 December+10
15 December0
14 December+23
13 December0
12 December+2
11 December+24
Channel Posts
የፀረ ሙስና ቀንን አስመልክቶ የሚካሄደው የምክክር መድረክ በ26/04/2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 በኢንተር ኮንቲኔታል ሆቴል// መሆኑን እያሳወቅን ከዚቀደም ጥሪ በተደረገላቹ መሰረት በተጠቀሰው ጊዜና ቦታ እንድትገኙልን እናሳስባለን፡፡

2
https://www.facebook.com/100064822533625/posts/pfbid0253xxC1RgxpcsBrskQsWyVcBckNuZf9Q3uSbHkPVXAgHMbhzURedjJGRLv3A157YQl/?app=fbl
1
3
https://t.me/+S3cRFdCmRXFGXP6S
953
4
No text...
741
5
እናስተዋውቅዎ ሰላም ጤና ይስጥልን ውድ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር የማህበራዊ ገጽ ተከታታዮቻችን ለዛሬ እናስተዋውቅዎ በተሰኘው አምዳችን ላይ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር የጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዘርፍ ስር አዲስ ስለተቋቋመው የቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች መከታተያ ዳይሬክቶሬት ጠቃሚ መረጃ አዘጋጅተንላቸኋል፡፡ በዚህም መሰረት ዳይሬክቶሬቱ የተቋቋመበትን ዓላማ፤ አደረጃጀት እና የተሰጡትን ተግባርና ኃላፊነቶች አስመልክቶ ያዘጋጀንላችሁን አጭር መረጃ እንደሚከተለው አቅርበንላችኋል፡፡ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች መከታተያ ዳይሬክቶሬት የተቋቋመበት ዓላማ፡-  በጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዘርፉ ስር በሚገኙ የስራ ክፍሎችና ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች እየተከናወነ ካለውና እየጨመረ ከመጣው የሥራ ፍሰት አንጻር የቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችን ተግባራት አቀናጅቶ እንዲመራ፤ እንዲሁም ክትትልና ድጋፍ እንዲያደርግ፤  የስራ ክፍል በማደራጀት፤ የቅርብ አመራር በመስጠት ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶቹ የሚያጋጥማቸውን ችግሮች ከስር ከስር እየቀረፉ ውጤታማ ተግባር እንዲያከናውን ለማስቻልም፤ ነው፡፡  የቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች መከታተያ ዳይሬክቶሬት፡- ተግባርና ኃላፊነት፡-  የዘርፉ ኃላፊ ስትራቴጂያዊ አመራር እንዲሰጥ ለዘርፉ ተጠሪ በሆኑ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች የሚከናወኑ ተግባራትን ያስተባብራል፣  በቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ውስጥ ዘመናዊ የመዝገብ አያያዝና አስተዳደር ስርዓት እንዲቀረጽ ያደርጋል፤ አፈጻጸሙን ይከታተላል፣  በቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች የወንጀል መዛግብት የመረጃ ስርዓት (CRIMS) በተሟላ ሁኔታ ተግባራዊ መደረጉን ይከታተላል፣  የሚቀርቡ አቤቱታና እና ቅሬታዎችን ሰንሰለቱን ጠብቀው መቅረባቸውን ያረጋግጣል፣ ያስተናግዳል፣ ዉሳኔ ይሰጣል፣ አፈፃፀሙን ይከታተላል፣  ለዘርፉ ተልዕኮ ስኬት ቁልፍ ድርሻ ያላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎችን፣ የህዝብ አደረጃጀቶችንና የግሉ ዘርፍ የሚሳተፉበት መድረክ እንዲካሄድ ሁኔታዎችን ያመቻቻል፣  ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን የቅንጅታዊ አሰራር ሁኔታ ያስተባብራል፣ እነዚህና ሌሎች ተግባርና ኃላፊነቶች ለዳይሬክቶሬቱ ተሰጥቶታል፡፡ በዳይሬክቶሬቱ ስር ስለተቋቋሙ ቡድኖች ተግባና ኃላፊነታቸው በዳይሬክተሩ ስር ሶስት ቡድኖች ተዋቅረው ወደ ስራ የገቡ ሲሆን ቡድኖቹም የቅ/ጽ/ቤት፤ ቅሬታና አቤቱታ ማስተናገጃ ቡድን፤ የልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ችሎት ክርክር ቡድን እና የቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ድጋፍና ክትትል ቡድን ይባላሉ፡፡ ቡድኖቹ የተሰጣቸውን ተግባር እና ኃላፊነት እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡ 1. የቅ/ጽ/ቤት ቅሬታና አቤቱታ ማስተናገጃ ቡድን ተግባር እና ኃላፊነት፡-  ይህ ቡድን ለጠቅላ ዐቃቤ ሕግ አገልግልት ዘርፍ ተጠሪ ሲሆን በዋናነት በቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች በሚሰጡ ውሳኔዎችን ላይ የሚቀርቡ ቅሬታዎችና አቤቱታዎችን ከማስተናገድ አኳያ የሚከተለት ተግባርና ኃላፊነቶች ይኖሩታል፡-  የሚቀርቡ አቤቱታና እና ቅሬታዎችን ሰንሰለቱን ጠብቀው መቅረባቸውን ያረጋግጣል፣ ያስተናግዳል፣ ዉሳኔ ይሰጣል፣ አፈፃፀሙን ይከታተላል፣  አቤቱታ እና ቅሬታ የሚቀርቡበትን የተለያዩ ቅጾችን አዘጋጅቶ ስራ ላይ ያውላል ወይም ስራ ላይ እንዲውል ያደርጋል፣  ቅሬታ በቀረበበት ጉዳይ ላይ የተሰጠው ውሳኔ ህግንና ማስረጃን ተመስርቶ የተሰጠ መሆኑን የማረጋገጥ የወንጀል ምርመራ መዝገቡን አስቀርቦ የመመርመር፣ ትንታኔ ወይም ማብራሪያ የመጠየቅ፣ እንዱሁም የተዘጋው መዝገብ ላይ ተጨማሪ ምርመራ እንዲካሄዱ አቅጣጫ መስጠት፣ የተሰጠውን ውሳኔ የሚያስቀይር ነገር ካለ የመቀየር፤  የተዘጉ መዝገቦች ላይ የቀረቡ ቅሬታዎችና አቤቱታዎች ላይ መስተካከል ያለባቸውን ችግሮች በመለየት የመፍትሔ አቅጣጫ የማመላከት፣ ለበላይ አመራሩ ሪፖርት የማቅረብ፤  በቅሬታ ወይም በአቤቱታ የተገኙ ዶክመቶች በዘላቂነት እንዲቀረፉ የአሰራር ስርዓት በመዘርጋት እንዲስተካከል የማድረግ፤  አቤቱታ ወይም ቅሬታ የቀረበባቸው ማመልከቻዎች፣ የቀረቡ አባሪ ማስረጃዎች እና ውሳኔ የተሰጠባቸውን ውሳኔ ሰነዶች አደራጅቶ የመያዝ፣  በመዝገብ ላይ በስነ-ምግባር ጉድለት ምክንያት ተጠያቂ መሆን ያለበት ዐቃቤ ሕግ ወይም ኃላፊ ካለ ለዐቃቤ ሕግ አስተዳደር ጉባዔ ክስ በሚመለከተው አካል እንዲቀርብ የማሳወቅ፣ ይህ ቡድን እነዚህንና ሌሎች ተግባራትን ያከናውናል፡፡ 2. የልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ችሎት ክርክር ቡድን ተግባርና ኃላፊነት፡- ይህ ቡድን ተጠሪነቱ ለቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ሆኖ የሚከተለት ተግባርና ኃላፊነጽ አሉት፡-  በአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ የሚቀርቡ የወንጀል ክሰ ክርክሮችን ይከታተላል፣  የይግባኝ መዝገብ ክርክሮችን በችሎት በመገኘት ያከናዉናል፣  ወቅታዊ የክርክር መዛግብት አፈፃጸም ሪፖርት አዘጋጅቶ ያቀርባል፣ እነዚህንና ሌሎች ተግባራትን በዚህ ቡድን የሚከናወን ይሆናል፡፡ 3. የቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ድጋፍና ክትትል ቡድን ተግባርና ኃላፊነት፡-  ለቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች የሚያስፈልጉ የሰው ኃይልና ግብዓት በመለየት እንዲሟሉ ድጋፍና ክትትል ያደርጋል፣  በቅርንጫፍ ጽ/ቤት እና በዘርፉ የስራ ክፍሎች መካከል ሊኖር የሚገባውን ትስስርና መስተጋብር ስርዓት ይዘረጋል፣ ያቀናጃል፣ ይመራል፣  በቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች በአካል በመገኘት ሱፐርቪዥን ያደርጋል፣ የስራ አፈፃፀም ይገመግማል፣ ግብረ መልስ ይሰጣል፣  ለዘርፉ ተልዕኮ ስኬት ቁልፍ ድርሻ ያላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎችን፣ የህዝብ አደረጃጀቶችንና የግሉ ዘርፍ የሚሳተፉበትን መድረክ እንዲካሄዱ ሁኔታዎችን ያመቻቻል፣  ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን የቅንጅታዊ አሰራር ሁኔታ ያስተባብራል፣ በዚህ ቡድን ደግሞ እነዚህ ተግባራት የሚከወኑ ይሆናል፡፡ የአድራሻ ጥቆማ የዳይሬክቶሬቱን አገልግሎት ፈልጋችሁ ለምትመጡ ተገልጋዮች አድራሻችን በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ለቡን አለፍ ብሎ ቫርኔሮ አደባባይ አጠገብ በተቋሙ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት 6ኛ ፎቅ ላይ ይገኛል፡፡
709
6
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ፍትሕ ሚኒስቴር ለኮልፌ ምድብ ጽ/ቤት እና ለፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ምድብ ችሎት እያስገነባ የሚገኘው ህንጻ ግንባታው በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል፡፡ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ፍት+3
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ፍትሕ ሚኒስቴር ለኮልፌ ምድብ ጽ/ቤት እና ለፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ምድብ ችሎት እያስገነባ የሚገኘው ህንጻ ግንባታው በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል፡፡ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ፍትሕ ሚኒስቴር ለኮልፌ ምድብ ጽ/ቤት እና ለፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ምድብ ችሎት መገልገያ እንዲሆን ያስጀመረው የግንባታ ፕሮጀክት ያለበትን ደረጃ አስመልክቶ ጉብኝት ተደረገ፡፡ በጉብኝቱ ላይም የመንግስት ህግና ፍትህ አገልግሎት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ የሆኑት አቶ አለምአንተ አግደው እና ሌሎች የተቋሙ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡ በጉብኝቱ ወቅት የግንባታ ፕሮጀክቱን የሚመሩት የስራ ኃላፊዎች ግንባታው ያለበትን ደረጃ በተመለከተ ለሚኒስትር ዴዔታው አጭር ገለጻ ያቀረቡ ሲሆን ግንባታው ያለበትን ደረጃ እና ቀሪ ስራዎችን በተመለከተም የአካል ምልከታ ተደርጓል፡፡ ሚኒስትር ዴኤታው አቶ አለምአንተ አግደው ከጉብኝቱ በኋላ ለፕሮጀክቱ መሪዎች በሰጡት የስራ አቅጣጫ ግንባታው በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ አሁን ያሉብንን ምቹ የስራ ቦታ እጥረቶች መፍታት እንዲቻል ተገቢው ጥረት እንዲደረግ አሳስበው ከተቋሙ የሚፈለጉ ድጋፎች ሲኖሩ ተገቢውን ድጋፍ ለመስጠት የተቋሙ አመራር ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡ በፕሮጀክቱ አስተባባሪዎች በኩልም በሀገራችን እየተፈጠረ ያለው የዋጋ ግሽበት ለስራው እንቅፋት እንዳይሆን ስጋታቸውን ገልጸው፤ ግንባታውን በተያዘለት የጊዜ ገደብ አጠናቀው ለማስረክብ ተገቢውን ጥረት እንደሚያደርጉ ተናግረዋል፡፡ ተቋሙ የአገልግሎት አሰጣጡን ምቹና ዘመናዊ ከማድረግ አንጻር ከዚህ ቀደም ለአዲስ ከተማ እና ለንፋስ ስልክ ምድብ ጽ/ቤቶች እና ምድብ ችሎቶች ያስገናባቸውን ህንጻዎች አጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቁ ማድረጉ የሚታወስ ነው፡፡
883
7
በጨርቅ ጠቅልላ ቦርሳ ውስጥ በማድረግ ልጇን የጣለችው እናት በፅኑ እስራት ተቀጣች ****** ተከሳሽ መክቤ መርሻ የተባለችው በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 574/2/ ላይ የተደነገገውን ድንጋጌ በመተላለፍ በፈፀመችው ሰውን ለአደጋ ማጋለጥ ወይም መተው ወንጀል ተከሳ ፍርድ ቤት ቀርባለች፡፡ የክስ መዝገቡ እንደሚያስረዳው ተከሳሽ በዕድሜው ምክንያት ራሱን መጠበቅ የማይችለውን እና እድሜው አንድ ቀን የሆነውን ህፃን ጥር 26 ቀን 2014 ዓ.ም በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 ልዩ ቦታው ጋሞ ሰፈር እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ወልዳ በጨርቅ በመጠቅለል ቦርሳ ውስጥ በማድረግ በአካባቢው በሚገኝ ወንዝ ዳር የጣለችው ሲሆን ጥር 27/2014 ዓ.ም ህፃኑ ሞቶ የተገኘ በመሆኑ በፈፀመችው ሰውን ለአደጋ ማጋለጥ ወይም መተው ወንጀል ተከሳለች፡፡ ተከሳሿ የተከሰሰችበት ክስ በችሎት ተነቦላት የወንጀል ድርጊቱን ፈፅሜያለሁ፣ ነገር ግን ህፃኑን ከሞተ በኋላ ነው የጣልኩት በማለት የተከራከረች ሲሆን፤ ዐቃቤ ህግም ተከሳሽ ድርጊቱን ፈፅሜያለሁ ሆኖም ግን የሞተ ልጅ ነው የጣልኩት በማለት መብቷን ጠብቃ የተከራከረች በመሆኑ የሰው ምስክር መስማት ሳያስፈልገን፤ ባቀረብነው የሰነድ ማስረጃዎች ተከሳሽ እንድትከላከል ተገቢውን ብይን ይሰጥልኝ ሲል ፍርድ ቤቱን ጠይቋል፡፡ ፍርድ ቤቱም ተከሳሿ በተከሰሰችበት ድንጋጌ ስር እንድትከላከል የመከላከያ ማስረጃ እንድታቀርብ ቀጠሮ ቢሰጣትም የመከላከያ ማስረጃ የለኝም በማለት ማቅረብ ባለመቻሏ ተከሳሽን ትከላከል በተባለችበት ድንጋጌ ስር ጥፋተኛ ነሽ ብሏታል፡፡ ጉዳዩን የተመለከተው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ቀራኒዮ ምድብ 1ኛ የሴቶችና ህፃናት የወንጀል ችሎት ተከሳሽ በ3 ዓመት ፅኑ እስራት እንድትቀጣ ሲል ወስኖባታል፡፡
218
8
+1
No text...
685
9
No text...
606
10
+2
No text...
1
11
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ፍትሕ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ ከአውሮፓ ፓርላማ አባላት ጋር ተወያዩ ======= የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የፍትሕ ሚኒስትር ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ በብራስልስ ባደረጉት የስራ ጉብኝት ከተለያዩ የአውሮፓ ህብረት ተቋማት የስራ ኃላፊዎች ጋር ተወያይተዋል። ሚኒስትሩ ከአውሮፓ ህብረት የፓርላማ አባላት ጋር ባደረጉት ቆይታ፣ ክብርት ማሪያ አሬና፣ የሰብአዊ መብት ንኡስ ኮሚቴ ሰብሳቢ፣ የተከበሩ ኡርማስ ፔት የውጭ ጉዳይ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ እና የአውሮፓ ፓርላማ የውጭ ጉዳይ ኮሚቴ አባል ከሆኑት ክብርት ጃቪየር ናርት ጋር ተገናኝተዋል። በስብሰባዎቹም ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ በተለይም በሰሜናዊ የኢትዮጵያ ክፍል በተከሰቱት ግጭቶች እና በሃገሪቱ ስላለው ወቅታዊ ሰላምና መረጋጋት እንዲሁም መንግስት ከሰብዓዊ መብት ጥሰት ጋር በተገናኘ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ የወሰዳቸውን እርምጃዎች አስመልክቶ ለፓርላማ አባላቱ ማብራሪያ ሰጥተዋል። የተከበሩ የፓርላማ አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ለሰጡት ሰፊ መግለጫ አመስግነው በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ወቅታዊ መረጃ መለዋወጥ እንደሚቀጥሉ ገልጸው በኢትዮጵያ እና በአውሮፓ ህብረት ፓርላማ መካከል በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ ግንኙነት እንዲፈጠር በቅርበት ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል። ሚኒስትሩ ደ/ር ጌዲዮን ከሳምንት በፊት የተከበሩ ካርሎስ ዞሪህኖ የአፍሪካ፣ የካሪቢያን እና የፓሲፊክ መንግስታት ድርጅት (OACPS) እና የአውሮፓ ህብረት የጋራ ፓርላማ ምክር ቤት ሰብሳቢን ማግኘታቸው የሚታወስ ነው።
612
12
+3
No text...
1 121
13
ለውጡን ተክትለው ከወጡ ህጎች መካከል በዘጠኙ ላይ በሚስተዋሉ የተፈጻሚነት ክፍተቶች ዙሪያ ጥናት በማድረግ ምክረ-ሃሳብ የሚያቀርብ ቡድን ተዋቅሮ ወደ ስራ መግባቱ ተገለጸ የጦር መሳሪያ አስተዳደር አዋጅ፣ የአስተዳደር ስነ-ሥርዓት አዋጅ፣ የጠበቆች አዋጅ፣ የማረሚያ ቤቶች አስተዳደር አዋጅ፣ የሲቪል ማህበራት ድርጅቶች አዋጅ፣ የሚዲያ አዋጅ፣ በሰዎች የመነገድ እና ሰዎችን በህገ ወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር ወንጀል አዋጅ፣ የንግድ ህግ እና የጸረ-ሽብር አዋጅ በድምሩ ዘጠኝ አዋጆችን በተመለከተ አፈጻተማቸውን የሚገመግም አብይ ኮሚቴ በክቡር ፍትሕ ሚኒስትሩ ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ አማካኝነት ተቋቁሞ ወደ ስራ ገብቷል ተብሏል፡፡ ይህ የተገለጸው የክልል ፍትህ ቢሮዎች ባዘጋጇቸው የጠበቆች፣ የሲቪክ ማህበራ ድርጅቶች፣ የአስተዳደር ሥነ-ስርዓት አዋጅ እና የማረሚያ ቤቶች የአስተዳደር ረቂቅ ህጎችን አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር በተደረገ የግበዓት ማሰባሰቢያ መድረክ ላይ ነው፡፡ በመድረኩ መልዕክቱን ያስተላለፉት በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ፍትሕ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴዔታ የሆኑት አቶ አለምአንተ አግደው ሲሆኑ በመልዕክታቸው ለውጡን ተከትሎ ከወጡ የህግ ማዕቀፎች ውስጥ በተለዩ 9 ሕጎች ላይ ተፈጻሚነታቸውን የሚገመግመው አብይ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ስራ መግባቱን ገልጸዋል፡፡ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የመንግስት ሕግ እና ፍትሕ አገልግሎት ዘርፍ ሚኒስትር ዴዔታ የሚመራው ይህ ኮሚቴ ህጎቹ ከወጡ በኋላ ለወጡበት ዓላማ መዋላቸውን በጥልቀት የሚመረምር ሲሆን በጥናቱ ያገኛቸውን መነሻ ችግሮች እና ችግሮቹ ሊፈቱ እና የህጎቹን ተፈጻሚነት የሚያረጋግጡ ምክረ ሃሳቦችን ይዘው ይቀርባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጸዋል፡፡ ኮሚቴው ስራውን በስኬት እንዲያጠናቅቅ ፍትህ ሚኒስቴር ተገቢውን ክትትል እና ድጋፍ እያደረገ መሆኑንም አክለው ገልጸዋል፡፡ በሌላ በኩል ትናንት በተጠናቀቀው የፍትህ ሚኒስቴር እና የክልል ፍትሕ ቢሮዎች የጋራ መድረክ ላይ የደቡብ ምእራብ ክልል ፍትህ ቢሮ ተወካይ በማረሚያ ቤት፣ በሲቪል ማሃበረሰብ ድርጅቶች፣ በአስተዳደር ሥነ-ሥርዓት፣ በጠበቆች አዋጅ ዙሪያ ያዘጋጇቸውን ረቂቅ ህጎች አስመልክቶ ማብራሪያ አቅርበው ውይይት ተካሂዷል፡፡ በዚሁ መድረክ በማረሚያ ቤት አስተዳደር እና በጥብቅና ፈቃድ አሰጣጥ እና አስተዳደር አዋጅ ረቂቆች ዙሪያ ከስርዓተ ጾታ አካታችነት አንጻር ከግምት ሊገቡ ይገባል የተባሉ ጉዳዮችን አስመልክተው ወ/ሮ አንቺነሽ ሽፈራው ገለጻ አድርገዋል፡፡ በሌላ በኩል መድረክ ክልሎች የራሳቸውን ህግ በሚያዘጋጁበት ወቅት በቦታው ተገኝተው ድጋፍ ያደረጉ የፍትሕ ሚኒስቴር ዐቃብያነ ሕግ እና በጎ ፈቃደኛ የህግ ምሁራን በህግ አረቃቅ ሂደቱ ስለተገነዘቡት ሁኔታ ሀሳባቸውን ለታዳሚው አቅርበዋል፤ ታዳሚዎችም የቀረቡትን ሃሳቦች አስመልክተው ጥያቄዎችን እና አስተያየቶችን ሰጥተው ከመድረክ ምላሽ ተሰጥቷል፡፡ በስተመጨረሻም የፍትሕ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታው አቶ አለምአንተ አግደው በበኩላቸው በፌዴራል እና በክልል የሚወጡ ህጎች እንዲናበቡና ተመሳሳይነት እንዲኖራቸው በሚደረገው ጥረት ጥሩ ውጤት እየታየ መሆኑ እንደሚበረታታ ገልጸው ይህም ለዜጎች ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖሊቲካዊ እድገት ጠቀሜታው የጎላ ነው ብለዋል፡፡
1 064
14
ከስምንት በላይ ስሞችን በመቀያየር ሀሰተኛ መታወቂያ እና ሰነድ በማዘጋጀት 1 ሚሊየን 618 ሺ ብር መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ቼኮችን ፊርማ በማስመሰል ክፍያ የተቀበለው ተከሳሽ 17 ተደራራቢ ክሶች ቀረቡበት፡፡ ወንድሙ ንጉሴ የተባለው ተከሳሽ የተለያዩ ወንጀሎችን በመፈፀም ከህግ ተጠያቂነት ለመሸሽ የሞከረ ቢሆንም ማህበረሰቡና የህግ አስከባሪ አካላት ባደረጉት ርብርብ በቁጥጥር ስር ውሎ በጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዘርፍ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ዐቃቤ ህግ ዳይሬክቶሬት ጄነራል ክስ ተመስርቶበታል ፡፡ ተከሳሸ ተገቢ ያልሆነ ጥቅም ለማስግኘት በማሰብ ከህዳር 06/2012 ዓ.ም እስከ መስከረም 23 /2013 ዓ.ም ባሉ ጊዚያት ውስጥ ከስምንት በላይ የራሱ መጠርያ ያልሆኑ ስሞችን በመቀያየር ሀሰተኛ መንግስታዊ߹የህዝባዊ ድርጅቶችን߹ መታወቂያዎችንና ሰነዶችን በመጠቀም ከተለያዩ የባንክ ደንበኛ ከሆኑ ግለሰቦች߹ ፕሮጀክቶች߹ከህንፃ ተቋራጮችና ከህብረት ስራ ማህበራት ሃሰተኛ ቼኮችን በመጠቀምና የቼኮችን ፊርማ አመሳስሎ በመፈረም በአጠቃላይ 1‚618‚000‚00 ( አንድ ሚሊየን ስድስት መቶ አስራ ስምንት ሺ ብር ) በተለያዩ ቀናት ክፍያ አንዲፈፀምለት በማድረግ ከህግ ተጠያቂነት ለመሸሽ ቢሞክርም የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ የግለሰቡን ፎቶ ግራፍና ግለሰቡ በሀሰት ሲጠቀምባቸው የነበሩ ሥሞችን ጠቅሶ ለጥቆማ የሚረዱ የተለያዩ አማራጮችን በማስቀመጥ ማህበረሰቡን በጠየቀው ትብብር መሰረት ግለሰቡ ብዙም ሳይቆይ ማህበረሰቡና የህግ አስከባሪ አካለት ባደረጉት ርብርብ በቁጥጥር ስር ውሎ በዐቃቤ ህግ ክስ ተመሰርቶበታል ። በዚህም መሰረት ተከሳሽ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ ሙስና ወንጀል ቸሎት ቀርቦ የክስ ማመልከቻው አንዲደርሰው ከተደረገ በኋላ ዛሬ ግንቦት 22/2014 ዓ.ም በንባብ የተሰማ ሲሆን ተከሳሽ በክሱ ላይ መቃወሚያ ካለው ለመጠባበቅ ለግንቦት 29/2014 ዓ.ም ቀጠሮ ተሰጥቷል
910
15
+5
No text...
689
16
በሰሜን ኢትዮጵያ ባለው ግጭት አውድ ጾታን መሰረት አድርገው የተፈጸሙ ጥቃቶችን ለማጣራት ለተሰማራው ከፍተኛ የወንጀል ምርመራ ቡድን ዓለማቀፋዊ ደረጃን መሰረት ያደረገ ስልጠና እየተሰጠ ነው በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በተከሰተው ግጭት አውድ የተፈጸሙ ወንጀሎችን ለማጣራት እና የድጋፍ ስራዎችን ለማስተባበር በተቋቋመው የሚኒስትሮች ግብረ-ኃይል ጽ/ቤት ስር ከተዋቀሩት አራት ኮሚቴዎች አንዱ ለሆነው የምርምራ እና ክስ ቡድን አባላት ጾታን መሰረት አድርገው የሚፈጸሙ ውስብስብ ጥቃቶች የሚመረመሩበት ህጋዊ እና ሳይንሳዊ አካሄድን አስመልክቶ ዓለማቀፋዊ ደረጃዎች እና የተመረጡ ልምዶችን መሰረት ያደረገ ከፍተኛ የአቅም ግንባታ ስልጠና ከግንቦት 13/9/2014 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ አራት ቀናት እየተሰጠ ነው፡፡ ስልጠናው የወንጀል ምርመራዎቹ ዓለማቀፍ ደረጃን በጠበቀ መልኩ እንዲከናወኑ በሚያስችል መልኩ የተዘጋጀ ሲሆን፡ የደቡብ ሱዳን እና ኮንጎን ጨምሮ በተመሳሳይ ችግር ያለፉ ሌሎች ሀገራት ተጨባጭ ተመክሮዎችን በመቀመር የሚካሄድ ነው። በዋናነትም የወንጀል ተጠያቂነትን ለመመስረት በሚያስችሉ የሀገር-አቀፍ እና አለም-አቀፍ ህግ ማእቀፎች፡ ጥሰቶች ሲከሰቱ ምርመራዎች በሚካሄዱባቸው ቴክኒካዊ ስልቶች፡ እንዲሁም ከጾታዊ ጥቃት ጋር በተያያዘ የወንጀል ሰለባዎች እና ምስክሮች የህግ፡ የስነ-ልቦና፡ የህክምና እና ማቴሪያል ድጋፎችን ከማህበረሰቡ እና መንግስት የሚያገኙበትን የተቀመረ አሰራር ምንነት የሚሸፍን ይሆናል። በስልጠና መድረኩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር የጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ የሆኑት አቶ ፍቃዱ ጸጋ ለተደራራቢ ጉዳት የተዳረጉ የወንጀሉ ሰለባዎች ተገቢ እና ሁሉን-አቀፍ ፍትህ እንዲያገኙ ከማድረግ አንፃር በምርመራው ሂደት የሚሳተፉ ባለሙያዎችን አቅም በከፍተኛ ደረጃ መገንባት ፍፁም አስፈላጊ መሆኑን ገልፀዋል። ስልጠናው ብዙውን ጊዜ የተለየ ባህሪ ባላቸው የጾታ ጥቃት ወንጀል ምርመራዎች በሚመሩበት ሳይንሳዊ እና ህጋዊ አግባብ ላይ ጥልቅ ግንዛቤ እና እውቀት እንዲፈጠር በማድረግ መርማሪዎች የተሻለ ስራ የሚሰሩበትን እድል ይፈጥራል ብለዋል። አያይዘውም አለማቀፉ የሰብአዊ መብት ጥበቃ ስርአት ተጠያቂነትን ከማረጋገጥ አንፃር የተጣለበት ኃላፊነት እንደተጠበቀ ሆኖ - እንዲህ አይነት ጉዳዮች ሲከሰቱ የዜጎችን ሰላምና ደህንነት የማስጠበቅ፡ ጾታዊ ጥቃቶችን የማስቆም፡ ተፈጽመው ሲገኙም መርምሮ የማስቀጣት ሃላፊነት በቀዳሚነት የመንግስት ሀላፊነት በመሆኑ፡ ሀገራዊ የፍትህ አካላትም የተቋቋሙት ይህንኑ ለመከወን ስለሆነ ሁላችንም ለተጠቁ ሰዎች ፍትህን ለመስጠት በተለየ ሁኔታ መንቀሳቀስ እና ከሌሎች አቻ ተቋማት ጋር በመቀናጀት መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል። በተባበሩት መንግስታት ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ሀገራዊ ፅህፈት ቤት ምክትል ተጠሪ የሆኑት ቻርለስ ንዴማ በበኩላቸው በግጭት ወቅት የሚከሰቱ ጥቃቶች ሰወኛ ያልሆኑ በጣም አዋራጅና አንዳንዴም እንደ ጦርነት ግብ ማስፈፀሚያ መሳሪያ ወይም ስልት ጥቅም ላይ የሚውሉ መሆኑን ገልጸው፡ በሰሜን ኢትዮጵያ ግጭት አውድ ለተፈፀሙ ከባድ ጥሰቶች ባህሪ የሚመጥን መፍትሄን ከማቅረብ አንፃር እስካሁን እየተካሄደ ያለው ጥልቅ ምርመራ እና አገር እንዲማርበት እየተሰራ ያለውን ሁሉን-አቀፍ ሂደት ማድነቅ እወዳለሁ ብለዋል፡፡ በፍጥነትም ምርመራዎች ተጠናቀው ክስ መመስረት መጀመር እንዳለበት ጠቅሰዋል፡፡ በመቀጠልም ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር የተለየ ኃላፊነት ስላለበት በጥቃቱ ሰለባዎች ላይ ትኩረት አድርጎ እንዲሰራ አሳስበው፡ ዛሬ የሚሰጠው ስልጠናም እጅግ አስፈላጊ እርምጃ መሆኑን አስገንዝበዋል። በአለማቀፍ ደረጃ ከሶስት ሴቶች አንዷ በህይወት ዘመኗ አካላዊ ወይም ወሲባዊ ጥቃት ይደርስባታል፡ እንደ ኢትዮጵያ ስነ-ህዝብ ዳሰሳ ጥናት 23 በመቶ የሚሆኑት እድሜያቸው ከ15-49 የሆኑ ሴቶች አካላዊ ጥቃት የሚያጋጥማቸው ሲሆን 10 በመቶዎቹ ደግሞ ወሲባዊ ጥቃት ይደርስባቸዋል ያሉት ደግሞ በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት የሴቶች ጉዳይ ተወካይ ሚስ አና ሙታቫቲ ናቸው። በተወካያቸው ባስተላለፉት መልእክትም ተቋማቸው በሴቶች እኩልነትና ማብቃት ላይ የሚሰራ አካል መሆኑን አውስተው የሴቶችን ጥቃት ከመከላከልና ምላሽ ከመስጠት አንጻር ዘርፈ-ብዙ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል፡፡ በመጨረሻም የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አለሚቱ ኦሞድ ተቋማቸው የሚመራውና በሚኒስትሮች ግብረ-ኃይል ስር ከተቋቋሙት አራት አበይት ኮሚቴዎች ውስጥ አንዱ የሆነው ኮሚቴ የፆታ እና ጾታን መሰረት ያደረጉ ጥቃት ተጎጂዎች ተገቢውን የስነ-ልቦና፡ ማህበራዊና የህክምና ድጋፍ እንዲያገኙ ለማስቻል ሁሉን-አቀፍ ምላሽ የሚሰጡ የአንድ መስኮት እና የተሓድሶ አገልግሎት መስጫ ማእከላት እንዲቋቋሙና እንዲጠናከሩ የማድረግ ስራ እየሰራ መሆኑን፡ ተጎጂዎችን መልሶ ለማቋቋምና ለመደገፍም ተጨባጭ እቅዶችን አውጥቶ እየተንቀሳቀሰ መሆኑንን ገልፀዋል። እንዲሁም ከአለም-አቀፍ የሰብአዊ መብት ህጎች አንፃር በግጭቶች በሚፈፀሙ የፆታ ጥቃት ከባድ የሰብዐዊ መብት ጥሰቶች ላይ ልዩ ትኩረት በማድረግ በዚህ ስራ ላይ የሚሰማሩ መርማሪዎች እውቀት፣ አመለካከትና ክህሎት ለማጠናከር ስልጠናውን ከተለያዩ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፡ አጋር ባለድርሻ አገራት እና ድርጅቶች ጋር በመተባበር መዘጋጀቱን ተናግረዋል፡፡
673
17
በቸኮሌት መጠቅለያ የኮኬን ዕፅ ይዞ ከኢትዮጵያ ለመውጣት የሞከረው የውጭ ሀገር ዜጋ በ12 ዓመት ፅኑ እስራትና በ75 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት እንዲቀጣ ተወሰነበት በቸኮሌት መጠቅለያ የኮኬን ዕፅ ይዞ በቦሌ አለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አድርጎ ከኢትዮጵያ ለመውጣት የሞከረው የውጭ ሀገር ዜጋ በ12 ዓመት ፅኑ እስራትና በ75 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት እንዲቀጣ ተወስኖበታል ። የቅጣት ውሳኔውን ያሳለፈው የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት ነው ። ሚ/ር አርፋን ሀይደር የተባለው የውጭ ሀገር ዜጋ መስከረም 11/2014 ዓ.ም በግምት ከምሽቱ 2፡00 ሰዓት ሲሆን በቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ ከአዲስ አበባ ወደ ኳታር ሃገር ዶሃ ለመጓዝ ሲል በተደረገበት ፍተሻ በእጁ በያዘው ቦርሳ ውስጥ በቸኮሌት መጠቅለያ የተጠቀለለ 5‚200 (አምስት ሺህ ሁለት መቶ ግራም ) የሚመዝን የኮኬን ዕፅ ይዞ የተገኘ ሲሆን ተከሳሹ በፈፀመው የናርኮቲክ ሳይኮትሮፒክ መድሐኒቶች ወይም ዕፆችን ይዞ መገኘት ወንጀል በጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዘርፍ የኢኮኖሚ ወንጀል ጉዳች ዐቃቤ ህግ ዳይሬክቶሬት ጄነራል ክስ ተመስርቶበታል ። ተከሳሽ በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት ቀርቦ ክሱ ደርሶትና ተነቦለት የእምነት ክህደት ቃሉን ሲጠየቅ ” እኔ ድርጊቱን አልፈፀምኩም ጥፋተኛም አይደለሁም ”ሲል ቃሉን በመስጠት ክዶ ተከራክሯል ። ዐቃቤ ህግ በበኩሉ የተከሳሽን ጥፋተኝነት ለፍርድ ቤቱ ያስረዱልኛል ያላቸውን ዝርዝር የሰው ߹ የሰነድና የኢግዚቢትነት (በክሱ ላይ የተጠቀሰውን የኮኬን ዕፅ) አቅርቦ በበቂ ሁኔታ ለችሎቱ በማስረዳቱ ግራ ቀኙን ክርክር ያዳመጠው ፍርድ ቤቱ በተከሳሽ ላይ የጥፋተኝነት ውሳኔ አስተላልፏል ። በዚህም መሰረት ፍርድ ቤቱ ተከሳሽ ከዚህ በፊት የጥፋተኝነት ሪከርድ የሌለበት በመሆኑ አንድ የቅጣት ማቅለያ በመያዝ ተከሳሽ በ12 ዓመት ፅኑ እስራትና በ75 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት እንዲቀጣ ተወስኖበታል ።
1 077
18
የዚሁ ስምምነት አንድ አካል የሆነዉ የዐቃቤያነ ሕግ የሙያ ስነ-ምግባር ስልጠና ከግንቦት 15 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ በአራት ዙሮች ለተቋሙ ዐቃቤያነ ሕግ የሚሰጥ ይሆናል፡፡
1 003
19
የዐቃቤያነ ህግ የሙያ ስነ-ምግባር እና ብቃት ጋር በተያያዘ በጋር ለመስራት የሚያስችል ዉይይት ተደረገ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር በህግ የተሰጡትን ኃላፊነቶች ለመወጣት የተለያዩ ሥራዎችን እየሰራ
የዐቃቤያነ ህግ የሙያ ስነ-ምግባር እና ብቃት ጋር በተያያዘ በጋር ለመስራት የሚያስችል ዉይይት ተደረገ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር በህግ የተሰጡትን ኃላፊነቶች ለመወጣት የተለያዩ ሥራዎችን እየሰራ ይገኛል፡፡ ተቋሙ የተጣለበትን ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት ያስችለዉ ዘንድም በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ የሥራ ኃላፊዎችንና ባለሙያዎችን አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ ስልጠናዎችን ሲሰጥ ቆይቷል፡፡ የተቋሙን ዐቃቤያነ ህግ የሙያ ስነ-ምግባር እና ብቃት ለማሳደግም ከUSAID- Feteh (Justice) Activity in Ethiopia ጋር በጋራ ለመስራት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ በፍትህ ሚኒስቴር የመንግስት ሕግና ፍትህ አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ዓለምአንተ አግደዉ ከድርጅቱ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በጽ/ቤታቸዉ ዉይይት አድርገዋል፡፡ ሚኒስቴር ዴኤታዉ በገለፃቸዉ የተቋሙን ዐቃቤያነ ሕግ የሙያ ስነ-ምግባር እና ብቃት ለማሳደግ የሚያስችሉ ልዩ ልዩ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን አንስተዋል፡፡ ለአብነትም በተቋሙ ያሉ ዐቃቤያነ ሕግ ሥነ-ምግባር ሁኔታ ያለበትን ደረጃ ለማወቅ ጥናት የተደረገ መሆኑንና የሥነ-ምግባር መመሪያ የመከለስ እና ሌሎች ተያያዥ ሥራዎችም እየተሰሩ ያሉ ተግባራት መሆናቸዉን አንስተዋል፡፡ ክቡር ሚኒስቴር ዴኤታዉ አክለዉም የተሟላ ስብዕና ያለዉ ዐቃቤ ሕግ ለማፍራት እንዲቻል ከUSAID Feteh (Justice) Activity in Ethiopia ጋር በጋራ ለመስራት ዝግጁ መሆናቸዉን ገልጸዉ ድርጅቱ በቀጣይም ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡ የUSAID Feteh (Justice) Activity in Ethiopia ምክትል ኃላፊ አቶ ማንደፍሮት በላይ በበኩላቸዉ ድርጅታቸዉ ከሚኒስቴር መ/ቤቱ ጋር በጋራ ለመስራት እና ለመደገፍ ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
952
20
+3
No text...
776