Lucius (ሉክዮስ ) Media
Open in Telegram
lucius ( ብርሃን የያዘ ፣ የሚያበራ) “ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ።” ማቴዎስ ፭፥፲፮ ይህ ቻናል ሉኪዮስ ክርስትያናዊ ቻናል ነው ። ወንጌል ተኮር የሆኑ ጽሑፎች፣ ስብከቶች ፣ ትምህርቶች እና መዝሙሮች ይጋሩበታል ። ቻናሉን ለሌሎች ወዳጆዎ ያጋሩት !!
Show more591
Subscribers
No data24 hours
+27 days
+930 days
Posts Archive
እኔ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይለኛል፤
በድነቴ አምላክ ሐሤት አደርጋለሁ።
ዕንባቆም 3፥18
የአንዳንዱ ደስታ ያለው በበለስ ዛፍ ማፍራት ፣ በወይን ተክልም ፍሬ መገኘት ውስጥ ነው ። በለስ ፍሬ ማፍራቱን ያቆመ ጊዜ ፣ ከወይን ተክል ፍሬ በታጣ ወቅትስ ሀዘን በልባቸው ይነግሥ እንደሆነ እንደምን አላስተዋሉም ?
ለአንዳንዳንዱም የወይራ ዛፍ ፍሬ መስጠት እና ዕርሻዎች ላይ ሰብል መበረከቱ ሐሤት ማድረጊያው ጉዳይ አድርገዋል ። ሌላኛውን ጊዜ ዝናም መዘንሙን ቢያቆም የሰብልን ምርት ማጣት ፣ ከወይራውም ዛፍ ፍሬ ሚነጥፍበት ጊዜ ያ ሁሉ ሓሤት በምሬት እና ልቅሶ ይተካ እንደሆነ ዘንግተው ይሆን ?
የበጎች ጕረኖ እንኳ በበግ መንጋ የተተረፈ ጊዜና ላሞች በበረት ውስጥ መገኘታቸው ጮቤ ሚያስረግጣቸው እልፍ ናቸው ። ዳሩ በሌላኛው ጊዜ በግ ከጉረኖ ጠፍቶ ፥ የላም ድምጽ እና ሽታ ርቆ እንኳን በሚናፈቅበት ጊዜ ያ ሁሉ ጮቤ ይሁን ዳንኪራ ወደ ጭንቀትና ድባቴ ይቀየር እንደሆነስ ስለምን አላሰቡም ?
እንደ ዘማሪው እኔ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይለኛል ። "ማለት ምነኛ እረፈት ነው ። ትላንት በማያስረጀው ፣ ዛሬም አዲስ በማያደርገው ፣ ነገም በማይቀየረው ፣ ለዘላለም ያው በሆነው ፥ አምላክ እግዚአብሔር መደሰትን ያለ ምንስ አለ ?!
በእግዚአብሔር መደሰት ትኩረቱ ጊዜና ሁኔታው ሳይሆን ራሱ እግዚአብሔር ነው ። ይሄ ደስታ ከምንም ጋ አይያያዝም ምንጭ መሠረቱ እግዚአብሔር ነው ። በእግዚአብሔር ለመደሰት ሌላ ተጨማሪ ነገር አያስፈልግም ራሱ እግዚአብሔር በቂ ነው ። በእግዚአብሔር ለመደሰት ሁነኛው መንገድ እግዚአብሔርን ማሰብ ነው ።
✍️ጌታሁን አያኖ
"አዲስ ዓመት የተባለው ቀን መቁጠሪያ አዲስ ስላለው ነው ወይስ በእርግጥ በሕይወታችሁ ውስጥ አዲስ ዓመት ስለሆነ ነው? ከተመሳሳይ ልማዶች፣ ከተመሳሳይ ጠባይና ከተመሳሳይ ስህተቶች ጋር የምትገቡበት ከሆነና በውስጣችሁ ያለውን ነገር ሳትቀይሩ የምትቀበሉት ከሆነ እንዴት አዲስ ዓመት ሊሆን ይችላል? ስብእናችሁ በእነዚህ የተለዩ መንገዶች እንዲደነዝዝ አታደርጉትምን!?
በዚህ አዲስ ዓመት ለተሻለ ኑሮ አንድ ተግባራዊ እርምጃ እንኳ መራመድ አለብኝ ብለህ ብትንቀሳቀስ ....
በአዲሱ ዓመት ለእግዚአብሔር ስእለቶችህን፣ ቃል ኪዳኖችህንና መሀላዎችህን ብቻ አትደርድርለት፤ እነዚህ ሁሉ ከአንተ ፈቃድና ጥንካሬ በላይ ናቸውና፡፡ ይልቁንም ድካምህን ሳትዘነጋ ፍላጎቶችህን ሁሉ ሰብስበህ ለእግዚአብሔር በጸሎትህ ውስጥ አቅርብለት፡፡ በራስህ ችሎታ ላይ በመደገፍም እነዚህን ቃል ኪዳኖች አትግባ!
ራስህን ለተሻለ ሕይወት እንደምትቀይር አድርገህ ለእግዚአብሔር ቃል ኪዳን ከምትገባለት ይልቅ እርሱ ለተሻለ ሕይወት ይለውጥህ ዘንድ ከእርሱ ቃል ኪዳን ተቀበል።"
(አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ- የሕይወት ልምድ ገጽ 29 በአያሌው ዘኢየሱስ የተተረጎመ)
መጠይቅ ወደ ጌታው ደስታ የሚገባ በምድር ላይ በጌታ ደስ መሰኘት አይኖርበትምን ? ተወዳጆች በጌታ ደስ ያልተሰኘ እንዴትስ ወደጌታ ደስታ ይገባል ? አይመስለኝም ። በዚህ ዓለም ስንኖር ምንግዜም በጌታ ደስ ስንሰኝ ወደ ጌታ ደስታ ለመግባት መዘጋጀታችንስ አይደለምን ?!✍️ ጌታሁን አያኖ
መጠይቅ
ወደ ጌታው ደስታ የሚገባ በምድር ላይ በጌታ ደስ መሰኘት አይኖርበትምን ? ተወዳጆች በጌታ ደስ ያልተሰኘ እንዴትስ ወደጌታ ደስታ ይገባል ? አይመስለኝም ። በዚህ ዓለም ስንኖር ምንግዜም በጌታ ደስ ስንሰኝ ወደ ጌታ ደስታ ለመግባት መዘጋጀታችንስ አይደለምን ?!
✍️ ጌታሁን አያኖ
ተስፋ የሕይወት ሽታ የሚሆነው ምንጭ እና መሠረቱ እግዚአብሔር ሲሆን ነው ። ተስፋ የሕይወት ሽታ ብቻ ሳይሆን የሕይወት ውሃ ወንዝ ነው ። ወንዝ ደግሞ ምንጭ አለው ። ምንጩም እግዚአብሔር ነው ። ወንዝ የተጓዘበት መንገድ ሁሉ ልምላሜን ይቸራል ። ከወንዝ አጠገብ ያለ ተክል ፍሬያማ ፣ ቅጠሉም እንደማይረግፍ ሁሉ በተስፋ የሚደረግ ጉዞ ሕይወት እና ስኬታማነትን ይጎናጸፋል ። መሠረቱ ምንጭ የሆነ ወንዝ የማይቆም ወንዝ ነው ። የማይቆም ወንዝ ደግሞ ድንጋዩን ሰንጥቆ ያልፋል ። ድንጋዩን ሰንጥቆ የሚያልፈው ግን በጉልበቱ ሳይሆን በጽናቱ ነው ። ለዚህም ጽናትን ወልደ ተስፋ ልንለው እንችላለን ። ያለተስፋ ጽናት እንዲሁ የሚመጣ ነገር አይደለም ። የምንጸናው በተስፋ ነውና ። ተስፋ ከእግዚአብሔር ስለሚመነጭ ተስፋ ቢስ ሆኖ ለደከመው የሰው ልጅ ልምላሜ እንዲሆን እግዚአብሔር አስቀድሞ የማይጠፋ ተስፋን ሰጠው ።...
የቀረውን ለማንበብ 👇
https://telegra.ph/%E1%89%B0%E1%88%B5%E1%8D%8B--%E1%8A%AD%E1%8D%8D%E1%88%8D-4-08-29
