471
Subscribers
No data24 hours
+47 days
+1230 days
Posts Archive
ጠቃሚ መረጃ ለትውልደ ኢትዮጵያውያን
-
በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ ቁጥር 73/2020 መሠረት ትውልደ ኢትዮጵያውያን የውጭ አገር ዜጎች የባንክ አክሲዮን መግዛት የምትችሉት :-
1) የአክሲዮን ግዥ ክፍያውን ከየትኛውም አገር ብትፈፅሙም የባንክ አክሲዮን ግዥውን ማከናወን የሚቻለው በኢትዮጵያ መልክዓምድር ውስጥ ብቻ ነው።
=> ስለሆነም በምትኖሩበት አገር እና ብሔራዊ ባንክ እውቅና ሰጥቶ በሚጠቀምባቸው የውጭ አገራት ገንዘቦች እና በቀረቡት የባንክ swift code እና የአማራ ባንክ የሂሳብ ቁጥሮች ካስገባችሁ በኋላ ግዢውን በአካል መፈፀም የማትችሉ: ግዢውን የሚፈፅምላችሁ ወኪል ያስፈልጋችኋል። በቀጣይ የባንኩ ውሳኔዎች ላይም የአክሲዮን ድርሻችሁን ወክሎ ለመሳተፍ ውክልናው አስፈላጊ ነው። ገንዘቡን በ Swift code ስታስገቡ የምትጠቀሙት የምንዛሬ ተመን የየቀኑ የባንካች የውጭ ምንዛሬ መግዣ (banks foreign exchange buying rate) ነው ።
2. ገንዘቡን በ swift code ካስገባችሁ በኋላ አገር ውስጥ ያለው ወኪል ግዠውን እንዲፈፅምላችሁ የሚከተሉትን ዶክመንቶች ለወኪሉ መላክ አለባችሁ ። የውክልና ኮፒ ፤ የፓስፖርት ኮፒ ፤ የቢጫ ካርድ ኮፒ ፤ ገንዘቡን ገቢ ያደረጋችሁበት ደረሰኝ ኮፒ ። ከዛ ወኪሉ እነዚህን ዶክመንቶች እና የራሱን መታወቂያ ኮፒ በመያዝ ገንዘቡ ገቢ በተደረገበት ባንክ ቀርቦ የአማራ ባንክ የአክሲዮን መግዣ ፎርሙን ሞልቶ ግዢውን መጨረስ ይችላል ።
3) በውጭ አገራት የሚኖሩና ዜግነት ያልቀየሩ ኢትዮጵያውያን የባንክ አክሲዮንን በብር አሊያም በውጭ ምንዛሬ የመግዛት መብት አላቸው። ካሉበት አገር ሆነው ገንዘቡን ለማስገባት ከፈለጉ በስማቸው ግዢውን የሚፈፅም ወኪል በማድረግ መፈፀም ይችላሉ።
4- ሙሉ ለሙሉ ከውጭ ወደ አገር ቤት ገብተው የሚኖሩና ዜግነታቸው የውጭ አገር የሆነ የአክሲዮን ግዢዎችን መፈፀም የሚችሉት በውጭ ምንዛሬ ነው። እነዚህ ኑሯቸው ኢትዮጵያ በመሆኑ ወኪል ላያስፈልጋቸው ይችላል። ራሳቸው ግዢውን መፈፀም ስለሚችሉ።
5- ከአገር ውስጥ በውጭ ምንዛሬ መግዛት የሚቻለው ትውልደ ኢትዮጵያውያን በባንኮች የውጭ ምንዛሬ ሂሳብ ካላቸው ብቻ ነው ። ከዚያ ሂሳብ ወደ አማራ ባንክ ሂሳብ በማዛወር መግዛት ይችላሉ ። በmoney laundering ህግ መሰረት የውጭ ምንዛሬ ገንዘቡን በጥሬው ባንክ ይዞ በመሄድ መግዛት አይቻልም ።
በአሜሪካና ካናዳ ÷ በአውሮፓ ÷ እስያ ÷ መካከለኛው ምስራቅና አፍሪካ የምትኖሩና የአማራ ባንክ አክሲዮንን የምትገዙ ትውልደ ኢትዮጵያውያን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እውቅና የሠጣቸውንና ለምንዛሬ በሚውሉ ገንዘቦች ሁሉ መግዛት ትችላላችሁ።
በብር የተቀመጠውን የአንድ አክሲዮን ዋጋና ዝቅተኛ የአክሲዮን ግዢ መጠን የአገልግሎት ክፍያን ጨምሮ በምትገዙበት ቀን የእለቱን የምንዛሬ መጠን በማስላት መፈፀም ትችላላችሁ።
የገዛችሁበትን ደረሰኝ ገንዘብ ገቢ ካደረጋችሁበት ባንክ በመያዝ በኢትዮጵያ ኤምባሲ የውክልና ደብዳቤ በመሙላት ኢትዮጵያ ላለ ወኪል በመላክ መስራችነትዎን ያረጋግጡ።
የአማራ ባንክ አክሲዮን ግዢ አፈፃፀም ላይ ግልፅነት የምትፈልጉ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ዝርዝር አፈፃፀሙን ከተያያዘው ፅሑፍ ላይ ማንበብና መረዳት ትችላላችሁ።
Amhara Bank s.c
Together we can!!
የተወደዳችሁ የአማራ ባንክ ቻናል ተከታታዮች እንዴት ናችሁ?
ባንኩ በሚገርም ፍጥነት አክሲዮኑ እየተሸጠ ነው በተለይ ለትውልደ እትዮጵያን ጥሩ አጋጣሚ ነው ምከንያቱም ከዚህ ቀደም ከዚህ ቀደም በውክልና ብቻ ነበር አክሲዮን መግዛት የሚቻለው ስለዚህ ፈጠን ፈጠን በሉ።
መልካም ለሊት!!!!
የአማራ ባንክ አክሲዮን ለሚገዙ ትውለደ ኢትዮጵያውያን የአክሲዮን ግዢ አፈፃፀሙን የተመለከተ መረጃ ከተያያዘው ፅሁፍ ይመልከቱ። የምንዛሬ ተመን አሠራር ሰንጠረዡ ለማሳያነት የቀረበ በመሆኑ አክሲዮን በሚገዛበት ቀን የሚወጣውን ምንዛሬ ተመን መጠቀም ተገቢ ነው። ዝርዝሩ ከላይ ባባለው ፅሁፍ ማስታወሻ ተቀምጧል።
አማራ ባንክ የአክሲዮን ሽያጭ ማራዘሙን አስመልክቶ ለፃፍኩት ማብራሪያ የጠየቃችሁ ጥያቄ እና መልሶቻቸው ።
1. ጥያቄ ፤ ለምን ለትውልደ ኢትዮጵያዊያን ብቻ አይራዘምም?
መልስ ፤ የአክሲዮን ሽያጭ ለህዝብ በይፋ የሚሸጥ ስለሆነ ለአንዱ ወገን አራዝመህ ለሌላው መከልከል አትችልም ። ወይ ለሁለቱም ታራዝማለህ ወይ ለሁለቱም ሽያጩን ትዘጋለህ ። ለዛ ነው ።
2. ጥያቄ ፥ ምስክር እንኳን በሶስት ይፀናል ። እና ከዚህ በላይ እንዳታራዝሙ ።
መልስ ፤ ከዚያ ወዲያማ አይራዘምም ። አብደናል እንዴ ?
3. ጥያቄ ፤ ፓለቲካ እየዘወራችሁ ይመስላል ።
መልስ ፤ ኧረ በፍፁም ። አደራጁ ውስጥ ፓለቲከኞች ቢኖሩም ወደ አደራጅነት ሲመጡ እንደ ግለሰብ ባላቸው ተቀባይነት ይረዱናል እና ይጠቅሙናል ተብሎ ታምኖበት ነው ። የሚያሳየውም ባንኩንም እየረዱት ነው ። እዚህ ሲመጡ የፓለቲካ ጃኬታቸውን አውልቀው ነው የሚሰሩት ። ይህን ማወቅ አለባችሁ ። ባንኩ የማንም የፓለቲካ ፓርቲ አጀንዳ አስፈፃሚ አይደለም ። ይህ ባንክ ነው እንጂ የፓለቲካ ፓርቲ አይደለም ። አለቀ ! ለህዝብ ኢኮኖሚያዊ ልማት እንስራ ብሎ የተነሳ እና ከ145,000 በላይ ባለ አክሲዮኖች ባለቤት የሆኑበት የህዝብ ባንክ ነው ። እንዲህ ሊሆን ነው እንዲያ ሊሆን ነው እያላችሁ አትወዛገቡ ። ምንም አይሆንም ። አንድ ሰው ደግሞ ፓለቲከኛም ይሁን ሌላ እንደ ግለሰብ በተለያዩ ኮሚቴዎች እና አደረጃጀቶች ውስጥ ገብቶ በሚችለው አስተዋፅኦ ማድረግ የተለመደ አሰራርና መኖርም ያለበት ነው ። የባንኩ አደራጆች ከተለያየ የማህበረሰብ ክፍል የተውጣጡ ናቸው ። ሁሉም አለ ። ምሁራን ፤ ፓለቲከኛ ፤ የባንክ ባለሙያ ፤ ባለሃብቶች ፤ የልማት ድርጅቶች ሃላፊዎች ወዘተ ። እና ምንም ችግር የለም ጎበዝ ። ጦር ከፈታው ወሬ የፈታው እየሆን ነው የተቸገርነው ። ችግር ካለ እኮ ችግር አለ እንላለን ። ውስጡ ያለን እኛ ። የሚሆነውን ሁሉ እናውቃለን ። እና እባካችሁ ወዲያ ወዲህ አትወዛገቡ ። ባንኩ በጣም በጥሩ ሁኔታ እየሄደ ነው ። ለዛም ነው አስደናቂ የአክሲዮን ሽያጭ ያስመዘገበው ።
4. ለዳያስፖራዎች በኋላ ሸር ሽጣችሁ ዶላር ማግኘት አትችሉም ነበር ወይ ? አሁን ለምን ወደ ምስረታው አልሄዳችሁም ?
መልስ ፤ አክሲዮን በኋላም መሸጥ ይቻላል ። የሚከለክል ህግ የለም ። ግን እንዳልኩት አንደኛ አሁን መሸጣችን ዳያስፖራውን መስራች ያደርገዋል ። በኋላ ስንሸጥ መስራች አይሆኑም ። መስራች ካልሆኑ ደግሞ የእኛን ባንክ አክሲዮን ለመግዛት ያላቸው ፍላጎት ይቀንሳል ። ስለዚህ ዳያስፖራዎችን መስራች አድርጎ መሄድ ለእነሱም ለባንኩም ጠቃሚ ነው ። ሁለተኛ እኛ አሁን ዶላሩን ለተለያዩ የውጭ ምንዛሬ ለሚፈልጉ ወጭዎች እንፈልገዋለን ። ኮር ባንኪንግ ፤ ከውጭ የምናስገባቸው ቋሚ ንብረቶችን ወዘተ ። ስራ ስንጀምርም ኢምፖርት ኤክስፖርቱ ላይ ተፎካካሪ ባንክ ለመሆንም ዶላሩ ያስፈልገናል ።
5. ጥያቄ ፤ ከተራዘመ አይቀር በትክክል ኘሮሞሽን ሰርታችሁ ጥሩ ሽያጭ ከዳያስፖራው መገኘት አለበት ።
መልስ ፤ በጣም ልክ ነው ። እንቀበለዋለን ። ኘሮሞሽኝ ላይ ድክመት አለብን ። እዚህ ላይ ጠንክረን በዚህ ወር እንሰራለን ።
6. ጥያቄ ፤ ከዳያስፖራ ሽያጭ የሚገኘው ዶላር የአማራ ባንክ ነው ወይ ?
መልስ፤ በብሄራዊ ባንክ ዳይሬክቲቪ መሰረት ከሽያጭ የሚገኘው ዶላር 30% ለብሄራዊ ባንክ ገቢ ይሆናል ። ይህ 30% ባለው የቀን ምንዛሬ ተመን ተሰልቶ ለአማራ ባንክ በብር ገቢ ይሆናል ። 70% ዶላሩ ግን የአማራ ባንክ ነው የሚሆነው ። ለሚሸጡት ባንኮችም አይደለም ፤ ለብሄራዊ ባንክም አይደለም ። ይህ የ 30-70 የዶላር አከፋፈል አሰራር ከኤክስፖርት ፤ እና ሬሚታንስ ከሚገኝ ገቢም ላይ ተፈፃሚ የሚሆን መመሪያ ነው ። አሁን ለሸር ሽያጭም ተፈፃሚ ነው ። ስለዚህ የሽያጩ 70% ዶላር የአማራ ባንክ ነው ።
7. ጥያቄ ፤ መራዘሙ ጥሩ ነው ። ጎን ለጎን ብዙ ስራዎችን ጨርሱና ባንኩ ቶሎ ስራ እንዲጀምር ።
መልስ ፤ ብዙ የዶክመንት እና የዝግጅት ስራዎች ተሰርተዋል ። እናም የስራ ፈቃድ ከብሄራዊ ባንክ ከ 3 ወር ባነሰ ጊዜ እናገኛለን ብለን እንጠብቃለን ። ስራ ለመጀመር ነሃሴ ምርጫ አንደርስም ብየ እጠብቃለሁ ።
አማራ ባንክ የመስራች አክሲዮን ሽያጩን ለአንድ ወር ከአንድ ሳምንት (በአምስት ሳምንት) አራዝሟል። እስከሚያዝያ አጋማሽ።
☝ ይሄ ራሱን የቻለ ምክንያት አለው።
1) ብሔራዊ ባንክ ከወራቶች በፊት ትውልደ ኢትዮጵያውያን የፋይናንስ ዘርፍ ባለቤት መሆን የሚችሉበት አዋጅ አውጥቶ ነበር። አዋጁን ተከትሎ ግን ማስፈፀሚያ መመሪያው ቶሎ መውጣት አልቻለም ነበር።
2) ከወራቶች በፊት የአማራ ክልል አመራሮች እና የአማራ ባንክ አደራጅ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ መላኩ ፈንታን ጨምሮ በውጭ አገራት በተለይ በአሜሪካ ከዲያስፖራ ጋር በነበራቸው ውይይት ዲያስፖራው በአማራ ጉዳይ ከሚያደርገው ተሳትፎ አንዱ የብሔራዊ አዋጅን ተከትሎ መመሪያ ሲወጣ የአማራ ባንክ አክሲዮን እንዲገዛ የሚያግባባ ነበር።
3) ብሔራዊ ባንክ ትውልደ ኢትዮጵያውያን በፋይናንስ ዘርፍ እንዲሳተፉ የሚፈቅደውን መመሪያ ለማውጣት ረጅም ጊዜ ሲወስድ የአማራ ባንክ የአክሲዮን ሽያጭ ለሁለት ወር ተራዝሞ ነበር። ይህ የብሔራዊ ባንክ መመሪያ ሁኔታ አዝጋሚ ሲሆን ቀጥታ ወደምስረታ ለመግባት ዝግጅት እያደረገ ባለበት : ብሔራዊ ባንክ መመሪያውን ባለፈው ሳምንት ነው ያወጣው።
4) ስለዚህ ለሰባት ወራት የቆየው የአክሲዮን ሽያጭ በአገር ውስጥ ከፍተኛ ገንዘብ ቢሰበሰብም ለዲያስፖራው ቃል በተገባው መሠረት መስራች ባለድርሻ ማድረግ አስፈላጊ ነው። መመሪያው ሁለቱ ወራቶቹ ሊጠናቀቁ ጥቂት ቀናት ሲቀር የወጣ በመሆኑና ዲያስፖራው ባለድርሻ እንዲሆን ስለሚያስፈልግ ድጋሚ ለአምስት ሳምንት እንዲራዘም ሆኗል።
5) ከዚህ ሁኔታ ሰዎች ሊረዱት የሚገባው በአንድ በኩል ትውልደ ኢትዮጵያውያን የባንኩ መስራች መሆናቸው ብቻ ሳይሆን አማራ ባንክ ከአምስት ሳምንት በኋላ ስራ ሲጀምር የራሱን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ይዞ ለመጀመር የሚያስችለው ነው።
ምክንያቱም የባንኩን አክሲዮን የሚገዙ ሰዎች ካሉበት አገር በተመረጡ ባንኮች በቀረቡ የswift code አድራሻዎችና በውጭ ምንዛሬ ነው።
ይህም በቀጥታ የቢዝነስ ደንበኞችን ይዞ ለመጀመር የሚያስችል ነው። በፕሮጀክት ፅ/ቤት በኩል ስራ ለማስጀመር የሚያስችሉ የቅርንጫፍ መክፈቻ አካባቢዎችና ሌሎች ተግባራትን ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው።
Amhara bank s.c
Together we can!!
Breaking news
የአማራ ባንክ አክሲዮን ሽያጭ ለ5 ሳምንታት ተራዘመ!!
የአማራ ባንክ አክሲዮን ሽያጭ ለምን ተራዘመ? (ክፍል 1)
ውድ ወገኖቻችን እንደምታውቁት አማራ ባንክ በባንክ ዘርፉ እጅግ ስኬታማ የሆነ የአክሲዮን ሽያጭ አከናውኗል ። የአጠቃላይ ሽያጩን ሪፖርት በሌላ ፅሁፍ እመለስበታለሁ ። ይህ ከፍተኛ የአክሲዮን ሽያጭ የተሳካው ደግሞ በህዝቡ ከፍተኛ ርብርብ ነው ። ከዚህ ቀደም የአክሲዮን ሽያጩን ለሁለት ጊዜ አራዝመናል ። በወቅቱም ለምን እንደተራዘመ ገልፀናል ። አሁን ወደዛ ሃተታ አልሄድም ምክንያቱም ያለፈ ነገር ስለሆነ ።
ያው እንግዲህ አሁንም አክሲዮን ሽያጩን ለሶስተኛ ጊዜ አራዝመናል ። አሁን ያራዘምነው ለአምስት ሳምንት (አንድ ወር ከአንድ ሳምንት) ነው ። እዚህ የማራዘም ውሳኔ ላይ ለመድረስ በጣም ከባድ እንደሆነ ይታወቃል ። ይህንንም የምንለው ህዝባችን ባንኩ ቶሎ ስራ እንዲጀምር ካለው ጉገት አንፃር ነው ። እናም በማራዘማችን እንደምትበሳጩብን ጠፍቶን አይደለም ። ነገር ግን መታወቅ ያለበት ለህዝብ እንሰራለን ብሎ የተነሳ ቡድን እናንተን ውድ ህዝባችንን የማበሳጨት ቅንጣት ታክል ፍላጎት የለውም ፤ ሊኖረውም አይችልም ። ይህንንም ትረዳላችሁ ብለን እንገምታለን ። ከዚያ ይልቅ ማራዘሙ ለባንኩ ጥቅም ስላለውና ለዚያም በቂ የሆነ አሳማኝ ምክንያት ስለነበረ ነው ። በአጠቃላይ የማራዘም ውሳኔው ላይ ለመድረስ ለእኛም አስጨናቂ የነበረ ቢሆንም ህዝቡን ስለምናሳምነው እና ስለሚረዳን ብለን እና ግራ ቀኙን አይተን አራዝመነዋል ። ትረዱናላችሁ ብለን እንገምታለን ።
አሁን ወደአራዘምንበት ዋነኛ ምክንያት ልምጣ ። እንግዲህ ሽያጩ አሁንም የተራዘመው ትውልደ ኢትዮጵያዊያን በውጭ ምንዛሬ አክሲዮን ገዝተውን መስራች ሁነው እንዲቀጥሉ ስለፈለግን ነው ። ያው እንደምታውቁት የባለፈውን ያራዘምንበት ምክንያትም በአገር ቤት ላሉና አክሲዮን ላልገዙ ሰዎች ጭምር ቢሆንም ዋነኛ የማራዘማችን ምክንያቶች ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ነበሩ ። ነገር ግን በብሄራዊ ባንክ ዳይሬክቲቪ መዘግየት ምክንያት ይኸ የትውልደ ኢትዮጵያውያን የአክሲዮን ግዢ ሊፈፀም አልቻለም ። የብሄራዊ ባንክ ዳይሬክቲቪ የወጣው ደግሞ ባለፈው ሳምንት ነው ። በዚች አጭር ጊዜ ውስጥ የውጭ ምንዛሬ አካውንት ተከፍቶ ፤ ትውልደ ኢትዮጵያውያን አገር ቤት ላለ ሰው ውክልና ሰጥተው ትርጉም ያለው ሽያጭ ማከናወን ከባድ ነው ። ስለዚህ ነው የተራዘመው ።
ለትውልደ ኢትዮጵያውን ሸር መሸጣችን ደግሞ ያው እንደምታውቁት በጣም ውድ የሆነውን እና ለአገራችን እንደ ነዳጅ አስፈላጊ የሆነውን የውጭ ምንዛሬ እንድናገኝ ይረዳናል ። የውጭ ምንዛሬውን ደግሞ የምንፈልገው ለብዙ አላማዎች ነው ።
1. ባንኩ ስራ ሲጀምር የኮር ባንኪንግ ሶፍትዌር ተጠቅሞ መጀመር አለበት ። መቸም በዚህ በሰለጠነ ዘመን ማኑዋሊ ስራ እንድንጀምር መጠበቅ የለበትም ። ተወዳዳሪም አንሆንም ። እናም የኮር ባንኪንግ ሶፍትዌር ለመግዛት የውጭ ምንዛሬ የግድ ያስፈልገናል ።
2. የውጭ ምንዛሬ ካገኘን ደግሞ ስራ በምንጀምርበት ወቅት የኢምፖርት እና ኤክስፖርቱ ዘርፍ ላይ ተፎካካሪ ባንክ ሆነን እንድንጀምር ያደርገናል ።
ለማራዘማችኝ ሌሎች ተጨማሪ ምክንያቶችን አሉ ። በተጨማሪም ትውልደ ኢትዮጵያዊያን አክሲዮን ሲገዙ ምን መከተል እንዳለባቸው የብሄራዊ ባንክ ዳይሬክቲቪ አለ ። እነዚህን ሁለት ነጥቦች በሚቀጥለው ክፍል 2 ፅሁፍ እናወጣለን ።
ጉዞአችን ተጠናክሮ ይቀጥላል ።
Via: Letenah Ejigu wale
የአማራ ባንክ የዛሬ ሙሉ ቀን የአክሲዮን ሽያጭ (March 06, 2020)
ያው እንደምታውቁት የአማራ ባንክ አክሲዮን የሚሸጠው በ 10 ባንኮች ነው ። የዛሬው የሽያጭ ሪፖርት ሽፋኑ ከፍተኛ ነው ። ማለትም የ 9 ባንኮች የቀን ሽያጭ የቀረበበት ነው ። የቀረው የአዋሽ ባንክ ሽያጭ ነው ። እሱም ሪፖርተሮች ባለመገኘታቸው ነው ። ይህንን አይተው ነገ ከነገ ወዲያ ሪፖርት ያደርጋሉ ብለን እንጠብቃለን ።
በስራ መብዛት ምክንያት ከእንግዲህ በቀሪ ቀናቶች ሪፖርት የምናደርገው እስከ 11:30 ያለውን የቀኑን ሙሉ ሽያጭ ነው ። ከይቅርታ ጋር የምሳ ሰአት የቢዝነስ ዜና አይኖረንም ።😂 የ 11:30 የቢዝነስ ዘገባችንን ስፖንሰር ለማድረግ ፍላጎት ያላችሁ MAAG ቢሮ ኑ እና አነጋግሩ 😂😂😂
የየቀኑን ሽያጭ ሪፖርት በማድረጋችን ሽያጩ እንደጨመረ በውስጥ ከሚደርሱን መልዕክቶች እንረዳለን ። እኛም ሽያጩን በየቀኑ ሪፖርት የምናደርገው የአክሲዮን ሽያጭ እንዲጨምርና ባንኩ ሪከርድ በሆነ የተከፈለ ካፒታል ስራ እንዲጀምር ካለን ጉጉት መሆኑ ይታወቅልን ። ሌላ ምንም አላማ የለንም ።
ጊዜ ስናገኝ ደግሞ በተሰበሰበው የየቀኑ የአክሲዮን የሽያጭ መረጃ ላይ ተተርሰን በግራፍ የታገዘ ትንታኔም ለመስጠት እንሞክራለን ። በዚህም ሰው ኢንቨስትመንትን እንዲለምደው እና ፖለቲካ ከማመንዠክ ወጥቶ ኢኮኖሚውን የየቀን አጀንዳው እንዲያደርገው ለማድረግ እንሞክራለን ። ይህም ወደ አክሲዮን ገብያ ማቋቋም የምናደርገውን ሽግግር ያሳልጠዋል ብለን እናምናለን ።
በአጠቃላይ የማንኛውም ኩባንያ የሸር ሽያጭ በየቀኑ ሪፖርት መደረጉ ብዙ ጥቅም ስላለው እንቀጥላለን ። ጌታ ወደፊት ሲለው ደግሞ የአክሲዮን ገብያ አቋቁመን በየ ሞባይላችን በሚጫን app የአክሲዮን online trading እንጀምር ይሆናል ።
አሁን ወደ ዛሬው የቀን ውሎ ሽያጭ ልውሰዳችሁ ። ሽያጩ እስከ 11:30 ያለውን ይይዛል ።
1. አባይ ባንክ
428 ባለአክሲዮኖች
9,384,500 ብር
2. አቢሲኒያ ባንክ
296 ባለአክሲዮኖች
8,046,000 ብር
3. የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
658 ባለአክሲዮኖች
27,064,500 ብር
4. ዳሸን ባንክ
158 ባለአክሲዮኖች
3,923,000 ብር
5. የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ
9 ባለአክሲዮኖች
132,000 ብር
6. ህብረት ባንክ
76 ባለአክሲዮኖች
1,913,000 ብር
7. ቡና ኢንተርናሽናል ባንክ
62 ባለአክሲዮኖች
1,635,000 ብር
8. ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ
45 ባለአክሲዮኖች
6,420,000 ብር
9. አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ
6 persons ባለአክሲዮኖች
165,000 ብር
10. አዋሽ ባንክ ፤
ሪፖርተር እስካሁን አልተገኘም ።
እናስ ደምርልኛ 😂 ነገሩ አሸወይና ነው ።
MAAG 💪💪💪
Via: Dr.Letenah Ejigu wale
Amahara bank
Together we can!!!
አመራ ባንክ የአክሲዮን ሺያጭ 4 ቀን ብቻ ቀረው እባካችሁ ያልሰሙ ስለሚኖሩ share አድርጉላቸው።
አማራ ባንክ አክሲዮን መዝጊያ-
እንዴት አመሻችሁ?
ታላቁ የአማራ ባንክ አክሲዮን ሽያጭ ክንውን ላለፋት ሰባት ወራት በብቃት ሲካሄድ ቆይቷል።
ከእስከ ዛሬ ድረስ 5 ቢሊዮን ብር የሚገመት የተፈረመ አክሲዮን ሽያጭ ተከናውኗል።
የአክሲዮን ሽያጭ ከ5 ቀናት በኋላ የካቲት 30 ቀን 2012 ዓ.ም ይጠናቀቃል።
እስከተጠቀሰው ጊዜ ገደብ ድረስ፦
1) የመሥራችነት ዕድሉ፥
2) 50% ከፍሎ ቀሪውን በ6 ወር ውስጥ የመክፈል ህጉ፥
3) ድጋሜ ተጨማሪ አክሲዮን የመግዛት አጋጣሚው፥
4) በልጆች ስም የመግዛት መብት፥
5) በተወካይ አማካኝነት የመግዛት አጋጣሚዎች..ወዘተ
አሁንም ክፍት ሆነው ይቆያሉ።
ዲያስፖራው በባንክ ምስረታ ላይ መሳተፍ የሚፈቅደው ዕድል፥ በብሄራዊ ባንክ ፀድቆ መውጣቱ የአክሲዮን ሽያጭ መጠንና ካፒታሉን ከፍ እንደሚያደርገው ከፍተኛ ግምት አለ።
ባንኩ መጋቢት 20 ቀን 2012 ዓ.ም የጠቅላላ ጉባኤ በማድረግ፥ የቦርድ አባላትን እና ዋና ስራ አስፈፃሚውን እንደሚሠይም ይጠበቃል።
መልካም ሌሊት!
የአማራ ባንክ የሥራ ቅጥር በተመለከተ
እንዴት አደራችሁ?
በርካታ ሰዎች የ አማራ ባንክ ሰራተኛ መቅጠር እንደጀመረ ለማወቅ ጥያቄዎቻቸውን ለአማራ ምጣኔ ሃብት መማክርትን እያቀረቡ ይገኛሉ።
የአማራ ባንክ የሥራ ማስታወቂያም ሆነ ቋሚ የሠራተኛ ቅጥር ሂደት አልጀመረም ።
የቅጥር ማስታወቂያ የሚወጣው እና ቅጥር የሚጀምረው፥
ጠቅላላ ጉባኤ ተሰብስቦ ቦርድ ከመረጠ በኋላ፥ ቦርዱ ደግሞ ዋና ዋና ስራ አስፈፃሚዎችን ከመረጠ ( ከሾመ) ፥ እና ሂደቱም በብሄራዊ ባንክ ከፀደቀ ብሎም በህግ መቋቋሙ በይፋ ለህዝብ ከተገለፀ በኋላ ነው።
ሂደቱቶችን በዝርዝር ስንመለከት፦
1. የአክሲዮን ሽያጭ ይጠናቀቃል ። (የካቲት 30፤ 2012)
2. የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ይካሄዳል፣ (በመጋቢት መጨረሻዎቹ ይጠበቃል)
3. የባንኩ የቦርድ አባላት ይመረጣሉ፥
4. ሁሉም አከሰሲዮን የገዙ ግለሠቦችና ድርጅቶች በአካል ወይም በወኪሎቻቸው አማካኝነት ውልና ማስረጃ ቀርበው በመተዳደሪያ ደንብና መመሥረቻ ፅሁፍ ላይ ይፈርማሉ። ይህ ሂደት አዲስና የተለየ አሠራር ከሌለ በስተቀር ጥቂት ሳምንታት ጊዜ ሊወስድ ይችላል።
5. ቦርዱ የባንኩን ከፍተኛ የስራ አመራሮች ይመረጣሉ ።
6. የቦርድ አባላት እና ቁልፍ አመራር ስም ዝርዝር ወደ ብሄራዊ ባንክ ተልኮ የብቃት ምርመራ ይደረግባቸዋል፤ ለህዝብም ይፋ ይሆናል።
(አሁን ያለው አሥተባባሪ ቡድን፥ የተመረመረ ሂሳብና የሥራ ሂደት አዲስ ለተመረጡ የቦርድ አባላት ያስረክባል)
የቦርድ አባላትና ዋና ስራ አስፈፃሚው በዋና የሃገሪቱ ጋዜጦች በይፋ ይወጣል።
7. በተራ ቁጥር 6 ላይ ምርመራ የተደረገባቸው የባንኩ ቦርድ አባላትና ስራ አስፈፃሚ(አንድ ሰው ቢሆንም) የብሄራዊ ባንክ መሥፈርት የማያሟሉ ከሆነ፥... ወዘተ በምትኩ ሌላ አባል ለመምረጥ ሂደቱ እነደ አዲስ ሊጀምር ይችላል።
8. ከላይ የተጠቀሱት ሂደቶች አልፎ በብሄራዊ ባንክ ክትትል መሥፈርት ይሁንታን ሲያገኝ፥ የቅርንጫፎች ኪራይ፥ የኮር ባንኪንግ እና የባንክ ቁሳቁሶች ግዢ ...ጎን ለጎን ደግሞ፥ የስራ ቅጥር ማስታወቂያ በዋና ዋና የሚዲያ አውታሮች ይለቀቃል።
ባንኩ ሁሉንም ቅርንጫፎች በራሱ ዲዛይን በመሥራት፥ የውስጥ አሠራር መዘርጋት፥ ዕቃዎችን ማሟላት፥ የ IT ፋሲሊቲ መዘርጋት/መትከል እና የሠው ሃይል ቅጥር ሂደት ካጠናቀቀ በኋላም በብሄራዊ ባንክ ተረጋግጦ ጊዜያዊ የሥራ ፍቃድ ማግኘት አለበት።
የቅጥር ማስታወቂያ፥ ቅጥር እና ምደባ በሃገሪቱ የሠው ሃይል ቅጥር ህግና ደንብ ተከትሎ ይከናወናል።
በአጠቃላይ የሠው ሃይል ቅጥር ቀደሞ(ጎን ለጎን) የሚሠራ ክንውን ቢሆንም፤ ሂደቶችን ሁሉ አጠናቅቆ ባንኩን መደበኛ ስራ ለማስጀመር ከ6 እስከ 12 ወራት የሚደርስ ጊዜ መታገስን ይጠይቃል።
መልካም ቀን ይሁንላችሁ!
